KUE Community / አዲስ ነገር መረጃ /
4.24K subscribers
545 photos
4 videos
180 files
101 links
Kotebe University of Education Community / አዲስ ነገር መረጃ /
Download Telegram
ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ካላንደርን ይፋ አድርጓል፡፡

በትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ኮራ ጡሹኔ በቀን ነሐሴ 12/2017 ዓ.ም የተፈረመ የ2018 ትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ካላንደር ዝርዝር ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተልኳል፡፡

መስከረም 05-06/2018 ዓ.ም

📌 የመጀመሪያ ዓመት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች (ሪሚዲያል ተማሪዎችን ጨምሮ) በየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ሪፖርት ያደርጋሉ፡፡

መስከረም 08-09/2018 ዓ.ም

📌 የሁሉም የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ተማሪዎች (ሪሚዲያል ተማሪዎችን ጨምሮ) ምዝገባ ያደርጋሉ፡፡

መስከረም 12/2018 ዓ.ም

📌 የሁሉም የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ተማሪዎች በቅጣት ምዝገባ፣

📌የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት ይጀመራል፡፡
4
ኃላፊነታቸውን የማይወጡ የግል የትምህርት ተቋማት ላይ ከባድ ርምጃ ይወሰዳል
++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በማይወጡ የግል የትምህርት ተቋማት ላይ ከበድ ያለ ቁጥጥር እየተደረገ ከባድ ርምጃ ወሰዳል ሲሉ አስጠነቀቁ።

የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በዳግም ምዝገባ አፈጻጸም ዙሪያ ከግል ከፍተኛ ተቋማት ጋር እየተወያየ ነው።

የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በውይይቱ ላይ እንዳሉት፤ በቀጣይ ዓመት የግል ተቋማት ላይ የሚደረገው ቁጥጥር ከበድ ያለ ነው።

በዚህም የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት የማይወጡ ተቋማት ላይ የሚወሰደው ርምጃም ከባድ ይሆናል ብለዋል።
ሚኒስትሩ እንዳሉት፣ በአዲስ አበባ ባለፈው አንድ ዓመት በሁሉም የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከፍቃድ ጋር ተያይዞ ምዘና ሲካሄድ ቆይቷል።

በዚህም ከተቋማቱ ጋር ስራዎች ሲሰሩ ቢቆዩም አሁንም ያልጠሩ ልክ ያልሆኑ አሰራሮች አሉ ብለዋል።

የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለትምህርት ሳይሆን ለገንዘብ ብቻ መስራታቸው ተገቢ አይደለም ሲሉም ገልፀዋል።

በዳግማዊት አበበ
+++++++++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ትምህርት #ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ
2
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ የትምህርት ባለስልጣናት ለሀገሪቱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጠንካራ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል፦ አዲስ የተቀመጡትን የጥራት ደረጃዎች በአንድ ዓመት ውስጥ ካላሟሉ ፈቃዳቸውን ሊነጠቁ እንደሚችሉ አስታውቀዋል።

ማስጠንቀቂያው ሰኞ ዕለት በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የተሰጠ ሲሆን፣ ይህም የፌደራል ስልጠና እና ትምህርት ባለስልጣን በመቶዎች የሚቆጠሩ የግል ኮሌጆችን ሲገመግም የቆየበትን የፍተሻ ሪፖርት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ነው።

"ከዚህ በኋላ ያለ ትምህርት ዲግሪ ያዥ መኖር የለበትም" ሲሉ ፕሮፌሰር ብርሃኑ በሚኒስቴሩ ዋና መስሪያ ቤት በሰጡት መግለጫ፣ በስፋት የተንሰራፋውን ነገር ግን ወጣ ገባ የሆነውን የሀገሪቱን የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በጠንካራ ቃላት ወቅሰዋል።

ባለስልጣኑ ተቋማት እንደገና ለመመዝገብ ከህንጻ ደረጃዎች እስከ ስርዓተ-ትምህርት ዝግጅት እና የመምህራን ብቃት ድረስ ከ500 በላይ አመላካቾችን አስቀምጧል። ለማመልከት ከሚጠበቁ 375 ተቋማት መካከል፣ ተደጋጋሚ የማጣራት ሂደቶችን አልፈው ለሙሉ ግምገማ ብቁ የሆኑት 290ዎቹ ብቻ ነበሩ። ከእነዚህም ውስጥ፣ ፈቃዳቸውን ለማቆየት የሚያስችለውን ዝቅተኛውን መስፈርት ሙሉ በሙሉ ያሟሉት ሶስት ተቋማት እና የሶስት ተቋማት ካምፓሶች ብቻ ናቸው።

የባለስልጣኑ የከፍተኛ ትምህርት ፈቃድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ህይወት አሰፋ እንደገለጹት፣ የፍተሻው ውጤት በሶስት ምድቦች ተከፍሏል፦ ሙሉ ፈቃድ ያገኙ፣ "በልዩ ሁኔታ" ስር ተመዝግበው የአንድ ዓመት የእፎይታ ጊዜ የተሰጣቸው፣ እና አንዳንድ መስፈርቶችን አሟልተው ሌሎችን ላላሟሉት የስድስት ወራት ጊዜያዊ እድል የተሰጣቸው ናቸው።

"ካምፓሶቹ የተማሪዎችን መሰረታዊ ፍላጎት የማያሟሉ ከሆነ፣ መኖር የለባቸውም" ያሉት ወ/ሮ ህይወት፣ ብዙ ኮሌጆች በተደራጀ ቦርድ ወይም የአስተዳደር መዋቅር ሳይሆን በግለሰቦች የሚመሩ ሆነው መገኘታቸውንም አክለዋል። ትልቁ ክፍተት የታየው በቢዝነስ እና በማርኬቲንግ ትምህርት ክፍሎች ላይ ሲሆን፣ እንደ ህክምና ያሉ ልዩ የትምህርት ዘርፎች ደግሞ ከማስተማሪያ ሆስፒታሎች እና ከላብራቶሪዎች ጋር የተያያዙ ጥብቅ አዲስ ግዴታዎች ተጥለውባቸዋል።

"የመጀመሪያዎቹ የጥራት ደረጃዎች እንደወረዱ ቢተገበሩ ኖሮ፣ አንድም ተቋም ብቁ አይሆንም ነበር" ሲሉ ወ/ሮ ህይወት ለ'ሸጋ' ድረ ገጽ ተናግረዋል።

የግል ተቋማት መሪዎች በበኩላቸው፣ የጥራት ደረጃዎቹ አስፈላጊ ቢሆኑም "ፈታኝ" እንደሆኑ ይገልጻሉ። የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ገበየሁ፣ አንዳንድ መስፈርቶች የሀገሪቱን የሀብት ውስንነት ከግምት ውስጥ ያላስገቡ እና "ተጨባጭነት የጎደላቸው" ናቸው ሲሉ ተከራክረዋል። ጥብቅ የመረጃ አሰባሰብ እና የእውቅና መስፈርቶችን እንደሚቀበሉ ገልጸው፣ ነገር ግን ይህንን ለማሟላት እንደ ከመንግስት ሆስፒታሎች ጋር ያሉ አዲስ አጋርነቶች እንደሚያስፈልጉ ተናግረዋል።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ግን አቋማቸውን የማለዘብ ምንም ምልክት አላሳዩም። ባለፉት አራት ዓመታት ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ ከግል ኮሌጅ ባለቤቶች ጋር በመሰብሰብ፣ ከገንዘብ ተነሳሽነት ወጥተው ለዛሬው የስራ ገበያ ዝግጁ የሆኑ ምሩቃንን የማፍራት ራዕይን እንዲከተሉ ሲወተውቱ ቆይተዋል።

ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የግል ኮሌጆች በፍጥነት በተበራከቱባት ኢትዮጵያ፣ የመንግስት ይህ እርምጃ ወሳኝ ለውጥን ያሳያል፦ ልል ቁጥጥር የነበረበትን ስርዓት በአለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎች በሚመራ ስርዓት ለመተካት የሚደረግ ጥረት ነው። በአሁኑ ሰዓት በዋና ከተማው እየተካሄደ ያለው ይህ የግምገማ ስራ፣ በቀጣዩ ዓመት ወደ ክልሎችም እንደሚሰፋ ይጠበቃል።
8👏1
*የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ፕሬዘዳንት የሥራ ርክክብ አደረጉ*
🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝🤝

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከህዳር 2009 ዓ.ም ጀምሮ ዩኒቨርሲቲውን በፕሬዘዳንትነት ሲያገለግሉ የቆዩትን ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠናን አመስግኖ በመሸኘት፣ ለአዲሱ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተሾመ ነቃጥበብ አቀባበል አድርጓል፡፡
በሥነስርዓቱ ላይ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የአስተዳደር ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ የተገኙ ሲሆን፣ ተሰናባቹ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና፣ ዩኒቨርሲቲውን ሲመሩ በቆዩባቸው ጊዜያት ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ተግባራትና ያጋጠሟቸውን ተግዳሮቶች፣ እንዲሁም በቀጣይ የታቀዱ ተግባራትን በመግለጽ፣ አመራርነት ቅብብሎሽ በመሆኑ አዲሱ ፕሬዘዳንት የተጀመሩትን ተግባራት እንዲያስቀጥሉ አደራ ብለዋል፡፡
አዲሱ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተሾመ ነቃጥበብ በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ለበርካታ ዓመታት ማገልገላቸውን በመጥቀስ፣ የሀገር ውስጥና ዓለምአቀፍ ልምዳቸውን በመጠቀም የተጣለባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እንደሚሠሩ፤ በቀጣይ ጊዜያትም ኮተቤ እንደ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ምንምን ጉዳዮችን አሻሽሎና አካቶ መቀጠል እንዳለበት፣ በሠራተኞችና በአመራሩ መካከል ስለሚኖረው ግንኙነት፣ በአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲው ስለሚጓዝባቸው አቅጣጫዎችና አሠራሮች ገለጻ አድርገዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የአስተዳደር ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ፣ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት ከአዲሱ ፕሬዘዳንት ጋር በትብብር በመሥራት የዩኒቨርሲቲውን ተልዕኮዎች የማሳካት ተግባራት እንዲያከናውኑ አሳስበው፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱም ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን ተግባራት በቅርብ ሆኖ እንደሚደግፍ ገልጸው የቀድሞ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና ተቋሙን በዚህ ደረጃ ለውጠው ለማሰረከብ ለከፈሉት ዋጋ በትምህርት ሚኒስቴር ስም አመስግነዋል ፣፡
በመጨረሻም የቀድሞው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና፣ ለአዲሱ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተሾመ ነቃጥበብ የዩኒቨርሲቲውን የ2017 ዓ.ም ሪፖርት፣ የዩኒቨርሲቲውን ፍኖተ ካርታ፣ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ እና ዩኒቨርሲቲው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የተሰጠውን የማስፋፊያ ቦታ ካርታ አስረክበዋል፡፡

_የህዝብ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት_
9👍3
ጥንዶቹ ዛሬ ተመረቁ

* የሁለት ልጆች እናትና አባት ናቸው
* ሁለቱም በተለያዩ አመራር ቦታ ያሉ ናቸው
* መማራችን ይቀጥላል! - ብለዋል

#Ethiopia | የኢምራልድ ኢንተርናሽናል ኮሌጅን የሊደርሺፕ ፕሮግራም አጠናቀው በዛሬው እለት በሒልተን አዲስ ሆቴል የተመረቁት ዶ/ር አልማው ክፍሌ እና ባለቤታቸው ወይዘሮ ፍሬህይወት ወልደማርያም፣ ትምህርት በየትኛውም የሕይወት ምዕራፍ ማቆሚያ እንደሌለው በጋራ ምረቃቸው ላይ ለ Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ዝግጅት ክፍላችን በሰጡት ገለጻ አብራርተዋል።

ዶ/ር አልማው የሕግና የታሪክ ባለሙያ ሲሆኑ፣ ወይዘሮ ፍሬህይወት ደግሞ በቢዝነስ ማኔጅመንት የማስተርስ ዲግሪ አላቸው። በሁለቱም የሙያ መስኮች ከፍተኛ ዕውቀትና ልምድ ቢኖራቸውም፣ በትምህርት ፍቅር ተነሳስተው ወደ ኮሌጁ የመጡት በጋራ ነው። ዶ/ር አልማው ወደ ኮሌጁ የገቡት በባለቤታቸው ተጽዕኖ መሆኑን ገልጸው፣ በሳቸው ላይ ያዩት የትምህርት ፍላጎትና ቁርጠኝነት “ለምን እኔ አልማርም?” ብለው እንዲወስኑ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።

ወይዘሮ ፍሬህይወት ይህን የሊደርሺፕ ትምህርት የወሰዱት በሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካኝነት ሴቶችን ለአመራርነት ለማብቃት በተሰጠ ዕድል መሆኑን ገልጸው የዛሬው ምረቃ ልዩ የሚያደርገውም ከባለቤታቸው ጋር በጋራ መመረቃቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ሁለቱም ጥንዶች ትምህርት የህይወት ዘመን ጉዞ እንደሆነ ይስማማሉ። “ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፣ መማር ደግሞ ብዙ ነገር ይጨምራል” ያሉት ዶ/ር አልማው፣ ዓለም በየጊዜው እያደገችና እየተስፋፋች ባለችበት በዚህ ዘመን ራስን ከአዳዲስ ዕውቀት ጋር ማዘመን የግድ መሆኑን አብራርተዋል።

ወይዘሮ ፍሬህይወት በበኩላቸው፣ ልጆቻቸው ትምህርት የማያልቅ ጉዞ መሆኑን ከእነሱ ሕይወትና ተግባር እንደሚማሩ ገልጸዋል። “የኛ ላይብረሪ የጋራ ነው” በማለትም ልጆቻቸውን በጋራ እንደሚያስተምሩና ለቀጣይ የትምህርት ደረጃም እንደሚያበረታቷቸው ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ባልና ሚስቱ ባሁኑ ጊዜ አመራርነት በሁሉም የሕይወት ዘርፍ አስፈላጊ ክህሎት መሆኑን አስረድተዋል። በተለይ በዲጂታል ዘመን ራስን፣ ቤተሰብንና ተቋምን መምራት በቂ እውቀትና ክህሎት እንደሚፈልግ ጠቁመዋል። “ዲጂታል ሊደርሺፕ አሁን አማራጭ ብቻ ሳይሆን የግድ አስፈላጊ ነው” ያሉት ዶ/ር አልማው፣ የቀድሞ ባህላዊ የአመራር ዘይቤ እየተለወጠ በመሆኑ አመራሮች ራሳቸውን ማሻሻል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

ወይዘሮ ፍሬህይወት እንደ ሀገር አሁን የሚታዩ የአመራር ክፍተቶችን ለመሙላት እያንዳንዱ አመራር የሊደርሺፕ ትምህርት መውሰድ ጠቃሚ መሆኑን አስረድተዋል። ከልምድ ብቻ የሚገኝ የአመራር ብቃት በትምህርታዊና ሳይንሳዊ ዕውቀት ቢታገዝ የተሻለ ውጤት እንደሚያመጣ ገልጸዋል።

በመጨረሻም ሁለቱም በጋራ በኢምራልድ ኢንተርናሽናል ኮሌጅ ያገኙትን ዕውቀት ለወደፊት ህይወታቸውና ለሚመሩዋቸው ተቋማት እንደሚጠቅም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
8
Delegation from China’s Henan Province Visits Kotebe University of Education
********

(KUE, September 7, 2017) – A high-level delegation from China’s Henan Province visited Kotebe University of Education (KUE), where they were warmly welcomed by the university’s senior leadership.

In his welcoming remarks, Dr. Teshome Nekatibeb, President of KUE, expressed appreciation for the visit and emphasized the university’s readiness to strengthen cooperation with the University of Science and Technology in Henan Province mainly with Zhengzhou Normal University. He highlighted opportunities for experience sharing, student and faculty exchanges, joint research projects, and the establishment of the International Laboratory of Psychological and Disability centre at Kotebe University of Education.

The head of the delegation, a Member of the Party Leadership Group and Director General of the Henan Provincial Department of Science and Technology, Chen Zhiqiang conveyed gratitude for the hospitality KUE rendered them. He noted that China has expanded cooperation with African countries and emphasized that their university, as a science and technology institution, and Psychological and Inclusion Studies, had already initiated joint initiatives with KUE. He underscored their collaboration in International Laboratory facilities and infrastructure support and reaffirmed their commitment to advancing ties in the spirit of partnership and brotherhood.

Dr. Melkamu Afeta, Director of the Industrial Linkage and Technology Transfer Directorate at KUE and member of research project, gave a presentation on collaboration and why for, KUE International Collaboration and Partnership experiences, the Project Progress and Future Cooperation areas between KUE and Henan Province of Science and Technology. He explained the cooperation agreement process, stressing the importance of knowledge and technology transfer and KUE’s strong interest in building long-term collaboration.

It is recalled that the two institutions had already cooperated in areas such as laboratory establishment, visit to International Laboratory for knowledge and innovative technology transfer, join research projects, arranging joint workshops, symposiums and conferences, collaborative consultancy and capacity building initiatives, and particularly Artificial Intelligence development and mental health. Both sides agreed to further strengthen cooperation in these key areas.

The Henan delegation also visited KUE’s computer laboratories, where they observed facilities including desktop computers and laptops that were donated by Zhengzhou Normal University. Their visit marked a continuation of discussions initiated nearly two years ago on the cooperation agreement between the two universities.

Public and International Relations Executive Office
2