ቅንጭብጭብ
7.21K subscribers
411 photos
9 videos
4 files
500 links
ካየሁት 👀 አስገራሚ
ከሠማሁት 👂 መሣጭ
ካነበብኩት 📖 አስተማሪ
ካሠብኩት ♀🅱 ልዩ ልዩ

እነሆ #ቅንጫቢ

ፅሁፎቻችሁን በ @bcrAzykid አካፍሉን።

ለማንኛውም አስተያየት ጥያቄ እና ጥቆማ @bcrAzykid ይጠቀሙ።
Download Telegram
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

ታሪክ ሲደገም
°°°°°°°°°°°°°
‹‹እዘምታለሁ!››
‹‹አትዘምትም!››
‹‹እዘምታለሁ!››
‹‹አይሆንም! አትዘምትም! . . . ዛሬ ከመቅፅበት አስነስቶ ካላዘመትኩ የሚያሰኝህ ምንድን ነው? ቆይ እኔ እናትህ ምን አጎደልኩብህ? እ?›› እናቴ አፈጠጠችብኝ፡፡ ምን ብዬ መልስ ልስጥ? መልሴስ እናቴን ያሳምናት ይሆን?

እናቴ ሁሌ ምትጨቃጨቀኝ በፀጉሬ ምክንያት ነበር፡፡ ‹‹ይኼ ፀጉርህ ተንጨብርሮ ሽፍታ አስመሰለህ፤ ምናለ ብታስቀንሰው!›› ትለኛለች፡፡ ‹‹አልስተካከልም!›› ብዬ እወጣለሁ፡፡ ለምን የሚል ጥያቄ ከማንሳቷ በፊት ሸሽቼ ማምለጥ እፈልጋለሁ፡፡

እንደ እውነቱ ከሆነ ፀጉሬን ማልስተካከለው ማሳደግ ፈልጌ አይደለም፡፡ ከፀጉር አስተካካይ ደንበኛዬ ድብን ያለ ፍቅር ስለያዘኝ፤ ከእሷ ውጭ ራሴን ለማንም አሳልፌ መስጠት አልፈልግም፡፡ (ራሴን ስል ፀጉሬ የተከመረበት የአዕምሮዬን ቅል መሆኑ ልብ ይባልልኝ) እሷ ደግሞ ቤተሰብ ልትጠይቅ ከሄደች ወር አለፋት፡፡ በሄደችበትም በጣም ቆየች፡፡ የኔም ፀጉር ያለቅጥ አደገ፡፡
.
.
ከትናንት በስቲያ የመጣችው ፍቅሬ… ዛሬ ፀጉር ቤቷን መክፈቷን ሳውቅ ዘው ብዬ ገባሁ፡፡ ደግሞ ይበልጥ አምሮበታል፡፡ ብር ቢኖረኝ በወር የምታገኘውን እየከፈልኳት የማንንም ፀጉር ሳትነካካ የኔ ብቻ ፀጉር አሽሞንሟኝ አደረጋት ነበር፡፡ እሷ ፀጉሬን ስታሽሞነሙን፤ ፊት ለፊት ባለው መስታውት ሙሉ ገጿን እያየሁ ሀሴትን እጠጣለሁ፡፡ ፀጉር ቤት ውስጥ መስታውት ባይኖር ምን ይውጠኝ ነበር? እንጃ!!

ፀጉሬን ስታበጥር በመስታውት እያጮለቅኩ ሳያት ቆየሁ፡፡ ለእሷ ስል ምንም ነገር አደርጋለሁ፡፡ ምንም ነገር!! እሷን የሚያስደስታትን ምንም ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ አልልም፡፡ ግን አፍ አውጥቼ ፍቅሬን ልገልፅላት ድፍረት የለኝም፡፡ ታፍቅረኝ አታፍቅረኝ እንኳ አላውቅም፡፡ ግን ተጫወችነቷና ለኔ ያላት አቀራረብ ተስፋን ይፈነጥቅልኛል፡፡

አበጥራ እንደጨረሰች ማስተካከያ መሳሪያውን አነሳችና በመስታውቱ ስታየኝ አየኋት፡፡ ፈገግ አልኩ! ፈገግ ብላ ‹‹አርበኛ መስለህልኝ የለ እንዴ! ፀጉርህን ከምትቆረጥ ብትዘምት ደስ ይለኛል›› አለችኝ፡፡ ፀጉሬ ልብሴ ላይ እንዳይራገፍ ያነጠፈችልኝን ጨርቅ ከላዬ ገፍፌ፤ ፀጉሬን እንዳጎፈርኩ ፀጉር ቤቱን ለቅቄ ወደ ቤቴ አቀናሁ፡፡ እናም ፍቅሬ ደስ የሚላትን ላደርግ ከእናቴ ጋር የጦፈ ጭቅጭቅ ጀመርኩ፡፡
.
.
ለእናቴ ይኼን እውነታ ነግሬ፤ በቃ ለፍቅር ስል በቁርጠኝነት ለመዝመት መወሰኔን ሳሳውቃት… ራሷን ይዛ ‹‹ለካ ታሪክ ራሱን ይደግማል የሚባለው እውነት ነው›› አለች፡፡
‹‹እንዴት?›› ግራ ገብቶኝ ጠየቅኩ፡፡

‹‹እኔ ባንተ እድሜ ሳለሁ… የሰፈሩን ኮበሌ በምላጭ ፀጉሩን እየሸለትኩ ሸጋ አስመስዬ እሰደው ነበር፡፡ … "የወርቅዬ እጅ ወርቅ ነው! ያውም የነጠረ!" እያለ፤ ከኔ ዘንድ መጥቶ ፀጉሩን ማይዋብ ኮበሌ አልነበረም፡፡ ከአባትህ በቀር!! አባትህ ለካ በዐይን ፍቅር ተለክፎ ወደኔ መጠጋት ይፈራ ነበር፡፡ … "ተው ወርቂቱ ዘንድ ሂደህ ተዋብ!" ቢባል… "ወይ ፍንክች!" ይል ነበር አሉ፡፡ ታዲያ አንዴ እንደምንም መጥቶ ከእግሬ ስር ተቀመጠ፡፡ እኔም ከመሸለቴ በፊት ፀጉሩን በጠር በጠር ሳደርገው፤ አርበኛ መስሎ ቁጭ! … "አንተዬ አርበኛ ስትመስል ሸጋ አይደለህ እንዴ! ከምትሸለትስ አርበኛ ብትሆን ደስ ይለኛል!" ከማለቴ ወፈፍ ብሎ ተነሳ፤ መዋቡን ትቶ ከጎኔ ራቀ፡፡ ከዛ ከሰፈሩ ሳላየው ስቀር ጭንቅ ጥብብ እያለኝ ወዳጆቹን ስጠይቃቸው፤ የአባቱን ነፍጥ አንግቶ አርበኛ ሊሆን ጫካ መውረዱን ሰማሁ እልኃለው፡፡››
.
.
‹‹እናቴ ታሪክ ሙሉ በሙሉ እንጂ ተቆንፅሎ በከፊል ሊደገም አይገባም!›› ብዬ ለመዝመት ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ፡፡
.
.
ኤልዳን ለፍቅር (ዳን ኤል)

@kinchebchabi @kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

ፀበል ፥ በሚፀበሉ ፥ የጋኔን ፥ ማደሪያ ፥ በሆኑ ፥ ሰዎች : መሀል : ተከብቤያለው ፥ እንደርቢ ፣ ቡዳ ፣ አዛዝኤል : መተት ፣ ሰላቢ ፣ ድግምት...ወ..ዘ.ተ..........እዝጎ: ብዛታቸው ፥ ግን : እግዜሩ : ብዙ : ተባዙ ያለው : እነሱን ፥ ሳይሆን ፥ አይቀርም። እንዲህ : አንደ : ምድር : አሸዋ : ያበዛቸው። ምናልባት :ውስጣቸው :ስለማይገኝ : ይሆናላ : ብዬ ፥ የጥያቄም ፥ አባት ፥ የመልሱም ፥ እናት ፥ ሆኜ ፥ ቁጭ አልኩ።

እኩለ : ሌት : ላይ ጋደም : ብዬ : ሳለ እማሆይ በደጃፌ : አለፉ ብሩኬ...... ብሩኬ........ በለሆሳስ : ተጣሩ

እ......... አቤት : እማሆይ .... በመደነባበር : ስሜት

አንት : ሙዠሌያም : በሩን : ክፈት .....

ቀጭን : ትእዛዝ ......

እጄ ፥ ወደበሩ ፥ መክፈቻው ፥ አኮበኮበ..... ሲጢጢጢጢጥ... በሩ ፥ ተከፈተ።

እማሆይ ፥ እርቃናቸውን ፥ ናቸው ደነገጥኩ ራሴን እማሆይ : ፃድቅ : ናቸው : የፀጋ : ልብስ : (ፀጉር) ፈጣሪ : አከናንቧቸዋል : ብዬ ራሴን : መሸወድ ፈለኩ።

በርግጥ ፥ እሳቸው ፥ አፍላ ፥ እድሜ ላይ ናቸው። ቁንጅናቸውም ፧ እንኳን ለንደኔ ፥ አይነቱ አለማዊ መናኝንም ፥ ከአቋሙ ፥ ያዋዥቃል።

የጌታ ፥ ፍቃድ : ሆነና : እማሆይም : በውበታቸው ማርከው : መደቡ : ላይ : አጋድመው ፧ ደጋግመው : ነጠሩብኝ....

መቼም ልጄ ነገር በሶስት ይፀናል አሉኝ...... ልክ አንደኛውን ፧ ዙር እንደጨረሱ....

በተወደደ ፥ መቅኔ ፥ መተኪያ በማይገኝበት ፥ ቦታ ላይ ምን ፥ ኩነኔ ፧ ገባሁ? ፥ ጃል! አዎንታዬን ፥ ራሴን በመነቅነቅ ፧ ሶስት ግዜ ፧ እንጢነጥሩብኝ ፈቀድኩላቸው።


ስብሀት ለአብ_____ ቸፍ
ስብሀት ለወልድ_____ ቸፍ
ስብሀት ለመንፈስ ቅዱስ____ ቸፍ

ጠበል ፥ የሚረጩኝ ፥ ግርማ ፧ የ ሞገስ ፥ ተላበሱ አባት በመስቀላቸው ፧ ጀርባዬን እየደለቁ። አንተ ማነህ ?
ፈርጠም ፧ ብለው ፧ በነጎድጓድ ፧ ድምፃቸው....

ሴት ነኝ ያውም መነኩሴ.....

ሴት......ምንድነሽ?

ሴት አይነጥላ ፣ ሴት ሳር

የምንኩስና ስምሽ ማነው?

#እማሆይ_ረታ_ነጠረች

ወደሲኦል ትገቢዘንድ በእግዚአብሄር ስም አዝሻለው ጮኸሽ ውጪ..

ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡ ጮሄ ወደኩኝ .

ከወደኩበት ስነሳ ብዙ ምዕመን በቤተክርስቲያን ውስጥ ታድሞ የሚሆነውን በጥሞና ይመለከታል

ስምህ ማነው አሉኝ ግርማቸው የሚያስፈራ አባት

#ካሳ_ውቤ_ልዋጥህ

ህምምም ¡ አለ ነገር......

ፀሀፊ
ሱራፌል ጌትነት
ሱራ ቢራቢሮ
@surabirabiro🦋

።።።።።👇👇👇👇።።።።።
🦋🦋 t.me/kinchebchabi 🦋🦋
🦋🦋 t.me/kinchebchabi 🦋🦋
🦋🦋 t.me/kinchebchabi 🦋🦋
🦋🦋 t.me/kinchebchabi 🦋🦋
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
////////////////////

#ልቤ_ልብ_እሚለው?!

ዘመን መቀየሩን በጋና ክረምቱን
ተፈራርቆ መቆም ጨረቃ ፀሐዩን
ሙቀትና ብርድን አካሌ እሚለየው
ብርሃንና ጨለማን ላይኔ የሚታየው
ከጎኔ ስትሆኝ ወይ ስትርቂ ነው
ልቤ ልብ እሚለው..
ከጎኔ ስትሆኝ በጋ፣ፀሐይ፣ሙቀትና ብርሃን
ከጎኔ ስትርቂ ጨረቃ፣ብርድና ጨለማን!!


✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

@kinchebchabi
@kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
////////////////////////
.
.
.
ቅድመ ሰው አዳም ያኔ በብቸኝነት ብርዱን ለመቋቋም መላ ሰዉነቱን ጨርቅ ሊጥልበት ጥጥ ሲባዝት ኩታ ሲጠልፍ ጋቢ አብጅቶ ሲጨርስ ብርዱን ለመደው..!
እኔ ግን በቀዝቃዛ ሐገር በደጋማ ቦታ መልመድን አልሻም የብቸኝነትን እዳ አንዳች ብርሃንን አንዳች ሙቀትን ሚቸር የተዘረጋ እጅሽን ይሄው እጠብቃለሁ አቅፎ እስኪሸሽገኝ ብርዱን ሳልላመድ ቀድሞ እንዲላመደኝ..!

መስከረም 2/2014 ዓ.ም

Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

@kinchebchabi
@kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

ፀሐይ ስትወጣ.. በዳመና የተሸፈነው ሰማይ ብርሃን ሲጎናፀፍ ከጠባብ ደረቴ ከአጭሩ አንገቴ ስር ከእቅፌ ዉስጥ ሁነሽ በረንዳ ላይ ቁመን አንችን ተጎናፅፌ ጀንበሯን እያየን ቀኑ ይጀምራል ታዲያ ከዚህ በላይ ምንስ ያስደስታል..?!


✍️ Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

@kinchebchabi
@kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
?!?!?!?!?!?!?!?!?!?!?!?!?!?!
.
.
.
እኛ..
ሁለት አንድ አካሎች ፍቅር ያቆራኘን
ሃገር ሞልቶ እያለ ቦታ ያላገኘን
እኛ..
ክንፋችን እረጅም ህልማችን መብረር
ጎጆ ያልቀለስን ተጠግተን ምንኖር
እኛ..
ሁለት አንድ ነብሶች ናፍቆት ያንገላታን
ጊዜ ሞልቶ እያለ ለእፎይታ አፍታ ያጣን
እኛ..
አንድ አካል አንድ ነብስ
ናፍቆት የፍቅር ቁስ
እኛ..

መስከረም 27/2014 ዓ.ም

✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

@kinchebchabi
@kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

#ቃል < #ስሜት!
.
.
እንዲህ ነው እምወዳት
እንዲያ ነው እሚያደርገኝ
ብየ ለማስቀመጥ
ቃላት ባመራርጥ
ስሜት ነው እሚተርፈኝ
ቃል ሁሌ ነው እሚያንሰኝ..

መስከረም 27/2014 ዓ.ም

✍️ Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

@kinchebchabi
@kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
!!︎!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

#ለእኒያ_ሰባኪዎች¡¡¡
.
.
በከንፈር ፍሬያቸው
የአገሬን ነፃ አውጮች፡እስካሁን ሳቃቸው
ሲገቡ እንደ እንጀራ
ላፍ ጣፍጠው ተስማምተው
ሲወጡ እንደ እዳሪ ሸተውና ገምተው፤
ነበር እስከ ዛሬ መንበር ላይ ሲነግሱ
አንጀት እየበሉ አንጀት ሚበጥሱ፤
አሁን ግን ዘንድሮ
በሆድ በአንጀት አልፈው ተገፍተው ሳይወጡ፤
ገና ከአፍ ጀምረው መግማማት አመጡ፤
ግን
ግን
ግን
ይኸው ግማታቸው ካለ ሚስማማቸው
ሀገሬ እዳሪ ቤት አትሆንም በሏቸው።
ለእኒያ ሰባኪዎች!!!🗣😑

Jonas_Yotode
thanks for sharing your poem😊🙏

የልብዎን ድርሰት፣ ግጥም፣ ፍልስፍና፣ ስዕል፣ አባባል፣ ተረት፣ ታሪክ..ያጋሩ አሁኑኑ ይቀላቀሉ!!😊🙏
👇👇👇👇 👇👇👇👇
@YelbeDrset @YelbeDrset
@YelbeDrset @YelbeDrset
✉️✉️✉️✉️✉️✉️✉️✉️✉️
inbox me @amanYTZ23
✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
.
.
.
በህይወት የተሞላ ተፈጥሮ ለአንድ አፍታ ቢያስተዉሉት ፍፁም ድንቅ የሆነ..አመሻሽ ላይ ፀሐይ አዘቅዝቃለች ሰዉነቶ እንኳ አይታይም የእሳት መክብብ የመሰለው ብርሃኗ ግን ለሰማዩ ዉበትን ችሮታል ይሄን ብርሃን ሳይርቅ ሳይሰለብ ደርሸ ብነካው በህይወት የሚሞላኝ ይመስል ተነስና እሩጥ ተከተለው አለኝ ግን ከተጎለትኩበት ዝቅታ አልተንቀሳቀስኩም በአካቢው እየበረሩ የነበሩትን አእዋፋት ባረገኝ ብየ ተመኘሁ'ጂ..

ጥቅምት 5/2014 ዓ.ም

✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join join join
👇👇👇👇👇
t.me/YelbeDrset
t.me/YelbeDrset
t.me/YelbeDrset
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
#ግዕዝ_ክብር_ይእቲ
#ዘዘዮሐንስ (አለቃ)

መፈወስ ነፍስ ወይነ ለምንት ኢተኃሥሢ?
ዘታፈቅሪ ነፍስየጨቤተ መያሲ ትጊሢ
ወእንዘ ታነብቢ ዘልፈ ምዕዳነ ዳዊት ነጋሢ
እም እኩይ ግብር ለምንት ኢትትጋኀሢ?
.
.
.
ጠዋት በማለዳ
ወደ ጠጅ አደይ ቤት
የምትገሰግሺ አንቺ የኔ ነፍስ ሆይ!
ከጠጅ የተሻለ
ሕይወት የተሞላ ጥበብ የተሞላ
የሚፈዉስ ወይንን ለምን አትፈልጊም እሱ አይሻልም ወይ?
አዉቃለሁ ታዉቂያለሽ
የንጉስ ዳዊትን
ቅኔዉን ምክሩን ዞትር ታነቢያለሽ
ዞትር ትደግሚያለሽ።
ነገር ግን በተግባር
ወይንን ተጸይፈሽ እዛው ጠጅ ቤት ነሽ
ከማለዳ አንስቶ ጀንበር እስክትሸሽ።
ታዲያ!
ከቶ ምን ዋጋ አለው ቢያዉቁ ቢራቀቁ
ከመፅሐፍ ዉቂያኖስ ጫፍ ድረስ ቢጠልቁ
በሕይወት ካልታየ
የዕዉቀት ወሰኑ የዳዊት ድጋሙ
ጸሎትና ዕዉቀትሽ
ያለ'ካል የሚታይ ረጅም ጥላን ነው ሚሆነው ትርጉሙ
እባክሽ ነፍሴ ሆይ?

✍️ዉርስ ትርጉም
#በኤፍሬም_ሥዩም_ተሰማ

📚ምንጭ #ተዋነይ_ብሉይ_የግዕዝ_ቅኔያት_ፍልስፍና_ከቀደምት_የኢትዮጵያ_ነገሥታት_እና_ሊቃዉንት

join join join join
👇👇👇👇👇
@YelbeDrset
@YelbeDrset
@YelbeDrset
👆👆👆👆👆
📚📚📚📚📚📚📚📚
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
"..አመታት ከሚመስሉ ወር ከማይሞሉ ቀናት በኋላ አየኋት፣ ቀረብኳት፣ የምትተነፍሰዉን አየር እኩል ተነፈስኩኝ፣ ደግሞ እጆቿን ያዝኩ በስስት ተሳለምኩ አክየም አቀፍኳት ትንፋሽ እስከሚያጥራት ከንፈሯን ጎረስኩኝ አንገቷ ስር ገባሁ ጠረኗ አወደኝ! ሰከርኩ! ሰከርኩ! ሰከረኩ! ይባስ ናፈቀችኝ!..ከጎኔ እንዳትርቅ ካይኔ ሰር እንድትኖር ቃልኪዳን አሰብኩኝ..አስቤ አልቀርም..!!

✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join join join join
👇👇👇👇👇
@YelbeDrset
@YelbeDrset
@YelbeDrset
👆👆👆👆👆
📚📚📚📚📚📚📚📚
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
.
ካሜራ ማን ነኝ..!
ሁሌ ባጋጣሚ በመንገድ ላይ ሳያት
እድልም ብሎልኝ በድንገት ሳገኛት
ስትስቅ ነው ማስተዉላት
ስትስቅ ነው እምቀርፃት
በካሜራየ አይን በአልበም እማሰፍራት
ሰርክ አዲስ ፈገግታዋን በፎቶ ምይዛት
በአካል ግን በቅርበት
አልነካት አላቅፋት..
ዛሬም ከርቀት በጎዳናው ሽር ስትል
ካሜራየን አነጣጥሬ ልክ ልስላት ስል
አይኔን አላመንኩም ፈገግታዋ የለም
መልኳ ደማምኗል ዝም ብላለች ዝም..?!?
.
.
✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join join join join
👇👇👇👇👇
@YelbeDrset @YelbeDrset @YelbeDrset
🤫🤫🤫🤫🤫🤫🤫🤫🤫
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ


#ሰው_ከመሆን_ሰውሩኝ! ፬
.
.
"..ሰው ማለት ሰው የሚሆን ነው ሰው የጠፋለት ሲባል ሰምቻለሁ፤ ሰው ሆኘ ለሰው ካላዘንኩ ሰው ሆኘ ሰው ሲሞት ከእነገሌ ስለሆን የማይገደኝ ከሆነ ሰው ከመሆን ሰውሩኝ፤ ከሰው ተራ አውጡኝ።"

✍️Unknown
(ከነፃ ሃሳብ ጋዜጣ ላይ የተወሰደ)

join join join join
💔💔💔💔💔💔
@YelbeDrset @YelbeDrset @YelbeDrset
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
"በልቤም ሆነ በአዕምሮዬ አላፈቅርሽም። እንዲያው ምንአልባት ልብም መምታቱን ስለሚያቆም አዕምሮም ስለሚረሳ። በነብሴ አፈቅርሻለሁ። ነብስ በፍፁም አትቆምም ወይም አትረሳምና።"

✍️Rumi

join and share
@YelbeDrset @YelbeDrset @YelbeDrset @YelbeDrset
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

#አበባ_አየሁ

©ሲራክ ወንድሙ

እሩቅ ለሩቅ ሆነን
ይጠባል መስከረም ፥ ይታጠናል ህዳር
ፀደይ እየዳኸ
ክረምት ይጋልባል ፥ ተስፋዬን ሳሳምር

አምና በዚህ ሰዓት ፥ ጠበቅኩሽ በውርጩ
እስኪያልፍብኝ ሀሩር ፥ ወፎች እስኪንጫጩ

ጠበቅኩሽ ፥ ጠበቅኩሽ
የሌት ውብ እንቅልፌን ፥ በናፍቆት መጅ ድጬ
በመምጣትሽ እርሾ ፥ ልቤን አሳብጬ።

የአንቺ ሀገር ወዴት ነው የአድማስሽ አቀበት ?
እግሬን ላወላዳ ፥
ይቆምልኝ እንደው የልቤ ትኩሳት
ተይ ንገሪኝ ባክሽ ፥ ወዴት ነው ባዕቱ
ካቻምና ላይ ቆሜ ፥ መነነ ዘመኑ ከነፈ ጊዜያቱ

የተራራው ደረት በአደይ ፂም ጎልምሶ
የሀምሌ ጨለማ
ባባረረው ብርሃን ፥ ሲሄድ ተለሳልሶ
እንደው ለአዲስ ዓመት ፥ ትጋቴን አስታውሰሽ
ናፍቆት ፣ ተስፋ ፣ ፍቅርን - አንድ ላይ ታቅፈሽ
በሬን ከፍተሽ ግቢ ፥ አበባ - አየሁ ብለሽ
....
©ሲራክ @siraaq
https://t.me/kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
#ከማስታዎሻየ_ማህደር!!
.
.
#ሌላ_ዓለም!!
(ክፍል አንድ)
.
.
.. ትናንት ህዳር 8/2015 ዓ.ም "አርባተንሳ" ክብረ በዓልን ልታደም ወደ ገጠራማው መንደር ካ'ንድ ወዳጄ በቀረበልኝ ጥሪ መሰረት ወርጀ ነበር። ወዳጀ ካለኝ ቦታ ደርሸ ካገኘሁት በኋላ ያው እንደተለመደው 'ቅርብ ነው ደርሰናል!' እያለ ሰፈር ለሰፈር ትንሽ ተጉዘን ከቤታቸው ደረስን የቤቱ ግቢ በላም በጥጃዎችና በእርሻ የተከበበ ነው። ግቢው በር ላይ የተቀመጡ ሰዎችን ሰላምታ ሰተን ወደ ቤቱ ዘለቅን.. የቤቱ አባወራ ከሳሎኑ ጥግ ይዘው ተቀምጠዋል..ቅድሚያ እርሳቸዉን ሰላምታ ሰተን በቤቱ ያሉ እንግዶችንም ጨበጥናቸው እና የበግ ቆዳ ከተጎዘጎዘበት መደብ ቁጭ አልን። ወዳጄ ቀልጠፍ አለና ወደ ኩሽናው ዘልቆ እህቱን ምግብ እንድታመጣ አዘዛትና "ክቡር ዘበኛ" እሚባለዉን ብርጭቆና በጆክ ጠላ ይዞ መቶ ከፊቴ ቆመ.. እኔም ከቤቴ እንደበላሁና ያው ጠላም እንደማልጠጣ በመናገር አስቤ የመጣሁት "ወተት ለመጠጣት!" እንደሆነ አስታወስኩት!😋 ቢሆንም 'ካልበላህ ወተት የለም!'😑 እሚል እይታ አሳይቶኝ ለራሱ ጠላዉን ቀድቶ ቁጭ አለ። በልቤም አንድ ቁርጥ አንስቼ እበላና ወተቴን እጠጣለሁ ብየ መጠበቅ ያዝኩ ታዲያ የወዳጄ እህት በሰሃን(ባቲ) የሰማይ ስባሪ እሚያክል እንጀራ በድንች በስጋ ወጥ ይዛ መታ አስረከበችኝ!! 'ኧረ በዝቷል ይተርፋል!' ብልም ሰሚ ስላላገኘሁ ወደ ወዳጄ አባት ፊቴን መልሸ 'አባት ይባርኩልኝ?' አላኳቸው(አክባሪ ለመባል) ምን ዋጋ አለው! 'ለወንድ አይባረክም! ዝም ብለህ ብላ!' ብለው ጨነገፉኝ።😬 ኩርኩሜን ተቀብየ ከወዳጀ ጋር የቀረበልኝን ምግብ መብላት ጀመርኩ.. ወዳጄ ምግቡን አቋርጦ ወደ ኩሽናው ተወነጨፈና በግራም ሰሃን እርጎ ይዞ መጣና እንጀራዉን መሸከም ያቃታት ሰሃን(ባቲ) ላይ እርጎዉን አጥለቀለቀው..😇 በላየላይ የወረደዉን መና እያጣጣምኩ በላሁ..😋 ታዲያ በየ መሃሉ አባወራው በመገረም ለምን ጠላ እንደማልጠጣ እየደጋገሙ ይጠይቁኛል! እኔም የተለያዩ መልሶችን እነግራቸዋለሁ.. ወዳጄና እህቱም እንጀራና ወጥ እያመጡ ጨምር እያሉ ከድንች በስጋው ወጥም ከእርጎና ከንጀራዉም ይከምሩብኛል..🙄'ኧረ በቃኝ!' ብልም የቤቱ አባዎራ ጨምሮ እንግዳቹ ሁሉ 'ትንሽ ብላ እንጅ!' እያሉ አጨናነቁኝ እኔ ግን ተሎ መሃላ ዉስጥ ገብቼ ድርቅ በማለት እጄን ታጠብኩና ቁጭ አልኩ..መቼም የገጠር ሰዎች እማይበላ እማይጠጣ አይወዱም።
.
.
ይቀጥላል..


✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join and share
@YelbeDrset
@YelbeDrset

inbox me @amanYTZ23
✍️✍️✍️✍️✍️✍️
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

#ከማስታዎሻየ_ማህደር!!
.
.
.
#ህይወት_የመኖር_እዳ!!
.
.
.. ከተወለድኩ ጀምሮ እድሜዬ በጨመረ ቁጥር ወደ ህይወት እየመጣሁ ይሆን ወይስ ወደ ሞት እየሄድኩ እንደሆን አላዉቅም! ስለ ህይወት እያወኩ ለመኖር እየጀመርኩ ግን ወደ ሞት እየሄድኩ ይመስለኛል! መኖር ታዲያ እንዴት ስጦታ ሊሆን ይችላል?? ሐይማኖተኛ ሰዎች አንደበት ላይ እማይጠፋ ቃል "በህይወት ስላለህ ብቻ አመስግን!!" እሚለው ነው!! ግን ለኔ አይታየኝም! መፈጠሬን እንደስጦታ አይቼ ለማመስገን ህይወት በቃኝ እስክል መኖር አለብኝ! ካልሆናማ እንዲሁ ወደ ህይወት እየመጣሁ ወደ ሞት ከሄድኩ ስጦታነቱ ቀርቶ ኑሮ እዳ ይሆንብኛል!! ሳልሞት በፊት ተሽቀዳድሜ መኖር ያለብኝ እዳ ሁኖ ይሰማኛል። ሰው ሳይኖርም ይሞታል!
   ህይወት ከፈጣሪ እምትሰጠን ብድር ትመስለኛለች ብድራችን ለመክፈል ስንፈጋ ስንታገል የተሰጠን የክፍያ የቀን ገደብ አልቆ እኛም በነፃነት ሳንኖር እምንነጠቃት ናት። የሰው ልጅ ሁሉ "የህይወት ግብ ደስተኛ መሆን ነው!" በምትለው ህግ ይተዳደራል! ይሄን ህግ ሐይማኖተኞች ቢያጥላሉትም በነሱ ልብ እንደማያምኑበት ቢናገሩም እነሱም በሆነ የህይወት ዘመናቸው ይከተሉታል። ሁሉም ሰው በራሱ ዛቢያ ኑሮን ለማሸነፍ ይሽከረከራል፤ ኑሮን ማሸነፍ ያው ሀፍታም መሆን ነው! ብሎ አዕምሮው ላይ በሰቀለው ሃሳብ ይነዳል። መፈጠሩን እንደ እዳ ለማየት ወይንም እንደ ስጦታ ለመቀበል በቀላሉ በአኗኗር ዘይቤው ይወስናል፤ ብዙዉን ጊዜ ሀፍትን ካካበተ ስጦተነቱን በተቃራኒው በድህነት ከተሰቃየ ደግሞ እዳነቱን ይቀበላል፤ እዚህ ላይ አንዳንድ ነገረኛ አንባቢ "ታዲያ አንተ በድህነት ተሰቃይተህ ነው! ህይወት የመኖር እዳ ናት የምትል" ይል ይሆናል! ግን ህይወት እንዳለህ ሀብት ወይም እዉቀት የምትወሰን ናት በሚለው አልስማማም!! ምክኒያቱም ህይወት አወቅንም አላወቅን ሀፍታም ሆን ወይ ፀደቅን እስክንሞት ድረስ እዳ ናት!! አዋቂው ህይወትን ተረዳኋት ባላት መጠን ሲያብራራና ሲያወጣ ሲያወርዳት ትንሽ በተጠጋት ቁጥር እማያዉቀው እልፍ መሆኑን እየተረዳ አለማወቁን አዉቆ እንኳ እረፍት ሳያገኝ የእዉቀት ጥሙን ሳያረካ ያርፋል!! አላዋቂዉም መኖር ባለማወቅ የሰጠችዉን ሰላም ተቀብሎ መኖሩ ሳይታወቅ በሚራመድበት መሬት የሆነ መስመር የእግሩ አሻራ ሳይታይ ይሞታል!! ሀፍታሙ ሃፍቱን የደከመበትን ያህል ሳያጣጥመው ወይ ደግሞ በሀፍቱ ልክ ደስተኛነቱ የወረደ ሲሆንበት! ወይ ሀፍቱ እረፍት እንደነሳው ሌላ አስደሳች ግብ ወይ ምላሽ ሲፈልግ ያልፋል!! ፃዲቁ ደግሞ የፈጣሪው ፍርድ እያስፈራው በአካባቢው ያሉ ሰዎች ኑሯቸዉን በሐጢያታቸው እየለካ የመኖር ጣእሙን እርግፍ አድርጎ ትቶ ሞቱ እንዲቀርብለት እየፀለየ ይኖራል!? መፈጠሩ ስጦታ ነው ብሎ ግን መኖሩን ከመሞት በላይ አይወደዉም! ስጦታ ብሎ የተቀበለዉን ህይወት በሞት መነጠቅን ይናፍቃል እንደናፈቀዉም አይቀርምና ያገኘዉና ይቀበላል!!
   በነዚህ ሁሉ መሃል እኛ "ሁሉን ቀመስ!" እምንባል አይነት ሰዎች አለን!! የማህል ዳኛ ማለት ነን፤ ሌሎች በተለያየ አቅጣጫ የመኖራችን ግብ ብለው ያመኑበትን ሲያስቆጥሩ እምናጨበጭብ አንዳንዶች ደግሞ ሲደናቀፉም (ፋዎል) ሲሰሩ እምንታዘብ!! አለን። ለኛ ህይወት ጥያቄ እንጅ መልስ ሁና እማታዉቅ!! ህይወት የመኖር እዳ እንጂ ስጦታ ሁና እማትታየን!! ብዙ የገባን ይመስለናል ግን አንዳች ነገር አንፈታም! እምናምን ግን ደግሞ እማናምን! ወደ ህይወት እንመጣል ግን ደግሞ እማንደርስ! ወደ ሞት እምንሄድ!! እዉቁ ፈላስፋ.. "ያልተመረመረ ህይወት ለመኖር ያልተገባ ነው!" እንዳለው የኛ እዳ ጥያቄ የሆነ ነን። የናንተስ የመኖር እዳ ምንድን ነው?? እዳ ካልሆነ ስጦታነቱን በምን አመናቹህ? ስጦታነቱ ምኑ ላይ ነው? ተሰቶ እሚነጠቅ ስጦታ መሆኑንስ እንዴት ታዩታላቹህ? ወደ ህይወት እየመጣቹህ ነው ወይስ ወደ ሞት እየሄዳቹህ??
.
.
.
ህዳር 28/2015 ዓ.ም

✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join 👇👇👇
@YelbeDrset
@YelbeDrset

inbox me @amanYTZ23


@kinchebchabi @kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ ተመልሷል። 🙏
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

#ትንሽ_ስለ..!

ክፍል - ፫
.
.
.
የህይወት መንገዷ ሰፊ ነው፤ ገደሏ ጥልቅ ነው፤ ወንዞቿ ለሁሉም እኩል አይፈሱም፤ ተራራዎቿ ሁሉን አይማርኩም!! አየህ ላንተ የተፈጥሮ ድንቅ ውበት ያልከው ተራራ የሌላ ሰው አድካሚ መመላለሻ መንገድ ነው!!
 
    እሩቅ ሳንሄድ እዚሁ ከሰፈራችን እንኳ ባለፈው ጫማ እያስጠረኩ ሰማዩ ማንጎዳጎድ ጀመረ ከዚያም "እሰይ ተመስገን ዝናብ ሊዘንብ ነው በቃ ወደ ቤት ሄጄ ወይ መጽሐፍ አነባለሁ ወይ ጥሩ እንቅልፍ እተኛለሁ!" አልኩ። ይሄኔ ታዲያ ጫማዬን የሚያፀዳው ፈላ ፊቱን ኩስኩስ አድርጎ "እኔ ግን እንዳይዘንብ እማፀናለሁ ምክንያቱም ከዘነበ የኔና የወንድሜን ምሳና እራት ይቀማናል!" አለኝ።

እኔም በመገረም 'እንዴት?' አልኩት..

እርሱም.."ትናንት ሲዘንብ ውሎ ለቁርስና ምሳ ምንም ስላልሰራን ፆማችን ነው የዋለን!! አሁን እሚዘንብ ከሆነ ደግሞ በዝናቡ መስራት ስለማንችል ምሳና እራታችንን ይቀማናል!" አለኝ።
በህይወቴ እንደዚያን ቀን አፍሬ አላውቅም!!
.
.

(ከ #ትንሽ_ስለ..! ተከታታይ ልቦለድ የተቀነጨበ)

👇👇👇👇👇👇👇

t.me/YelbeDrset

👆👆👆👆👆👆👆
ቤተሰብ ይሁኑ!
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
#ለጊዜ_ጌታ_የተፃፈ_ደብዳቤ!
.
.
ፈጣሪዬ ሆይ በሰማያት የምትኖር..
ብዙ መንገድ መተናል፣
ብዙ ትዝታዎችን ቋጥረናል፣
ብዙ ተስፋዎችን ሰንቀናል፣
ብዙ ሰዎችን አቅርበናል፣
ልብ ለልብ ተሳስረናል፣
መኖር አስከፊ ገፅ ቢኖረውም!
ለመሰንበት ጓጉተናል፣
ገና መኖርን ናፍቀናል፣
አዲስ ትዝታዎችን መመስረት አስበናል፣
በጥልቅ ፍቅር ወድቀናል፣
አብሮ ማርጀትን ተመኝተናል፣
ሞትን አርቀህ ትንሽ ጊዜ ስጠን ብለናል፣

እባክህ ጌታ ሆይ..
ቅጣት ያልካት ምድር አቅፋ አኑራኛለች፣
ስረግጣት ቢመራት ልትውጠኝ 'ጠብቃለች..!
እማይቻልህ የለ
ሁሉ በጅህ አይደለ!
በቃ ጊዜን አቁመው ቀናተም ይዘግዩ፣
የሰው እድሜ ይርዘም የወጣትነቱ፤

ኧረ ባክህ ጌታ ያላየነው አለ..
አታሳልፍብን ትንፋሽህን አትንሳን
ከመምጣታችን በፊት መቆየት እንሻለን..
ወይ ደግሞ ሁሉም ይቅር! ሁሉም ባንዴ ይጥፋ፣
የቀደመው ሞቶ! ቀሪው ከሚከፋ!
ወይ ሁሉም ባንድ ይሁን..!!
.
.
.

✍️Aman😑 YTZ