STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.8K subscribers
11K photos
271 videos
452 files
1.93K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
#MoE

የትምህርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙት ሃላፊ ወ/ሮ አመለወርቅ ህዝቅኤል ትላንት ለአሀዱ በሰጡት ቃለ ምልልስ ወቅት የአቅም ማሻሻያ ትምህርት " ለአንድ ዓመት " በሚል የተገለፀው ስህተት እንደሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀው እንዲታረም ብለዋል።

የአቅም ማሻሻያ (ሬሜዲያል) የሚሰጠው ከዚህ በፊት እንደተገለፀው ለአራት ወራት እንደሆነ አመልክተዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ውጤታቸው ከግማሽ በታች የሆኑትን በቅድመ መደበኛ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ጉድለታቸውን እንዲሞሉ ኮርስ እንደሚወስዱ ከዚህ ቀደም መግለፁ ይታወሳል።

እነኚህ ተማሪዎች ያለባቸውን ጉድለት የሚሞላው የሬሜዲያል ፕሮግራም ይከታተላሉ፤  ዋና ዋና ይዘቶች እና መታወቅ ያለባቸውን እስከ #አራት_ወር ተወስዶ ተማሪዎቹ አቅማቸውን የሚሞላ ትምህርቶችን እንዲማሩና እንዲከልሱ ይደረጋል።

የሬሚዲያል ፕሮግራሙ ተጠቃሚ ተማሪዎች ተከታታይ ምዘና እንዲኖራቸው ተደርጎ በየተቋማት የሚሰጠው ምዘና 30 % እና በማዕከል የሚዘጋጀው ፈተና 70% ተመዝነድ በድምሩ አማካይና ከዚያ በላይ (50 ከመቶና በላይ) የሚያመጡት በመንግስት ተቋማት ሲከታተሉ የቆዩት በዚያው ተቋም መቀጠል የሚችሉ ሲሆን በራሳቸው ወጪ ሸፍነው ወደ ግል ተቋማት ሄደው መማር ቢፈልጉ መብታቸው የተጠበቀ ይሆናል።


የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot