STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.7K subscribers
11K photos
272 videos
452 files
1.94K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
#እንድታውቁት

የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ፤ የአቃቂ ክፍል 2 (New CT) የውሃ ግፊት መስጫ የሀይል አስተላላፊ መስመር ፖሎች መውደቃቸውን አሳውቋል።

ባለስልጣኑ የሀይል አስተላላፊ ፖሎቹ ትላንት መውደቃቸውን ገልፆ ተተክለው ስራ እስከሚጀምሩ የውሃ ስርጭት ከታች በተዘረዘሩት አካባቢዎች በከፊል እና በሙሉ መቋረጡን አሳውቋል።

አካባቢዎቹ ፦

• ቦሌ ክፍለ ከተማ፡- ወረዳ 1፣ 2፣ 3፣ 12፣ 13
• ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፡- ወረዳ 1፣ 2፣ 3፣ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 8፣ 9፣ 10፣ 11
• ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፡- ወረዳ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 8፣ 9፣ 10፣ 11፣ 12
• አቃቂ ክፍለ ከተማ፦ ወረዳ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 8
• ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8

ችግሩ ስፋት እንዳለው የገለፀው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የአዲስ አበባ ኤሌትሪክ አገልግሎት የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ጠይቋል።

መረጃዎችን እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#እንድታውቁት‼️

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ተከልክሏል / ታገዷል።

ከዛሬ ጀምሮ በከተማዋ በየትኛውም አካባቢ ላልተወሰነ ጊዜ የባጃጅ አገልግሎት መከልከሉን / መታገዱን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ " የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን በተሻለ መልክ ለመምራት እንዲያስችል አሰራር ማሻሻያ ስራዎችን በማከናወን ላይ እገኛለው " ብሏል።

የአሰራር ማሻሻያ ስራው ተጠናቆ እንዲሁም የአገልግሎቱ አስፈላጊነት በዝርዝር ተጠንቶ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ከዛሬ የካቲት 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በከተማዋ በየትኛውም አከባቢ #ላልተወሰነ_ጊዜ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት የታገደ መሆኑን ቢሮው አሳውቋል።

የተጣሩ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#እንድታውቁት

የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን የመማር ማስተማር ሂደት ለማስቀጠል በዝግጅት ላይ እንደሆነ ገልጿል።

በመሆኑም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ #የማይገኙ ሁሉም የዲግሪ (መደበኛ፣ ኤክስቴንሽን፣ ክረምት) እንዲሁም የማስተርስ (መደበኛ፣ ኤክስቴንሽን ፣ ክረምት) ተማሪዎች ከዚህ በታች ባለው ሊንክ እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል።

ሊንክ ፦ http://196.190.28.50

ምዝገባው የሚያበቃበት ቀን ሚያዚያ 18 ቀን 2015 ዓ/ም መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።

ለበለጠ መረጃ ደግሞ ዘውትር በየስራ ሰአት በሚከተሉት ቁጥሮች መወደወል ይቻላል ፦ 0914485592 / 0921990158

ከኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ #የራያ_ዩኒቨርሲቲም በጦርነት የተቋረጠውን መደበኛ ትምህርት ለማስቀጠል እየሰራ ይገኛል።

በዚህም ከ2ኛ እስከ 5ኛ ዓመት በራያ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩና ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የመማር እድል ያላገኙ ተማሪዎች ከ09/08/2015 ዓ/ም እስከ 13/08/2015 ዓ/ም ባሉ የስራ ቀናት እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።

ተማሪዎች የሚመዘገቡት ለዩኒቨርስቲው ረጅስትራር እየደሉ ሲሆን የስልክ ቁጥሮቹ 0970140000፣ 0970240000 ፣ 0970230000 ናቸው። ተማሪዎች ዘውትር በስራ ሰዓት ብቻ እንዲደውሉ ጥሪ ቀርቧል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot