EECMY Children Ministry: MY Sunday School
840 subscribers
947 photos
14 videos
174 links
MY Sunday School is the official page of EECMY Children Ministry.

Wholistic Growth For Our Children!

Access Sunday School learning materials at www.mysundayschool.org
Download Telegram
Forwarded from EECMY Youth Ministry
*የድንበር ዘለል አገልግሎት ሚስዮናዊ ምደባና የሽኝት መርሃግብር ተካሄደ *

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በውጪና በአገር ውስጥ የምስራቹን ይዘው የሚሄዱ ጥሪ ያላቸውን አገልጋዮችን በመመልመል፣ በማሰልጠን እያሰማራች ትገኛለች፡፡
በማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ስር የምትገኘው የሐዋሳ ቤቴል ማኅበረ ምዕመናንም የድንበር ዘለል አገልግሎት ሚስዮናዊ ደበላ ቦቴን ከነቤተሰቡ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ለመላክ የምደባና ሽኝት መርኃግብር አድርጋለች፡፡
በዕለቱም: ከቤተክርስቲያኒቱ ዋና ጽ/ቤት: ከዓለም አቀፍ ሚስዮን ማኅበር ቦርድ: የተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ተወካዮች እና መሪዎች እንዲሁም የሲኖዶስ መሪዎች እና የሐዋሳ ከተማ ማኅበረ ምእመናናት መሪዎች ተገኝተዋል:: በዕለቱም የቤተክርስቲያኒቱ ተባባሪ ጠቅላይ ፀሐፊና የዓለም አቀፍ ሚስዮን ማኅበር ቦርድ ሰብሳቢ ቄስ ፈቃዱ ቤኛ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የምደባና የሽኝት ሥነ ሥርዓቱ በሚስዮን ማኅበሩ ዳይሬክተር ቄስ ጥላዬ ከበደ መሪነት ተከናውኗል፡፡
በቀጣይም ይህን ታላቁን የወንጌል ተልዕኮ ከግብ ለማድረስ በፀሎት፣በገንዘብ በተለያዩ መንገዶች ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል::
(Source: EECMY- International Mission Society)
***
''በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።'' 1ቆሮንቶስ 9:23

ስለ ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገናችሁ
በጸሎት፣ በምክር ፣ በድጋፍ ከአለምአቀፍ የሚስዮን ማህበር አገልግሎት ጎን እንድትቆሙ በጌታ ፍቅር ጥሪ እናቀርባለን።

EECMY-IMS

1000008166432 CBE/ EECMY-IMS
2600280004746 BIRHAN BANK /EECMY-IMS
01320008596702AWASH/ EECMY-IMS

@eecmyyouthministry
*የታዳጊ ወጣቶች አውደ ርዕይ ተካሄደ*

በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የመካኒሳ ማህበረ ምዕመናን በወጣቶች አገልግሎት ስር በሚገኘው የታዳጊ ወጣቶች የተዘጋጀ አውደ ርዕይ/ኤግዚቢሽን ተካሄደ::  የኤግዚቢሽኑ ዋና አላማ ታዳጊዎች ባለፈው አመት የተማሩትን ትምህርት በራሳቸው የፈጠራ መንገድ ለማሳየት ነው። በዚህ ዝግጅት ላይ ከ85 በላይ ታዳጊዎች በ5 የተለያዩ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን: እያንዳንዱ ቡድን ስለ ፕሮጀክታቸው የፈጠራ ጥበብ ስራዎችን አሳይተው ለጎብኝወች ገለጻ አድርገዋል።
የቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምርያ ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሳ በኤግዚቢሽኑ ተገኝተው ከጎበኙ በኋላ: የመካኒሳ ማ/ም ወጣት መሪዎችንም ስለ መልካም ስራቸው አበረታተው:  ስራቸው ለሌሎችም መልካም ምሳሌ መሆኑን ገልጸዋል::

#EECMY #Teenager #Ministry #Mekanisa #Congregation
https://t.me/MYSundaySchool
የታዳጊ ወጣቶች ስልጠና በሀዋሳ
====
"በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ " በሚል መሪ ቃል
በማዕከላዊ ደቡብ ኢ/ያ ሲኖዶስ  በልጆች አገልግሎት መምርያ የተዘጋጀ የታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ከ ሐምሌ 1-5 - 2016 ዓ.ም ቀኑን ሙሉ ለተከታታይ አምስት ቀናት ዕድሜያቸው  ከ14-17 ዓመት ላሉ ታዳጊ  ወጣቶች በሀዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ  ግቢ ውስጥ ተዘጋጅቷል። ወላጆች ልጆችን ምሳ በማስያዝ እንድትልኩ የልጆች መምርያ  ያሳስባችኃል: ሁላችሁም ተጋብዛችኃል ተባረኩ።

#EmpoweringGeneration #EECMY #SouthCentralEthiopiaSynod #ChildrenMinistry  #Teenagers #Hawassa
@MYSundaySchool
የኢ/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ ካለንደር: ሐምሌ 2016 ዓ.ም

Kaalandarii WKWWMYI, Adoolessa 2016/2024

(Source: EECMY- Yemisrach Dimts Communication Service)

https://t.me/eecmyyouthministry
https://t.me/MYSundaySchool