STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
39.7K subscribers
11.1K photos
272 videos
452 files
1.94K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
#ETA

በትምህርት ስልጠና ባለሥልጣን የትክክለኛነት ማጣራት ከሚደረግባቸው የትምህርት ማስረጃዎች ውስጥ ከ5 እስከ 10 በመቶ የሚሆኑት ሐሰተኛ ሆነው እንደሚገኙ ተቋሙ ኣሳውቋል፡፡

ማስረጃዎቹ በተጭበረበረ መንገድ ከመዘጋጀታቸው በተጨማሪ ከባለሥልጣኑ ዕውቅና ባላገኘ ተቋም አማካይነት የተሰጡ መሆናቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል፡፡

ማስረጃዎቹ በብዛት የትምህርት ክፍሉን ለማስተማር ፈቃድ ሳይኖረው ከሚያስተምር የትምህርት ተቋም የተወሰዱ መሆናቸውን በባለሥልጣኑ የተቋማት ቁጥጥርና ኢንስፔክሽን የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቸሩጌታ ገነነ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።

የግል እና የመንግስት ተቋማት የሠራተኞቻቸውን የትምህርት ማስረጃ ትክክለኛነት ወደ ተቋሙ ልከው እንዲጣራ የማድረግ ፍላጎታቸው እየጨመረ እንደሚገኝ ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የስነ-ስርዓት ጥሰት በሚፈጽሙ ተቋማት ላይ አስተማሪ ቅጣት ለማሳለፍ የሚያስችለውን የስነ-ስርዓት መመሪያ አሻሽሏል።

መመሪያው በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ በባለሥልጣኑ የፈቃድ እና ጥራት ኦዲት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ውብሸት ታደለ በተለይ ለቲክቫህ ተናግረዋል።

አዲሱ መመሪያ የስነ-ስርዓት ጥሰት በሚፈጽሙ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ ጠንካራ፣ ተመጣጣኝ እና የሚያስተምር እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

ተደጋጋሚ ጥፋት በሚፈጽሙ ተቋማት ላይ ፈቃድ መሰረዝ እና ማዘጋት እርምጃዎችም ይወሰዳሉ ብለዋል።

ተቋማቱ ከሚነሱባቸው የስነ-ስርዓት ጥሰቶች መካከል
ፈቃድ ባልተሰጣቸው የትምህርት መስኮችና ካምፓሶች ማስተማርን ጨምሮ ከተፈቀደላቸው ቁጥር በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይገኙበታል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በርቀት መርሐ ግብር በ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም በሚያስተምሩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ዕርምጃ ይወስዳል።

በርቀት መርሐ ግብር በ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም ማስተማር የማይቻል መሆኑን የገለጸው ባለሥልጣኑ፤ ተማተማሪዎች ሲመዘግቡም ሆነ ሲያስተምሩ በሚገኙ ተቋማት ላይ ጠበቅ ያለ ዕርምጃ ይወሰዳል ብሏል።

በተመሳሳይ በየትኛውም መርሐ ግብር በሕግ፣ በግብርና እና በመምህራን ትምህርት ስልጠና መስጠት እንደማይቻል ባለሥልጣኑ አስታውሷል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#የትምህርትና_ስልጠና_ባለሥልጣን

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን መረጃ አሟልተው የላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

እስካሁን አንድ ዩኒቨርሲቲ፣ አንድ ተቋም እና 18 ኮሌጆች የተሟላ መረጃ መላካቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል።

(የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን የተሟላ መረጃ የላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ።) #ETA

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና (Exit Exam) የሚወስዱ ተማሪዎችን መረጃ የላኩ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዝርዝር፡-


1. ሐይላንድ ኮሌጅ
2. አሜሪካን ኮሌጅ ኦፍ ቴክኖሎጂ
3. ሆፕ ኢንተርፕራይዝ ዩንቨርስቲ ኮሌጅ
4. ፕሪሚየም ኮሌጅ
5. አንድነት ኢንተርናሽናል ኮሌጅ
6. ያኔት ኮሌጅ
7. ኢትዮጵያ ካቶሊክ ከፍተኛ የትምህርት
8. ካኔኑስ ኮሌጅ
9. አክሞንሊንክ ኮሌጅ
10. መካነየሱስ ማኔጅመንትና ሊደርሺፕኮሌጅ
11. ሳታ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ
12. ሉናር ኢንተርናሽናል ኮሌጅ
13. ብሉ ናይል ኮሌጅ
14. ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ
15. ፋሆባ ኮሌጅ
16.  ባምባ ኮሌጅ
17.  አዲስ አምባ ኮሌጅ
18.  ባቢት  ቢዝነስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
19. ግዮን ቴክኖሎጂ ኮሌጅ እና
20. ጮቄ ፋና ኮሌጅ ናቸው፡፡
21. ድሪም ላንድ ኮሌጅ                        
22. ቤቴል ሜዲካል ኮሌጅ
23. ላልዛግ ኮሌጅ
24. ጉዛራ ኮሌጅ
25. ፍኖተ ብርሀን ኮሌጅ
26. አግሮ ቴክኒካል ኮሌጅ
27. ፋርማ ኮሌጅ
28. .ምስራቅ ግዮን ኮሌጅ
29. አባይ ምንጭ
30. አርባምንጭ መካነየሱስ ቴክኒክ ኮሌጅ
31. ፓራሜድ ኮሌጅ
32. ትሮፒካል ኮሌጅ ኦፍ ሜዲስን
33. ጎቶኒያል ኮሌጅ
34. አያት ሜዲካል ኮሌጅ
35. ሆራይዘን ኮሌጅ
36. እናት ኮሌጅ
37. ራዳ ኮሌጅ
38. ኢንኮዶ ኮሌጅ
39. ግሎባል ኮሌጅ
40. ጋምቢ ኮሌጅ
41. ቢፍቱ ኮሌጅ እና
42. ቴክ- ዞን ኢንጅነሪንግና ቢዝነስ ኮሌጅ ናቸው፡፡

#ETA

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
#የትምህርትና_ስልጠና_ባለሥልጣን

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን መረጃ አሟልተው የላኩ 145 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

እስካሁን የተሟላ ዝርዝር ከላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል አምስት ዩኒቨርሲቲዎች ማለትም ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ፣ ሐራምቤ ዩኒቨርሲቲ፣ አድማስ ዩኒቨርሲቲ፣ ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ እና ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ይገኙበታል።

(የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን የተሟላ መረጃ የላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዝርዝር ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ።) #ETA

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ የሚፈልጉ ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው የማረጋገጫ ወረቀት ማግኘት የሚችሉበት ስርዓት እየዘረጋ መሆኑን የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አሳውቋል።

ዲጂታል ስርዓቱ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገባ በተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች የሚገኙ ተገልጋዮች ካሉበት ሆነው ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።

እስካሁን በተደረገ የትምህርት ማስረጃ የማረጋገጥ ሥራ ከ5 እስከ 6 በመቶ የሚሆኑት ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ሆነው መገኘታቸውን የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቸሩጌታ ገነነ ለኢፕድ ተናግረዋል።

"ይህንን በሚፈጽሙ ተቋማት ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ የመረጃ ማደራጀት ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ" ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎችን የተመለከተ መረጃ ለትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የላኩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተፈታኝ ተማሪዎቻቸውን የመግቢያ ስም እና የይለፍ ቃል መውሰድ እንደሚችሉ ተገለጸ፡፡

ባለሥልጣኑ ከትምህርት ሚኒስቴር የመጣለትን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተፈታኝ ተማሪዎች የመግቢያ ስም እና የይለፍ ቃል እንዲወስዱ ለተቋማቱ ጥሪ አድርጓል፡፡

ለዚህም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የተቋማቸውን ህጋዊ የኢ-ሚይል አድርሻ እና የአንድ ተወካይ ሙሉ ስም እንዲሁም የስልክ አድራሻ በባለሥልጣኑ የኢ-ሚይል አድራሻ eta.gov.et@gmail.com እንዲልኩ ባለሥልጣኑ አሳስቧል፡፡

የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎችን የተመለከተ ሁሉም መረጃ ተቋማቱ በሚልኩት የኢ-ሚይል አድርሻ ብቻ የሚላክ መሆኑን ባለሥልጣኑ ገልጿል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ እና የአቻ ግመታ አገልግሎት ከመስከረም 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ በኦንላይን መስጠት ጀምራል፡፡

በመሆኑ አገልግሎቱን የምትፈልጉ በሙሉ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን ስካን በማድረግና https://neta.gov.et በመጠቀም ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡

በኦንላይን ቀጠሮ ካስያዙ ተገልጋዮች በስተቀር ሌሎች ተገልጋዮችን በአካል #የማያስተናግድ መሆኑን ባለሥልጣኑ አሳውቋል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስኮቻቸው የፈቃድ ወቅታዊ መረጃን አውጥቷል፡፡

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈቃድ ያገኙበትን የትምህርት መስክ፣ ካምፓስ እና መርሐግብር አሟልቶ የያዘና በየጊዜው ወቅታዊ የሚደረግ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈቃድን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፦ https://bit.ly/43Z1Rck

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በቀረበው መረጃ ላይ አስተያየት እና ጥቆማ አዲስ አበባ ጉለሌ ክ/ከተማ ሽሮ ሜዳ አሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኝው የባለሥልጣን መ/ቤቱ በአካል በመገኘት ወይም በኢ-ሚይል አድራሻ hemis.info@gmail.com አማካኝነት እስከ ዓርብ ታህሳስ 19/2016 ዓ.ም ብቻ መላክ የምትችሉ መሆኑን ባለሥልጣኑ አሳስቧል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
እስከ የካቲት 30/2016 ዓ.ም በሶፍት እና በሃርድ ኮፒ እንዲልኩ

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት የተማሪዎቻቸውን ዝርዝር መረጃ እንዲልኩ ጠይቋል፡፡

ፈቃድ በተሰጣቸው የትምህርት መስኮች በ2016 ዓ.ም ተመዝግብው እየተማሩ ያሉ ተማሪዎችን ዝርዝር መረጃ እና በ2015 ዓ.ም የተመረቁ ተማሪዎች (የመውጫ ፈተና ያለፉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች) ዝርዝር መረጃን እስከ የካቲት 30/2016 ዓ.ም በሶፍት እና በሃርድ ኮፒ እንዲልኩ ባለሥልጣኑ አሳስቧል፡፡

ይህም የትምህርት ጥራትና አግባብነት ለማስጠብቅ እንዲሁም የተመረቁ ተማሪዎች መጉላላት እንዳይገጥማቸው ባለሥልጣኑ ለሚያከናውናቸው ተግባራት አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል፡፡ #ETA

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot