Minber TV
38.9K subscribers
7.2K photos
368 videos
20 files
4.63K links
#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!

ይከታተሉ፣ ለወዳጅዎ ያጋሩ!

#ሚንበር_ቲቪን ለማግኘት

📡 በኢትዮሳት ይከታተሉ:– 👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 30000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★
Download Telegram
ወ/ሮ ነኢማ ሙዘይን ተሸለመች።

መጋቢት 8/2016
ረመዳን 7/1445
ሚንበር ቲቪ

በሰሜን አሜሪካ "ድንቅነሽ " በተሰኘ መጋቢት ወርን ጠብቆ የሴቶችን ስኬት በሚያጎላው  የሽልማት እና የእዉቅና ፕሮግራም የ"ይመለከተኛል በጎ አድራጎት ድርጅት" መስራች እና ሥራ አስኪያጅ የሆነችዉ ወ/ሮ ነዒማ ሙዘይን ተሸላሚ ሆናለች።

ለ5ተኛ ጊዜ በተካሄደው በዚህ የሽልማት ሥነሥርዓት ወ/ሮ ነኢማ በማኅበረሰብ አገልግሎት ድጋፍ ለተነፈጋቸው ወገኖች ተስፋ በመሆን ነው ሽልማቱ የተበረከተላት።

ሽልማቱን በተወካዩዋ በኩል የተቀበለችው ወ/ሮ ነኢማ የተሰማትን ጥልቅ ደስታ  ለ"ድንቅነሽ" አዘጋጆች በሙሉ ምስጋናዋን በማቅረብ ገልጻለች።

የይመለከተኛል በጎ አድራጎት በ27ኛው የምርኩዝ መድረክ በረመዳን ቀለማት 5 የካቲት 26/2016 በሚሊኒየም አዳራሽ በነበረው ደማቅ ፕሮግራም ድርጅቱን በተምሳሌትነቱ የማስተዋወቅ ሥራ የተሠራ ሲሆን ሚንበር ቲቪ በረመዳን የኢፍጣር ሰዓት በሚያቀርበው አብሮነት 8 ፕሮግራም ላይ የይመለከተኛል ተምሳሌታዊ ወጣቶች እየቀረቡ መሆኑ ይታወቃል።

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
#ልዩ_የረመዳን_መሰናዶ

በታዳጊዎች የተዘጋጀ ልዩ የረመዳን ዝግጅት ከብሩህ ልጆች

ዛሬ ከቀኑ 11 ሰዓት በሚንበር ቲቪ ይጠብቁን።

ዕለተ ሰኞ መጋቢት 9 - 2016 | ረመዳን 8  - 1445

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
Audio
#ኡስታዝ_ካሊድ_ክብሮም

በኡስታዝ ኻሊድ ክብሮም ተዘጅቶ በአብሮነት በረመዳን 8 ፕሮግራም ላይ እየቀረበ የሚገኘው "ተመለስ ... አትፍራም!" የተሰኘው ተከታታይ ፕሮግራም ከክፍል 1 እስከ 6 በድምጽ አቅርበንላችኋል።
በጥቂት ሜ.ባ ብቻ የተዘጋጁ ስለሆኑ አውርዶ ለመጠቀም ቀላል ናቸው። እናም ሼር በማድረግ ይህንን ወርቃማ ትምህርት ለወዳጆችዎ ያጋሩ።

#አብሮነት_በረመዳን_8 | ተመለስ ... አትፍራም! ክፍል 1 እስከ 6

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
#ዘምዘምን_ከምንጩ

"ፈጣን ለውጥ ያስፈልገናል!"

ዓለም በሶስቱ ጉዳዮች ርቆ ሄዷል። በሚዲያ ኢኮኖሚና ትምህርት። እኛ በዚህ ዘርፍ ፈጣን ለውጥ ያስፈልገናል ይላል ኡስታዝ ያሲን ኑሩ። በዛሬው "ዘምዘምን ከምንጩ" ፕሮግራማችን ኢኮኖሚና እኛ ሙስሊሞች ያለንበትን ሁኔታ በመጠኑ እንቃኛለን።

ዕለተ ሰኞ መጋቢት 9 - 2016 | ረመዳን 8  - 1445

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
#አብሮነት_በረመዳን_8

ተመለስ ... አትፍራም! - ክፍል 7
ምርጥ ዳዕዋ በኡስታዝ ኻሊድ ክብሮም

ዛሬ በኢፍጣር ሰዓት ይጠብቁን።

ዕለተ ሰኞ መጋቢት 9 - 2016 | ረመዳን 8  - 1445

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
#አብሮነት_በረመዳን_8

ዛሬ በኢፍጣር ሰዓት ይጠብቁን።

ዕለተ ሰኞ መጋቢት 9 - 2016 | ረመዳን 8  - 1445

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
#ካስማ_6

ዛሬ ከምሽቱ 4፡00 ላይ በሚንበር ቲቪ ይጠብቁን።

ዕለተ ሰኞ መጋቢት 9 - 2016 | ረመዳን 8  - 1445

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
#አብሮነት_በረመዳን_8

ይሳተፉ ••• የዑምራ ጉዞ ዕድል ያሸንፉ!

ዛሬ ምሽት በኢፍጣር ሰዓት በሚንበር ቲቪ  ይጠብቁን።

9282 ላይ ABን በማስቀደም ትክክለኛ ብለው ያሰቡትን መልስ ይላኩልን።                          

ዕለተ ሰኞ መጋቢት 9 - 2016 | ረመዳን 8  - 1445

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
Minber TV
Photo
"በሲስተም ማሻሻያ ሰበብ ነው ችግሩ የተፈጠረው።"  - ንግድ ባንክ

መጋቢት 9/2016
ረመዳን 8/1445
ሚንበር ቲቪ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ ሰሞኑን በንግድ ባንክ የተፈጠረው ችግር ሲስተም ለማሻሻል በተደረገ ጥረት ነው በማለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አሳውቀዋል።

አቶ አቤ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ "ችግሩ የተከሰተው ቅልጥፍና እንዲያመጣ አንድ ሂሳብ ማስታረቅ ታስቦ የተሰራ የሲስተም ማሻሻያ ሲተገበር ስህተት በመፈጠሩ ነው። የተፈጠረው ስህተት ለሌቦች ቀዳዳ ከፍቶ ነበር። ብለዋል አክለውም

"የሲስተም ማሻሻያው የተተገበረው አርብ መጋቢት 6/2016  ከምሽቱ 3 ሰዓት አካባቢ ሲሆን ከሌሊቱ 8 ሰዓት ችግሩ እንዳለ ሊለይ ተችሏል። ይህን ተከትሎም አንዳንድ የተጠረጠሩ አገልግሎቶች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ይህም ሆኖ ሙሉ በሙሉ ችግሩ ስላልቆመ ሁሉም የዲጂታል ባንክ ሥርዓቶች እንዲቋረጡ ተደርጎ ነበር። " ብለዋል

" ባንኩ ችግሩ በተከሰተበት ወቅት ከ490 ሺህ በላይ የገንዘብ ልውውጥ ተካሂዷል ሌሊቱን ሙሉ ግብይት ሲፈጸምባቸው የነበረባቸው የባንክ ሂሳቦች በሙሉ እስኪጣራ ድረስ እንዲታገድ ተደርጓል።  በቀጣይ ከፍተኛ እና ያልተገባ ግብይት የፈጸሙ አካላትን እየለየን ለህግ የማቅረብ ሥራ ይሠራል። " ብለዋል።

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በወንጀሉ ዋነኛ ተዋናይ መሆናቸው አሳዝኖናል ያሉት አቶ አቤ በየአካባቢው ያሉ የዲስትሪክት ኃላፊዎች በየአካባቢው ከሚገኝ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ተማሪዎች የወሰዱትን ገንዘብ እንዲመልሱ እየተደረገ ነው። ከተፈጠረው ችግር ጋር ተያይዞ አጠቃላይ የደረሰው ጉዳት ላይ ምርመራ እየተደረገም ነው። የችግሩ መሰረታዊ መንስዔ እና ያስከተለውን ጉዳትም ምርመራው ሲጠናቀቅ ይፋ ይደረጋል። " ብለዋል።

"ባንኩ ካለው ሀበት እና አቅም አንጻር ባንኩ ላይ የጎላ ተጽእኖ የለውም፤ ከደንበኞች ሂሳብ ጋርም አይገናኝም። " በማለት ማብራሪያቸውን አሳርገዋል።

ምንጭ :-  አልአይን

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
ዓለም አቀፍ የሙስሊሞች ሊግ ኮንፈረንስ በመካ እየተካሄደ ይገኛል

መጋቢት 9/2019
ረመዷን 8/1445
ሚንበር ቲቪ

ከትላንት ጀምሮ የሁለቱ ቅዱስ መስጂዶች የበላይ ጠባቂ በንጉስ ሰልማን ቢን አብዱላዚዝ አል ሳዑድ መሪነት በእስልምና መዝሃብና አስተሳሰቦች መካከል ድልድይ መገንባት በሚል መሪ ቃል በእስልምና ሀይማኖት ተከታዮች መካከል መግባባት እና ትብብርን ለመፍጠር ያለመ ታሪካዊ ኮንፈረንስ  በመካ በመካሄድ ላይ ነው ።

የጉባኤው ዋና ዓላማ በተለያዩ የእስልምና አስተምህሮዎች መካከል ያለውን ትስስር በውይይት እና በትብብር ለማጠናከር የታለመ እንደነበር ተገልጿል ።

ኮንፈረንሱ "ኢስላሚክ እሴቶቻችንን በመጠበቅ ረገድ ሥራዎችን ለመሥራት እና በመካከላችን ድልድይ ለመገንባት የሚያስችል ሰነድ" በማዘጋጀት ለበለጠ ኢስላማዊ ግንዛቤ ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቷል ተብሏል።

የጉባዔው ወሳኙ ገጽታ አንድ ወጥ የሆነ ኢስላማዊ አመለካከትን በሚፈልጉ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር በመግለጽ ዓለም አቀፍ ግጭት እንዲባባስና የእስልምናን ገጽታ ያበላሹትን የቡድናዊ አክራሪነት ንግግሮችን እና ተግባራትን መከላከል ነው ሲሉም አክለዋል ።
በኮንፈረንሱ ማጠቃለያ ላይ ይፋ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ሰነድ በታዋቂ የእስልምና ሊቃውንት እና ሙፍቲዎች የቀረቡ የተለያዩ ምሁራዊ ርዕሰ ጉዳዮችን ይዳስሳል። ኤም ደብሊውኤል የእስልምና ሊቃውንትን አንድ ለማድረግ ያለውን ወሳኝ ሚና በመገንዘብ ኢስላማዊ እሴቶችን መሰረት ባደረገ መልኩ በእስላማዊ ድርጅቶች መካከል መተማመንን እና ትብብርን ለማጎልበት ይህ ጉባኤ ያለውን ፋይዳ ይበልጥ ያጎላል ተብሎ ይታሰባል።

በውይይቱ መርኃ ግብሩም ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ፕሬዝደንት ክቡር ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን፣ ከተለያዩ ዓለም ሀገራት የተወከሉ ሙፍቲዎች፣ ምሑራንና ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን ለተከታታይ ቀናት ዉይይቱ  እየተካሄደ ይገኛል ።

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
ለፍልስጤማውያን ዘካ እንዲሰጥ ጥሪ ቀረበ!

መጋቢት 9/2016
ረመዳን 8/1445
ሚንበር ቲቪ

በነ ሸይኽ ዶክተር ሀሰን አልደደውና በነ ዶክተር ሸይኽ አሊ የተዘጋጀው  "ዘካችሁን ለፍልስጤማውያን አውጡ " ዘመቻ ብዙዎች እየተቀላቀሉት እንደሆነ ተገለጸ።

ለፍልስጤማውያን ህይወት እጅጉን ከብዳ የስቃይ ናዳ እየጎረፈባቸው ነው፣ አንጀታቸው በረሀብ እየተቀጣ የሞት ፅዋን ተቀቋዳሽ ከሆኑ ከርሟል ።

ፍልስጤም በእስራኤል ወሰን አልባ ጭቆና በኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ጉዳይ ላይ በብዙ ነገር ከዓለም ወደ ኋላ በመቅረት ከፍተኛ ስቃይ እና ጉዳት  እያስተናገደች ትገኛለች ። ይህንንም የዓለም ሕዝብ ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ያለ የሰው ዘር የሚያውቀው እውነታ ነው ። ለዚህም ሲባል ሕዝበ ሙስሊሙ ዘካውን ወደ ፍልስጤም መላክ አስፈላጊ መሆኑን መሻኢኾቹ ተናግረዋል ።

እስራኤል በፍልስጤም በያዘችው የዘር ማጥፋት ዘመቻ ከአንድ ሚሊዮን ተኩል በላይ የሚሆኑ ሰዎች ቤት አልባ በሆኑበት፣ በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ሕፃናት የአንድ ወይም የሁለቱም ወላጆቻቸው ወላጅ አጥ በመሆናቸው ለረሀብ እና ለሞት ተጋልጠዋል ። ይህንን እውነታ የሚያውቅ ልባችን "ፍልስጤማውያንን እንዴት እንርዳቸው!? ብላችሁ በሀሳብ ስትወጥኑ ለነበራችሁ ይህ "ብስራት" እንደሆነ እናምናለን" ብለዋል።
ሼኽ ሙሐመድ ሐሰን ወልድ አል ደደው አል ሽንቂጢ  ዘካህ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ማዘዋወር የሚፈቀደው በአስፈላጊ ወቅት እና በፍላጎት ነው በማለት ፈትዋ የሰጡ ሲሆን ዛሬ በፍልስጤም ያለውን ሁኔታ የሚመለከቱ የዓለም ሙስሊሞች ሀብታቸውን ችግሩን ለመቅረፍ ሊያውሉት ይገባል ብለዋል ። አክለውም" ከአቅም በላይ የሆኑ ሁኔታዎች ላይ የሚገኙትን ወገኖቻችን እንዲረዷቸው እና ስቃያቸውን እንዲያቃልሉ ልንረዳቸው ይገባል ብለዋል"

ለፍልስጤማውያን ዘካ ለማድረስ ድረ ገፅ የተከፈተ ሲሆን (በኡማህ ኢንዶውመንት) አማካኝነት ዘካ ለሚገባቸው ለማድረስ በመስራት ላይ የሚገኙ ወንድም አህቶች መኖራቸው ለማወቅ ተችሏል።

★★★★★
ሚንበር ቲቪን በኢትዮሳት በተሻለ የምስል
ጥራት ለመከታተል👇
ፍሪኩዌንሲ:- 11545
ሲምቦልሬት:- 45000
ፖላራይዜሽን:- ሆሪዞንታል
★★★★★

#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!