የቁርኣን ተፍሲር በሐረሪ ቋንቋ - በሸይኽ የሕያ እስማዒል (ረ)
ሱረቱል ሉቅማን 12-22
ዛሬ ከቀኑ 11:45 ጀምሮ በሚንበር ቲቪ
#ቁርኣን #ተፍሲር #ሐረሪ
#ሸይኽ_የሕያ_እስማዒል_ረ
ዕለተ ቅዳሜ ሰኔ 1 - 2016 | ዙል ሒጃ 2 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ሱረቱል ሉቅማን 12-22
ዛሬ ከቀኑ 11:45 ጀምሮ በሚንበር ቲቪ
#ቁርኣን #ተፍሲር #ሐረሪ
#ሸይኽ_የሕያ_እስማዒል_ረ
ዕለተ ቅዳሜ ሰኔ 1 - 2016 | ዙል ሒጃ 2 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍10
የመጨረሻዎቹ ኢትዮጵያውያን ሑጃጆች በዛሬው እለት ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ በረራ ያከናውናሉ ተባለ
ዕለተ ቅዳሜ ሰኔ 1 - 2016 | ዙል ሒጃ 2 – 1445 | ሚንበር ቲቪ
ለ1445ኛ ዓ.ሂ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የመጨረሻዎቹን ሑጃጆች ዛሬ እንደሚሸኝ አስታወቀ። ምክር ቤቱ ይህን ያስታወቀው ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 1/2016 በጽሕፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ ነው።
ምክር ቤቱ በመግለጫው ከግንቦት 13/2016 አንስቶ የተጓዙ ሑጃጆች በረራ ያደረጉት በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በሳዑዲ አየር መንገድ መሆኑን ገልጿል።
መግለጫውን ከሰጡት መካከል የሆኑት የሐጅና ዑምራ ዘርፍ ኃላፊ ዐብዱልፈታህ ሙሐመድ፣ በርካታ ሑጃጆች ጉዞ ያደረጉት በኢትዮጵያ አየር መንገድ መሆኑን ገልፀዋል። ምክር ቤቱ ከላካቸው 12 ሺሕ ምዕመናን ውስጥ በአየር መንገዱ የበረሩ ሑጃጆች ቁጥር 8 ሺሕ 500 መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፣ ቀሪዎች 3 ሺሕ 500 ሑጃጆች በሳዑዲያ አየር መንገድ በረራ ማድረጋቸውን አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በዛሬው መግለጫ ያነሳው ሌላው ጉዳይ ሑጃጆች በሳዑዲ ዐረቢያ ቆይታቸው ለሚገጥማቸው ሕመም የተዘጋጀውን ሕክምና በተመለከተ ነው። የምክር ቤቱ ኃላፊዎች በሳዑዲ ዐረቢያ ለኢትዮጵያውያን ሕክምና የሚሰጡ ሦስት ተንቀሳቃሽ ክሊኒኮች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል። ለክሊኒኮቹ በቂ መድኃኒት መዘጋጀቱን የገለፁት ኃላፊዎቹ፣ መድኃኒቶች ባለፈው ዓመት በኦማን መንግሥት ከተሰጠው በተጨማሪ የተገዙ መሆናቸውንም አብራርተዋል።
የዘንድሮው ዓመት የሐጅ ሥነ ሥርዐት ከቀጣይ ሳምንት ጁመዓ ጀምሮ እንደሚከናወን የሳዑዲ ዐረቢያ የሐጅ እና ሚኒስቴር የዙልሒጃ ወር ትናንት መግባቱን አስመልክቶ አስታውቋል።
ከግንቦት 1 አንስቶ ከመላው ዓለም ምዕመናንን እየተቀበለች የምትገኘው ሳዑዲ ዐረቢያ፣ እስካሁን ድረስ ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ምዕመናን ወደ ሀገሯ መግባታቸውን ገልጻለች።
ባለሥልጣናቱ ይፋ ባደረጉት አሐዝ መሠረት ከተለያዩ ሀገራት ሳዑዲ የደረሱ ምዕመናን ቁጥር አንድ ሚሊዮን ይደርሳል፡፡ በባሕር፣ በየብስ እና በአየር ወደ ሳዑዲ ከገቡት ምዕመናን ውስጥ ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት እነዚህ በአየር ተሳፍረው መዲና የደረሱት ናቸው፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ በዘንድሮው ዓመት የሐጅ ሥነ ሥርዐት ከመላው ዓለም የምትቀበላቸው ምዕመናን ብዛት ከሁለት ሚሊዮን ይሻገራል ተብሎ ይጠበቃል።
ዝርዝሩን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፦ https://minbertv.com/?p=8354
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ዕለተ ቅዳሜ ሰኔ 1 - 2016 | ዙል ሒጃ 2 – 1445 | ሚንበር ቲቪ
ለ1445ኛ ዓ.ሂ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የመጨረሻዎቹን ሑጃጆች ዛሬ እንደሚሸኝ አስታወቀ። ምክር ቤቱ ይህን ያስታወቀው ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 1/2016 በጽሕፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ ነው።
ምክር ቤቱ በመግለጫው ከግንቦት 13/2016 አንስቶ የተጓዙ ሑጃጆች በረራ ያደረጉት በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በሳዑዲ አየር መንገድ መሆኑን ገልጿል።
መግለጫውን ከሰጡት መካከል የሆኑት የሐጅና ዑምራ ዘርፍ ኃላፊ ዐብዱልፈታህ ሙሐመድ፣ በርካታ ሑጃጆች ጉዞ ያደረጉት በኢትዮጵያ አየር መንገድ መሆኑን ገልፀዋል። ምክር ቤቱ ከላካቸው 12 ሺሕ ምዕመናን ውስጥ በአየር መንገዱ የበረሩ ሑጃጆች ቁጥር 8 ሺሕ 500 መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፣ ቀሪዎች 3 ሺሕ 500 ሑጃጆች በሳዑዲያ አየር መንገድ በረራ ማድረጋቸውን አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በዛሬው መግለጫ ያነሳው ሌላው ጉዳይ ሑጃጆች በሳዑዲ ዐረቢያ ቆይታቸው ለሚገጥማቸው ሕመም የተዘጋጀውን ሕክምና በተመለከተ ነው። የምክር ቤቱ ኃላፊዎች በሳዑዲ ዐረቢያ ለኢትዮጵያውያን ሕክምና የሚሰጡ ሦስት ተንቀሳቃሽ ክሊኒኮች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል። ለክሊኒኮቹ በቂ መድኃኒት መዘጋጀቱን የገለፁት ኃላፊዎቹ፣ መድኃኒቶች ባለፈው ዓመት በኦማን መንግሥት ከተሰጠው በተጨማሪ የተገዙ መሆናቸውንም አብራርተዋል።
የዘንድሮው ዓመት የሐጅ ሥነ ሥርዐት ከቀጣይ ሳምንት ጁመዓ ጀምሮ እንደሚከናወን የሳዑዲ ዐረቢያ የሐጅ እና ሚኒስቴር የዙልሒጃ ወር ትናንት መግባቱን አስመልክቶ አስታውቋል።
ከግንቦት 1 አንስቶ ከመላው ዓለም ምዕመናንን እየተቀበለች የምትገኘው ሳዑዲ ዐረቢያ፣ እስካሁን ድረስ ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ምዕመናን ወደ ሀገሯ መግባታቸውን ገልጻለች።
ባለሥልጣናቱ ይፋ ባደረጉት አሐዝ መሠረት ከተለያዩ ሀገራት ሳዑዲ የደረሱ ምዕመናን ቁጥር አንድ ሚሊዮን ይደርሳል፡፡ በባሕር፣ በየብስ እና በአየር ወደ ሳዑዲ ከገቡት ምዕመናን ውስጥ ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት እነዚህ በአየር ተሳፍረው መዲና የደረሱት ናቸው፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ በዘንድሮው ዓመት የሐጅ ሥነ ሥርዐት ከመላው ዓለም የምትቀበላቸው ምዕመናን ብዛት ከሁለት ሚሊዮን ይሻገራል ተብሎ ይጠበቃል።
ዝርዝሩን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፦ https://minbertv.com/?p=8354
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍19❤4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መድረሳዎቻችን አቅም የሌላቸው ሰዎች መጠለያ እንደሆኑ ተደርጎ ተስሏል!
ለመድረሳ ያለው አመለካከት
ሙሉ ፕሮግራሙን የዩትዩብ ቻነላችን ላይ ያገኙታል።
🔗 https://youtu.be/jewe15cMw7Y 🔗
#መርከዝ #መድረሳ
#ከቁርአን_ጋር
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ለመድረሳ ያለው አመለካከት
ሙሉ ፕሮግራሙን የዩትዩብ ቻነላችን ላይ ያገኙታል።
🔗 https://youtu.be/jewe15cMw7Y 🔗
#መርከዝ #መድረሳ
#ከቁርአን_ጋር
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍20❤7
ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ባላቸው 10ቱ የዙል ሒጃ ቀናቶች ከኛ ምን ይጠበቃል? እንዴት አድርገንስ ልንጠቀምባቸው እንችላለን? ወደ ዒባዳ መመለስ ከሴቶች አንፃርስ እና መሰል ነጥቦችን ከእንግዳችን የሕይወት ልምድ ጋር በማጣመር "ሴቶች በ10ቱ ቀናት" በሚል ርዕስ ያዘጋጀነውን ልዩ መሰናዶ በዛሬው የሰሞነ ሐጅ ፕሮግራማችን ምሽት 01:00 ጀምሮ በሚንበር ቲቪ ይቀርብላችኃል!
#ሰሞነ_ሐጅ
#ሴቶች_በ10ቱ_ቀናት
ዕለተ እሁድ ሰኔ 2 - 2016 | ዙል ሒጃ 3 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
#ሰሞነ_ሐጅ
#ሴቶች_በ10ቱ_ቀናት
ዕለተ እሁድ ሰኔ 2 - 2016 | ዙል ሒጃ 3 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍16❤3👏2😍2🙏1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ከነሺዳ በተለቃቀሙ ዜማዎች ቁርአን መቅራት የለብንም!
ሙሉ ፕሮግራሙን የዩትዩብ ቻነላችን ላይ ያገኙታል።
🔗 https://youtu.be/jewe15cMw7Y 🔗
#ነሺዳ #ቁርአን
#ከቁርአን_ጋር
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ሙሉ ፕሮግራሙን የዩትዩብ ቻነላችን ላይ ያገኙታል።
🔗 https://youtu.be/jewe15cMw7Y 🔗
#ነሺዳ #ቁርአን
#ከቁርአን_ጋር
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍20👌4
#ሐጅ_በሐረመይን
የሂጅራ ባንክ የሐረመይን የቁጠባ ሂሳብ ደንበኞች ወደ ሐጅ ተጓዙ
ምሸት ከ02:00 ጀምሮ በሚንበር ቲቪ!
#ሂጅራ_ባንክ
#ከሚንበር_ቲቪ_ጋር_በመተባበር
ዕለተ እሁድ ሰኔ 2 - 2016 | ዙል ሒጃ 3 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
የሂጅራ ባንክ የሐረመይን የቁጠባ ሂሳብ ደንበኞች ወደ ሐጅ ተጓዙ
ምሸት ከ02:00 ጀምሮ በሚንበር ቲቪ!
#ሂጅራ_ባንክ
#ከሚንበር_ቲቪ_ጋር_በመተባበር
ዕለተ እሁድ ሰኔ 2 - 2016 | ዙል ሒጃ 3 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
❤8🙏1😍1
አብዮት የተጫረበት ገላ ነው። ሙሐመድ ቡዓዚዚ! አትክልትና ፍራፍሬ በኩሩኩር እየሸጠ ኑሮውን ለመግፋት ሲታትር ፖሊሶች ቁምስቅሉን ከሳዩት! መራራውን እርምጃ ራሱ ላይ ፈጸመ። የአረቡ ዓለም የፀደይ አብዮትን ከሱ በእሳት ከሚገረፍ ገላ ላይ አየ! በዛሬው #እነሆ_ኸበር ፕሮግራማችን ምሽት 03:00 በሚንበር ቲቪ ይጠብቁን!
#እነሆ_ኸበር
#የሱቅ_በደረቴው_ማስታወሻ
ዕለተ እሁድ ሰኔ 2 - 2016 | ዙል ሒጃ 3 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
#እነሆ_ኸበር
#የሱቅ_በደረቴው_ማስታወሻ
ዕለተ እሁድ ሰኔ 2 - 2016 | ዙል ሒጃ 3 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍14❤8
ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የተቀማጭ ገንዘብ መጠን በየዓመቱ በአማካይ 24 በመቶ እያደገ መምጣቱ ተገለጸ
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 – 1445 | ሚንበር ቲቪ
በኢትዮጵያ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የተቀማጭ ገንዘብ መጠን በየዓመቱ በአማካይ 24 በመቶ እያደገ መምጣቱ ተገለጸ፡፡ ባንኮቹ እስካሁን ድረስ በአጠቃላይ 222.8 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ ሰብስበዋል ተብሏል፡፡
በሀገሪቱ የሚገኙ ከወለድ ነፃ አገልግሎት የሚሰጡ ባንኮች ተቀማጭ ገንዘብ መጠን በየዓመቱ በአማካይ ከ24 በመቶ እያደገ መምጣቱን ያመለከተው የባንኮቹን ወቅታዊ አፈጻጸም የሚያመለክተው መረጃ ነው፡፡ ከተቀማጭ ገንዘብ በተጨማሪ በባንኮቹ የሚሰጠው ብድር ምጣኔም በተለይ በ2016 የሒሳብ ዓመት ከቀዳሚዎቹ ዓመታት የተሻለ ዕድገት ማሳየት ጀምሯል ነው የተባለው፡፡
በዚህ ዘርፍ ትልቁን የገበያ ድርሻ የያዘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሆኑን መረጃውን ጠቅሶ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ በዘገባው የተጠቀሰው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እስከ 2016 የሒሳብ ዓመት አሥር ወራት ማሰባሰብ የቻለው አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ 114.8 ቢሊዮን ብር መሆኑ ተገልጧል፡፡ ይህም በአሥር ወራት ውስጥ ብቻ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ አዲስ ተቀማጭ ገንዘብ ማሰባሰብ መቻሉን የሚያመለክት ነው፡፡
የአስቀማጭ ደንበኞችን ቁጥር በተመለከተም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከወለድ ነፃ እያስቀመጡ ያሉ ደንበኞች ቁጥር 7.2 ሚሊዮን በላይ ደርሷል ተብሏል፡፡ በአሥር ወራት ውስጥ የአስቀማጭ ደንበኞች ቁጥር ከ20 በመቶ በላይ ዕድገት አሳይቷል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከብድር አሰጣጥ ጋር በተያያዘም ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ያቀረበው ብድር ከሌሎች ዓመታት በተለየ ጭማሪ ማሳየቱ ሲገለጽ፣ የተሰጠው የብድር ክምችት 40.5 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡ ሚንበር ቲቪ ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ ባንክ አገልግሎት ከሚሰጡ ባንኮች ተጨማሪ መረጃ ለማካተት ያደረገው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡
በኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በመስኮት ደረጃ የሚሰጡ ከሃያ በላይ ባንኮች ይገኛሉ፡፡ ከባንኮቹ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጡ አራት ባንኮች በኢንዱስትሪው ውስጥ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡
ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- HTTPS://MINBERTV.COM/?P=8357
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 – 1445 | ሚንበር ቲቪ
በኢትዮጵያ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የተቀማጭ ገንዘብ መጠን በየዓመቱ በአማካይ 24 በመቶ እያደገ መምጣቱ ተገለጸ፡፡ ባንኮቹ እስካሁን ድረስ በአጠቃላይ 222.8 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ ሰብስበዋል ተብሏል፡፡
በሀገሪቱ የሚገኙ ከወለድ ነፃ አገልግሎት የሚሰጡ ባንኮች ተቀማጭ ገንዘብ መጠን በየዓመቱ በአማካይ ከ24 በመቶ እያደገ መምጣቱን ያመለከተው የባንኮቹን ወቅታዊ አፈጻጸም የሚያመለክተው መረጃ ነው፡፡ ከተቀማጭ ገንዘብ በተጨማሪ በባንኮቹ የሚሰጠው ብድር ምጣኔም በተለይ በ2016 የሒሳብ ዓመት ከቀዳሚዎቹ ዓመታት የተሻለ ዕድገት ማሳየት ጀምሯል ነው የተባለው፡፡
በዚህ ዘርፍ ትልቁን የገበያ ድርሻ የያዘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሆኑን መረጃውን ጠቅሶ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ በዘገባው የተጠቀሰው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እስከ 2016 የሒሳብ ዓመት አሥር ወራት ማሰባሰብ የቻለው አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ 114.8 ቢሊዮን ብር መሆኑ ተገልጧል፡፡ ይህም በአሥር ወራት ውስጥ ብቻ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ አዲስ ተቀማጭ ገንዘብ ማሰባሰብ መቻሉን የሚያመለክት ነው፡፡
የአስቀማጭ ደንበኞችን ቁጥር በተመለከተም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከወለድ ነፃ እያስቀመጡ ያሉ ደንበኞች ቁጥር 7.2 ሚሊዮን በላይ ደርሷል ተብሏል፡፡ በአሥር ወራት ውስጥ የአስቀማጭ ደንበኞች ቁጥር ከ20 በመቶ በላይ ዕድገት አሳይቷል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከብድር አሰጣጥ ጋር በተያያዘም ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ያቀረበው ብድር ከሌሎች ዓመታት በተለየ ጭማሪ ማሳየቱ ሲገለጽ፣ የተሰጠው የብድር ክምችት 40.5 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡ ሚንበር ቲቪ ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ ባንክ አገልግሎት ከሚሰጡ ባንኮች ተጨማሪ መረጃ ለማካተት ያደረገው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡
በኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በመስኮት ደረጃ የሚሰጡ ከሃያ በላይ ባንኮች ይገኛሉ፡፡ ከባንኮቹ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጡ አራት ባንኮች በኢንዱስትሪው ውስጥ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡
ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- HTTPS://MINBERTV.COM/?P=8357
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍19
ሳዑዲ ዐረቢያ የሐጅ ቪዛ አልያዙም ያለቻቸውን በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከመካ ከተማ እንዲወጡ አደረገች
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 – 1445 | ሚንበር ቲቪ
ከመላው ዓለም ለሐጅ ሥነ ሥርዐት ክንውን ወደ ሀገሯ የሚገቡ ምዕመናንን እያስተናገደች የምትገኘው ሳዑዲ ዐረቢያ፣ የሐጅ ቪዛ አልያዙም ያለቻቸውን ከ300 ሺሕ በላይ ሰዎች ከመካ ከተማ እንዲወጡ ማድረጓ ተሰማ፡፡ ከከተማዋ እንዲወጡ ከተደረጉት ውስጥ 150 ሺሕ የሚሆኑት ከውጪ ሀገራት በጉብኝት ቪዛ የገቡ መሆናቸው ተገልጧል፡፡
የሳዑዲ ዐረቢያ ባሥልጣናት እንደገለጹት፣ የሀገሪቱ ፖሊስ እነዚህን ግለሰቦች ከመካ ያስወጣው የሐጅ ቪዛ ከያዙ ምዕመናን ውጪ ወደ ከተማዋ መግባት የሚከለክለው መመርያ ተግባራዊ መደረግ ከተጀመረ በኋላ ነው፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ ፖሊስ ከመካ እንዲወጡ ካደረጋቸው መካከል 153 ሺሕ 998 ሰዎች በጉብኝት ቪዛ የገቡ የውጭ ሀገራት ዜጎች ናቸው፡፡ በተጨማሪም 171 ሺሕ 587 ነዋሪነታቸው ሳዑዲ ዐረቢያ ውስጥ ቢሆንም መቀመጫቸው መካ አይደለም የተባሉና የሐጅ ቪዛ ያልያዙ ሰዎች ለቀው እንዲወጡ መደረጉን የሳዑዲ ዜና አገልግሎት ዘገባ ያመለክታል፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ በዘንድሮው የሐጅ ሥነ ሥርዐት ክንውን ለመሳተፍ ከመላው ዓለም ሀገራት የተነሱ ምዕመናንን መቀበሏን በመቀጠል እስካሁን ድረስ ወደ ሀገሯ የገቡት ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ደርሰዋል፡፡ በዚህ ሳምንት ለሚፈጸመው የሐጅ ክንውን፣ በቀጣይ ቀናት ሌሎች አንድ ሚሊዮን ምዕመናን ወደ ሀገሪቱ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ እንግዶቹን የምታስተናግደው ለሥነ ሥርዐቱ ብቻ በሚል የተለየ ቪዛ አዘጋጅታ ሲሆን፣ በዚህ ምክንያት የሐጅ ቪዛ ከያዙ ምዕመናን ውጪ ሌሎች እንግዶች ወደ ሀገሯ ቢገቡም ወደ ቅድስቲቱ መካ ከተማ እንዲዘልቁ ፍቃድ እንደማትሰጥ ቀድማ አሳውቃ ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ያለ ሐጅ ቪዛ ወደ መካ ከተማ የገቡ ምዕመናን ቅጣት እደሚጠብቃቸው ገልጻለች፡፡
ሀገሪቱ መቀጮ የሚያስከፍለውን ደንብ ያወጣችው በሥነ ሥርዐቱ ወቅት ሊከሰት የሚችለውን መጨናነቅ ለመቀነስ ነው በሚል ነው፡፡ ሳዑዲ ዐረቢያ ይህን ርምጃ ይበልጥ ያጠናከረችው ከዘጠኝ ዓመታት በፊት ሚና ላይ አደጋ ከተከሰተ በኋላ መሆኑን የሀገሯ ባለሥልጣናት ይናገራሉ፡፡
የ1445 ዓ.ሂ የሐጅ ሥነ ሥርዐት መከናወን የሚጀምረው ከፊታችን ጁመዓ አንስቶ ባሉት ተከታታይ ቀናት መሆኑ ይታወቃል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)
ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- https://minbertv.com/?p=8360
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 – 1445 | ሚንበር ቲቪ
ከመላው ዓለም ለሐጅ ሥነ ሥርዐት ክንውን ወደ ሀገሯ የሚገቡ ምዕመናንን እያስተናገደች የምትገኘው ሳዑዲ ዐረቢያ፣ የሐጅ ቪዛ አልያዙም ያለቻቸውን ከ300 ሺሕ በላይ ሰዎች ከመካ ከተማ እንዲወጡ ማድረጓ ተሰማ፡፡ ከከተማዋ እንዲወጡ ከተደረጉት ውስጥ 150 ሺሕ የሚሆኑት ከውጪ ሀገራት በጉብኝት ቪዛ የገቡ መሆናቸው ተገልጧል፡፡
የሳዑዲ ዐረቢያ ባሥልጣናት እንደገለጹት፣ የሀገሪቱ ፖሊስ እነዚህን ግለሰቦች ከመካ ያስወጣው የሐጅ ቪዛ ከያዙ ምዕመናን ውጪ ወደ ከተማዋ መግባት የሚከለክለው መመርያ ተግባራዊ መደረግ ከተጀመረ በኋላ ነው፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ ፖሊስ ከመካ እንዲወጡ ካደረጋቸው መካከል 153 ሺሕ 998 ሰዎች በጉብኝት ቪዛ የገቡ የውጭ ሀገራት ዜጎች ናቸው፡፡ በተጨማሪም 171 ሺሕ 587 ነዋሪነታቸው ሳዑዲ ዐረቢያ ውስጥ ቢሆንም መቀመጫቸው መካ አይደለም የተባሉና የሐጅ ቪዛ ያልያዙ ሰዎች ለቀው እንዲወጡ መደረጉን የሳዑዲ ዜና አገልግሎት ዘገባ ያመለክታል፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ በዘንድሮው የሐጅ ሥነ ሥርዐት ክንውን ለመሳተፍ ከመላው ዓለም ሀገራት የተነሱ ምዕመናንን መቀበሏን በመቀጠል እስካሁን ድረስ ወደ ሀገሯ የገቡት ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ደርሰዋል፡፡ በዚህ ሳምንት ለሚፈጸመው የሐጅ ክንውን፣ በቀጣይ ቀናት ሌሎች አንድ ሚሊዮን ምዕመናን ወደ ሀገሪቱ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ እንግዶቹን የምታስተናግደው ለሥነ ሥርዐቱ ብቻ በሚል የተለየ ቪዛ አዘጋጅታ ሲሆን፣ በዚህ ምክንያት የሐጅ ቪዛ ከያዙ ምዕመናን ውጪ ሌሎች እንግዶች ወደ ሀገሯ ቢገቡም ወደ ቅድስቲቱ መካ ከተማ እንዲዘልቁ ፍቃድ እንደማትሰጥ ቀድማ አሳውቃ ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ያለ ሐጅ ቪዛ ወደ መካ ከተማ የገቡ ምዕመናን ቅጣት እደሚጠብቃቸው ገልጻለች፡፡
ሀገሪቱ መቀጮ የሚያስከፍለውን ደንብ ያወጣችው በሥነ ሥርዐቱ ወቅት ሊከሰት የሚችለውን መጨናነቅ ለመቀነስ ነው በሚል ነው፡፡ ሳዑዲ ዐረቢያ ይህን ርምጃ ይበልጥ ያጠናከረችው ከዘጠኝ ዓመታት በፊት ሚና ላይ አደጋ ከተከሰተ በኋላ መሆኑን የሀገሯ ባለሥልጣናት ይናገራሉ፡፡
የ1445 ዓ.ሂ የሐጅ ሥነ ሥርዐት መከናወን የሚጀምረው ከፊታችን ጁመዓ አንስቶ ባሉት ተከታታይ ቀናት መሆኑ ይታወቃል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)
ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- https://minbertv.com/?p=8360
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍15😢5❤3
🕋 #የካዕባ_ማዕዘናትና ሌሎች መረጃዎች...
በዛሬው የሰሞነ ሐጅ መሰናዶ ከሐጅ ጋር የተያያዙ ሃሳቦችን ይዞ
የካዕባ ማዕዘናትና ሌሎች መረጃዎችን ወደ እናንተ ውድ ተመልካቾች ያደርሳል።
#ሰሞነ_ሐጅ ክፍል 9
ዛሬ ምሽት 01፡30 በሚንበር ቲቪ!
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
በዛሬው የሰሞነ ሐጅ መሰናዶ ከሐጅ ጋር የተያያዙ ሃሳቦችን ይዞ
የካዕባ ማዕዘናትና ሌሎች መረጃዎችን ወደ እናንተ ውድ ተመልካቾች ያደርሳል።
#ሰሞነ_ሐጅ ክፍል 9
ዛሬ ምሽት 01፡30 በሚንበር ቲቪ!
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍7❤1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አልሓምዱሊላህ የማይለያቸው አንደበቶች! 🌴
📌 ከጉሊት አስቤዛ በመሸመት አቅመ ደካማ እና ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው የማህበረሰባችን ክፍሎች እናግዝ! ትንሽ ድጋፍ ትልቅ ተስፋን ትጭራለችና!
ሙሉ ፕሮግራሙን የዩትዩብ ቻነላችን ላይ ያገኙታል።
🔗 https://youtu.be/1c8dMNkitBc 🔗
#አልሓምዱሊላህ #አመስጋኝ_አንደበቶች
#መወዳ_መዝናኛ
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
📌 ከጉሊት አስቤዛ በመሸመት አቅመ ደካማ እና ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው የማህበረሰባችን ክፍሎች እናግዝ! ትንሽ ድጋፍ ትልቅ ተስፋን ትጭራለችና!
ሙሉ ፕሮግራሙን የዩትዩብ ቻነላችን ላይ ያገኙታል።
🔗 https://youtu.be/1c8dMNkitBc 🔗
#አልሓምዱሊላህ #አመስጋኝ_አንደበቶች
#መወዳ_መዝናኛ
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍11❤5😢5
እንደሊበራሊዝም ከሆነ ነፃ ገበያ በራሱ ምክኒያታዊ ነው። ስለሆነም ልክ እንደ ምክኒያታዊ ሰው ሁሉ ገበያም የየትኛውንም አካል ጣልቃ ፍፁም ነፃ መሆን አለበት የሚል ሙግት አለ። ይህም ለሰው ልጆች የተሻለ የኑሮ ስርአትን ይፈጥራል ተብሎ ተዘምሮለታል።
ተጨባጩ ተቃርኖ መኖሩን ያሳያል። ነፃ ገበያ በአብዛሀኛው ዘንድ አሉታዊ ተፅእኖው ጎልቶ ይታያል። በነፃ ገበያ ውስጥ የሚሸጡ ነገራቶችም ሁለንተናዊ ቀውስን አስከትለዋል።
በዛሬው ፕሮግራማችን ወንድም ኢብራሂም ነፃ ገበያን ከመሠረተ-ሀሳቡ ጀምሮ ያስቃኘናል።
#በኢስላም_ጥላ_ሥር
#ነፃ_ገበያ
ዛሬ ምሽት 02፡00 በሚንበር ቲቪ!
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ተጨባጩ ተቃርኖ መኖሩን ያሳያል። ነፃ ገበያ በአብዛሀኛው ዘንድ አሉታዊ ተፅእኖው ጎልቶ ይታያል። በነፃ ገበያ ውስጥ የሚሸጡ ነገራቶችም ሁለንተናዊ ቀውስን አስከትለዋል።
በዛሬው ፕሮግራማችን ወንድም ኢብራሂም ነፃ ገበያን ከመሠረተ-ሀሳቡ ጀምሮ ያስቃኘናል።
#በኢስላም_ጥላ_ሥር
#ነፃ_ገበያ
ዛሬ ምሽት 02፡00 በሚንበር ቲቪ!
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 - 1445
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍12❤1
ልዩ “ኸበር” - ከበዳይ ጎን የቆመው ሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 – 1445 | ሚንበር ቲቪ
የአሜሪካው ሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን ካስመረቀ ሁለት ሳምንት ተቆጥሯል፡፡ በተጠናቀቀው የትምህር ዘመን የተመረቁ ተማሪዎች ሁልጊዜም በሁሉም የትምህርት ተቋም ውስጥ እንደሚደረገው የትምህርት ማሥረጃቸውን ወስደዋል፡፡ ይህ አሠራር ግን ለሁሉም የሚፈቀድ አይመስልም፡፡ አስመር አስራር ሳፊ እና ሽራዳ ጆሺ ለዚህ ማሳያ ናቸው፡፡
ሁለቱም ያለፉትን አራት ዓመታት በሐርቫርድ ቆይተው ትምህርታቸውን ቢያጠናቅቁም ዲግሪያቸውን ማግኘት አልቻሉም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ፍልስጤምን ደግፈው ሠልፍ በመውጣታቸው ነው፡፡
የዘር ግንዱ ከፓኪስታን የሚመዘዘው አስመር አስራር፣ ሌሎች 12 ተማሪዎች በተመሣሣይ ዲግሪያቸው እንደተያዘባቸው አሁን ካለበት ቦስተን ለአልጀዚራ ዘጋቢ ነግሮታል፡፡ አስመር እንደሚለው እነዚህ ተማሪዎች በተያዘው ዓመት የተመረቁ ብቻ አይደሉም፤ ከመሃላቸው ለአንድ ዓመት ዲግሪያችንን ስጡን በሚል ሲከራከሩ የቆዩ አሉበት፡፡
በመደበኛው አሠራር የሐርቫርድ ምርቃ ሥነ ሥርዐት በተከናወበት እለት ዲግሪያቸውን ማግኘት የነበረባቸው አስመር እና ሽራዳ በአሁኑ ወቅት ለዩኒቨርሲቲው ይግባኝ ጠይቀው ውሳኔ እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡
በተማሪዎቹ አቤቱታ የቀረበበት ሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ድረስ የእነአስመርን ዲግሪ ለመስጠት አልያም ማብራሪያ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆነም፡፡ ይህ ደግሞ ቀጣይ ትምህርታቸው ላይ ጥላውን አጥልቷል፡፡ ከተማሪዎቹ ውስጥ በቴክሳሰ ተወልዳ ያገችው ጆሺ፣ በዩናይትድ ኪንግደም በሚገኘው ኬምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በሶሽዮሎጂ የማስተርስ ዲግሪ ለመቀጠል እቅድ ቢኖራትም የቀድሞ ዩኒቨርሲቲዋ ዲግሪዋን ስለያዘው ስለመሳካቱ ርግጠኛ መሆን ቸግሯታል፡፡
የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ከአንድ ወር በፊት ፍልስጤምን በሚደግፉ ሠልፈኞች ተሞልተው እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ የተማሪዎቹ ድምጽ ወደ አውሮፓ እና አውስትራሊያ ዩኒቨርሲቲች ጭምር ተዛምቷል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)
በድረ ገጽ ያንብቡ፡- https://minbertv.com/?p=8365
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 – 1445 | ሚንበር ቲቪ
የአሜሪካው ሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን ካስመረቀ ሁለት ሳምንት ተቆጥሯል፡፡ በተጠናቀቀው የትምህር ዘመን የተመረቁ ተማሪዎች ሁልጊዜም በሁሉም የትምህርት ተቋም ውስጥ እንደሚደረገው የትምህርት ማሥረጃቸውን ወስደዋል፡፡ ይህ አሠራር ግን ለሁሉም የሚፈቀድ አይመስልም፡፡ አስመር አስራር ሳፊ እና ሽራዳ ጆሺ ለዚህ ማሳያ ናቸው፡፡
ሁለቱም ያለፉትን አራት ዓመታት በሐርቫርድ ቆይተው ትምህርታቸውን ቢያጠናቅቁም ዲግሪያቸውን ማግኘት አልቻሉም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ፍልስጤምን ደግፈው ሠልፍ በመውጣታቸው ነው፡፡
የዘር ግንዱ ከፓኪስታን የሚመዘዘው አስመር አስራር፣ ሌሎች 12 ተማሪዎች በተመሣሣይ ዲግሪያቸው እንደተያዘባቸው አሁን ካለበት ቦስተን ለአልጀዚራ ዘጋቢ ነግሮታል፡፡ አስመር እንደሚለው እነዚህ ተማሪዎች በተያዘው ዓመት የተመረቁ ብቻ አይደሉም፤ ከመሃላቸው ለአንድ ዓመት ዲግሪያችንን ስጡን በሚል ሲከራከሩ የቆዩ አሉበት፡፡
በመደበኛው አሠራር የሐርቫርድ ምርቃ ሥነ ሥርዐት በተከናወበት እለት ዲግሪያቸውን ማግኘት የነበረባቸው አስመር እና ሽራዳ በአሁኑ ወቅት ለዩኒቨርሲቲው ይግባኝ ጠይቀው ውሳኔ እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡
በተማሪዎቹ አቤቱታ የቀረበበት ሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ድረስ የእነአስመርን ዲግሪ ለመስጠት አልያም ማብራሪያ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆነም፡፡ ይህ ደግሞ ቀጣይ ትምህርታቸው ላይ ጥላውን አጥልቷል፡፡ ከተማሪዎቹ ውስጥ በቴክሳሰ ተወልዳ ያገችው ጆሺ፣ በዩናይትድ ኪንግደም በሚገኘው ኬምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በሶሽዮሎጂ የማስተርስ ዲግሪ ለመቀጠል እቅድ ቢኖራትም የቀድሞ ዩኒቨርሲቲዋ ዲግሪዋን ስለያዘው ስለመሳካቱ ርግጠኛ መሆን ቸግሯታል፡፡
የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ከአንድ ወር በፊት ፍልስጤምን በሚደግፉ ሠልፈኞች ተሞልተው እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ የተማሪዎቹ ድምጽ ወደ አውሮፓ እና አውስትራሊያ ዩኒቨርሲቲች ጭምር ተዛምቷል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)
በድረ ገጽ ያንብቡ፡- https://minbertv.com/?p=8365
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍21❤2💔2
ለፍልስጤማዊያን ሰማዕታት ቤተሰቦች ተጨማሪ የሐጅ ዕድል ተፈቀደ
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 – 1445 | ሚንበር ቲቪ
ሳዑዲ ዐረቢያ ከዚህ ቀደም ከነበረው በተጨማሪ ሌሎች አንድ ሺሕ ፍልስጤማዊያን ሰማዕታት ቤተሰቦች የሐጅ ዕድል እንዲያገኙ ፍቃድ መስጠቷን አስታወቀች፡፡ ሀገሪቱ ለፍልስጤማዊያኑ ተጨማሪ መስጠቷን ያስታወቀችው ዛሬ ሰኞ ነው፡፡
በንጉሥ ሰልማን ቢን ዓብዱልዓዚዝ አማካይነት የተሰጠው የሐጅ ዕድል፣ በዘንድሮው ዓመት የሐጅ ዕድል ያገኙ የፍልስጤማዊያን ሰማዕታት ቤተሰቦችን ቁጥር ሁለት ሺሕ ያደርሰዋል፡፡
ሁለቱን ቅዱሳን ሥፍራዎች የያዘችው ሳዑዲ ዐረቢያ፣ ከመላው ዓለም የተለያዩ ሀገራት እስከ ቅዳሜ ድረስ 1.3 ሚሊዮን ምዕመናንን ተቀብላለች፡፡ ሀገሪቱ ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ለአንድ ሺሕ ፍልስጤማዊያን ሰማዕታት ቤተሰቦች የሐጅ ዕድል ሰጥታ ነበር፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ ከዚህ ቀደም እንዳስታወቀችው፣ ከፍልስጤማዊያን ውጪ ከመላው ዓለም ከ88 ሀገራት የተውጣጡ 1 ሺሕ 300 ምዕመናን የሐጅ ዕድሉን ሰጥታለች፡፡ ከእነዚህ ውስጥ የተካተቱት 22 ምዕመናን ተጣብቀው የተወለዱና በተለያዩ ጊዜያት በሀገሪቱ ሕክምና አግኝተው እንዲነጣጠሉ የተደረጉ መንትያ ሕፃናት ቤተሰቦች ናቸው፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ በዘንድሮው 1445 ዓ.ሂ የሐጅ ሥነ ሥርዐት ከመላው ዓለም ከሁለት ሚሊዮን በላይ ምዕመናንን ትቀበላለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በዚህ ሳምንት ለሚፈጸመው የሐጅ ክንውን፣ በቀጣይ ቀናት ሌሎች አንድ ሚሊዮን ምዕመናን ወደ ሀገሪቱ እንደሚገቡ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ገልጸዋል፡፡
የ1445 ዓ.ሂ የሐጅ ሥነ ሥርዐት መከናወን የሚጀምረው ከፊታችን ጁመዓ ዙልሒጃ 8 አንስቶ ባሉት ተከታታይ ቀናት መሆኑ ይታወቃል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)
ዝርዝሩን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡-https://minbertv.com/?p=8368
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ዕለተ ሰኞ ሰኔ 3 - 2016 | ዙል ሒጃ 4 – 1445 | ሚንበር ቲቪ
ሳዑዲ ዐረቢያ ከዚህ ቀደም ከነበረው በተጨማሪ ሌሎች አንድ ሺሕ ፍልስጤማዊያን ሰማዕታት ቤተሰቦች የሐጅ ዕድል እንዲያገኙ ፍቃድ መስጠቷን አስታወቀች፡፡ ሀገሪቱ ለፍልስጤማዊያኑ ተጨማሪ መስጠቷን ያስታወቀችው ዛሬ ሰኞ ነው፡፡
በንጉሥ ሰልማን ቢን ዓብዱልዓዚዝ አማካይነት የተሰጠው የሐጅ ዕድል፣ በዘንድሮው ዓመት የሐጅ ዕድል ያገኙ የፍልስጤማዊያን ሰማዕታት ቤተሰቦችን ቁጥር ሁለት ሺሕ ያደርሰዋል፡፡
ሁለቱን ቅዱሳን ሥፍራዎች የያዘችው ሳዑዲ ዐረቢያ፣ ከመላው ዓለም የተለያዩ ሀገራት እስከ ቅዳሜ ድረስ 1.3 ሚሊዮን ምዕመናንን ተቀብላለች፡፡ ሀገሪቱ ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ለአንድ ሺሕ ፍልስጤማዊያን ሰማዕታት ቤተሰቦች የሐጅ ዕድል ሰጥታ ነበር፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ ከዚህ ቀደም እንዳስታወቀችው፣ ከፍልስጤማዊያን ውጪ ከመላው ዓለም ከ88 ሀገራት የተውጣጡ 1 ሺሕ 300 ምዕመናን የሐጅ ዕድሉን ሰጥታለች፡፡ ከእነዚህ ውስጥ የተካተቱት 22 ምዕመናን ተጣብቀው የተወለዱና በተለያዩ ጊዜያት በሀገሪቱ ሕክምና አግኝተው እንዲነጣጠሉ የተደረጉ መንትያ ሕፃናት ቤተሰቦች ናቸው፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ በዘንድሮው 1445 ዓ.ሂ የሐጅ ሥነ ሥርዐት ከመላው ዓለም ከሁለት ሚሊዮን በላይ ምዕመናንን ትቀበላለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በዚህ ሳምንት ለሚፈጸመው የሐጅ ክንውን፣ በቀጣይ ቀናት ሌሎች አንድ ሚሊዮን ምዕመናን ወደ ሀገሪቱ እንደሚገቡ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ገልጸዋል፡፡
የ1445 ዓ.ሂ የሐጅ ሥነ ሥርዐት መከናወን የሚጀምረው ከፊታችን ጁመዓ ዙልሒጃ 8 አንስቶ ባሉት ተከታታይ ቀናት መሆኑ ይታወቃል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)
ዝርዝሩን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡-https://minbertv.com/?p=8368
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👏14👍9
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"እብዶች" ሰው ቢፈነክቱ ተጠያቂ ይሆናሉ?
ሙሉ ፕሮግራሙን የዩትዩብ ቻነላችን ላይ ያገኙታል።
🔗 https://youtu.be/7FELdSXUj9Q 🔗
#አንዲት_አንቀጽ
#መወዳ_መዝናኛ
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ሙሉ ፕሮግራሙን የዩትዩብ ቻነላችን ላይ ያገኙታል።
🔗 https://youtu.be/7FELdSXUj9Q 🔗
#አንዲት_አንቀጽ
#መወዳ_መዝናኛ
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👍10❤3
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለምን ፈተና ይበዛብናል?!
ሙሉ ፕሮግራሙን የዩትዩብ ቻነላችን ላይ ያገኙታል።
🔗 https://youtu.be/T_A4_h876JM 🔗
#የዱንያ_ፈተና #ሴቶች_በ10ቱ_ቀናት
#ሰሞነ_ሐጅ
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
ሙሉ ፕሮግራሙን የዩትዩብ ቻነላችን ላይ ያገኙታል።
🔗 https://youtu.be/T_A4_h876JM 🔗
#የዱንያ_ፈተና #ሴቶች_በ10ቱ_ቀናት
#ሰሞነ_ሐጅ
★ ★ ★
Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
👌8👍7