ንቂ ኢትዮጵያ
541 subscribers
261 photos
83 videos
32 files
179 links
እዚ ገፅ ላይ የምናነሳቸዉ ነገሮች

፩ ስለ ኢሉሚናቲ
፪ ስለ 5G
፫ ኢትዮጵያ ላይ ስለሚደረጉ ሴራዎች
፬ ስለ GMO
፭ ስለ ግብረሰዶማዊነት
፮ ስለ ማይክሮ ቺፕ

1% CONTROL THE WORLD
4% ARE SELL OUT PUPPETS
90% ARE ASLEEP
5% KNOW AND ARE TRYING
TO WAKE UP THE 90%
THE 1% DONT WANT THE
5% WAKING UP THE 90%
Download Telegram
Forwarded from Tamene Mengste Wube (ታመነ መንግስቴ ውቤ)
ውሎ አዳር በጎንደር

(ታመነ መንግስቴ ነኝ)

ስሆነው ፣ሳደርገው የዋልኩትን በሰንበት ላውጋችሁ!

ይችን እሁድ የምትሰኝ ዕለት ፈጣሪ እኛን አበጅቶ እርፍ ብሎባታል ሲባል እሰማለሁ፣አንብቤማለሁ።

"ብታምኑም ባታምኑም ጦር ግንባር ሳለሁ ሁልጊዜ ጠዋት ጠዋት ለኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ ደውየ የግድቡን ሁኔታ እጠይቅ ነበር" እንዳሉት የአገሬ መራሔ መንግስት(ሀሳብዎ ላይ ተሳስቸ ያላሉት ነገር ብየ ተሆነ እርስዎ ተሳስተው 'የኤርትራ ጦር አልገባም' እንዳሉት ይቁጠሩት) እኔም 'ብታምኑም ባታምኑም እሁድ የእረፍት ዕለት ናት' ብያችሗለሁ።

ግን ግን ጠቅላያችን "ነገርዮሹ ስራዎት መስሎኝ? ለምን ማሳመን አስፈለገዎት_እያ!?"

ደሞስ ኢትዮጵያ ውስጥ ምን የሚሉት አለማመን ነው? አሁን እኒህ የመኪናችን ዘዋሪ እስላሙ፣ጠዋት ቁርጥ ስንበላ'ቁርስ በልቻለሁ' ያሉን ኦርቶዶክሱ ጓዴ መኪና ውስጥ መተኛትን ተልባቸው መያዛቸውን ለማረጋገጥ 'ማርያምን?' ሲላቸው 'ማርያምን' ብለው የለም? ቢራስ አብረን አልጠጣንም? ይህችን እንቆቅልሽ አገር ምን ማድረግ ይሻላል? ማሳደግ😀

ውሎ አዳር በጎንደር፦

"ምን ተሰራ ፤ምን ተወራ
ጎንደር በጀግኖች ጎራ?
ይበሰራ፣
እውቀት ሐቅ ይነገራ።"

በሚል ዘፈን ተጀመረ።የመፃፍ ጸጋየን ተጠቅሜ "የጎንደር ወዳጆቸ ጋሽ ንዋይ"ጎንደር የወርቁ ልጅ ዘውዴ ናት እናቴ!" ያለላትን በሙሉ ስሟ ዘውዴ ወርቁ የምትሰኘን የጎንደር እናት ፈልጋችሁ አገናኙኝ" ብየ ለመንኩ።ልመናየን የሰማው እግዜር(እግዜር ግን ያነባል?) ቃልኪዳን(ቃልየ ብየ ስሟን አላቀልም) የዘውዴን ምትክ ፍቅርን አገናኙኝ።ፍቅር እኮ የባለከዘራው እህት ናት።እዚያ ቤት ያጎረሰችኝን ልጅ እግዜሩ መና ያውርድላት።እግዜሩ ግን ሳልሞትበት ለአፋር ሕዝብ የሚያጠግብ ውሃም ይስጠው።

ቀኑን ሙሉ ስንፈልገው የዋልነው ሰውየ ደመቀ ዘውዱ አይደለም? እኔስ ቤቱን፣ሚስቱን፣ልብሱን፣ጉርሱን አይቸ"እንደሰው ነው የምትኖር ጋሸ!?" ብየ ብደነቅበት "እህ እንደምን ልኑር?" አለኝ።

እኔማ እንደ 'ከንቲባ' አዳነች አበቤ ብየ ነበር።እናንተ 'እዳነች አበበች'የምትሉ ነገር ሰንጣቂዎች ግን ለአማራ ሕዝብ ምን አድርጋችሁለታል?

"አማራው ያጣው መሪ ነው።መሪዎች ለራሳቸው ክብር እንጅ ለሕዝቡ አይጨነቁም።"ብላችሁስ 'ማን አለህ'? ልትሉኝ አይደል?

'ደመቀ ዘውዱ' ልበላችሁና ዳግም አስከብቡት! እናንየ 'ጎንደር ባለ ማተብ ነው፤በደመቀ ዘውዴ እና ወልቃይት ጠገዴ አይደራደርም።'

የልቅ እንየ ታከለ የባህል አዳራሽ ብቅ ብለን እንመለስ። እዚያ 'ዶፔል ቢራ 22 ብር' ተብሎ ዋጋው በር ላይ የተፃፈለት ምን ያህል አስቀያሚ መጠጥ ቢሆን ነው? ጣፋጭ መጠጥና ልባም ጎንደሬ እማ 'ሽሽግ' ተደርገው እንደ መይሳው ካሳ ላለው የአገር ዋልታ ይሰጣሉ።የራስ አሊ እናት ተዋበችን ለዳግማዊ ቴዎድሮስ የዳሩለት እኮ ዋጋዋን ለጥፈው አይደለም!

'አንች በቀሚስ የምትዋቢው ጎንደሬ ወዳጀ እነበብሻለሁ!?"

"እኔን ጎንደር ጎንደር እኔን ጎንደር ያርገኝ
የበሉት ሲስማማ የፈለጉት ሲገኝ"

የባለከዘራው እህት ቤት የበላሁት እዚህ የማይፃፍ ነገር ተስማምቶኛል።እንደምሳ በልቸው እነሆ ራትም ሆኖኛል።ኤርምያስ አመልጋ ለምን በ24 ሰዓት አንዴ ብቻ እንደሚበላ ተገለጠልኝ ልበል እንዴ? ይልቅስ 'ከኤርምያስ አመልጋ ጋር ማዕከላዊ እስር ቤት ነበርኩ" ያለኝን መኩሪያ የሆነ ፋኖ_ሻለቃ ጠዋት ቃለ መጠይቅ አድርጌ አለሁ።

አዝማሪ አማረን...!

እንየ ታከለ ቤቷ ሞልቶባታል።ባልደረባየ"እናንተ ፈስሳችሁ ነው?" ያላቸው ጎንደሬዎች(ተሌላም አገር ሊመጡ ይችላሉ።አርብ ዕለት አዘዞ ጥይቱ እንደፈነዳ ዘብ(Police )ጣቢያ ተመቶ ሁለት ሰውም ሞቶ ገብተን ወላ ሐድያ ወላ ወላይታ ብቻ ሴቶች ለስደት ሊያመልጡ ሲሉ ተይዘው አላየንም እንዴ?) በሩን አልፈው መንገዱን እየዘጉት ነው።

ተስፋ ቆርጠን('ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጥም'ሲባል እሰማለሁ።እስላምስ? እሱም አይቆርጥም።አብሮን የነበረው ሰውየ እስላም መሆኑን ተላይኛው አንቀጽ ጥፌ የለም እንዴ?) ስንጓዝ "ባላገሩ " የሚሉት የአዝማሪ ቤት አገኘን።

"እኔን ጎንደር ያርገኝ"

እዚያ ቤት ገብተን የገበየነውንስ ታልሞትኩ ተድሉ በሗላ አወጋችሗለሁ።ተሞትኩም አትደነቁ ሌላ ታመነ ወይም ሌላ እገሌ ያወጋችሗል።

"ከሰማይ በታች አዲስ ነገር የለም።" ጎንደርም በላሊበላ ዘመን ዝም ብላ ጋራ እና ሸንተረር ነበረች።ሗላ "እሽሩሩ ጎንደር"ተባለች።የፋሲል ግቢን አሃለች።አሁንም ደርግና ወያኔን ተቋቁማ እየቆዘመች፣እያስቆዘመችኝ አለች።

t.me/Gazetaw
Forwarded from ሀser
ኦርቶዶክስን በኦርቶዶክሳውያን የማዳከም አዲስ ስልት!

ባለፉት የታሪክ ገጽታዎቻችን ውስጥ በጉልበትና በይፋዊ ተቃርኖ ኦርቶዶክስን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት ሲደረጉ የነበሩ እንቅስቃሴዎች ኹሉ አልተሳኩም፤ እንዲያውም የበለጠ ሲያጠናክሯትና ሲያስፋፏት ተስተዋሉ እንጂ፡፡ ለምሳሌ፡- በግራኝ አህመድ ወረራ ዘመን
ኦርቶዶክሳውያኑን በግዳጅ የማስለም ድርጊቶች ተፈጽመው ነበር፤ ሕዝቡም ወደ እስልምና ሲገባ አምኖበት ሳይኾን ተገዶ ስለነበር ጊዜ እስኪያልፍ በትዕግሥት ሲጠባበቅ ቆይቶ ነበር፡፡ እናም፥ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እነዚያ የመከራ ዘመናት ሲያልፉ ሃይማኖታቸውን እንዲክዱ
ተገደው የነበሩ ምእመኖቿን መልሳ ወደ ጉያዋ ለመሰብሰብ እንዲያስችላት ‹‹አንቀጸ አሚን›› የተባለ የማስተማሪያ መጽሐፍ አዘጋጅታ፣ ‹‹መጽሐፈ ቄዴር›› የተባለ የማጥመቅያ ሥርዓትም
ሠርታ ተልእኮዋን መልሳ ለማጠናከር ችላለች። ኦርቶዶክሳዊነትን ለማክሰም የተሠራ ሴራ ጭራሹን እንዲጠናከር ዕድል መፍጠሩን ይኽ አንዱ የታሪክ ምስክርነት ነው፡፡
በኋላ በጣልያን ወረራ ጊዜም ካቶሊኮች የእስልምናውን ክንፍ በመደገፍ ሁለቱ ‹‹የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው›› በሚመስል መርሕ ተባብረው ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም ሲሠሩ ነበር፡፡ ለምሳሌ፡- በካቶሊኮቹ ሴራ ‹‹ሁለቱ እሾሆች›› የተባሉ ቅባትና ጸጋ በኢትዮጵያ ምድር በተተከሉ ጊዜ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እነርሱን ለመንቀል ትግል ላይ ስትጠመድ እስልምናው ደግሞ ድምጹን አጥፍቶ ውስጥ ውስጡን ሲስፋፋ እንደነበር ተዘግቧል፡፡ በዚኽ ታሪካዊ ተሞክሮ መሠረት ደግሞ የጋራ ጠላትን እንዴት በትብብር መዋጋት እንደሚቻል ልምድ ተቀስሞበታል፤ ይበልጥ አዘምኖና አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግም የታመነበት ይመስላል፡፡
አሁንም በግላጭ ኦርቶዶክሳውያንን አስገድዶ ለመጠምዘዝ መሞከር የማይታሰብ ነውና ሌላ ስልት አስፈለጋቸው! ይልቁንም፥ ተፈጥሯዊ በኾነ መንገድ (biological strategy) ቤተ ክርስቲያኒቱ ራሷን በራሷ እንድታጠፋ ኹኔታዎችን ማመቻቸት አዲሱ ስልት ተደርጎ የተያዘ ይመስላል፡፡ ይኽ ስልት አንድ እንዲጠቃ የተፈለገው ተቋም ራሱን በራሱ እንዲያጠፋ መርዳት (helping the institution to self-suicide) የማድረጊያ ዘዴ ነው፡፡ ይኽ ተፈጥሯዊ
የመባሉም ምስጢር ችግሩን በሚመስል መፍትሔ የመከላከል ስልትን ስለሚከተል ነው፡፡
ለምሳሌ፡- በሥነ-ሕይወታዊ የጥናት ዘርፍ ትላትሎችን ከግብርና ሰብል ጥቃት ለመከላከል ሲፈለግ ለሰብሉ ጎጂ ያልኾኑ፣ ነገር ግን ትላትሎቹን የሚበሉ ሌሎች እንስሳት የማርባት ዘዴ
ማለት ነው፤ በዚኽ የተፈጥሮ ሚዛን (ecological balance) ይጠበቃል፡፡ ከሌሎች ስልቶች የበለጠም ውጤታማ ነው (ኬሚካልን የመሰሉ መፍትሔዎች ለጎጂ ተባዮች ተረጭተው
ጠቃሚዎቹንና ሰብሎችን ጭምር የሚያደርቁ ‹‹ጅምላ ጨራሽ›› ከመኾናቸውም በላይ ለአየር
ብክለት ስለሚያጋልጡ አይመከሩም)፡፡ ተባዮቹን የሚመስሉ ሌሎች ተጻራሪ ተባዮች ሲኾኑ ግን ተመሳሳይ የአኗኗር ዘይቤ ስላላቸው በቀጥታ ከመገናኘታቸውም በላይ ጎጂዎቹ ተባዮችን አዘናግተው (ዘመድ መስለው) እንዲያጠቁአቸው ዕድል ይሰጣቸዋል፡፡
ይኽንኑ ኹኔታ ወደ ተቋም ስናመጣው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ፊት ለፊት በመንግሥታዊ ሥልጣን ተጠቅመው፣ በሰይፍ አስፈራርተውና በሃይማኖታዊ ጉዳዮች ተከራክረው ማሸነፍ
እንደማይቻል ከታሪክ የተረዱት አካላት አንድነቷን ለመክፈል መጠቀም የጀመሩት አዲሱ ስልት መኾኑ ነው፡፡ ይኽ ስልት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ በቀጥታና በይፋ የሚሰነዝረውን ጥቃት በይፋ ሳያሳውቅ (ለትችት በማያጋልጠው፣ ነገር ግን የተሻለ ውጤታማ በሚያደርገው መልኩ) እንዲያዳክማት የሚያስችላቸው ነው፡፡
ይኽ ተፈጥሯዊ ስትራቴጂ ‹‹ራስን በራስ እንዲያጠፋ የመርዳት›› መርሕን ስለሚከተል ቤተ ክህነቱ እንደተጻራሪ ክንፍ በፈረጃቸው የእስልምናና ሌሎች የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች ከመገዳደር ይልቅ በውስጡ ባሉት ሰዎቹ ተጠቅሞ፣ ስያሜውን በሚመስል ዘዴ፣ የራሱን ተልእኮ
የሚያፋጥንለት የሚመስለውን አሠራር መዘርጋት ይበልጥ ውጤታማ ያደርገዋል፡፡ መዋቅርን በመዋቅር፣ ጳጳስን በጳጳስ፣ ቤተ ክህነትን በቤተ ክህነት፣ ሲኖዶስን በሲኖዶስ፣ ማኅበራትን በማኅበራት፣ አሠራርን በአሠራር ተክቶ ከመጀመሪያው አቅጣጫዋ ወደ ሚፈለገው መሥመር ማስቀየስ፤ በሒደትም ግብዓተ መሬቷን ለመፈጸም እንደማለም ያለ ስልት ነው፡፡
ይኽ ከሰሞንኛ ኹኔታዎች አንጻር ምን ምን ነገሮችን እንድናስተውል ያደርገናል?

(1) ትናንት ‹‹የኦሮሚያ ቤተ ክህነት›› እያሉ ሲያጨናንቁን የነበሩ ‹‹ኦርቶዶክሳውያን›› ወንድሞቻችን ዘግይተው ደግሞ በመስቀል አደባባይ ጉዳይ፥ ‹‹ሙስሊም ወንድሞቻችን
ቢያፈጥሩበት ምን ችግር አለበት?›› እያሉ ሲከራከሩን አስተውለናል፡፡ የገዛ ወገኖቻችን ከተቀናቃኞቻችን ጎን ኾነው ሞገቱን፤ ኦርቶዶክሳውያንን በኦርቶዶክሳውያን መዋጋት ይሏል ይኽ
ነው!

(2) ይኽንኑ ጉዳይ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጠቅላይ ቤተ ክህነቷ አማካይነት ተቃውሞ ስታቀርብ መንግሥት ደግሞ የእርሷኑ ሌላ መዋቅር (የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን) ተጠቅሞ
‹‹ይቅርታ›› አስጠየቀ፤ በመዋቅራችን አማካይነት መዋቅራችንን አጠቃው ማለት ነው!

(3) ለኦርቶዶክሳዊ ቀኖናት ደንታ የሌላቸውና ከመሰል እሴቶች ሊያንሸራትቱን የሚሹ ተሓድሶዎች ‹‹ኦርቶዶክሳውያን›› መስለው፣ ለትግራይ ሕዝብም እንደተቆረቆሩ አስመስለው
በበዓለ ሃምሳ ጾም ዐወጁ፡፡ ይኽንን ሲያደርጉ ግን ‹‹የገዳም አባቶችና የትግራይ ሊቃነ ጳጳሳት አዘዋል›› እያሉ ነው፡፡ ከእኛው ጾምና ትእዛዘ አበው ጋር ታክከው የእኛኑ ቀኖና ለመናድ የሚደረግ ሌላኛው እንቅስቃሴ!

(4) በውስጣችን ኾነው፣ ለሀገርና ለቤተ ክርስቲያንን አሁናዊ ጭንቀት መፍትሔ እንዳገኙ አስመስለው ‹‹ደጉ ንጉሥ ቴዎድሮስ ይገለጣል!›› የሚሉንም በዝተዋል፡፡ ለዚኽ ማሳመኛቸው
ደግሞ ‹‹ፍካረ ኢየሱስ›› እና ‹‹የገዳም አባቶች መልእክት›› የሚሉ የማግባቢያ አካሔዶችን ይጠቀማሉ፡፡ ገዳማውያኑ ግን በአንድነት ኾነው ‹‹መልእክቱ ከእኛ አይደለም!›› ማለታቸውን ልብ ይሏል፡፡

ይቀጥላል...
Forwarded from ሀser
ኦርቶዶክስን በኦርቶዶክሳውያን የማዳከም አዲስ ስልት!

....የቀጠለ

(5) ከዚኽን በፊትም በተለመደው የፖለቲካ ሴራ አካሔድ መሠረት ቅዱስ ፓትርያርኩን ከመንበር አውርደው በሌላ ተረኛ ለመተካት ባለሥልጣናቱ ፊት ለፊት መምጣቱን አልፈለጉትም፡፡ እናም፥ መጀመሪያ ቅዱስነታቸውን እነርሱ ‹‹ጁንታ›› ከሚሉት አካል ጋር ፈርጀው ለማሸማቀቅ፣ በምእመኑ ዘንድ ለማስጠላትና ‹‹በፈቃዳቸው ለቀቁ›› ለማስባል ሞከሩ፡፡ ‹‹እኔም ኦርቶዶክሳዊ
ነኝ›› የሚሉ፣ በተግባር ግን ያልኾኑ ‹‹መምህራን›› እና አክቲቪስቶችን ከጀርባ ‹‹አይዟችሁ!›› እያሉ በጸያፍ አገላለጾች አስሰደቧቸው፤ ከልክ በላይም አፍ አስከፈቱባቸው፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስን
ዋና ጸሐፊ ‹‹አይወክሉንም!›› የሚል መግለጫ አስሰጡ፡፡ ኦርቶዶክሳዊ ኹሉ ግን በሚገርም ኹኔታ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ እንደ አንድ ልብ መካሪ ኾኖ ‹‹ከአባታችን ጎን ነን!›› ብሎ አሳፈራቸው፡፡ ይኽንን የሕዝቡን ሥነ ልቡና ያስተዋሉት ፖለቲከኞቹ ከቅዱስነታቸው ጋር የ ግል ቅራኔ ያላቸውንና የሥልጣን ጥም ያሰከራቸውን ‹‹ጳጳሳት›› በኅቡዕ አደራጅተው መንቀሳቀስ ይዘዋል፡፡ ‹‹ደኅንነቶች ነን›› በሚሉ ሰዎችና ለተረኛው መንግሥት እንቀርባለን በሚሉ ‹‹አባቶች›› አማካይነት ‹‹መንግሥት የሚፈልገው ይኽንን ነው›› ብለው እያስወሩ በአባቶችን ውሳኔ ላይ ከወዲሁ ጫና ለማሳደር እየተሞከረ፣ ቤት ለቤትም ቅስቀሳዎች እየተደረጉ መኾኑ እየተሰማ
ነው፡፡ ገና ቅዱስ ሲኖዶሱ ሳይሰበሰብም፡- ‹‹ቅዱስ ፓትርያርኩ በሌሉበት ምልዓተ ጉባኤ እንደሚካሔድ፣ እንደራሴ እንደሚሾም›› ማስወራት ይዘዋል፡፡ የእኛን አባቶች እየተዋጓቸው ያሉት በእኛው አባቶች ነው የሚያስብለውም ይኸው ነው!

(6) ሕገ ቤተ ክርስቲያንን በማርቀቅና በማጽደቅ ሒደት ውስጥም የግለሰቦች ፍላጎትና የውጭ አካላት እጅ እየገባ እንደኾነ ተሰምቷል፡፡ ገና ሕጉ በቅዱስ ሲኖዶስ ታይቶ ሳይጸድቅ ‹‹የማስፈጸሚያ ሰነድ›› የሚል ረቂቅ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ውስጥ ባሉት የወቅቱ ፈላጭ
ቆራጮች አማካይነት ሌላ አጀንዳ ማስቀየርያ መዘጋጀቱም ታውቋል፡፡ ስሙን ‹‹ሕገ ቤተ ክርስቲያን›› እያሰኙት የቤተ ክርስቲያንን ጥቅም ለግለሰቦች ፍላጎት አሳልፎ የሚሰጠውን አካሔድ ግን ‹‹ሕጋዊ›› ለማስመሰል የሚሔዱበት ርቀት ያስተዛዝባል! ሌላው ቀርቶ ‹‹እኛ
መነኮሳት ነን፤ ንብረታችን ኹሉ የቤተ ክርስቲያን እንጂ የእኛ መኾን የለበትም›› የሚል ሐሳብ የሰጡ ሊቃነ ጳጳሳትን እንኳን ምን ያኽል ሲያገልሏቸው እንደነበር የምናስታውሰው ነው!

(7) የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶሳዊ አንድነትና መዋቅራዊ ጥንካሬ ለጎሣ ፖለቲካቸው የመከፋፈል ሴራ አልመች ሲል የ16ኛውን መቶ ክፍለ ዘመን እሾኽ (‹‹ቅብዓት›› የሚባል ኑፋቄ)
በ21ኛው ክፍለ ዘመን መልሰው ለመትከል ምሥራቅ ጎጃምን የሚያስጨንቋትም አሉ፡፡
በየትኛውም የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሥርዓት ‹‹ጳጳሳት›› እንደተሾሙ ተነገረ፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስን ምልዓተ ጉባኤ ትኩረት ለመሳብና አጀንዳውንም ለማስቀየርም ሲሉ ‹‹የጳጳሳቱ በዓለ ሢመት ተዘጋጅቷል›› ብለው የጥሪ ካርድ በተኑ፡፡ ይኽ ኹሉ ሲኾንና ከመደበኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ተደጋጋሚ አቤቱታ ለመንግሥት መዋቅሮች ሲቀርብ ግን ጆሮ ዳባ ልበስ ብለዋል፤ በአጥፊው ፋንታም ሰላማውያኑ ታስረዋል፡፡ ‹‹ተለያይቶ
የነበረውን ሲኖዶስ አንድ አደረግሁ›› ብለው የሚመጻደቁት አካላት ‹‹ሌላ ሲኖዶስ›› ለመፍጠር ለምን እንደሚሯሯጡ ግን ግልጽ አይደለም!
ኦርቶዶክስን በራሳቸው በኦርቶዶክሳውያን አማካይነት የማዳከም ስልት፤ አዲሱ የአጽራረ ቤተ ክርስቲያን ሴራ!

👉ከ ‹‹ግንጊልቻ›› መጽሐፍ፣ ምዕ.4፥ ገጽ.89-92 ላይ ባለው ሐሳብ መነሻነት የተጠናቀረ
ንቂ ኢትዮጵያ pinned «ኦርቶዶክስን በኦርቶዶክሳውያን የማዳከም አዲስ ስልት! ባለፉት የታሪክ ገጽታዎቻችን ውስጥ በጉልበትና በይፋዊ ተቃርኖ ኦርቶዶክስን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት ሲደረጉ የነበሩ እንቅስቃሴዎች ኹሉ አልተሳኩም፤ እንዲያውም የበለጠ ሲያጠናክሯትና ሲያስፋፏት ተስተዋሉ እንጂ፡፡ ለምሳሌ፡- በግራኝ አህመድ ወረራ ዘመን ኦርቶዶክሳውያኑን በግዳጅ የማስለም ድርጊቶች ተፈጽመው ነበር፤ ሕዝቡም ወደ እስልምና ሲገባ አምኖበት ሳይኾን…»
Forwarded from ኖህ ኢትዮጵያ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ ዋና ስር መሠረታዊ ችግር - አንቀጽ 39

ምዕራባውያኑ ስለ አንቀጽ 39 በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2014 ዓ.ም የሰጡት የሴራቸውን ማብራሪያ አድምጡት። ሀገሪቱን በብሔር ብሔረሰብ መብት ማስከበር ስም በህገመንግስቱ እንዲካተት የተደረገው በማር የተለወሰ መርዝ አንቀፅ አደገኝነት በሰፊው ተብራርቶበታልና አድምጡት ሼርም ተደረጋጉት። አዲሱ ትውልድ ሊነቃና ካለፈው ታሪኩ ሊማር ይገባዋልና።
Forwarded from ኖህ ኢትዮጵያ
ስለ NIKE ጫማ ማወቅ ያለብን

Nike በአለማችን ተወዳጅ የሆነው Brand ጫማ ስያሜውን ያገኘው ከጥንት የግሪክ አማልክት የ Pallas(Titan) እና የStyx ልጅ ከሆነችው Nike ነው ፡፡Styx መሬትንና የሲዖልን መግቢያ የሚከፍል ወንዝ ነው ብለው ግሪኮች ያምኑ ነበር፡፡
Nike የጥንታዊ ግሪኮች ጣዖት የነበረች ሲሆን የፍጥነት የጥንካሬና የድል አምላክ ብለው ያመልኳት ነበር፡፡መመለኳም አሁን ድረስ ቀጥሏል፡፡

Nike በ Zeus(የጥንት ግሪክ ዋና አምላክ) የፍጥነት የጥንካሬና የድል አምላክ ለዘላለም እንደሆነች ቃል ስለተገባላት አምላክነቷ አሁንም ድረስ ቀጥሎ በእሷ ስም የተሰየሙት ምርቶች የሚከተሉት ናቸው፡
1.Honda motor cycles የ Nike'ን ምልክት እንደ አርማ/logo ይጠቀማል፡፡
2.በአሜሪካ anti aircraft missile system የ nike'ን ምልክት ይጠቀማል፡፡
3.በዋነኛነት የ nike ጫማ አምራች የ nike'ን ምልክት ይጠቀማል፡፡

ስለዚህ አብዛኞቻችን የምንጠቀመው Nike ጫማ ሰይጣንን የሚወክል ስለሆነ ልንጠነቀቅ ይገባል፡፡በዙ ሰወች "ካላመለኩት ምን ችግር አለው" ይሉ ይሆናል ነገር ግን እኛ የእግዚአብሔር ተከታዮች እንጂ የሰይጣን አደለንም፡፡ ሰይጣን አምላኪዎቹ ኢሉሚናቲዎች ብዙ በጀት መድበው ይህንን ሁሉ የሚከውኑት የሚያመልኩትን ሰይጣን ከፍ ከፍ ለማረግና የዓለም ህዝብን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሱ አቀንቃኝ ለማረግ ነው።

አሁን አሁን ላይ ለእኛ ለክርስቲያኖች ጊዜው ከባድና በፈተናዎች የተሞላ ነው::እያንዳንዷን እርምጃችን ቆም ብለን ማሰብ ይገባናል፡፡ምክንያቱም እኛ ግሎባላይዜሽን በሚባል በዘመናዊ ባርነት የታጠርን ሰወች አብዛኛው እንቅስቃሴያችን በእኛ ሳይሆን የሰይጣን ጭፍራ በሆኑ ሀገሮች የተወሰነ ስለሆነ ነው፡፡የሚሰጡንን ቀጥታ እንቀበላለን ለምን ብለን አንጠይቅም። የእነሱን እንቀበላለን የእኛን እንንቃለን የእነሱ የሆነው ሁሉ ይጥመናል፡፡ ነገር ግን ምን ያህል ስለምንከተላቸው ሰወች ፣ ስለ አለባበሳቸው ፣ ስለምንመገበው ምግብ ፣ ስለምንጠቀመው ቴክኖሎጂ እናውቃለን?

አሁንም ለመንቃትና ለማስተዋል ጊዜው አረፈደም!

#ፀረ_ኢሉሚናቲዝም
Forwarded from ኖህ ኢትዮጵያ
ቅዱስ ጊዮርጊስ - ቢራ ወይስ ሰማዕት?

የቅዱሳን ስዕል አድህኖ በክብር መቀመጥ ሲገባው የቅዱስ ገዮርጊስ ስዕል ግን

1/ በየጠርሙሱ ተለጥፎ የሰካራም እጅ ያለ ንጽህና በድፍረት ይጨብጠዋል።

2/ ስዕል አድህኖው በየመጠጥ ቤቱ እየወደቀ ይረገጣል። ከቆሻሻ ጋር ተጠርጎ ይጣላል።

3/ በስሙ ታቦት መቀረጽ ሲገባው የሚያሰክር መጠጥ ሆኖ ስሙን ለማርከስ ተሰርቷል

4/ ኢትዮጵያ ከሰማዕቱ የምታገኘውን ክብርና ጥበቃ ለማሳጣት በ1915 ዓ.ም ጣሊያኖች አቅድው አቋቋሙት።

የሚገርመው መጠጡን የሚጠጣው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተከታዩ ነው።
አንዳዴ እንደቀላል የምናያቸው ነገሮች ከፍተኛ የሆነ ጥፋቶች ናቸውና እንንቃ።

ይህን ጽሁፍ ያነበበ ለነፍሱ ይወስን!
Forwarded from ኖህ ኢትዮጵያ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አደገኛው የ 5ጂ ቴክኖሎጂ በኢትዮጵያ::
ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ስራ የጀመረው የ5ጂ ኢንተርኔት ቴክኖሎጂ እጅግ አደገኛ የሆነ አላማ በዚህች አጭር ቪዲዬ ገለፃ ተደርጎበታልና ተከታተሉት።
#የግዮን_ምንጭ
Forwarded from ኖህ ኢትዮጵያ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ዘመን አመጣሾቹ ቢትኮይን (beast coin) እና ክሪፕቶ ከረንሲ ምን ማለት ነው? እንዴትስ ይሰራል?

ኢሉሚናቲዎች ለመጨረሻው የዲጂታላይዜሽን ጥቅለላ ይህን መገበያያ እንዴት ሊጠቀሙበት አስበው እንዳመጡት የሚያብራራ ቪዲዬ ነውና አድምጡት።

ስለ አውሬው የወደፊት ገንዘብ በቂ ግንዛቤ ይያዙ!

#የግዮን_ምንጭ
Forwarded from ኖህ ኢትዮጵያ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያን የቴሌኮም ዘርፍ የተረከበው ሳፋሪ ኮም እና ቀጣይ ዕቅዱ

- ዲጂታላይዜሽንን በኢትዮጵያ ለማስፋፋትና ሀገሪቱን በሰይጣን ቁጥጥር ስር ለማንበርከክ በቅርቡ ስራውን የሚጀምረው ሳፍሪኮም የመጨረሻ እቅዱ በዩሃንስ ራዕይ የተጠቀሰውን ትንቢት ማስፈፀም ነው።

የዩሃንስ ራዕይ 13:-16-18

"ታናናሾችና ታላላቆችም ባለጠጎችና ድሆችም ጌታዎችና ባሪያዎችም ሁሉ በቀኝ እጃቸው ወይም በግምባራቸው ምልክትን እንዲቀበሉ ፥ የአውሬውም ስም ወይም የስሙ ቁጥር ያለው ምልክት የሌለበት ማንም ሊገዛ ወይም ሊሸጥ እንዳይችል ይደረጋል። ጥበብ በዚህ አለ። አዕምሮ ያለው የአውሬውን ቁጥር ይቁጠረው ፤ ቁጥሩም የሰው ቁጥር ነውና ፥ ቁጥሩም 666 ነው። "
Forwarded from ኖህ ኢትዮጵያ
ከዚህ በፊት የቅዱስ ጊዎርጊስ ቢራ መወገዝ እንደሚገባ ፅፈንላቹ ነበር። አሁን ደሞ ቅዱስ ዮሃንስ ቢራን ይዘው መጥተዋል። በአሜሪካ አንድ የሀበሻ ሬስቶራንት ውስጥ ለገበያ የቀረበው ይህ ቢራ በቀጥታ የቅዱስ ዮሃንስን በረከት ከሀገራችን ሊያሳጣ የሚችልና ለመቅሰፍትም የሚያደርስ ነው።

የሰማዕታት ስዕል በኦርቶዶክስ ሀይማኖት ትልቅ ትልቅ ስፍራ ያለው ነገር ነው። እንኳን ቢራ ላይ ሊታተምና በየመንገዱ ሊጣል ቀርቶ ትንሽ የቆሸሸ ስፍራም አይቀመጥም። እጅግ ከባድ የሆኑ ነገሮችን እያቀለልን በማለፋችን ነው አሁን ለደረስንበት ውድቀት የደረሰነው። ውድቀታችንን ብቻ ከማየት ባለፈ የውድቀታችንን ምንጮች ፈልገን ማድረቅ ስንችል ነው ከችግሮቻችን ወጥተን ወደ ቀደምት ልዕልናችን የምንመለሰው።

ለሀገራችን ችግሮቻችን አንዱ ምንጭ የኢትዮጵያን ባለውለታ የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዎርጊስን ስዕለ አድኖ በዚህ ደረጃ አርክሰን ከቆሻሻ ጋር መጣላችን ነው። ያለፈው ትውልድ የሰራውን ስህተቶች አዲሱ ትውልድ በንቃት እያረመ ካልሄደ በስተቀር መቀመቅ ነው ተያይዘን የምኖርደው።

👉ይህን ጽሁፍ ያነበበ ለነፍሱ ይወስን!

ቢያንስ እኛ ቢራውን ባለመጠቀምና ሌሎችን በማንቃት ግዴታችንን እንወጣ!
Forwarded from ኖህ ኢትዮጵያ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሔዋን ገ\ወልድ በኢሉሚናቲ ተጠልፋለች!! | ሔዋን እና ግብረ-ሰዶማውያኑ ሙዚቀኞች | ጋዜጠኛ አብይ ይልማ ያጋለጠው ምስጢር | Haleta tv
Forwarded from ኖህ ኢትዮጵያ
ኖህ ኢትዮጵያ
ሔዋን ገ\ወልድ በኢሉሚናቲ ተጠልፋለች!! | ሔዋን እና ግብረ-ሰዶማውያኑ ሙዚቀኞች | ጋዜጠኛ አብይ ይልማ ያጋለጠው ምስጢር | Haleta tv
የኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንደስትሪ በኢሉሚናቲ ቁጥጥር ስር እየወደቀ ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት በዓለም ላይ እየተስፋፋ የሄደው በሙዚቃ ሰይጣንን የማስመለክ ስልት በሀገራችንም ተግባራዊ ለማረግ ከፍተኛ በጀት በሚስጥር ማህበራቱ ተመድቦለት ከፍተኛ ስራዎች እየተሰራ ይገኛል።

በኢትዮጵያ ዛሬ ላይ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ነፍሳቸውን ለሰይጣን የሸጡና የሰይጣን አገልጋይና ዘማሪ ሆነው ትውልዱን እያሳቱ የሚገኙ የሙዚቃ ሰዎች ብቅ ብቅ እያሉ ይገኛሉ። እነዚህን ሙዚቃዎች ደጋግመን ባየንና በሰማን ቁጥር ነብሳችንን እያስኮነናትና ለአጋንንቱ አለም ተገዢ እየሆንን ነው ምንሄደው።

ከላይ ባለው ቪዲዮ ላይ የጃኖ ባንድ አባል የነበረችው ሔዋን ገ/ወልድ አዲስ የሙዚቃ ስራ እንዴት ከአጋንንቱ አለም ጋር የተሳሰረ ስለመሆኑ #በአብይ_ይልማ ተተንትኖ ቀርቦበታልና በጥሞና እዩት ለሌሎችም ሼር በማረግ ወጣቱን ትውልድ ከጥፋት ለመታደግ የቡኩላችንን እናበርክት።
Forwarded from ኖህ ኢትዮጵያ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
👉ድምፃዊ አቤልና ኢሉሚናቲ

አለምአቀፍ የሙዚቃ ኢንደስትሪ ላይ ስሙ በገናናነት የሚነሳው ኢትዮጵያዊው ድምፃዊ አቤል ወይም በመድረክ ስሙ The Weeknd (xo) ነፍሱን ለአጋንንቱ አለም የሸጠ ስለመሆኑና በርካታ ተከታዬቹን እያሳተ ስለመሆኑ በማስረጃ የተደገፈ ትንተና የተሰጠበትን ይህን አጭር ቪዲዬ በበመልከት ራሳችንና ልጆቻችንን በዘፈን ስም እየተሰራጩ ካሉት ከሰይጣን አምልኮ መዝሙሮች እንጠብቅ።

በዚህ ጊዜ ካልነቃን አሰፍስፎ በሚጠብቀን አውሬ እራሳችንንም ሆነ ልጆቻችንን ነው ምናስበላውና #እንንቃ
ፈጣሪ ሀገራችንን ከክፉ ይመልስልን!

#day_7_tube
~ሙሉ ወንጌል Vs የብልፅግና ወንጌል...?!

✍️እንሆ የነማርቲን ሉተርና የነ ጆን ካልቪን የፕሮቴስ ሙሉወንጌል ቅሌት በ20ኛው ክፍለዘመን በግሎባሊስቶቹ እጅ አዙር አማካኝነት እግዚሀቤር ድሀ ይጠየፋል(ድህነት ሀጢያትና ርግማን ነው) ከሚል እሳቤ ተነስተው ክርስትናን የማደባለቅና የማጥፋት አብዮት(illumination) መሠረት አድርገው የብልፅግና ወንጌልን (prosperity gospel) መሠረቱ።ይሄም አደገኛ አስተሳሰብ ፍሬ አፍርቶ አውሮፓና አሜሪካ ያለውን አብዛኛውን ሙሉ ወንጌል አማኝ በገንዘብ እየደለለ ከሙሉወንጌል የነ ሉተር ጵንጠጣ አላቆ አዳዲስ ቸርቾች እንዲመሠረቱ መሠረት ጣለ።

...ብሉይ ኪዳን አያስፈልግም አሉ!...ሀዲስ ኪዳን ካህናት ቸርችን መሠረቱ...ግብረሰዶም ተፈቅዷል ፈጣሪ አልከለከለም ፍቅር ፆታ የለውም አሉ...በየቸርቹ አፀደቁት....ወንድና ወንድ ሴትና ሴት በነፃነት በፓስተር እየተባረኩ ተጋቡ.....ቀስ በቀስ ግሎባሊስቶቹ ፈጣሪ ምን ያረጋል አሉና...እንዳውም ከ8 አመት ጀምሮ ያለ ልጅ ፆታውን መምረጥ መብቱ ነው....ፆታን በፈቃደኝነት ትቀበለዋለህ እንጂ ተገደህ አትጋተውም አሉና(sexual orientation እሚሏት ፈሊጥ መሆኗ ነው)....

...ከነ ሉተር ወንጌል ወደ ብልፅግና ወንጌል የተቀየሩትን የፔንጤ ቸርቾች ቀስ በቀስ ፆታ መለየት እንዲሳናቸው አደረጉ።ምን ቸገራቸው ብላችሁ ነው...እድሜ ለሂላሪ ክሊንተን በሱፕሬም ኮርት በኩል እንዲፀድቅ ስላደረገችው...የግብረሰዶም መብት ከጤነኛ ባለትዳር መብት የተሻለ ዋስትና እንዲኖረው ተደረገ።ነገሩ እየባሰ ሄደ የአማኙም ድንቁርና ተስፋፋና አዲሱ ትውልድ እንዳውም ፈጣሪ አያስፈልግም ተብሎ...ምንም ያለማመን ፓጋኒዝም አብዮት ደቆሳቸው....ምናባቱ ብለው ግብረሰዶም ያጋባ የነበረው ቸርችም ለአንድያው ተጠረቀመ.....ባርና ጭፈራ ቤት ዳንስ ቤት አደረጉት።.....የግሎባሊስቶቹ ቀልሀ ሉሲፈርን ለማስመለመክ ቀድመው የጠነሰሱት ጥይት ነበርና እሱን ቃታ እየሳቡ ሲተኩሱት የሉሲፈር ቸርች ተስፋፍቶ...ቅድመ አያቱ የሉተር ተከታይ....አያቱ የብልፅግና ወንጌል ተከታይ....አባቱ ሀይማኖት ለምኔ ያለ ሜዲቴተር የሆነበት የነጭ ትውልድ ሁሉ ይሄን ሰይጣን ያመልከው ጀመር።ተፈጠመ....!!

✍️ወዴት ወዴት?! ምኑ አለቀና....የሉተር ቸርች መሀበራት በሙሉ ግብረሰዶምን ሲቀበሉ....አብይ አህመድ ከመምጣቱ በፊት እኛ ሀገር ኢትዮጵያ የነበረችው የጥንቷ የሉተር ተከታይ የሙሉ ወንጌል አማኞች አንድ ቀጭን ደብዳቤ ተላከላቸው።"...የተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪ(ሰዶሜውያንን) በበጎ ተቀብለናቸዋል።መብታቸውን ልንጠብቅ ይገባል....በኛ ማህበር ውስጥ መቀጠል ከፈለጋችሁ ይሄንም በሀገራችሁ ተቀበሉ...." እሚል ትዕዛዝ ደረሳቸው።ነገሩ ወዲህ ነው....በወቅቱ ዲሞክራቱና የግሎባሊስቶች ተላላኪ ባራክ ኦባማ ስልጣን ላይ ወጥቶ ስለነበር...ዲሞክራቶቹ እነ ሂላሪ ክሊንተን መፈነጫ ሜዳው አልበቃ ብሎአቸው ስለነበር...."...ግብረሰዶም ከሌለ ዶላር የለም...." እሚለው የኦባማ ፖሊሲ ለወያኔ መንግስት ተልኮ ነበር።...

...የጤና ሚኒስትሩ ቴድሮስ አድሀኖም የውርጃና ህጉንና የሰዶማውያንን መብት በተመለከተ በውስጥ መስመር ጭጭ ምጭጭ ብሎ ነበር ያለፈው።ከተሳፈጠ ዶላር ከየት ይመጣል?!....መንግስት ቢያጎበድድም ከፔንጤው አለም ጤነኛ ሁና የተረፈችው የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቸርች ለካናዳው ቸርች ደብዳቤ ፃፈች።"....ይሄን በፍፁም አንቀበለውም...ራሳችንን ከሉተር ቸርች መሀበር አግለናል..." ብላ ግብረሰዶም አፀያፊ መሆኑን መሠከረች።

✍️ታዲያ ፓስተር ዮናታን ማነው?....በደርግ ዘመን በCIA በኩል ለፖለቲካ አጀንዳ(ግሎባሊስቶች ግን በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ መምታታቸው ነው) ሾልኮ የገባው የብልፅግና ወንጌል ትርምስ ብዙም ለውጥ አላመጣ ብሎ...የኢትዮጵያ አምላክ ጠብቆን በቤተክርስትያን ሰዶማውያንን ማጋባት እማይታሰብ ሆነባቸውና መለስ ዜናውም ንኩት ብሎ አለፋቸው።ግን እድሜ ለአብይ አህመድ....የብልፅግና ወንጌል ከነ አርማው ከነማኒፌስቶው ጀምሮ ከኢንሳ ጀምሮ ሲላላካቸው ለነበረው አብይ አህመድ በዶናልድ ትራምፕ በኩል ተሰፍቶ ተሰጠው።አብይ አህመድን የት እናውቀዋለን? ፓስተር ዮናታንን የት አባታችን እናውቀዋለን?!... እንዲህ እንደ ስኳር ድንች ከመሬት ቡልቅ ያሉ ይመስልሀል?......

✍️የውልህ የብልፅግና ፓርቲ ከነረቂቁ ጀምሮ የአብይ አህመድ ምርት ነው።".... ፕሮቴስታንት ሀብት ማፍራትን ስለሚደገፍ በፓርቲው እሚበረታታ ሀይማኖት መሆኑን በግልፅ አስቀምጠውታል።አርማውስ ብትል የብልፅግና ወንጌል ጋር በምን ይለያል?.....ፓስተር ዮናታን ሁለተኛው ፌዝ ላይ የገባ ሰው ነው።ሁለተኛው ፌዝ የአዲስ ኪዳን ካህናት ቸርች የተባለው የሱ እምነት ነው።ይሄ እምነት ለቀጣዩ ኢትዮጵያ ውስጥ ለታሰበው ግብረሰዶምን ህጋዊ እናርግ ትርምስ የተጣለ እርሾ ነው።ፓስተር ዮናታን ብቻ አደለም ሌሎችም መጤ አዳዲስ የፔንጤ ቸርቾች አሉ....ፈፅሞ ከሉተር የሙሉ ወንጌል እምነት የተለዩ ናቸው።

✍️የመልካም ወጣት ፕሮጀክት አላማው የኦርቶዶክሱን ሱሰኛ ትውልድ በእምነቱ ተስፋ አስቆርጦ መዝረፍ ነው።"...ወደ ቸርቻችን ለሚመጣ 50 ሺህ ብር...ለባለትዳር 100000 ብር...ድጎማ እናረጋለን..." ያለውን የፓስተር ዮናታን ንግግር ረስትህ ከሆነ ሞተሀል።ወዳጄ ለገባው ሁሉ ይሄን ሁሉ ገንዘብ ከየት አምጦ ይመስልሀል?....የኦርቶዶክሱ ትውልድ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እሚሰራ ለምን አላማ ይመስልሀል?!....ከስራኤል መንግሰሰት ጀምሮ እሚደረግለት ሚስጥራዊ ድጋፍ ከየት የመጣ ነው?...የአብይ አህመድ እምነት ሙሉ ወንጌል ነው ወይስ የብልፅግና ወንጌል?! አብይ ፕሮደክቱን በገንዘብ ጭምር የደገፈው ከምን ተነስቶ ነው?...

...መነሻውም መዳረሻውም ግብረሰዶምን ህጋዊ ከለላ ሰጥቶ ወደ ፌዝ 3 ሉሲፈርን የማስመለክ ሂደት ውስጥ መግባት ነው።እነ ፓስተር ዮናታን የሂደቱ አካል ናቸው።አብይ አህመድ አፍ አውጥቶ አይናገርም እንጂ ግብረሰዶምን እንደመብትና በመርህ ደረጃ ተቀበሎታል።ግዜው ሲደርስ ይታወቃል።ወደዱትም ጠሉትም አስገዳጅ ዶላርና አይዶሎጂ እስካለ ድረስ የነሱ ተላላኪ ናቸው።እኛንም አንገት ማስደፋት ፈልገው ከሆነ....በዛሬው ቀን የተወለዱት ነጩን አንገት ያስደፉት የአባባ ጃንሆይ(የራስ ተፈሪ) ልጆች ነን።

✍️እንደ ጣት ቁጥር እየተዋጡ የመጡት ሀይማኖታቸውን የጠበቁትን የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞችን ግን አመስግኑልኝ።በፓፓ ፍራንሲስ ስም ካልማልኩ ያልሽውን የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቸርች ግን አልፋታሽም! ከማን እርዳታ እንደምትቀበሉ ጠንቅቄ አውቃለሁ....ዋ! አከተመ!!

"....የተዋህዶ ሰባኪዎች ግን ትውልዳችን ሲበላ ያለስራችሁ ፖለቲካ ስትፈተፍቱ እምትውሉ ምን አስባችሁ ነው?!....ኧረ ተው የክርስቶስ አደራ አለባችሁ?!.." ፀሀፊው


@እይታዬ
Mark Abyssinia
ሀምሌ 17/2014 ዓ/ም
ብልፅግና ወንጌል(prosperity gospel) እስልምናና ክርስትናን ብቻ አደለም የሙሉ ወንጌል አማኞችንም እንደ እድገት ፀር የደነገገ ፍልስፍና ነው።ማብራሪያው የአብይ አህመድ መደመር መፅሀፍ ላይ አለላችሁ!!

mark
Welcome
እርዳታችሁን እፈልጋለሁ

ከዚህ በፊት ስለ ሀገራችው ሚቆረቁራቹ ምንለው አለን የምትሉ ወይም በነፃ ወጣቱን ማማከር ችግሩን መስማት እንዲሁም በሱስ እየተሰቃዩ ያሉ ወገኖቻችንን መርዳት ምትፈልጉ @yooman16 አካውንት አናግሩኝ