Minber TV
45K subscribers
14.9K photos
2.25K videos
35 files
7.77K links
#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
ይከታተሉ፣ ለወዳጅዎ ያጋሩ!

📡 ሳተላይት ፡ EthioSAT 11545/45000/H
📱 የሶሻል ሚድያ አድራሻዎቻችን ፡ https://linktr.ee/minbertv
Download Telegram
ወታደራዊ ኃይሎች በሚያምንማር ሲትዌ ወታደራዊ ይዞታዎች አቅራቢያ የሚገኙ የሙስሊም መንደሮችን አወደሙ

ለዝርዝሩ፦ https://t.me/minberkheber/4016
😢17💔9
#ሚንበር_ቲቪ_ከሥፍራው፡ ከተመሠረተ ዐሥር ዓመት ያስቆጠረው ቴምር ፕሮፐርቲስ፤ የምሥረታ በዓሉ በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረ ይገኛል። የዚሁ ክብረ በዓል አንድ አካል የሆነው መርሃ ግብር ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 29/2018 በተለያዩ ሁነቶች በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል እየተከናወነ ይገኛል።

በዛሬው መርሐ ግብር ከስታር አሊያንስ አባሉ የኢትዮጵያ አየርመንገድ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት ተፈራርሟል። በተጨማሪም ማኅበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት ረገድ ሥጦታ እንደሚያበረክት ይጠበቃል። ለደንበኞች ልዩ ምሥጋና እና ሽልማት ያበረክታል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የቴምር ፕሮፐርቲስና የኢትዮጵያ አየርመንገድ ከፍተኛ ሥራ ኃላፊዎችና የማኔጅመንት አባላት፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ አምባሳደሮች፣ የሚዲያ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። (ሚንበር ቲቪ)
9👍1
ቴምር ፕሮፐርቲስ በምሥረታው ዐሥረኛ ዓመት ክብረ በዓል በማኅበራዊ ኃላፊነት ለልቡ ሕሙማን መርጃ ማዕከል መሪ ሥጦታ አበረከተ

ቴምር ፕሮፐርቲስ የኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ማዕከልን ለ18 ዓመታት ለመሩት ለዶ/ር ህሩይ ዓሊ የ300 ሺሕ ማይልስ ሥጦታ በዛሬው እለት አበርክቷል።

ድርጅቱ የአውሮፓ ደርሶ መልሶ ስጦታውን ያበረከተው ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 29/2018 ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ይፋዊ የፊርማ መርሃ ግብር ባካሄደበት ወቅት ነው።
ኩባንያው ከዚህ በተጨማሪም ከፍተኛ ከፍዮች ለሆኑ ሁለት ደንበኞቹ የሼባ ማይልስ ሥጦታ አበርክቷል።

ቴምር ፕሮፐርቲስ ባለፈው ሳምንት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ሼባ ማይልስ ጋር ስምምነት እንደሚፈርም ማሳወቁን ተከትሎ በዛሬው ዕለት  ይፋዊ ስምምነቱን ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የተፈራረሙት የቴምር ፕሮፐርቲስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጃዕፈር ሙሐመድ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኃይለመለኮት ማሞ ናቸው።

የቴምር ፕሮፐርቲስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የኩባንያው ግንባታዎች በቴክኖሎጂ የበለፀጉ እና ደንበኛ ተኮር መሆናቸውን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ በበኩላቸው ሼባ ማይልስ ከ 5.5 ሚሊዮን በላይ አባላት እንዳሉት ገልጸው ቴምር ለደንበኞቹ የሼባ ማይልስ ገዝቶ ይሠጣል ብለዋል።

ቴምር ከ2008 ጀምሮ በሪል ስቴት ዘርፍ ላይ ተሰማርቶ የቤት ፍላጎትን ለማሟላት እየሠራ የሚገኝ ድርጅት ሲሆን በዐሥር ዓመታት ውስጥ አስር ፕሮጀክቶችን ጨርሶ ማስረከቡ ተገልጿል። (ሚንበር ቲቪ)

★ ★ ★
Ethio Sat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #MinberTV
11😍2
29🥰13