STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.8K subscribers
11K photos
271 videos
452 files
1.93K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
#ETA

የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን እስከ የካቲት 2014 ዓ.ም ድረስ ያጠናቀራቸውን የ350 ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን እና የትምህርት መስኮቻቸውን የእውቅና ፈቃድ የሚገልጽ የተሟላ መረጃ ይፋ አድርጓል፡፡

ይፋ የተደረገው መረጃ እስከ የካቲት ወር 2014 ዓ.ም ድረስ ያለውን የእውቅና ፈቃድ መሆኑን ያሳወቀው ባለሥልኑ በሂደት ላይ ያሉ የእውቅና ፈቃድ እና የእውቅና ፈቃድ እድሳት ጥያቄዎች ውሳኔ ሲያገኙ፣ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች የእውቅና ፈቃድ ሲሰረዝ እና በሌሎች ምክንያቶች ውሳኔዎች ምክንያት ለውጦች በሚኖሩበት ወቅት የመረጃ ለውጥ ሊኖር እንደሚችል ገልጿል፡፡

በመሆኑም ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ ቀጣሪና የሙያ ፈቃድ የሚሰጡ ድርጅቶች፣ የሚዲያና ማስታወቂያ ተቋማት፣ እንዲሁም መላው ህብረተሰብ የተቋማቱን ወቅታዊ መረጃ በመከታተል ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ባለሥልጣኑ በጥብቅ አሳስቧል።ተቋማትም ይፋ ከተደረገው የእውቅና ፈቃድ መረጃ ውጪ ተማሪ ተቀብለው ቢያስተምሩ ህጋዊና አስተዳደራዊ #እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ባለስልጣኑ አሳውቋል፡፡

ተጨማሪ ማሳሰቢያ(ለተቋማት)፡- ይፋ በተደረገው መረጃ የማስተካከያ ጥቆማ የሚኖራቸው ተቋማት በህጋዊ ተወካዮቻቸው በኩል ለባለስልጣኑ ማሳወቅ የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ተማሪ ነክ መረጃዎችን እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
ከኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የተሰጠ ማሳሰቢያ

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ መርሀ ግብር ለመማር የሚመዘገቡ ተማሪዎች የሚከተሉትን የቅበላ መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል።

እነዚህም፡-
1. የመሰናዶ ትምህርት ያጠናቀቁ ተማሪዎች ከሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ለትምህርት ዘመኑ ያስቀመጠውን የመቁረጫ ነጥብ ሊያሟሉ ይገባል፡፡

2. ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም የተመረቁ ባለሙያዎች ከሆኑ ከሠለጠኑበት የሙያ መስክ ጋር ተዛማጅነት ባለው የሥልጠና መስክ በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ በደረጃ 4 (ወይም በቀድሞ 10+3 ወይም 12+2) ያጠናቀቁ ሆነው በሙያው ደረጃ 4 የብቃት ማረጋገጫ ምዘና (COC level 4) ተፈትነው ያለፉበትን፤ እንዲሁም በሙያው ቢያንስ የሁለት ዓመት ሥራ ልምድ ያላቸው መሆኑን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች በምዝገባው እለት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

3. ከውጭ ሀገር የተገኘ የትምህርት ማስረጃ ለዲግሪ መርሃ-ግብር መግቢያ የሚያገለግለው በባለስልጣኑ የአቻ ግምት ሲሰራለት ብቻ ይሆናል፡፡


4. በየተቋማቱ የሚዘጋጁትን የመግቢያ ፈተናዎች ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፤ ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች በምዝገባው ዕለት ማቅረብ ያልቻለ ተመዝጋቢ ህጋዊ ተቀባይነት አይኖረውም።

ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን እና ሌሎች ህጋዊ መመሪያዎችን ጥሶ የተገኘ ተቋም በከፍተኛ ትምህርት ተቋም የስነ ስርዓት መመሪያ መሠረት በህግ ተጠያቂ እንደሚሆን እየገለጽን፤ ከህግ ውጪ ገብተው የሚማሩ ተማሪዎችም ሊደርስባቸው የሚችለውን የጊዜ፣ የገንዘብና የስነ-ልቦና ኪሳራ አውቀው አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ባለስልጣኑ ያሳስባል። #ETA


ተማሪ ነክ መረጃዎችን እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#ETA

ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው ተማሪ መዝግበው ሲያስተምሩ የነበሩ ሦሥት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማግኘቱን የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን አሳውቋል።

ተቋማቱን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሠራ መሆኑን ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡

ባለስልጣኑ ከግንቦት 13 እስከ ሰኔ 01/2014 ዓ.ም በተለያዩ የክልል ከተሞች ባካሄደው ድንገተኛ ፍተሻ፤ ምንም አይነት የእውቅና ፈቃድ ሳይኖራቸው በከፍተኛ ትምህርት ደረጃ ተማሪ መዝግበው በማስተማር ላይ የነበሩ ሦሥት ተቋማት ማግኘቱን ተናግሯል።

ተቋማቱ የሚከተሉት መሆናቸውን ባለስልጣኑ ገልጿል፡-

• "ጅኤ ኢንደስትሪያል ኮሌጅ" ~ በአማራ ክልል (በደብረማርቆስ ከተማ እና አካባቢው)
• "ኦሞ ቫሊ ዩኒቨርሳል ኮሌጅ" ~ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል (በዳውሮ ፣ በተርጫ)
• "ሆርን ኦፍ አፍሪካ ቢዝነስ ኮሌጅ" ~ በኦሮሚያ ክልል (በአምቦ ከተማ እና አካባቢው)

የክልሎቹ መንግስታት ህግ የማስከበር ድርሻቸውን እንዲወጡ የጠየቀው ባለስልጣኑ፤ ህገ-ወጥ ተቋማቱን የከፈቱ አካላት የፈጸሟቸው የህግ ጥሰቶች ካሉ በሚመለከታቸው የፍትሕ አካላት ተጠያቂ እንደሚደረጉ ባለሥልጣኑ አረጋግጧል።

ከዚህ በፊት በደቡብ ክልል 'ፊንላንድ ኮሌጅ' በሚል እና በአማራ የክልል 'ሀምበርቾ ኮሌጅ' በሚል ራሳቸውን የሰየሙ ህገ-ወጥ አካላት መኖራቸውን ለክልል መንግስታቱ ማሳወቁን ባለሥልጣኑ አስታውሷል።

ተማሪ ነክ መረጃ እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#ETA

የትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን ሁሉም የግል የከፍተኛ  ትምህርት ተቋማት አሁን በመማር ላይ የሚገኙ ተማሪዎችን ዝርዝር መረጃ እንዲልኩ አሳሰበ።

ባለሥልጣኑ አሁን በግል የከፍተኛ ትምህርት ቋማት በመማር ላይ የሚገኙ  ተማሪዎች የተመዘገቡበትን አግባብ ማየት አስፈላጊ ሆኖ በማግኝቱ እውቅና በሰጣቸው የትምህርት መስኮች በትምህርት ላይ የሚገኙ የተማሪዎችን  የስም ዝርዝር የያዘ መረጃ በሶፍትና በሀርድ ኮፒ በማጠናቀር በ30 ቀናት ውስጥ እንዲልኩ አሳስቧል፡፡

የሚላከው የተማሪዎች መረጃ  #በፕሬዝዳንት ወይም #በበላይ_ኃላፊ ተፈርሞ መውጣት እንዳለበት ከዚህ ውጪ ፈራሚ አካል ካለ  ስምና  ኃላፊነት የሚገልጽ ደብዳቤ  በነዚሁ የበላይ ኃላፊዎች እንዲገለጽ  እና  የተማሪዎችን መረጃ  በተናጥል በሚልኩ  ተቋማት ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በሁለት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ካምፓሶች ላይ የእርምት እርምጃ ወስዷል፡፡

ባለሥልጣኑ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ባደረገው ድንገተኛ የፍተሻ ጉብኝት የስነ ስርዓት ጥሰት ፈጽመው በተገኙ ሁለት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃ መውሰዱን አሳውቋል፡፡

ባለስልጣኑ ግሬት ኮሌጅ መገናኛ፣ ቦሌ ሚካኤል እና ቡልቡላ ካምፓሶች እንዲሁም ሮያል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሰሜን ካምፓስ ላይ የማስተካከያ እርምጃ ወስዷል፡፡

ከተፈቀደለት የተማሪዎች ቁጥር በላይ መዝግቦ ማስተማር፣ ፈቃድ ሳያገኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር፣ ከባለስልጣኑ ባልተሰጠው ፈቃድ ትምህርት መስጠት፤ ተቋማቱ ከፈጸሟቸው ጥሰቶች መካከል ይጠቀሳሉ።

ተቋማቱ ጥሰት በፈጸሙባቸው የትምህርት መስኮች ያሉ ተማሪዎችን እንዲያሰናብቱ እንዲሁም በመስኮቹ ለተከታታይ ከሁለት እስከ ሦሥት ዓመታት ፈቃድ እንዳይጠይቁ እግድ ተጥሎባቸዋል፡፡

በተፈፀመው የህግ ጥሰት ግኝት የተቋሙ ባለሀብቶች እና የበላይ አመራሮች በፍትሐ ብሄር እና በወንጀል ህግ የሚያስጠይቅ ተግባር ካለ በሚመለከታቸው የፍትህ አላካት ተጠያቂ የሚያደረግ መሆኑን ባለሥልጣኑ ገልጿል፡፡

ተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

በትምህርት ስልጠና ባለሥልጣን የትክክለኛነት ማጣራት ከሚደረግባቸው የትምህርት ማስረጃዎች ውስጥ ከ5 እስከ 10 በመቶ የሚሆኑት ሐሰተኛ ሆነው እንደሚገኙ ተቋሙ ኣሳውቋል፡፡

ማስረጃዎቹ በተጭበረበረ መንገድ ከመዘጋጀታቸው በተጨማሪ ከባለሥልጣኑ ዕውቅና ባላገኘ ተቋም አማካይነት የተሰጡ መሆናቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል፡፡

ማስረጃዎቹ በብዛት የትምህርት ክፍሉን ለማስተማር ፈቃድ ሳይኖረው ከሚያስተምር የትምህርት ተቋም የተወሰዱ መሆናቸውን በባለሥልጣኑ የተቋማት ቁጥጥርና ኢንስፔክሽን የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቸሩጌታ ገነነ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።

የግል እና የመንግስት ተቋማት የሠራተኞቻቸውን የትምህርት ማስረጃ ትክክለኛነት ወደ ተቋሙ ልከው እንዲጣራ የማድረግ ፍላጎታቸው እየጨመረ እንደሚገኝ ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የስነ-ስርዓት ጥሰት በሚፈጽሙ ተቋማት ላይ አስተማሪ ቅጣት ለማሳለፍ የሚያስችለውን የስነ-ስርዓት መመሪያ አሻሽሏል።

መመሪያው በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ በባለሥልጣኑ የፈቃድ እና ጥራት ኦዲት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ውብሸት ታደለ በተለይ ለቲክቫህ ተናግረዋል።

አዲሱ መመሪያ የስነ-ስርዓት ጥሰት በሚፈጽሙ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ ጠንካራ፣ ተመጣጣኝ እና የሚያስተምር እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

ተደጋጋሚ ጥፋት በሚፈጽሙ ተቋማት ላይ ፈቃድ መሰረዝ እና ማዘጋት እርምጃዎችም ይወሰዳሉ ብለዋል።

ተቋማቱ ከሚነሱባቸው የስነ-ስርዓት ጥሰቶች መካከል
ፈቃድ ባልተሰጣቸው የትምህርት መስኮችና ካምፓሶች ማስተማርን ጨምሮ ከተፈቀደላቸው ቁጥር በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይገኙበታል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በርቀት መርሐ ግብር በ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም በሚያስተምሩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ዕርምጃ ይወስዳል።

በርቀት መርሐ ግብር በ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም ማስተማር የማይቻል መሆኑን የገለጸው ባለሥልጣኑ፤ ተማተማሪዎች ሲመዘግቡም ሆነ ሲያስተምሩ በሚገኙ ተቋማት ላይ ጠበቅ ያለ ዕርምጃ ይወሰዳል ብሏል።

በተመሳሳይ በየትኛውም መርሐ ግብር በሕግ፣ በግብርና እና በመምህራን ትምህርት ስልጠና መስጠት እንደማይቻል ባለሥልጣኑ አስታውሷል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#የትምህርትና_ስልጠና_ባለሥልጣን

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን መረጃ አሟልተው የላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

እስካሁን አንድ ዩኒቨርሲቲ፣ አንድ ተቋም እና 18 ኮሌጆች የተሟላ መረጃ መላካቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል።

(የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን የተሟላ መረጃ የላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ።) #ETA

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና (Exit Exam) የሚወስዱ ተማሪዎችን መረጃ የላኩ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዝርዝር፡-


1. ሐይላንድ ኮሌጅ
2. አሜሪካን ኮሌጅ ኦፍ ቴክኖሎጂ
3. ሆፕ ኢንተርፕራይዝ ዩንቨርስቲ ኮሌጅ
4. ፕሪሚየም ኮሌጅ
5. አንድነት ኢንተርናሽናል ኮሌጅ
6. ያኔት ኮሌጅ
7. ኢትዮጵያ ካቶሊክ ከፍተኛ የትምህርት
8. ካኔኑስ ኮሌጅ
9. አክሞንሊንክ ኮሌጅ
10. መካነየሱስ ማኔጅመንትና ሊደርሺፕኮሌጅ
11. ሳታ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ
12. ሉናር ኢንተርናሽናል ኮሌጅ
13. ብሉ ናይል ኮሌጅ
14. ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ
15. ፋሆባ ኮሌጅ
16.  ባምባ ኮሌጅ
17.  አዲስ አምባ ኮሌጅ
18.  ባቢት  ቢዝነስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
19. ግዮን ቴክኖሎጂ ኮሌጅ እና
20. ጮቄ ፋና ኮሌጅ ናቸው፡፡
21. ድሪም ላንድ ኮሌጅ                        
22. ቤቴል ሜዲካል ኮሌጅ
23. ላልዛግ ኮሌጅ
24. ጉዛራ ኮሌጅ
25. ፍኖተ ብርሀን ኮሌጅ
26. አግሮ ቴክኒካል ኮሌጅ
27. ፋርማ ኮሌጅ
28. .ምስራቅ ግዮን ኮሌጅ
29. አባይ ምንጭ
30. አርባምንጭ መካነየሱስ ቴክኒክ ኮሌጅ
31. ፓራሜድ ኮሌጅ
32. ትሮፒካል ኮሌጅ ኦፍ ሜዲስን
33. ጎቶኒያል ኮሌጅ
34. አያት ሜዲካል ኮሌጅ
35. ሆራይዘን ኮሌጅ
36. እናት ኮሌጅ
37. ራዳ ኮሌጅ
38. ኢንኮዶ ኮሌጅ
39. ግሎባል ኮሌጅ
40. ጋምቢ ኮሌጅ
41. ቢፍቱ ኮሌጅ እና
42. ቴክ- ዞን ኢንጅነሪንግና ቢዝነስ ኮሌጅ ናቸው፡፡

#ETA

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
#የትምህርትና_ስልጠና_ባለሥልጣን

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን መረጃ አሟልተው የላኩ 145 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

እስካሁን የተሟላ ዝርዝር ከላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል አምስት ዩኒቨርሲቲዎች ማለትም ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ፣ ሐራምቤ ዩኒቨርሲቲ፣ አድማስ ዩኒቨርሲቲ፣ ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ እና ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ይገኙበታል።

(የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን የተሟላ መረጃ የላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዝርዝር ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ።) #ETA

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ የሚፈልጉ ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው የማረጋገጫ ወረቀት ማግኘት የሚችሉበት ስርዓት እየዘረጋ መሆኑን የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አሳውቋል።

ዲጂታል ስርዓቱ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገባ በተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች የሚገኙ ተገልጋዮች ካሉበት ሆነው ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።

እስካሁን በተደረገ የትምህርት ማስረጃ የማረጋገጥ ሥራ ከ5 እስከ 6 በመቶ የሚሆኑት ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ሆነው መገኘታቸውን የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቸሩጌታ ገነነ ለኢፕድ ተናግረዋል።

"ይህንን በሚፈጽሙ ተቋማት ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ የመረጃ ማደራጀት ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ" ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎችን የተመለከተ መረጃ ለትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተፈታኝ ተማሪዎቻቸውን የመግቢያ ስም እና የይለፍ ቃል መውሰድ እንደሚችሉ ተገለጸ፡፡

ባለሥልጣኑ ከትምህርት ሚኒስቴር የመጣለትን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተፈታኝ ተማሪዎች የመግቢያ ስም እና የይለፍ ቃል እንዲወስዱ ለተቋማቱ ጥሪ አድርጓል፡፡

ለዚህም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የተቋማቸውን ህጋዊ የኢ-ሚይል አድርሻ እና የአንድ ተወካይ ሙሉ ስም እንዲሁም የስልክ አድራሻ በባለሥልጣኑ የኢ-ሚይል አድራሻ eta.gov.et@gmail.com እንዲልኩ ባለሥልጣኑ አሳስቧል፡፡

የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎችን የተመለከተ ሁሉም መረጃ ተቋማቱ በሚልኩት የኢ-ሚይል አድርሻ ብቻ የሚላክ መሆኑን ባለሥልጣኑ ገልጿል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ እና የአቻ ግመታ አገልግሎት ከመስከረም 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ በኦንላይን መስጠት ጀምራል፡፡

በመሆኑ አገልግሎቱን የምትፈልጉ በሙሉ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን ስካን በማድረግና https://neta.gov.et በመጠቀም ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡

በኦንላይን ቀጠሮ ካስያዙ ተገልጋዮች በስተቀር ሌሎች ተገልጋዮችን በአካል #የማያስተናግድ መሆኑን ባለሥልጣኑ አሳውቋል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስኮቻቸው የፈቃድ ወቅታዊ መረጃን አውጥቷል፡፡

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈቃድ ያገኙበትን የትምህርት መስክ፣ ካምፓስ እና መርሐግብር አሟልቶ የያዘና በየጊዜው ወቅታዊ የሚደረግ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈቃድን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፦ https://bit.ly/43Z1Rck

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በቀረበው መረጃ ላይ አስተያየት እና ጥቆማ አዲስ አበባ ጉለሌ ክ/ከተማ ሽሮ ሜዳ አሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኝው የባለሥልጣን መ/ቤቱ በአካል በመገኘት ወይም በኢ-ሚይል አድራሻ hemis.info@gmail.com አማካኝነት እስከ ዓርብ ታህሳስ 19/2016 ዓ.ም ብቻ መላክ የምትችሉ መሆኑን ባለሥልጣኑ አሳስቧል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
እስከ የካቲት 30/2016 ዓ.ም በሶፍት እና በሃርድ ኮፒ እንዲልኩ

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት የተማሪዎቻቸውን ዝርዝር መረጃ እንዲልኩ ጠይቋል፡፡

ፈቃድ በተሰጣቸው የትምህርት መስኮች በ2016 ዓ.ም ተመዝግብው እየተማሩ ያሉ ተማሪዎችን ዝርዝር መረጃ እና በ2015 ዓ.ም የተመረቁ ተማሪዎች (የመውጫ ፈተና ያለፉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች) ዝርዝር መረጃን እስከ የካቲት 30/2016 ዓ.ም በሶፍት እና በሃርድ ኮፒ እንዲልኩ ባለሥልጣኑ አሳስቧል፡፡

ይህም የትምህርት ጥራትና አግባብነት ለማስጠብቅ እንዲሁም የተመረቁ ተማሪዎች መጉላላት እንዳይገጥማቸው ባለሥልጣኑ ለሚያከናውናቸው ተግባራት አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል፡፡ #ETA

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot