የሰሙነ ሕማማት ረቡዕ
ምክረ አይሁድ ይባላል፦
ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር ያጠናቀቁበት ቀን ነውና፡፡ በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ቀን የተቃረበ በመሆኑ ብዙው ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለ ነበር ሁከት እንዳይፈጠር ነው፡፡ በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ (ማቴ. 26÷1-14፣ ማር. 14÷1-2፣ ሉቃ. 22÷1-6) የሐዲስ ኪዳን ካህናትና ምእመናን በዚሁ ዕለት በቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው መላ ሰውነታቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው የሞት ፍርዱን በማሰብና በማልቀስ ሐዋርያት ከጌታችን መያዝ በኋላ በኀዘን በፍርሐት እንደነበሩ እያሰቡ መጻሕፍትን በማንበብ በጾም በጸሎትና በስግደት ተወስነው ይቆዩና ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡
የመልካም መዓዛ ቀንም ይባላል፦
ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለሽቱዋ ማርያም) "ከእንግዲህ ወዲህ በኃጢአት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ" ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የተሞላ ሽቱ ይዛ በመሔድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባችው ረቡዕ የመዓዛ ቀን ይባላል፡፡
የእንባ ቀንም ይባላል፦
ማርያም እንተ እፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና። (ማቴ. 26÷6-13፣ ማር. 14÷9፣ ዮሐ. 12÷8) ኃጢአትን በማሰብ ማልቀስና ራስን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ከምታስተምረን ማርያም እንተ እፍረት እንባን ለንስሐ ሕይወት ልንጠቀምበት ይገባል፡፡
ምክረ አይሁድ ይባላል፦
ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር ያጠናቀቁበት ቀን ነውና፡፡ በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ቀን የተቃረበ በመሆኑ ብዙው ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለ ነበር ሁከት እንዳይፈጠር ነው፡፡ በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ (ማቴ. 26÷1-14፣ ማር. 14÷1-2፣ ሉቃ. 22÷1-6) የሐዲስ ኪዳን ካህናትና ምእመናን በዚሁ ዕለት በቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው መላ ሰውነታቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው የሞት ፍርዱን በማሰብና በማልቀስ ሐዋርያት ከጌታችን መያዝ በኋላ በኀዘን በፍርሐት እንደነበሩ እያሰቡ መጻሕፍትን በማንበብ በጾም በጸሎትና በስግደት ተወስነው ይቆዩና ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡
የመልካም መዓዛ ቀንም ይባላል፦
ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለሽቱዋ ማርያም) "ከእንግዲህ ወዲህ በኃጢአት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ" ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የተሞላ ሽቱ ይዛ በመሔድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባችው ረቡዕ የመዓዛ ቀን ይባላል፡፡
የእንባ ቀንም ይባላል፦
ማርያም እንተ እፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና። (ማቴ. 26÷6-13፣ ማር. 14÷9፣ ዮሐ. 12÷8) ኃጢአትን በማሰብ ማልቀስና ራስን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ከምታስተምረን ማርያም እንተ እፍረት እንባን ለንስሐ ሕይወት ልንጠቀምበት ይገባል፡፡
Telegram
ነአምን media
Buy adds:- https://telega.io/c/neamn_media
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
👏1
፬
ድርሳን በእንተ ሕማማቲሁ ለክርስቶስ
.....በግራ የተሰቀለውን ሽፍታም አንተ እግዚአብሔርን አትፈራውምን ለእኛስ ይህ በእኛ ላይ የመጣው ፍርድ ይገባናል፡፡ ይህ ጻድቅ ግን ምንም ምን የሠራው ክፉ ነገር የለም አለው፡፡ ይህ ድንቅ ታላቅ ነው:: ወንበዴው እጅግ ጥበበኛን ሆኗልና፡፡ ነፍሰ ገዳዩም ከፍጹም ኃጢአቱ ድኖ በአንዲት ቃል ባለ ሃይማኖት ሆኗልና፡፡
በግራ የተሰቀለውን ወንበዴ ባለንጀራውን እንዲህ ብሎ አሳፈረው፡፡ አንተ ሰነፍ ሆይ የእግዚአብሔር ልጅ ባይሆን ኑሮስ ፀሐይ ባልጨለመ ነበር፡፡ ከኃጢአት ሁሉ ንጹሕ ባይሆን ኑሮስ የቤተ ምኵራቡ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለሁለት ክፍል ባልተቀደደም ነበር፡፡ የሰማይና የምድር ጌታ ባይሆን ኑሮስ መቃብራት ባልተከፈቱም ነበር፡፡
አንተ ወንበዴ ሆይ አሁን እንኳ እስኪ ከስሕተትህ ተመለስ፡፡ ለመሞት ተቃርበሃል ጊዜህም ደርሷልና፡፡ ነፋሳት በታላቅ ኃይል እንዴት እንደሚነፍሱ አታይምን? የሰማያትና የምድር ኃይላት እንዴት እንደሚርዱ አትመለከትምን? የፀሐይስ ብርሃኑ እንዴት እንደ ጠፋ አታይምን? ከዋክብትስ እንዴት እንደ ወደቁ አትመለከትምን? ባሕርንስ እንዴት እንደታወከች አትመለከታትምን?
አንተ ወንበዴ ሆይ ጌታ አባት ሆይ ይህንን ኃጢአት ይቅር በላቸው ብሎ በታላቅ ቃል ባይናገር ኑሮስ ከዐይን ጥቅሻ ፈጥነው በጠፉ ነበር። ወንበዴው ሆይ ዝም በል። ይህ ጻድቅ ምንም ምን ክፉ ሥራ አልሠራምና። ነገርግን አይሁድ በቅናት ሰቀሉት እንጂ፡፡ የቀኙ ሽፍታ በግራ ለተሰቀለው ሽፍታ እንደዚህ በማለ ተናገረ፡፡
ከዚህም በኋላ የቀኙ ሽፍታ ወደ ጌታ ኢየሱስ ተመልሶ አቤቱ ጌታዬ እና አምላኪየ ነፍሴን ከዚህ ከሓዲ ጋር አታጥፋት፡፡ ነገር ግን በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ እንጂ አለ፡፡ እነሆ አሁን በጌትነትህ ክብር የግርማህን ታላቅነት ዐይቻለሁ፡፡ አቤቱ አንተ ያልካደኝ ብፁዕ ነው ብለሃልና፡፡ እኔ ከጌትነትህ ኃይል የተነሣ ከተቀደደው ከቤተ ምኵራቡ መጋረጃ በዕውቀት የተሻልሁ አይደለሁም፡፡....
ይቀጥላል...
(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 153-179)
ድርሳን በእንተ ሕማማቲሁ ለክርስቶስ
.....በግራ የተሰቀለውን ሽፍታም አንተ እግዚአብሔርን አትፈራውምን ለእኛስ ይህ በእኛ ላይ የመጣው ፍርድ ይገባናል፡፡ ይህ ጻድቅ ግን ምንም ምን የሠራው ክፉ ነገር የለም አለው፡፡ ይህ ድንቅ ታላቅ ነው:: ወንበዴው እጅግ ጥበበኛን ሆኗልና፡፡ ነፍሰ ገዳዩም ከፍጹም ኃጢአቱ ድኖ በአንዲት ቃል ባለ ሃይማኖት ሆኗልና፡፡
በግራ የተሰቀለውን ወንበዴ ባለንጀራውን እንዲህ ብሎ አሳፈረው፡፡ አንተ ሰነፍ ሆይ የእግዚአብሔር ልጅ ባይሆን ኑሮስ ፀሐይ ባልጨለመ ነበር፡፡ ከኃጢአት ሁሉ ንጹሕ ባይሆን ኑሮስ የቤተ ምኵራቡ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለሁለት ክፍል ባልተቀደደም ነበር፡፡ የሰማይና የምድር ጌታ ባይሆን ኑሮስ መቃብራት ባልተከፈቱም ነበር፡፡
አንተ ወንበዴ ሆይ አሁን እንኳ እስኪ ከስሕተትህ ተመለስ፡፡ ለመሞት ተቃርበሃል ጊዜህም ደርሷልና፡፡ ነፋሳት በታላቅ ኃይል እንዴት እንደሚነፍሱ አታይምን? የሰማያትና የምድር ኃይላት እንዴት እንደሚርዱ አትመለከትምን? የፀሐይስ ብርሃኑ እንዴት እንደ ጠፋ አታይምን? ከዋክብትስ እንዴት እንደ ወደቁ አትመለከትምን? ባሕርንስ እንዴት እንደታወከች አትመለከታትምን?
አንተ ወንበዴ ሆይ ጌታ አባት ሆይ ይህንን ኃጢአት ይቅር በላቸው ብሎ በታላቅ ቃል ባይናገር ኑሮስ ከዐይን ጥቅሻ ፈጥነው በጠፉ ነበር። ወንበዴው ሆይ ዝም በል። ይህ ጻድቅ ምንም ምን ክፉ ሥራ አልሠራምና። ነገርግን አይሁድ በቅናት ሰቀሉት እንጂ፡፡ የቀኙ ሽፍታ በግራ ለተሰቀለው ሽፍታ እንደዚህ በማለ ተናገረ፡፡
ከዚህም በኋላ የቀኙ ሽፍታ ወደ ጌታ ኢየሱስ ተመልሶ አቤቱ ጌታዬ እና አምላኪየ ነፍሴን ከዚህ ከሓዲ ጋር አታጥፋት፡፡ ነገር ግን በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ እንጂ አለ፡፡ እነሆ አሁን በጌትነትህ ክብር የግርማህን ታላቅነት ዐይቻለሁ፡፡ አቤቱ አንተ ያልካደኝ ብፁዕ ነው ብለሃልና፡፡ እኔ ከጌትነትህ ኃይል የተነሣ ከተቀደደው ከቤተ ምኵራቡ መጋረጃ በዕውቀት የተሻልሁ አይደለሁም፡፡....
ይቀጥላል...
(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 153-179)
Telegram
ነአምን media
Buy adds:- https://telega.io/c/neamn_media
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
፭
ድርሳን በእንተ ሕማማቲሁ ለክርስቶስ
....አቤቱ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ፡፡ አቤቱ ከሓዲ፣ ነፍሰ ገዳይ፣ የረከስሁና ሥራህን የምጠላ የነበርሁ እኔን ወንበዴውን አስበኝ፡፡ አቤቱ ከሕዝቦችህ መካከል ብዙዎችን ያጠፋሁ እኔን አስበኝ፡፡ ብዙ ሰዎችን በሥውርገድዬ ያለ ልቅሶ የቀበርሁ ነኝና አቤቱ እኔን በቸርነትህ አስበኝ፡፡ አቤቱ በደለኛ የሆንሁ እኔን ኃጢአተኛውን አስበኝ፡፡ አቤቱ በቸርነትህና በምሕረትህ አስበኝ፡፡ አቤቱ በፍርድህ ዐደባባይ አስበኝ፡፡
አቤቱ የቀደመ በደሌን አታስብብኝ፡፡ አንተ ከነውርና ከኃጢአት ሁሉ ንጹሕ የሆንህ ጌታ ነህና፡፡ አቤቱ በሥጋህ በተቀበልኸው ሕማምህ እንድሳተፍ እዳደረግኸኝ ሁሉ እንዲሁም የመንግሥት ወራሽ አድርገኝ፡፡ አቤቱ ግሩም ንጉሥ ሆይ በጌትነትህ ዙፋን ለፍርድ በተቀመጥህ ጊዜ አስበኝ፡፡ አቤቱ የሰማይ ሠራዊት በፊትህ በፍርሀትና በመንቀጥቀጥ በሚቆሙባት ሰዓት አስበኝ፡፡
አቤቱ መቃብራት ተከፍተው ነፍሳት ሁሉ ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ሰው በሚነሡበት በዚያ ጊዜ አስበኝ፡፡ አቤቱ ጻድቃንና ኃጥአን በፍርድህ ዐደባባይ በታላቅ ፍርሀት በሚቆሙበት ዕለት አስበኝ፡፡ አቤቱ በሰማያት ባለችው የሰርግ ቤት አስበኝ፡፡ አንተ ሰማያዊ ሙሽራ ነህና፡፡ አቤቱ ቸሩ ሆይ እኔን ሽፍታውን ወደ አንተ እንዲያመጡኝ፣ በአንተም እንዳምን መላእክትን ትነግራቸው ዘንድ እለምንሃለሁ፤ እማልድሃለሁ፡፡
ያንጊዜም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መለሰለት፡፡ በቀኙ የተሰቀለውንም እውነተኛው ሆይ ታላቅ አደርግሃለሁ፡፡ አንተ ዛሬ በእኔ አመንህ፤ እኔም በመንግሥቴ ስመጣ አስብሃለሁ አለው፡፡ አንተ በሕማሜ ተካፍለሃልና ልመናህን አልተውም ቸልም አልልም፡፡ እውነተኛው ምስክር ሆይ በእውነት ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ፡፡
ዳግመኛም የሰውን ጸሎቱን የምሰማ እኔ ነኝ። የበደልና የኃጢአት ሥርየትን የምሰጥ እኔ ነኝ፡፡ ሁሉን የማዝዝ የአዘዝሁት ሁሉም በሰማይም በምድርም የሚሆንልኝ እኔ ነኝ፡፡ በውኑ ይህ እንጨት ፈቃዴን ይከለክለኛልን? በውኑ ይህስ መስቀል ትእዛዜን ይሽራልን? በውኑ ይህ ሕማም ወደ መለኮቴ ይቀርብ ዘንድስ ይችላልን? እንደዚህ ይሆን ዘንድ አይችልም፡፡ ነገር ግን የችንካሮች ሕማም ለሥጋዬ ብቻ ነው እንጂ ወደማይመረመረው መለኮታዊ ኃይሌ ይቀርብ ዘንድ አይችልም አለው፡፡
በመስቀል ላይ እንዳለሁ የፈለግኸውን ሁሉ እሠጥህ ዘንድ ሥልጣን አለኝ፡፡ እውነተኛው ሆይ እነሆ አሁን ልመናህን ሰማሁ፤ መሻትህንም እፈጽምልሃለሁ፡፡ በውንብድና ኑረህ ነበር፤ ዛሬ ግን ጻድቅ አደርግሃለሁ፡፡ ለአንተ ያደረግሁትንም ዳግመኛም በእኔ ለአመኑ ሁሉ አደርግላቸዋለሁ፡፡....
ይቀጥላል...
(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 153-179)
ድርሳን በእንተ ሕማማቲሁ ለክርስቶስ
....አቤቱ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ፡፡ አቤቱ ከሓዲ፣ ነፍሰ ገዳይ፣ የረከስሁና ሥራህን የምጠላ የነበርሁ እኔን ወንበዴውን አስበኝ፡፡ አቤቱ ከሕዝቦችህ መካከል ብዙዎችን ያጠፋሁ እኔን አስበኝ፡፡ ብዙ ሰዎችን በሥውርገድዬ ያለ ልቅሶ የቀበርሁ ነኝና አቤቱ እኔን በቸርነትህ አስበኝ፡፡ አቤቱ በደለኛ የሆንሁ እኔን ኃጢአተኛውን አስበኝ፡፡ አቤቱ በቸርነትህና በምሕረትህ አስበኝ፡፡ አቤቱ በፍርድህ ዐደባባይ አስበኝ፡፡
አቤቱ የቀደመ በደሌን አታስብብኝ፡፡ አንተ ከነውርና ከኃጢአት ሁሉ ንጹሕ የሆንህ ጌታ ነህና፡፡ አቤቱ በሥጋህ በተቀበልኸው ሕማምህ እንድሳተፍ እዳደረግኸኝ ሁሉ እንዲሁም የመንግሥት ወራሽ አድርገኝ፡፡ አቤቱ ግሩም ንጉሥ ሆይ በጌትነትህ ዙፋን ለፍርድ በተቀመጥህ ጊዜ አስበኝ፡፡ አቤቱ የሰማይ ሠራዊት በፊትህ በፍርሀትና በመንቀጥቀጥ በሚቆሙባት ሰዓት አስበኝ፡፡
አቤቱ መቃብራት ተከፍተው ነፍሳት ሁሉ ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ሰው በሚነሡበት በዚያ ጊዜ አስበኝ፡፡ አቤቱ ጻድቃንና ኃጥአን በፍርድህ ዐደባባይ በታላቅ ፍርሀት በሚቆሙበት ዕለት አስበኝ፡፡ አቤቱ በሰማያት ባለችው የሰርግ ቤት አስበኝ፡፡ አንተ ሰማያዊ ሙሽራ ነህና፡፡ አቤቱ ቸሩ ሆይ እኔን ሽፍታውን ወደ አንተ እንዲያመጡኝ፣ በአንተም እንዳምን መላእክትን ትነግራቸው ዘንድ እለምንሃለሁ፤ እማልድሃለሁ፡፡
ያንጊዜም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መለሰለት፡፡ በቀኙ የተሰቀለውንም እውነተኛው ሆይ ታላቅ አደርግሃለሁ፡፡ አንተ ዛሬ በእኔ አመንህ፤ እኔም በመንግሥቴ ስመጣ አስብሃለሁ አለው፡፡ አንተ በሕማሜ ተካፍለሃልና ልመናህን አልተውም ቸልም አልልም፡፡ እውነተኛው ምስክር ሆይ በእውነት ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ፡፡
ዳግመኛም የሰውን ጸሎቱን የምሰማ እኔ ነኝ። የበደልና የኃጢአት ሥርየትን የምሰጥ እኔ ነኝ፡፡ ሁሉን የማዝዝ የአዘዝሁት ሁሉም በሰማይም በምድርም የሚሆንልኝ እኔ ነኝ፡፡ በውኑ ይህ እንጨት ፈቃዴን ይከለክለኛልን? በውኑ ይህስ መስቀል ትእዛዜን ይሽራልን? በውኑ ይህ ሕማም ወደ መለኮቴ ይቀርብ ዘንድስ ይችላልን? እንደዚህ ይሆን ዘንድ አይችልም፡፡ ነገር ግን የችንካሮች ሕማም ለሥጋዬ ብቻ ነው እንጂ ወደማይመረመረው መለኮታዊ ኃይሌ ይቀርብ ዘንድ አይችልም አለው፡፡
በመስቀል ላይ እንዳለሁ የፈለግኸውን ሁሉ እሠጥህ ዘንድ ሥልጣን አለኝ፡፡ እውነተኛው ሆይ እነሆ አሁን ልመናህን ሰማሁ፤ መሻትህንም እፈጽምልሃለሁ፡፡ በውንብድና ኑረህ ነበር፤ ዛሬ ግን ጻድቅ አደርግሃለሁ፡፡ ለአንተ ያደረግሁትንም ዳግመኛም በእኔ ለአመኑ ሁሉ አደርግላቸዋለሁ፡፡....
ይቀጥላል...
(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 153-179)
Telegram
ነአምን media
Buy adds:- https://telega.io/c/neamn_media
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
፮ (መጨረሻ)
ድርሳን በእንተ ሕማማቲሁ ለክርስቶስ
.....ፈያታዊ ሆይ አባትህ አዳም ትቷት ወደ ወጣ ወደ ጌታህ ደስታ ወደ ገነት ግባ፡፡ ፈያታዊ ሆይ ወደ ገነት ግባ፡፡ ከሚትጠብቃት የእሳት ሰይፍ የተነሣም አትፍራ፡፡ በስሜ የሚያምነውን ሁሉ ከእንግዲህ በኋላ አታቃጥለውምና፡፡ ፈያታዊ ሆይ በአሸናፊነት ኃይል ወደ ገነት ግባ፡፡
በመስቀሉ ደስታ ፈያታዊው ዳነ። መስቀል ኃጥአንን ወደ ጽድቅ መለሰ፡፡ አይሁድን ግን አሳፈራቸው፡፡ እነሆ ዛሬ ታላቅ ድንቅ ነገር ሆነ፡፡ ወንበዴው ድኅነትን አግኝቶ ወደ ገነት ገብቷልና፡፡ ደቀመዝሙር የነበረው ይሁዳ ደግሞ በጥፋቱ ወደ ሲኦል ገባ፡፡ በውኑ ፈያታዊ ዘየማን ጌታ ኢየሱስን በባሕሩ ላይ በየብስ ላይ እንደሚራመድ ሰው ሲሄድ ዐይቶታልን? ወይንስ ጌታ ባርያውን እንደሚያዝዘው ባሕርንና ነፋሳትን ሲገሥጽ ዐይቷልን?
በውኑ ፈያታዊው ክርስቶስ እጁን ሲዘረጋ እና ሙታንን ፈጥኖ ሲያስነሣ ዐይቷልን በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ጉንጮችን በጥፊ ሲመታ ከማየት በቀር ከተአምራት ወገን ምንም ምን አላየም፡፡ ዳግመኛም በላዩ ላይ ሲሳለቁበት፣ ጎኑን በጦር ሲወጉት፣ ራሱንም በዘንግ ሲመቱት እና ሆምጣጣ ሲያጠጡት ዐየ እንጂ፡፡ ይህንንም ሁሉ ተመልክቶ በእርሱ አመነ፡፡ ጌታችንም ፈጥኖ ጸሎቱን ሰማው፡፡ ልመናውንም ተቀበለው፡፡
የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ እነሆ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ወደ ዓለም እንደመጣ ከኃጢአት ቀንበርም ነፃ ያወጣን ዘንድ ስለ እኛ እንደ ታመመ ከእንግዲህ ዕወቁ፡፡ ነቢዩ ኢሳያይስ “እንደ በግ ሊታረድ መጣ" ያለውን ስሙ፡፡ ዳግመኛም እንደሚሸልቱት በግ፤ እርሱ ግን በሸላቾቹ ፊት በሕማሙ አፉን አልከፈተም፡፡
ይህንንም በግ አይሁድ፣ ሊቃውንቶቻቸውና የሕግ መምህሮቻቸው አረዱት። እኛ ግን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙንም በላን ጠጣን፡፡ ነፍሳችንም ዳነች፡፡ ልቡናችንን አበራልን፡፡ ከኃጢአታችን አነፃን፡፡ በከበረች ጥምቀትም ለመንገሥተ ሰማያት የበቃን አደረገን፡፡ ኖኅን እና ልጆቹን ከጥፋት ውኃ ያዳናቸው በግ ይህ ነው፡፡ ዓለምንም ሁሉ ያዳነው በግ ይህ ነው፡፡ በኦሪት እንደ ተጻፈው ምድራዊው በግ ለእስራኤል ትምክሕታቸው ሆነ፡፡ ሰማያዊው በግ ክርስቶስ የክርስቲያኖች መመኪያ ሆነ።
አይሁድ አስቀድመው በጉን ያርዱታል የቤታቸውንም ደጃፍ ደሙን ይቀቡታል፡፡ እኛም አማናዊውን በግ እንሠዋለን ነፍስና ሥጋችንንም ቀደሰን፡፡ አይሁድ የአባቶቻቸውን የበዓል መታሰቢያ ያከብራሉ፡፡ እኛ ግን የጌታችን የመድኃኒታች የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ ልዩ የምትሆን የፋሲካን በዓል እናከብራለን፡፡
አይሁድ ከእውነት መንገድ ሳቱ፡፡ ዘመናቸውም በከንቱ አለፈ፡፡ ከኢየሩሳሌም ውጭ በዓል አያድርጉ ተብሏልና፡፡ እኛ ግን በምድር ሁሉ የፋሲካን በዓል በፍጹም ደስታ እናደርጋለን፡፡ ነቢይ ምድር በመላዋ ለእግዚአብሔር ናት፡፡ ዓለምና በውስጧ ያለ ሁሉ የእርሱ ነው ያለውን ስሙ:: አይሁድ የኤርትራን ባሕር ተሸገሩ፡፡ ትእዛዙንም በመሻር እግዚአብሔርን አስቈጡት፡፡ እኛ ግን ልዩ በምትሆን በጥምቀት ከኃጢአታችን ነጻን፡፡
ነቢዩ ኃጢአታቸው የተተወላቸው ንዑዳን ክቡራን ናቸው፡፡ እግዚአብሔር በደላቸውን የማይቈጥርባቸው ንዑዳን ክቡራን ናቸው በማለት የተናገረውን የደስታ ቃል ስሙ፡፡ አይሁድ ከሥጋ ሕግ ተወልደዋልና ሥጋዊ የሆነ ሀብት ተሰጣቸው፡፡ እኛ ግን ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ተወለድን፡፡ ስለዚህም መንፈሳዊ ሀብት ተሠጠን፡፡
እነርሱን የእሳት ዐምድ መራቸው፡፡ እኛን ግን የጽድቅ ፀሐይ መራን፡፡ ለእነርሱ ሙሴ አላቸው፡፡ ለእኛ ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አለን፡፡ ለእነርሱ የድንጋይ ጽላት አላቸው፡፡ ለእኛ ግን ቅዱስ ወንጌል አለን፡፡ ለእነርሱ የወርቅ መሶብ አላቸው፡፡ ለእኛ ግን የተቀደሰው ታቦት አለን፡፡ ለእነርሱ መብራት አላቸው፡፡ ለእኛ ግን የብርሃናት ሁሉ ጌታ አለን፡፡ ለእነርሱ ጸናጽል አላቸው፡፡ ለእኛ ግን የከበሩ ቅዱሳን ሰማዕታት አሉን፡፡
ለእነርሱ አበባን ያበበች የአሮን በትር አለቻቸው፡፡ ለእኛ ግን የሕይወት ፍሬን ያፈራ ክቡር መስቀል አለን፡፡ ይህ የሕይወት ፍሬም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡
ለእርሱ ክብር ምስጋናና አምልኮት ይገባል፡፡ ዛሬም ዘወትርም እስከ ዘለዓለሙ ድረስ አሜን፡፡
(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 153-179)
ድርሳን በእንተ ሕማማቲሁ ለክርስቶስ
.....ፈያታዊ ሆይ አባትህ አዳም ትቷት ወደ ወጣ ወደ ጌታህ ደስታ ወደ ገነት ግባ፡፡ ፈያታዊ ሆይ ወደ ገነት ግባ፡፡ ከሚትጠብቃት የእሳት ሰይፍ የተነሣም አትፍራ፡፡ በስሜ የሚያምነውን ሁሉ ከእንግዲህ በኋላ አታቃጥለውምና፡፡ ፈያታዊ ሆይ በአሸናፊነት ኃይል ወደ ገነት ግባ፡፡
በመስቀሉ ደስታ ፈያታዊው ዳነ። መስቀል ኃጥአንን ወደ ጽድቅ መለሰ፡፡ አይሁድን ግን አሳፈራቸው፡፡ እነሆ ዛሬ ታላቅ ድንቅ ነገር ሆነ፡፡ ወንበዴው ድኅነትን አግኝቶ ወደ ገነት ገብቷልና፡፡ ደቀመዝሙር የነበረው ይሁዳ ደግሞ በጥፋቱ ወደ ሲኦል ገባ፡፡ በውኑ ፈያታዊ ዘየማን ጌታ ኢየሱስን በባሕሩ ላይ በየብስ ላይ እንደሚራመድ ሰው ሲሄድ ዐይቶታልን? ወይንስ ጌታ ባርያውን እንደሚያዝዘው ባሕርንና ነፋሳትን ሲገሥጽ ዐይቷልን?
በውኑ ፈያታዊው ክርስቶስ እጁን ሲዘረጋ እና ሙታንን ፈጥኖ ሲያስነሣ ዐይቷልን በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ጉንጮችን በጥፊ ሲመታ ከማየት በቀር ከተአምራት ወገን ምንም ምን አላየም፡፡ ዳግመኛም በላዩ ላይ ሲሳለቁበት፣ ጎኑን በጦር ሲወጉት፣ ራሱንም በዘንግ ሲመቱት እና ሆምጣጣ ሲያጠጡት ዐየ እንጂ፡፡ ይህንንም ሁሉ ተመልክቶ በእርሱ አመነ፡፡ ጌታችንም ፈጥኖ ጸሎቱን ሰማው፡፡ ልመናውንም ተቀበለው፡፡
የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ እነሆ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ወደ ዓለም እንደመጣ ከኃጢአት ቀንበርም ነፃ ያወጣን ዘንድ ስለ እኛ እንደ ታመመ ከእንግዲህ ዕወቁ፡፡ ነቢዩ ኢሳያይስ “እንደ በግ ሊታረድ መጣ" ያለውን ስሙ፡፡ ዳግመኛም እንደሚሸልቱት በግ፤ እርሱ ግን በሸላቾቹ ፊት በሕማሙ አፉን አልከፈተም፡፡
ይህንንም በግ አይሁድ፣ ሊቃውንቶቻቸውና የሕግ መምህሮቻቸው አረዱት። እኛ ግን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙንም በላን ጠጣን፡፡ ነፍሳችንም ዳነች፡፡ ልቡናችንን አበራልን፡፡ ከኃጢአታችን አነፃን፡፡ በከበረች ጥምቀትም ለመንገሥተ ሰማያት የበቃን አደረገን፡፡ ኖኅን እና ልጆቹን ከጥፋት ውኃ ያዳናቸው በግ ይህ ነው፡፡ ዓለምንም ሁሉ ያዳነው በግ ይህ ነው፡፡ በኦሪት እንደ ተጻፈው ምድራዊው በግ ለእስራኤል ትምክሕታቸው ሆነ፡፡ ሰማያዊው በግ ክርስቶስ የክርስቲያኖች መመኪያ ሆነ።
አይሁድ አስቀድመው በጉን ያርዱታል የቤታቸውንም ደጃፍ ደሙን ይቀቡታል፡፡ እኛም አማናዊውን በግ እንሠዋለን ነፍስና ሥጋችንንም ቀደሰን፡፡ አይሁድ የአባቶቻቸውን የበዓል መታሰቢያ ያከብራሉ፡፡ እኛ ግን የጌታችን የመድኃኒታች የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ ልዩ የምትሆን የፋሲካን በዓል እናከብራለን፡፡
አይሁድ ከእውነት መንገድ ሳቱ፡፡ ዘመናቸውም በከንቱ አለፈ፡፡ ከኢየሩሳሌም ውጭ በዓል አያድርጉ ተብሏልና፡፡ እኛ ግን በምድር ሁሉ የፋሲካን በዓል በፍጹም ደስታ እናደርጋለን፡፡ ነቢይ ምድር በመላዋ ለእግዚአብሔር ናት፡፡ ዓለምና በውስጧ ያለ ሁሉ የእርሱ ነው ያለውን ስሙ:: አይሁድ የኤርትራን ባሕር ተሸገሩ፡፡ ትእዛዙንም በመሻር እግዚአብሔርን አስቈጡት፡፡ እኛ ግን ልዩ በምትሆን በጥምቀት ከኃጢአታችን ነጻን፡፡
ነቢዩ ኃጢአታቸው የተተወላቸው ንዑዳን ክቡራን ናቸው፡፡ እግዚአብሔር በደላቸውን የማይቈጥርባቸው ንዑዳን ክቡራን ናቸው በማለት የተናገረውን የደስታ ቃል ስሙ፡፡ አይሁድ ከሥጋ ሕግ ተወልደዋልና ሥጋዊ የሆነ ሀብት ተሰጣቸው፡፡ እኛ ግን ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ተወለድን፡፡ ስለዚህም መንፈሳዊ ሀብት ተሠጠን፡፡
እነርሱን የእሳት ዐምድ መራቸው፡፡ እኛን ግን የጽድቅ ፀሐይ መራን፡፡ ለእነርሱ ሙሴ አላቸው፡፡ ለእኛ ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አለን፡፡ ለእነርሱ የድንጋይ ጽላት አላቸው፡፡ ለእኛ ግን ቅዱስ ወንጌል አለን፡፡ ለእነርሱ የወርቅ መሶብ አላቸው፡፡ ለእኛ ግን የተቀደሰው ታቦት አለን፡፡ ለእነርሱ መብራት አላቸው፡፡ ለእኛ ግን የብርሃናት ሁሉ ጌታ አለን፡፡ ለእነርሱ ጸናጽል አላቸው፡፡ ለእኛ ግን የከበሩ ቅዱሳን ሰማዕታት አሉን፡፡
ለእነርሱ አበባን ያበበች የአሮን በትር አለቻቸው፡፡ ለእኛ ግን የሕይወት ፍሬን ያፈራ ክቡር መስቀል አለን፡፡ ይህ የሕይወት ፍሬም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡
ለእርሱ ክብር ምስጋናና አምልኮት ይገባል፡፡ ዛሬም ዘወትርም እስከ ዘለዓለሙ ድረስ አሜን፡፡
(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 153-179)
Telegram
ነአምን media
Buy adds:- https://telega.io/c/neamn_media
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
ዐቢይ ጦም ሊጠናቀቅ ሲል የተሰጠ ምዕዳን
እነሆ የተቀደሰውን ወርኃ ጦም ወደ ማጠናቀቅ ተቃርበናል፤ የጦሙን ጉዞ ወደ ማገባደድ ደርሰናል፤ እግዚአብሔር ረድቶንም ወደ ወደቡ ልንደርስ ተጠግተናል፡፡
ነገር ግን እንዲህ በመኾኑ ልል ዘሊላን ልንኾን አይገባንም፤ ይህን ምክንያት አድርገን ከከዚህ በፊቱ ላይ ትጋታችንንና ንቃታችንን እጅጉን እንጨምር እንጂ፡፡
የመርከብ አለቆች ብዙ ባሕረኞችንና ዕቃ ጭነው ረጅም የባሕር ላይ ጉዞ ካደረጉ በኋላ ወደ ወደቡ ሊደርሱ ሲሉ መርከባቸው ከዓለት ጋር እንዳትጋጭና ድካማቸውን ኹሉ ከንቱ ላለማድረግ ከፍ ያለ ጥንቃቄ ያደርጋሉ፡፡ ሯጮችም እንደዚሁ ወደ መጨረሻው መስመር ሊቃረቡ ሲሉ ኃይላቸውን ኹሉ አሟጥጠው ተጠቅመው ሽልማቱን ለመውሰድ ይጥራሉ፡፡ ትግለኞችም ምንም እንኳን ስፍር ቊጥር የሌለው ቡጢ ቢደርስባቸውም፣ ምንም እንኳን ብዙ ጊዜ ተመትተው ቢወድቁም ሽል ማቱን ይወስዱ ዘንድ የመጨረሻውን ዙር ትግል እጅግ ከፍ ባለ ጉልበ ት ይታገላሉ፡፡
ስለዚህ የመርከብ አለቆች፣ ሯጮችና ትግለኞች ድል ወደ ማድረግ ሲቃረቡ እጅግ ከፍ ያለ ትጋትና ጥንቃቄ ኃይልም እንደሚጠቀሙ፥ እኛም ወደ ታላቁ ሳምንት ደርሰናልና እግዚአብሔር ስለረዳን እያመሰገንን ጸሎታችንን፣ ተአምኖ ኃጢአታችንን፣ በጎ ምግባራችንን፣ ምጽዋ ታችንን፣ ከሌሎች ሰዎች ጋር ያለን መስተጋብራችንን፣ ራስን የመግዛት ጠባያችንን፣ እንደዚሁም ይህን የመሰለው ሌላው ምግባራችንን ከፍ ባለ ትጋትና ጥንቃቄ ልንፈጽም ይገባናል፡፡ እነዚህን በጎ በጎ ነገሮችን ወደ ጌታ ቀን (ወደ በዓለ ትንሣኤ) የምንደርስ ከኾነ ከጌታችን ዘንድ ባለሟልነትን እናገኛለን፤ ከማዕዱ ዘንድ መሳተፍ ይቻለናል፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አምስቱ የንስሐ መንገዶች፣ ገጽ 148)
እነሆ የተቀደሰውን ወርኃ ጦም ወደ ማጠናቀቅ ተቃርበናል፤ የጦሙን ጉዞ ወደ ማገባደድ ደርሰናል፤ እግዚአብሔር ረድቶንም ወደ ወደቡ ልንደርስ ተጠግተናል፡፡
ነገር ግን እንዲህ በመኾኑ ልል ዘሊላን ልንኾን አይገባንም፤ ይህን ምክንያት አድርገን ከከዚህ በፊቱ ላይ ትጋታችንንና ንቃታችንን እጅጉን እንጨምር እንጂ፡፡
የመርከብ አለቆች ብዙ ባሕረኞችንና ዕቃ ጭነው ረጅም የባሕር ላይ ጉዞ ካደረጉ በኋላ ወደ ወደቡ ሊደርሱ ሲሉ መርከባቸው ከዓለት ጋር እንዳትጋጭና ድካማቸውን ኹሉ ከንቱ ላለማድረግ ከፍ ያለ ጥንቃቄ ያደርጋሉ፡፡ ሯጮችም እንደዚሁ ወደ መጨረሻው መስመር ሊቃረቡ ሲሉ ኃይላቸውን ኹሉ አሟጥጠው ተጠቅመው ሽልማቱን ለመውሰድ ይጥራሉ፡፡ ትግለኞችም ምንም እንኳን ስፍር ቊጥር የሌለው ቡጢ ቢደርስባቸውም፣ ምንም እንኳን ብዙ ጊዜ ተመትተው ቢወድቁም ሽል ማቱን ይወስዱ ዘንድ የመጨረሻውን ዙር ትግል እጅግ ከፍ ባለ ጉልበ ት ይታገላሉ፡፡
ስለዚህ የመርከብ አለቆች፣ ሯጮችና ትግለኞች ድል ወደ ማድረግ ሲቃረቡ እጅግ ከፍ ያለ ትጋትና ጥንቃቄ ኃይልም እንደሚጠቀሙ፥ እኛም ወደ ታላቁ ሳምንት ደርሰናልና እግዚአብሔር ስለረዳን እያመሰገንን ጸሎታችንን፣ ተአምኖ ኃጢአታችንን፣ በጎ ምግባራችንን፣ ምጽዋ ታችንን፣ ከሌሎች ሰዎች ጋር ያለን መስተጋብራችንን፣ ራስን የመግዛት ጠባያችንን፣ እንደዚሁም ይህን የመሰለው ሌላው ምግባራችንን ከፍ ባለ ትጋትና ጥንቃቄ ልንፈጽም ይገባናል፡፡ እነዚህን በጎ በጎ ነገሮችን ወደ ጌታ ቀን (ወደ በዓለ ትንሣኤ) የምንደርስ ከኾነ ከጌታችን ዘንድ ባለሟልነትን እናገኛለን፤ ከማዕዱ ዘንድ መሳተፍ ይቻለናል፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አምስቱ የንስሐ መንገዶች፣ ገጽ 148)
Telegram
ነአምን media
Buy adds:- https://telega.io/c/neamn_media
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
የሰሙነ ህማማት ሐሙስ
ጸሎተ ሐሙስ
በቤተ ክርስቲያን የተለያዩ ስያሜዎች ያሏቸው በርካታ ድርጊቶች የተፈጸሙበት ዕለት ነውና ጸሎተ ሐሙስ ይባላል፡፡ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋን የተዋሐደ አምላክ፣ መሆኑን ለመግለጥና ለአርአያነት ጠላቶቹ መጥተው እስኪይዙት ድረስ ሲጸልይ ያደረበት ነውና ጸሎተ ሐሙስ ተባለ፡፡ (ማቴ. 26፥36-46 ዮሐ.17)
ሕፅበተ ሐሙስ ይባላል፡-
ጌታችን በዚህ ዕለት የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትሕትና ዝቅ ብሎ አጥቧል፡፡ ይህም የሚያሳየው የዓለምን ሁሉ ኃጢአት ለማጠብ የመጣ መሆኑን ነው፡፡ ይህን ለማስታወስ ዛሬም ካህናት በተለይም ሊቃነ ጳጳሳት፣ የደብር አስተዳዳሪዎች፤ «በመካከላችን ተገኝተህ የእኛንና የሕዝብህን ኃጢአት እጠብ እኛም የአንተን አርአያ አንዘነጋም የሌላውን እግር እናጥባለን፤» ሲሉ በቤተ ክርስቲያን የተገኙትን ምእመናንን እግር በወይንና በወይራ ቅጠል ያጥባሉ፡፡
የምስጢር ቀን ይባላል፡-
ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ በዚህ ዕለት ተመሥርቷልና፡፡ ይኸውም «ይህ ስለ እናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው፡፡ እንካችሁ ብሉ» ጽዋውንም አንስቶ አመሰገነ «ይህ ስለ እናንተ ነገ በመስቀል የሚፈስ ደሜ ነው ከእርሱም ጠጡ» በማለት፤ እኛ ከእርሱ ጋር፣ እርሱ ከእኛ ጋር አንድ የምንሆንበትን ምስጢር ከጠላት ዲያብሎስ ሰውሮ፣ ለደቀ መዛሙርቱ የገለጠበት ቀን በመሆኑ የተሰጠ ሥያሜ ነው፡፡ በዚህ ዕለት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ በንስሐ ታጥቦ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለመቀበል ይዘጋጃል፡፡
የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል፡-
ምክንያቱም መሥዋዕተ ኦሪት ማለትም በእንስሳት ደም የሚቀርበው መሥዋዕት ማብቃቱን ገልጦ፣ ለድኅነተ ዓለም ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ያቀረበበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡ «ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን ሐዲስ ኪዳን ነው፡፡ ከእርሱ ጠጡ» በማለቱ ይታወቃል (ሉቃ. 22፥20) ኪዳን ማለት በሁለት ወገን መካከል የሚደረግ ውል፣ ስምምነት፣ መሐላ ማለት ነው፡፡ በዚህ መሠረት ጌታችን ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ዘለዓለማዊውን ቃል ኪዳን በራሱ ደም የፈጸመበት ዕለት ስለሆነ የሐዲስ ኪዳስ ሐሙስ ተባለ፡፡
የነጻነት ሐሙስ ይባላል፡-
ለኃጢአትና ለዲያብሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱ፣ የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ ጌታችን ስለ ሰው ልጅ ነጻነት ሲናገር «ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም ባርያ ጌታዉ የሚያደርገውን አያውቅምና ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ» በማለት (ዮሐ. 15፥15)፤ ከባርነት የወጣንበት ልጆች የተባልንበትን ቀን የምናስብበት በመሆኑ ሊቃውንቱ የነጻነት ሐሙስ አሉት፡፡ እያንዳንዱ ክርስቲያንም ከኃጢአት ባርነት ርቆ፣ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያወዳጀውን መልካም ሥራ በመሥራት ሕይወቱን መምራት ይኖርባታል፡፡ ባሮች አልላችሁም ተብለናልና፡፡
ጸሎተ ሐሙስ
በቤተ ክርስቲያን የተለያዩ ስያሜዎች ያሏቸው በርካታ ድርጊቶች የተፈጸሙበት ዕለት ነውና ጸሎተ ሐሙስ ይባላል፡፡ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋን የተዋሐደ አምላክ፣ መሆኑን ለመግለጥና ለአርአያነት ጠላቶቹ መጥተው እስኪይዙት ድረስ ሲጸልይ ያደረበት ነውና ጸሎተ ሐሙስ ተባለ፡፡ (ማቴ. 26፥36-46 ዮሐ.17)
ሕፅበተ ሐሙስ ይባላል፡-
ጌታችን በዚህ ዕለት የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትሕትና ዝቅ ብሎ አጥቧል፡፡ ይህም የሚያሳየው የዓለምን ሁሉ ኃጢአት ለማጠብ የመጣ መሆኑን ነው፡፡ ይህን ለማስታወስ ዛሬም ካህናት በተለይም ሊቃነ ጳጳሳት፣ የደብር አስተዳዳሪዎች፤ «በመካከላችን ተገኝተህ የእኛንና የሕዝብህን ኃጢአት እጠብ እኛም የአንተን አርአያ አንዘነጋም የሌላውን እግር እናጥባለን፤» ሲሉ በቤተ ክርስቲያን የተገኙትን ምእመናንን እግር በወይንና በወይራ ቅጠል ያጥባሉ፡፡
የምስጢር ቀን ይባላል፡-
ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ በዚህ ዕለት ተመሥርቷልና፡፡ ይኸውም «ይህ ስለ እናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው፡፡ እንካችሁ ብሉ» ጽዋውንም አንስቶ አመሰገነ «ይህ ስለ እናንተ ነገ በመስቀል የሚፈስ ደሜ ነው ከእርሱም ጠጡ» በማለት፤ እኛ ከእርሱ ጋር፣ እርሱ ከእኛ ጋር አንድ የምንሆንበትን ምስጢር ከጠላት ዲያብሎስ ሰውሮ፣ ለደቀ መዛሙርቱ የገለጠበት ቀን በመሆኑ የተሰጠ ሥያሜ ነው፡፡ በዚህ ዕለት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ በንስሐ ታጥቦ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለመቀበል ይዘጋጃል፡፡
የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል፡-
ምክንያቱም መሥዋዕተ ኦሪት ማለትም በእንስሳት ደም የሚቀርበው መሥዋዕት ማብቃቱን ገልጦ፣ ለድኅነተ ዓለም ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ያቀረበበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡ «ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን ሐዲስ ኪዳን ነው፡፡ ከእርሱ ጠጡ» በማለቱ ይታወቃል (ሉቃ. 22፥20) ኪዳን ማለት በሁለት ወገን መካከል የሚደረግ ውል፣ ስምምነት፣ መሐላ ማለት ነው፡፡ በዚህ መሠረት ጌታችን ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ዘለዓለማዊውን ቃል ኪዳን በራሱ ደም የፈጸመበት ዕለት ስለሆነ የሐዲስ ኪዳስ ሐሙስ ተባለ፡፡
የነጻነት ሐሙስ ይባላል፡-
ለኃጢአትና ለዲያብሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱ፣ የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ ጌታችን ስለ ሰው ልጅ ነጻነት ሲናገር «ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም ባርያ ጌታዉ የሚያደርገውን አያውቅምና ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ» በማለት (ዮሐ. 15፥15)፤ ከባርነት የወጣንበት ልጆች የተባልንበትን ቀን የምናስብበት በመሆኑ ሊቃውንቱ የነጻነት ሐሙስ አሉት፡፡ እያንዳንዱ ክርስቲያንም ከኃጢአት ባርነት ርቆ፣ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያወዳጀውን መልካም ሥራ በመሥራት ሕይወቱን መምራት ይኖርባታል፡፡ ባሮች አልላችሁም ተብለናልና፡፡
Telegram
ነአምን media
Buy adds:- https://telega.io/c/neamn_media
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
❤1
ነአምን media
የክርስቶስ 13ቱ ሕማማት👇
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዐሥራ ሦስቱን ሕማማተ መስቀል በዕለተ ዓርብ ተቀብሏል እነዚህም👇
1) ተአስሮተ ድኅር ( የኋሊት መታሰር )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 18 ÷ 12 )
👉 ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ ( ም 1 ÷ 46 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ብንያሚ ( ም 89 ÷ 15 )
2) ተጸፍዖ መልታሕት ( ፊትን በጥፊ መመታት )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 26 ÷ 67 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 14 ÷ 65 )
👉 የሉቃስ ወንጌል ( ም 22 ÷ 64 )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 18 ÷ 22 )
👉 ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ ( ም 1 ÷ 49 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ዮሐንስ ( ም 103 ÷ 14 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ዘዮሐንስ ( ም 113 ÷ 9 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ዘዮሐንስ ( ም 114 ÷ 25 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤጲፋንዮስ ( ም 55 ÷ 35 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አትናቴዎስ ( ም 30 ÷ 37 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎዶስዮስ ( ም 82 ÷ 21-23 )
3) ወሪቀ ምራቅ (ምራቅ መተፋት)
👉 ትንቢተ ኢሳይያስ ( ም 50 ÷ 6 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 26 ÷ 67 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 27 ÷ 30 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 10 ÷ 34 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 14 ÷ 65 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 15 ÷ 19 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ሄሬኔዎስ ( ም 7 ÷ 25 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ዮሐንስ ( ም 103 ÷ 14 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤጲፋንዮስ ( ም 55 ÷ 35 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አትናቴዎስ ( ም 30 ÷ 37 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎዶስዮስ ( ም 82 ÷ 21-23 )
4) ተኰርዖተ ርዕስ (ራስ በዘንግ መመታት)
👉 ትንቢተ ኢሳይያስ ( ም 1 ÷ 5 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 27 ÷ 30 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 15 ÷ 19 )
5) ተቀሥፎ ዘባን (ጀርባን መገረፍ)
👉 ትንቢተ ኢሳይያስ ( ም 50 ÷ 6 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 20 ÷ 19 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 27 ÷ 26 )
👉 የሉቃስ ወንጌል ( ም 23 ÷ 16 )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 19 ÷ 1 )
👉 1ኛ የጴጥሮስ መልዕክት ( ም 2 ÷ 24 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤጲፋንዮስ ( ም 55 ÷ 35 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አትናቴዎስ ( ም 30 ÷ 37 )
6) አክሊለ ሦክ ( የእሾህ አክሊል መድፋት )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 27 ÷ 29 )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 19 ÷ 2 - 5 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎዶስዮስ ( ም 82 ÷ 21 )
7) ጸዊረ መስቀል ( መስቀል መሸከም )
👉 የሉቃስ ወንጌል ( ም 23 ÷ 26 )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 19 ÷ 17 )
👉 መጽሐፈ ምስጢር ( ም 14 ÷ 27 )
8) ሰትየ ሐሞት (አሞት / ሆምጣጤ መጠጣት )
👉 መዝሙረ ዳዊት ( ም 68 ÷ 21 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 27 ÷ 34 - 48 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 15 ÷ 36 )
👉 የሉቃስ ወንጌል ( ም 23 ÷ 36 )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 19 ÷ 28 - 30 )
የተቀሩት አምስቱ ቅንዋተ መስቀል ናቸው። ስማቸውም የዕብራይስጥ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ አራቱ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መጽሐፈ ምስጢር በተሰኘው መጽሐፋቸው ጠቅሰዋቸዋል ( መጽሐፈ ምስጢር 14 ÷ 27 ) እነርሱም 👇
👉 ሳዶር | የመጀመሪያ :- ሁለቱን መስቀል በማያያዝ የተቸነከረ ነው።
👉 አላዶር | ሁለተኛ :- ቀኝ እጁን የተቸነከረበት ችንካር ነው።
👉 ዳናት | ሦስተኛ :- ግራ እጁን የተቸነከረበት ችንካር ነው።
👉 አዴራ | አራተኛ :- እግሮቹን አጣምረው የቸነከሩበት ችንካር ነው።
👉 ሮዳስ | አምስተኛ :- ኢናንአ (ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ) የሚለውን ጲላጦስ በዕብራይስጥ ፣ በሮማይስጥ ፣ በግሪክ ተፅፎ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራስ በላይ የተሰቀለበት ችንካር ነው።
1) ተአስሮተ ድኅር ( የኋሊት መታሰር )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 18 ÷ 12 )
👉 ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ ( ም 1 ÷ 46 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ብንያሚ ( ም 89 ÷ 15 )
2) ተጸፍዖ መልታሕት ( ፊትን በጥፊ መመታት )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 26 ÷ 67 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 14 ÷ 65 )
👉 የሉቃስ ወንጌል ( ም 22 ÷ 64 )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 18 ÷ 22 )
👉 ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ ( ም 1 ÷ 49 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ዮሐንስ ( ም 103 ÷ 14 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ዘዮሐንስ ( ም 113 ÷ 9 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ዘዮሐንስ ( ም 114 ÷ 25 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤጲፋንዮስ ( ም 55 ÷ 35 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አትናቴዎስ ( ም 30 ÷ 37 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎዶስዮስ ( ም 82 ÷ 21-23 )
3) ወሪቀ ምራቅ (ምራቅ መተፋት)
👉 ትንቢተ ኢሳይያስ ( ም 50 ÷ 6 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 26 ÷ 67 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 27 ÷ 30 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 10 ÷ 34 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 14 ÷ 65 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 15 ÷ 19 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ሄሬኔዎስ ( ም 7 ÷ 25 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ዮሐንስ ( ም 103 ÷ 14 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤጲፋንዮስ ( ም 55 ÷ 35 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አትናቴዎስ ( ም 30 ÷ 37 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎዶስዮስ ( ም 82 ÷ 21-23 )
4) ተኰርዖተ ርዕስ (ራስ በዘንግ መመታት)
👉 ትንቢተ ኢሳይያስ ( ም 1 ÷ 5 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 27 ÷ 30 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 15 ÷ 19 )
5) ተቀሥፎ ዘባን (ጀርባን መገረፍ)
👉 ትንቢተ ኢሳይያስ ( ም 50 ÷ 6 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 20 ÷ 19 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 27 ÷ 26 )
👉 የሉቃስ ወንጌል ( ም 23 ÷ 16 )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 19 ÷ 1 )
👉 1ኛ የጴጥሮስ መልዕክት ( ም 2 ÷ 24 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤጲፋንዮስ ( ም 55 ÷ 35 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አትናቴዎስ ( ም 30 ÷ 37 )
6) አክሊለ ሦክ ( የእሾህ አክሊል መድፋት )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 27 ÷ 29 )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 19 ÷ 2 - 5 )
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎዶስዮስ ( ም 82 ÷ 21 )
7) ጸዊረ መስቀል ( መስቀል መሸከም )
👉 የሉቃስ ወንጌል ( ም 23 ÷ 26 )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 19 ÷ 17 )
👉 መጽሐፈ ምስጢር ( ም 14 ÷ 27 )
8) ሰትየ ሐሞት (አሞት / ሆምጣጤ መጠጣት )
👉 መዝሙረ ዳዊት ( ም 68 ÷ 21 )
👉 የማቴዎስ ወንጌል ( ም 27 ÷ 34 - 48 )
👉 የማርቆስ ወንጌል ( ም 15 ÷ 36 )
👉 የሉቃስ ወንጌል ( ም 23 ÷ 36 )
👉 የዮሐንስ ወንጌል ( ም 19 ÷ 28 - 30 )
የተቀሩት አምስቱ ቅንዋተ መስቀል ናቸው። ስማቸውም የዕብራይስጥ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ አራቱ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መጽሐፈ ምስጢር በተሰኘው መጽሐፋቸው ጠቅሰዋቸዋል ( መጽሐፈ ምስጢር 14 ÷ 27 ) እነርሱም 👇
👉 ሳዶር | የመጀመሪያ :- ሁለቱን መስቀል በማያያዝ የተቸነከረ ነው።
👉 አላዶር | ሁለተኛ :- ቀኝ እጁን የተቸነከረበት ችንካር ነው።
👉 ዳናት | ሦስተኛ :- ግራ እጁን የተቸነከረበት ችንካር ነው።
👉 አዴራ | አራተኛ :- እግሮቹን አጣምረው የቸነከሩበት ችንካር ነው።
👉 ሮዳስ | አምስተኛ :- ኢናንአ (ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ) የሚለውን ጲላጦስ በዕብራይስጥ ፣ በሮማይስጥ ፣ በግሪክ ተፅፎ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራስ በላይ የተሰቀለበት ችንካር ነው።
የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡
ወየው ወየው ወየው አማኑኤል አምላካችን፡፡
ወየው ወየው ወየው መድኃኒታችን ኢየሱስ፡፡
ወየው ወየው ወየው መድኃኒታችን ኢየሱስ፡፡
ወየው ወየው ወየው ንጉሣችን ክርስቶስ፡፡
ወየው ወየው ወየው ጻድቁን ከዕንጨት አወረዱት፡፡
ሥጋውንም ለመገነዝ ከርቤ የሚባል የጣፈጠ ሽቱንና ንጹሕ በፍታን አመጡ፡፡
ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው የማይሞት የማይለወጥ፡፡
ከድንግል ማርያም የተወለደ አቤቱ ይቅር በለን፡፡
ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ የማይሞት የማይለወጥ በዮርዳኖስ የተጠመቀ በመስቀልም የተሰቀለ አቤቱ ይቅር በለን፡፡"
#ቅዳሴ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
ወየው ወየው ወየው አማኑኤል አምላካችን፡፡
ወየው ወየው ወየው መድኃኒታችን ኢየሱስ፡፡
ወየው ወየው ወየው መድኃኒታችን ኢየሱስ፡፡
ወየው ወየው ወየው ንጉሣችን ክርስቶስ፡፡
ወየው ወየው ወየው ጻድቁን ከዕንጨት አወረዱት፡፡
ሥጋውንም ለመገነዝ ከርቤ የሚባል የጣፈጠ ሽቱንና ንጹሕ በፍታን አመጡ፡፡
ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው የማይሞት የማይለወጥ፡፡
ከድንግል ማርያም የተወለደ አቤቱ ይቅር በለን፡፡
ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ የማይሞት የማይለወጥ በዮርዳኖስ የተጠመቀ በመስቀልም የተሰቀለ አቤቱ ይቅር በለን፡፡"
#ቅዳሴ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
❤1
ቄጠማ በግንባራችን ለምን እናስራለን ?
ቄጠማ የምሥራች ምልክት ነው ቄጠማው የምሥራች ምልክት ተደርጐ የተወሰደው በኖኅ ዘመን ከተፈጸመው ታሪክ ጋር በማቆራኘት ነው ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን በጻድቁ ኖኅ ዘመን የነበሩ ሕዝቦች ከሕገ እግዚአብሔር ውጪ ኾነው እጅግ የሚያሳዝን ኃጢአት በሠሩ ጊዜ በንፍር ውኃ ተጥለቅልቀዋል፡፡ በወቅቱ ጻድቁ ኖኅ ወደ መርከብ ይዞአቸው ከገባው እንስሳት መካከል የውኃውን መጉደል ለመረዳት ርግብን በመርከብ መስኮት አሾልኮ ይለቃታል፤ እርሷም ቄጠማ በአፍዋ ይዛ ትመልሳለች፡፡ ኖኅም በዚህ ቄጠማ የውኃውን መድረቅ ተረድቶ ተደስቷል
ቄጠማ ለጥፋት ውኃ መድረቅ የምሥራች መንገሪያ እንደ ኾነ ዅሉ
አሁንም ‹‹በክርስቶስ ሞት ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ፤›› ስትል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለልጆቿ ቄጠማ ታድላለች፡፡
ምእመናንም የምሥራች ተምሳሌት የኾነውን ቄጠማ በግንባራቸው ያስሩታል፡፡ የክርስቶስ ተከታዮች ዅሉ ከጨለማ ወደ ብርሃን፤ ከዋዕየ ሲኦል (የሲኦል ቃጠሎ) ወደ ጥንተ ማኅደራቸው ገነት መመለሳቸውን በዚህ አኳኋን እየገለጡ በዓለ ትንሣኤን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያከብራሉ፡፡
መ/ር ነቢዩ ኤልያስ
https://t.me/neamn_media
ቄጠማ የምሥራች ምልክት ነው ቄጠማው የምሥራች ምልክት ተደርጐ የተወሰደው በኖኅ ዘመን ከተፈጸመው ታሪክ ጋር በማቆራኘት ነው ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን በጻድቁ ኖኅ ዘመን የነበሩ ሕዝቦች ከሕገ እግዚአብሔር ውጪ ኾነው እጅግ የሚያሳዝን ኃጢአት በሠሩ ጊዜ በንፍር ውኃ ተጥለቅልቀዋል፡፡ በወቅቱ ጻድቁ ኖኅ ወደ መርከብ ይዞአቸው ከገባው እንስሳት መካከል የውኃውን መጉደል ለመረዳት ርግብን በመርከብ መስኮት አሾልኮ ይለቃታል፤ እርሷም ቄጠማ በአፍዋ ይዛ ትመልሳለች፡፡ ኖኅም በዚህ ቄጠማ የውኃውን መድረቅ ተረድቶ ተደስቷል
(ዘፍ. ፱፥፩-፳፱)
ቄጠማ ለጥፋት ውኃ መድረቅ የምሥራች መንገሪያ እንደ ኾነ ዅሉ
አሁንም ‹‹በክርስቶስ ሞት ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ፤›› ስትል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለልጆቿ ቄጠማ ታድላለች፡፡
ምእመናንም የምሥራች ተምሳሌት የኾነውን ቄጠማ በግንባራቸው ያስሩታል፡፡ የክርስቶስ ተከታዮች ዅሉ ከጨለማ ወደ ብርሃን፤ ከዋዕየ ሲኦል (የሲኦል ቃጠሎ) ወደ ጥንተ ማኅደራቸው ገነት መመለሳቸውን በዚህ አኳኋን እየገለጡ በዓለ ትንሣኤን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያከብራሉ፡፡
መ/ር ነቢዩ ኤልያስ
https://t.me/neamn_media
Telegram
ነአምን media
Buy adds:- https://telega.io/c/neamn_media
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
<< ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአበሔር!>>
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ
#ትምህርቶች
#ዝማሬዎችና
#ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስነ-ፅሁፎች
የሚለቀቁበት ቻናል ነው።
ለሁሉም መረጃና አስተያየትና በቻናሉ ላይ ለመፃፍና ለመሳተፍ @theofloss ያናግሩን መረጃውንም ያካፍሉን።
"ዓለም እንደ አጠቃላይ በጨለማ ተውጦ ሲተረማመስ የሚታየው ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ምርጫው ስላደረገ ነው።" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወስምንቱ ዓመተ ምሕረት!
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን-
በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ከሀገር ዉጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፣
በቤዛዊ መሥዋዕትነቱ ከሞተ ኃጢአት ታድጎ የትንሣኤ ሙታንን በር የከፈተልን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
"ወአነ እሜው ነፍስየ ቤዛ አባግዕየ ከመ ካዕበ አንሥእ፤አንሥእ፤
ዳግመኛ አነሣት ዘንድ ነፍሴን የበገቼ ቤዛ አድርጌ እሰጣለሁ ዮሐ 10፥17
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰብአዊ ክዋኔው ሰው ቢሆንም በመለኮታዊ ክዋኔው የአብና የመንፈስ ቅዱስ ቃል ወይም ወልደ እግዚአብሔር ነው፣
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወስምንቱ ዓመተ ምሕረት!
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን-
በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ከሀገር ዉጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፣
በቤዛዊ መሥዋዕትነቱ ከሞተ ኃጢአት ታድጎ የትንሣኤ ሙታንን በር የከፈተልን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
"ወአነ እሜው ነፍስየ ቤዛ አባግዕየ ከመ ካዕበ አንሥእ፤አንሥእ፤
ዳግመኛ አነሣት ዘንድ ነፍሴን የበገቼ ቤዛ አድርጌ እሰጣለሁ ዮሐ 10፥17
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰብአዊ ክዋኔው ሰው ቢሆንም በመለኮታዊ ክዋኔው የአብና የመንፈስ ቅዱስ ቃል ወይም ወልደ እግዚአብሔር ነው፣
በመሆኑም በሰብአዊ ክዋኔው መዋች ሲሆን በመለኮታዊ ክዋኔው ተነሽና አንሺ ነው፤ ከዚህ አንጻር ሥግው ቃል ሁለቱንም ተግባራት በአንድ አካልና ክዋኔ የመፈጸም ሥልጣን አለው፣ ይህም በመሆኑ ራሴን የማኖርና የማንሣት ሥልጣን አለኝ በማለት እውነታውንና ምንነቱን አሳየ፤
ጌታችን ይህንን አስመልክቶ ከመሞቱና ከመነሣቱ በፊት ለቅዱሳን ሐዋርያት በተደጋጋሚ አስረድቶአል፣ ስለሆነም የጌታችን ሞትና ትንሣኤ ድንገተኛና የግድ ሳይሆን ታውቆ ያደረና የውድ እንደሆነ ከዚህ እውነታ እንረዳለን፤
ጌታችን ይህንን ተግባር በውድ ፈቃዱ የፈጸመው በእግዚአብሔር አሰራር ከዚህ ውጭ የዓለም ድኅነት የሚከናወንበት ዕድል ስለሌለ ነው፤ በእግዚአብሔር አሰራር ኃጢአትና በደል የሚሰረዘው በቤዛዊ መሥዋዕት ብቻ እንደሆነ ከብሉይ ኪዳን ጀምሮ በነበረው የቤዛዊ መሥዋዕት አቀራረብ የታወቀ ነው፤
በመሆኑም የሰውን ምልአት ኃጢአት ሙሉ በሙሉ ሰርዞ ሰውን ከሞት ቅጣት ነጻ ለማውጣት ብቃት ያለው ቤዛዊ መሥዋዕት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ነበረበት፤ ይሁን እንጂ ለዚህ ዓይነቱ ቤዛዊ መሥዋዕት ብቁ የሆነ ከፍጡራን ወገን ስላልተገኘ "ለሊሁ መሥዋዕት፣ ወለሊሁ ሠዋዒ፣ ወለሊሁ ተወካፌ መሥዋዕት ማለትም" ራሱ መሥዋዕት፣ ራሱ መሥዋዕት አቅራቢ ሊቀ ካህናት፣ ራሱ ተወካፌ መሥዋዕት አምላክ ሆኖ የቤዛነታችንን መሥዋዕት ራሱ በራሱ ለራሱ አቀረበ"፤
በዚህ ቤዛዊ መሥዋዕትም እኛን ከሞት ቅጣት ነጻ አደረገን፤ትንሣኤያችንንም በትንሣኤው አበሰረ፣ በክርስትና ሃይማኖት የሚገኝ ፍጹም ድኅነትና ነጻነት በዚህ ቤዛዊ መሥዋዕት ላይ የተመሠረተ ነው፤
የተወዳደችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ጌታችን በትንሣኤው ትንሣኤያችንን ሲያበስረን የትንሣኤ ሰዎች ሆነን በመንፈስና በሞራል በማደግ ብርሃናተ ዓለም ልንሆን እንጂ እንደገና የጨለማው ኃይል መሳሪያዎች ልንሆን አይደለም፤ የሞቱና የትንሣኤው ምስጢር በንጹሁ ኅሊናችን ካስተዋልነው ውስጣችን እሱን ለመቀበል የሚያዳግተው አይደለም፤
ከዚህ አንጻር በትንሣኤው አምነን ትንሣኤያችንን እየተጠባበቅን የምንገኝ ሕዝበ ክርስቲያን በቅን አስተሳሰብ፣በርቱዕ አእምሮና በኃይለ ሃይማኖት እየታገዝን ጨለማውን ዓለም ወደ ብርሃን ለመለወጥ መጣርና መትጋት ይጠበቅብናል፤
የጨለማው ዓለም መንፈስ ሊያጠፋን ካልሆነ በቀር እንደማይጠቅመን በተጨባጭ የምናውቀው ነው፤ ወደድንም ጠላንም ያለን ብቸኛ አማራጭ ብርሃንን መከተል ነው፤ እሱም እግዚአብሔር ነው በብርሃን የሚመላለስ እንደማይጐዳ በእግዚአብሔር የሚኖርም ተጐድቶ አያውቅምና ነው፤
ዓለም እንደ አጠቃላይ በጨለማ ተውጦ ሲተረማመስ የሚታየው ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ምርጫው ስላደረገ ነው፤ ስለሆነም የኛ ምርጫ ብርሃን የሆነውን እግዚአብሔር እንዲሆን የቤተ ክርስቲያን የዘወትር ጥሪ ነው ፤
በመጨረሻም፡-
የትንሣኤ በዓላችንን ስናከብር ዓለም በክፋቱ ያጨለመባቸውን ወገኖች ጦማችው እንዳይውሉ ካለን ከፍለን የተራቡትን በማብላት፤ የተጠሙትን በማጠጣት፣ የታረዙትን በማልበስና የዕለቱ ደስታ ተካፋይ እንዲሆኑ በማድረግ ቀኑ ለሁላችንም ፍጹም ብርሃን ሆኖ ይውል ዘንድ ክርስቲያናዊ ግዴታችንን እንድንወጣ ጥሪያችንን በእግዚአብሑር ስም እናስተላልፋለን፤
መልካም የትንሣኤ በዓል ያድርግልን!!
“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ"
“ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አባ ማትያስ
ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፤
ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ' ኢትዮጵያ
ጌታችን ይህንን አስመልክቶ ከመሞቱና ከመነሣቱ በፊት ለቅዱሳን ሐዋርያት በተደጋጋሚ አስረድቶአል፣ ስለሆነም የጌታችን ሞትና ትንሣኤ ድንገተኛና የግድ ሳይሆን ታውቆ ያደረና የውድ እንደሆነ ከዚህ እውነታ እንረዳለን፤
ጌታችን ይህንን ተግባር በውድ ፈቃዱ የፈጸመው በእግዚአብሔር አሰራር ከዚህ ውጭ የዓለም ድኅነት የሚከናወንበት ዕድል ስለሌለ ነው፤ በእግዚአብሔር አሰራር ኃጢአትና በደል የሚሰረዘው በቤዛዊ መሥዋዕት ብቻ እንደሆነ ከብሉይ ኪዳን ጀምሮ በነበረው የቤዛዊ መሥዋዕት አቀራረብ የታወቀ ነው፤
በመሆኑም የሰውን ምልአት ኃጢአት ሙሉ በሙሉ ሰርዞ ሰውን ከሞት ቅጣት ነጻ ለማውጣት ብቃት ያለው ቤዛዊ መሥዋዕት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ነበረበት፤ ይሁን እንጂ ለዚህ ዓይነቱ ቤዛዊ መሥዋዕት ብቁ የሆነ ከፍጡራን ወገን ስላልተገኘ "ለሊሁ መሥዋዕት፣ ወለሊሁ ሠዋዒ፣ ወለሊሁ ተወካፌ መሥዋዕት ማለትም" ራሱ መሥዋዕት፣ ራሱ መሥዋዕት አቅራቢ ሊቀ ካህናት፣ ራሱ ተወካፌ መሥዋዕት አምላክ ሆኖ የቤዛነታችንን መሥዋዕት ራሱ በራሱ ለራሱ አቀረበ"፤
በዚህ ቤዛዊ መሥዋዕትም እኛን ከሞት ቅጣት ነጻ አደረገን፤ትንሣኤያችንንም በትንሣኤው አበሰረ፣ በክርስትና ሃይማኖት የሚገኝ ፍጹም ድኅነትና ነጻነት በዚህ ቤዛዊ መሥዋዕት ላይ የተመሠረተ ነው፤
የተወዳደችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ጌታችን በትንሣኤው ትንሣኤያችንን ሲያበስረን የትንሣኤ ሰዎች ሆነን በመንፈስና በሞራል በማደግ ብርሃናተ ዓለም ልንሆን እንጂ እንደገና የጨለማው ኃይል መሳሪያዎች ልንሆን አይደለም፤ የሞቱና የትንሣኤው ምስጢር በንጹሁ ኅሊናችን ካስተዋልነው ውስጣችን እሱን ለመቀበል የሚያዳግተው አይደለም፤
ከዚህ አንጻር በትንሣኤው አምነን ትንሣኤያችንን እየተጠባበቅን የምንገኝ ሕዝበ ክርስቲያን በቅን አስተሳሰብ፣በርቱዕ አእምሮና በኃይለ ሃይማኖት እየታገዝን ጨለማውን ዓለም ወደ ብርሃን ለመለወጥ መጣርና መትጋት ይጠበቅብናል፤
የጨለማው ዓለም መንፈስ ሊያጠፋን ካልሆነ በቀር እንደማይጠቅመን በተጨባጭ የምናውቀው ነው፤ ወደድንም ጠላንም ያለን ብቸኛ አማራጭ ብርሃንን መከተል ነው፤ እሱም እግዚአብሔር ነው በብርሃን የሚመላለስ እንደማይጐዳ በእግዚአብሔር የሚኖርም ተጐድቶ አያውቅምና ነው፤
ዓለም እንደ አጠቃላይ በጨለማ ተውጦ ሲተረማመስ የሚታየው ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ምርጫው ስላደረገ ነው፤ ስለሆነም የኛ ምርጫ ብርሃን የሆነውን እግዚአብሔር እንዲሆን የቤተ ክርስቲያን የዘወትር ጥሪ ነው ፤
በመጨረሻም፡-
የትንሣኤ በዓላችንን ስናከብር ዓለም በክፋቱ ያጨለመባቸውን ወገኖች ጦማችው እንዳይውሉ ካለን ከፍለን የተራቡትን በማብላት፤ የተጠሙትን በማጠጣት፣ የታረዙትን በማልበስና የዕለቱ ደስታ ተካፋይ እንዲሆኑ በማድረግ ቀኑ ለሁላችንም ፍጹም ብርሃን ሆኖ ይውል ዘንድ ክርስቲያናዊ ግዴታችንን እንድንወጣ ጥሪያችንን በእግዚአብሑር ስም እናስተላልፋለን፤
መልካም የትንሣኤ በዓል ያድርግልን!!
“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ"
“ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አባ ማትያስ
ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፤
ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ' ኢትዮጵያ
❤1👍1
Forwarded from Orthodox Tewahdo
🧕👉🏾 ሴት በወር አበባዋ ጊዜ መጸለይ ትችላለች⁉️
👉🏾 ግለ አውናን / ሴጋ /ማስተርቤሽን/ የፈጸመ ሰው ተክሊል ማግባት ይችላልን❔
👉🏾 በሱባኤ ወቅት ህልመ ሌሊት (ዝንየት) ቢመታን ምን እናደርጋለን❓
👉🏾 ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን‼️
👉🏾 ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል❕
👉🏾 ከዝሙት አጋንንት እና ከዝንየት በተጨማሪ በሕልመ ሌሊት የሚፈትነን አጋንንት የትኛው ነው❓
👉🏾 የሕልመ ሌሊት መፍትሔ ምንድን ነው⁉️
👉🏾 ቁርባን ቆርበን ሕልመ ሌሊት እንዳይጸናወተን ምን ማድረግ አለብን⁉️❤️በማርያም ይህን ቻናል ይቀላቀሉ❤️
👇👇👇
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
█ 𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲ █
◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢
👉🏾 ግለ አውናን / ሴጋ /ማስተርቤሽን/ የፈጸመ ሰው ተክሊል ማግባት ይችላልን❔
👉🏾 በሱባኤ ወቅት ህልመ ሌሊት (ዝንየት) ቢመታን ምን እናደርጋለን❓
👉🏾 ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን‼️
👉🏾 ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል❕
👉🏾 ከዝሙት አጋንንት እና ከዝንየት በተጨማሪ በሕልመ ሌሊት የሚፈትነን አጋንንት የትኛው ነው❓
👉🏾 የሕልመ ሌሊት መፍትሔ ምንድን ነው⁉️
👉🏾 ቁርባን ቆርበን ሕልመ ሌሊት እንዳይጸናወተን ምን ማድረግ አለብን⁉️❤️በማርያም ይህን ቻናል ይቀላቀሉ❤️
👇👇👇
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
█ 𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲ █
◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢
Forwarded from Zᴇᴍɴᴇ Aᴅᴠᴇʀᴛɪsɪɴɢ.
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM