ቃለ ጽድቅ ዘመካነ ሕይወት | የመ/ሕ/ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ንዑስ ክፍል
1.01K subscribers
2.66K photos
44 videos
102 files
752 links
ይኽ የፈረንሳይ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን መካነ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ቻናል ነው። በዚኽ ቻናል በመንፈሳዊ ሕይወትዎ የሚበረቱባቸውን መንፈሳዊ ጽሑፎችና መልእክቶች ባሉበት ሆነው መከታተል ይችላሉ።
Download Telegram
ሰኞ ማዕዶት
ማዕዶት ማለት (ዐደወ-ተሻገረ) ከሚል የግእዝ ግስ የተወረሰ ሲሆን በጥሬው "መሻገር" ማለት ነው:: ይሕም በደመ ክርስቶስ ተቀድሰን: በትንሳኤውም ድኅነት ተደርጐልን መከራን: መርገምን: የኃጢአትን ባሕር: አንድም ባሕረ እሳትን መሻገራችንን ያመለክታል::
+ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ ደሙ
*ከባርነት ወደ ነጻነት
*ከጨለማ ወደ ብርሃን
*ከሞት ወደ ሕይወት
*ከኃጢአት ወደ ጽድቅ
*ከሲዖል ወደ ገነት
*ከገሐነመ እሳት ወደ መንግስተ ሰማያት
አዳምንና እኛን ልጆቹን አሸጋግሮናል::
+አባታችን አዳምና ልጆቹ ከሲዖል የወጡት በዕለተ ዐርብ በሠርክ ቢሆንም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚሕ ዕለት እዲታሰብ ታዛለች::
+ጌታችን ምርኮን ማርኮ: ጥጦስ መንገድ ጠራጊ ሆኖለት ወደ ገነት ሲያስገባቸው ለድንግል ማርያም አሳይቷታል:: እመ አምላክም በፍጹም ልቧ ደስ ተሰኝታለች:: አዳምና ልጆቹ እመቤታችንን ከላይ ሆነው እጅ ነስተዋታል:: እርሷ የድኅነታቸው ምክንያት ናትና::
=>አማናዊው ብርሃን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ጨለማችንን በምሕረቱ ያብራልን::
=>+"+ ክርስቶስም እኮ ስለ ሰው ኃጢአት አንድ ጊዜ ሞቶአል:: ኃጢአት የሌለበት ክርስቶስ ጻድቁ ስለ እኛ ሞተ:: ስለ ኃጢአታችን እኛን ወደ እግዚአብሔር ያቀርበን ዘንድ::
በሥጋ ሞተ: በመንፈስ ግን ሕያው ነው:: ነፍሳቸው ታስራ ወደ ነበረችበት ሔደ:: ቀድሞ ክደውት ለነበሩት ነጻነትን ሰበከላቸው:: +"+ (1ጴጥ. 3:18)
Forwarded from 𝚜𝚊𝚖𝚛𝚒-19
ማክሰኞ ቶማስ

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ትንሣኤው ሐዋርያት ተሰብስበው በነበረበት በዝግ ቤት ገብቶ ሲገለጽላቸው ሐዋርያው ቶማስ ከእነርሱ ጋር አልነበረም፡፡ ሐዋርያትም የጌታችንን ከሙታን ተለይቶ መነሣት ቢነግሩት ‹‹እኔ ሳላይ አላምንም›› አላቸው፡፡ በሚቀጥለው ሳምንትም ጌታችን ቶማስ በተገኘበት በድጋሜ  ተገለጠላቸው፡፡ ጌታችንም ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስን ‹‹ጣትህን ወደዚህ አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን›› ብሎ በጦር የተወጋ ጎኑን ፥ በችንካር  የተቸነከረ እጁንና እግሩን እንዲዳስሰው በማድረግ ትንሣኤውን  አረጋገጠለት፡፡ ቶማስም ሲዳስሰው እጅ ከእሳት እንደገባ ጅማት ስለተኮማተረ ‹‹ጌታዬ አምላኬም›› ብሎ መሰከረ፡፡  በኋላ ግን ፈውሶታል፤ ኢየሱስም ‹‹ስለ አየኸኝ አምነሀል ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዐን ናቸው›› አለው፡፡  ምንም አንኳን ድርጊቱ የተፈጸመው በዳግም ትንሣኤ ቢሆንም የሐዋርያው መታሰቢያ ሆኖ ዕለተ ማክሰኞ ‹ቶማስ› ተብሎ ተሰይሟል፡፡ (ዮሐ. ፳ ፥ ፳፬ -፴)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#ክፉ_አሳብ

ልጆቼ! ከመጀመሪያውኑ ክፉ አሳብ ባታስቡ መልካም ነው፡፡ ካሰባችሁ ግን ቢያንስ አትናገሩት፡፡ በዚያው በሕሊናችሁ ውስጥ እያለ ዝም አሰኙት፤ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላም ወዳለመኖር ይኼዳል፡፡

እኛ ሰዎች ነን፡፡ በመኾኑም ብዙውን ጊዜ ክፉ፣ ያልተገቡና ጸያፍ ነገሮችን እናስባለን፡፡ ነገር ግን ቢያንስ እነዚህን አሳቦች አንናገራቸው፤ ቢያንስ ወደ ቃል አንለውጣቸው፡፡ ወደ ውጭ እንዳይወጡ አምቀን እንያዛቸው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ እየከሰሙና እየደከሙ እየጠፉም ይኼዳሉ፡፡ አንድን እንስሳ ወደ ጉድጓድ ብትጥሉትና ጉድጓዱንም በመክደኛ ብትከድኑት ያ ወደ ጕድጓድ የጣላችሁት እንስሳ የሚተነፍሰውን አየር አጥቶ ይሞታል፡፡ ምናልባት ጥቂት ቀዳዳ ካገኘ ግን በዚያች ቀዳዳ በምትገባው አየር በሕይወት መቆየት ይችላል፡፡ ሲጨንቀውም እናንተን ክፉኛ ለመጉዳት ይዝታል፤ ከወጣም በኋላ ይጎዳችኋል፡፡ ልክ እንደዚሁ እናንተም በልቡናችሁ የተመላለሰውን ኩላሊታችሁ ያጤሰውን ክፉ አሳብ መውጫ ቀዳዳ እንዳይኖረው አድርጋችሁ ብትከድኑት (ብታፍኑት) ይሞታል፤ ከመኖር ወዳለመኖር ይለወጣል፡፡ በአንደበታችሁ በመናገር ጥቂት ቀዳዳ ከከፈታችሁለትና እንደ እንስሳው እንዲተነፍስ ከፈቀዳችሁለት ግን ክፉው አሳብ ክፉ ግብርን ይወልዳል፡፡ ያቆጠቁጣል፡፡ በአሳብ ሳለ ከጎዳችሁ በላይም በገቢር ተወልዶና ተለውጦ ክፉኛ ይጎዳችኋል፡፡

(#የክርስቲያኖች_መከራ #በቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ ገጽ 7➛በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
#እንኳን_ለእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_የልደት_በዓል_በሰላም_አደረሳችኹ
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
''ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ:
ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ:: ''

" ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን:
ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን (ወለደች-አስገኘችልን) "
እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

+*" 🌷ልደታ ለማርያም ድንግል🌷 "*+

ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ:
ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ::
" ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን:
ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን (ወለደች-አስገኘችልን) "

=>የዓለማችን ወላጆች ነቢያት ሐዋርያትን: ጻድቃን ሰማዕታትን ወልደው ከብረዋል: ተመስግነዋል:: ኢያቄምና ሐና ግን ፍጥረት ሁሉ በአንድነት ቢሰበሰብ በእግሯ የረገጠችውን ትቢያ እንኩዋ መሆን የማይችል: የሰማይና የምድር ንግሥት: የእግዚአብሔርን እናት: እመቤታችን ማርያምን ወለዱልን::

+ኢያቄም ወሐና ለእግዚአብሔር የሥጋዌ አያቶቹም ተባሉ:: እስኪያረጁ ድረስ በመካንነት አዝነው ፀልየዋል:: ንጽሕናቸውና ደግነታቸው ተመስክሮላቸው ድንግል ማርያምን አግኝተዋል::

+እመቤታችን ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተወለደች የመጀመሪያዋ ሰው ድንግል ማርያም ሆናለች:: (ኢሳ. 1:9)

+ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ቀን: በሊባኖስ ተራራ ከ2,022 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::

"ሙሽራዬ ሆይ! ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ" (መኃልይ. 4:8)

=>ከነገደ ይሁዳ የሚወለድ ቅዱስ ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ ሌዊ (አሮን) የተወለደች ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች ልጅ የላችሁም በሚል ይናቁ ነበር::

+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ::
እነሱ ግን የሚያመልኩት የአብርሃምና ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::

+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች ቅድስት ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: "እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን ሳይቀር በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::

+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- ነጭ ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::

+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::

+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::

+እንደ ሥርዓቱም አብረው አድረው እመ ብርሃን ተጸነሰች::
"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ . . .
ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: (ቅዳሴ ማርያም)

+"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ . . ."
"ድንግል ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው . . ." (መጽሐፈ ሰዓታት, ኢሳ. 1:9)

+እመቤታችን ነሐሴ 7 ቀን ተጸንሳ ግንቦት አንድ ቀን ተወልዳለች::

=>የእመቤታችን የዘር ሐረግ:-
*አዳም-ኖኅ-አብርሃም-ይስሐቅ-ያዕቆብ=
*በእናቷ:-
-ሌዊ-ቀዓት-እንበረም-አሮን-ቴክታና በጥሪቃ-ሔኤሜን-ዴርዴን-ቶና-ሲካር-ሔርሜላና ማጣት-ሐና::
*በአባቷ በኩል:-
-ይሁዳ-ፋሬስ-ሰልሞን-ቦኤዝ-እሴይ-ዳዊት-ሰሎሞን-ሕዝቅያስ-ዘሩባቤል-አልዓዛር-ቅስራ-ኢያቄም ይሆናል::

+ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም: በሊባኖስ ተራራ ከ2,026 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::

=>የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን::

=>ግንቦት 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም (ልደታ)
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቴክታና በጥሪቃ
4.አባ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ (የእመቤታችንን ቅዳሴ የደረሰበት)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት
2.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ሚልኪ ትሩፈ ምግባር

=>+"+ መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው::
ከያዕቆብ ድንኩዋኖች ይልቅ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል::
የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! በአንቺ የተደረገው ድንቅ ነው . . .
ሰው እናታችን ጽዮን ይላል::
በውስጧም ሰው ተወለደ::
እርሱም ራሱ ልዑል መሠረታት:: +"+ (መዝ. 86:1-6)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/kaletsidkzm
#እንደ_ወሮቻችን_ኑ_በእርሷ_እንጀምር
(ዲ/ን ሕሊና በለጠ)

የወር መጀመሪያ የእርሷ ልደት ነው። ወሮቻችን ኹሉ በእርሷ ልደት ጀምረው በመጨረሻው የብሉይ ኪዳን ነቢይና የሐዲስ ኪዳን መንገድ ጠራጊ በመጥምቁ ዮሐንስ ያበቃሉ። እርሱ የብሉይን ማለፍና የሐዲስን መምጣት በማብሰር መንገድ እንደ ጠረገ ፣ የብሉይ ምሳሌ የኾነውን የአሮጌውን ዓመት ማለፍና የሐዲስ ምሳሌ የሚሆነውን የአዲሱን ዓመት መምጣት ያበሥር ዘንድ መስከረም አንድ ቅዱስ ዮሐንስ እንዲባል ኾነ። ልክ እንዲሁ ደግሞ የአሮጌው ወር መጨረሻ ላይ ወርኀዊው መታሰቢያው በመሆኑ በእርሱ ትምህርት ላይ ቆመው፣ እርሱ መንገድ ጠርጎላቸው ሐዲስን እንዳዩት የብሉይ ኪዳን ሰዎች፣ እኛም በእርሱ መታሰቢያ በዓል ላይ (በ30) ላይ ቆመን ሐዲስ ወርን እናያለን። እነርሱ በእርሱ ትምህርት ጸንተው የአሮጌውን ኪዳን መጨረሻነት ተረድተው የሐዲስ ኪዳንን ሐዲስ ሕይወት "1" ብለው እንደ ጀመሩ፣ እኛም 30 ላይ ቆመን የአሮጌው ወር ብልየታችንን መጨረሻነት ተረድተን የአዲሱን ወር ሐዲስ ሕይወት "1" ብለን እንጀምራለን። "1" ደግሞ ልደታ ለእግዝእትነ ነው - የኹሉ ነገር ጅማሬ የኾነችው የእመቤታችን ልደት።

ወሮቻችን ኹሉ በእርሷ ልደት ስለሚጀምሩ ቀና ናቸው። ወሩን እርሷን አክብሮ፣ ዘክሮ ስሟን ጠርቶ የሚጀምር ሰው መንገዱ የቀና ነው። በእርሷ ጀምሮ ያፈረ የለም።

የአዳም የመዳን ተስፋ "እምወለተ ወለትከ" በሚለው እርሷን በሚያነሣው ቃል ኪዳን ተጀምሮ ፍጻሜው ያማረ ሆነ። ኖሕ ከጥፋት ውኃ መዳኑን ለእርሷ ምሳሌ በሚሆን መርከቡ ጀምሮ አላፈረም። ሙሴ እስራኤልን ከፈርዖን የማዳን ሥራውን የጀመረው ሐመልማሉ እሳቱን ሳያጠፋው እሳቱም ሐመልማሉን ሳያቃጥለው ባየው ድንቅ ምሥጢር ነው፤ ይህ ደግሞ እሳተ መለኮት ሐመልማል የሆነች እርሷን ላለማቃጠሉና ላለመዋጡ፣ በእርሷ የተፈጸመውን ተዋሕዶ የሚያሳይ ነው።

ሠለስቱ ዮሐንሶችም እንዲሁ ናቸው። ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ የፍቅር እናትን ተቀብሎ የጀመረው ሕይወት "ነባቤ መለኮት" አስብሎታል። ዮሐንስ መጥምቅ በእናቱ ማህጸን ሳለ ለእርሷ ሰግዶ የጀመረው ሕይወት "ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከእርሱ የሚበልጥ አልተነሣም" አስብሎታል። (ማቴ.11:11)። አፈ በረከት ዮሐንስ ስለ እርሷ አመሥጥሮ የጀመረው ሕይወቱ "አፈ ወርቅ" አስብሎታል። (ግንቦት 1 ዓመታዊ በዓሏ እንደ ሆነው ግንቦት 12 የሊቁ ፣ ግንቦት 16ም የሐዋርያው በዓል መሆኑን ልብ ይሏል)

እርሷ የወራችን ብቻ ሳይሆን የሰማይና የምድርም መጀመሪያ ናት። (ሰማይና ምድር በውስጣቸውም ያሉት ስላንቺ ተፈጠሩ እንዲል ድርሳነ ማርያም)። ሰማይና ምድር ሳይጋፉ ፣ ሳይራበሹ "ይህ የኔ ክልል ነው፣ ይህ የኔ ወሰን ነው" ሳይባባሉ ሺህ ዘመናትን በፍቅር የጸኑት እርሷን መጀመሪያቸው ስላደረጉ ይሆን?

እርሷ የአዳምና ሔዋን መጀመሪያ ናት። ስለ እርሷ አዳምና ሔዋን ተፈጥረዋል። (መላእክትን ከፈጠረ በኋላ በጸፍጸፈ ሰማይ ቀጥሎ ማንን እንደሚፈጥር ያሳያቸው ነበር። ቀጥሎ የሚፈጠረው ሰው: አምላኩን እንደሚክድ ሲያዩ መላእክቱ "አትፍጠረው" አሉ። ድንግልን አሳያቸው፤ ሊያዩት የሚጓጉለትን አምላክን መውለዷን ሲያዩ "ይህችን ፍጠርልን" ብለው ተማጸኑ። "ካለ እርሱ (አዳም) እርሷ አትገኝም" ቢላቸው "እንግዲያውስ ስለ እርሷ እርሱን ፍጠርልን" አሉ። \ትርጓሜ. ኢዮብ? ኩፋሌ?)። ነገረ ልደቱ በእርሷ የጀመረለት አዳም ነገረ ልደቱ በእርሷ እንዳልጀመረለት ሳጥናኤል ወድቆ አልቀረም - ተነሣ እንጂ።

በእርሷ የሚጀምር ቢወድቅ እንኳን ይነሣል።

መጽሐፍ ቅዱስ ካምና ያፌትን ትቶ የሴም የትውልድ ሐረግን ለምን ተረከ? እመቤታችን ከሴም ዘር ስለምትወለድ ነው። ከሌሎች ሕዝቦች መኻል እስራኤልን መርጦ ለምን ቀጠለ? እመቤታችን ከእስራኤል ስለምትወለድ ነው። የካም ዘር የሆነውን መልከጼዴቅን ትቶ የሴም ዘር ስለ ሆነው ስለ አብርሃም እየተረከ ለምን ቀጠለ? አብርሃም ስለሚበልጥ ነውን? አይደለም። መልከጼዴቅ ታላቅ አብርሃም ታናሽ እንደ ሆነ ቅዱስ ጳውሎስ ነግሮናል። (ዕብ.7)። ታዲያ ምክንያቱ ምንድን ነው? እርሷ ከአብርሃም ዘር ስለምትወለድና ጌታችንና አምላካችንም ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ስለሚሆን ነው። መጽሐፍ ቅዱሳችን እንኳን እርሷን በሩቅ ዐይቶና በእርሷ ላይ ተመሥርቶ የተጻፈ ነው።

ድኅነታችን በእርሷ ምክንያትነት የተገኘ ነው። "አንዲት ዘር" የሆነች እርሷን ባያስቀርልን ኖሮ ከምድር በታች መውደቃችን ለመቀበር እንጂ ተዘርቶ ለማበብ አይሆንም ነበር።

ኢትዮጵያውያን በእርሷ በመጀመር አንታማም። በእርሷ እየጀመርን ከብዙ ውድቀትም ተርፈናል፣ ተነሥተናል።

እርስ በእርስ የመባላታችንም ሆነ የመጠላላታችን ነገር ምናልባት የፍቅር እናት የሆነች እርሷን ዘንግተን የመጡብን ይሆኑ ይሆን? ምናልባትም እርሷን የማይጠሩ ዜጎች በርክተው እኛም በዚህ ደክመን ይሆን?

ኑ ልክ እንደ ወሮቻችን በእርሷ እንጀምር። ያለፈውን ብልየት ኹሉ በመጥምቁ ትምህርት ላይ ቆመን እንሻገርና እርሷን ይዘን እንጀምር።

ባለፈው ወር ያለቀስን፣ ያዘንን፣ የወደቅን፣ የከፋን፣ ያቄምን፣ የሞትን፣ የዘረፍን፣ የገደልን፣ የዘሞትን በክፋትና በሥጋ ሥራ ያረጀን ኹሉ በመጥምቁ ትምህርት ላይ እንቁምና ብሉዩን እንሰናበተው፤ ሐዲሱን ሕይወት ልክ እንደ ወሮቻችን "1" ብለን በእርሷ እንጀምር።
🔔
✥✥✥
ሰዓት
✥ተንስኡ ለጸሎት✥

#መዝሙረ ዳዊት 118_25
አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አድን አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አቅና።

#በዚህ ሰዓት ይህንን የምታዩ የምታደርጉትን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔርን እያሰብን አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ

የእግዚሐብሔር ልጅ ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ማረን

የእግዚሐብሔር ልጅ ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ማረን

የእግዚሐብሔር ልጅ ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ማረን
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ ግንቦት 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

+"+ አባ መቃርስ ካልዕ +"+

+ይህ ቅዱስ "መቃርዮስ: መቃርስ: መቃሬም" ይባላል::
ትርጉሙ በ3ቱም መንገድ አይለወጥም:: ምክንያቱም
ሥርወ ቃሉ
በዮናኒ ልሳን "ብጹዕ: ንዑድ: ክቡር" ማለት ነውና::

+ከስሙ ቀጥሎ "ካልዕ-2ኛው": አንዳንዴ ደግሞ
"እስክንድርያዊ" እየተባለ ይጠራል:: "ካልዕ-2ኛው"
የሚባለው ከቀዳሚው
(ታላቁ መቃርስ) ለመለየት ሲሆን "እስክንድርያ" ደግሞ
ተወልዶ ያደገባት ሃገር ናት::

+አባ መቃርስ በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረ ገዳማዊ:
ጻድቅና ትሩፈ-ምግባር ነው:: በዓለም ለ40 ዓመት ሲኖር
እንደ ሕጉ
ፈጣሪውን ደስ ያሰኘ ሰው ነው:: ጻድቃን እንደ ከዋክብት
በበዙበት በዚያ ዘመን የታላቁ መቃርስን ዜና ሰምቷልና
ይህቺን
ክፉ ዓለም ከነግሳንግሷ ንቋት በርሃ ገብቷል::

+እንደሚገባ ሥርዓተ ገዳምን ጠብቆ: ለአበው ታዞ:
በጾም: በጸሎት: በትሕትናና በስግደት ተጠምዶ ቢያገኘው
ፈጣሪ አከበረው::
በዚያ ጊዜም ለታላቁ ገዳመ አስቄጥስ መናንያን አበ
ምኔት ሊሆን መረጡት::

+እርሱም እረኝነትን ያውቃልና በጐቹን (መነኮሳትን)
ከተኩላ (ሰይጣናት) ይጠብቅ ዘንድ ብዙ ተጋ:: ከብቃቱ
የተነሳም
ሳያስታጉል: ሳይበላ: ሳይጠጣና ሳይቀመጥ እስከ 40 ቀን
ይጸልይ ነበር:: ሲጸልይ ደግሞ በልቡ እየተቃጠለ በፍቅረ
ክርስቶስ ነበርና አጋንንት ይርዱለት ነበር::

+እርሱ ጸሎት ሲጀምርም በገዳሙ ዙሪያ ያሉ አጋንንት
እየጮሁ ይሸሹ ነበር:: ከተጋድሎው ጽናትና ከትሕትናው
ብዛት የተነሳ
ያዩት ትዕቢተኞች ሁሉ ይገሠጹ ነበር:: በዘመኑም ብዙ
ተአምራትን ሠርቷል::

+አንድ ቀን በበዓቱ ሳለ ጅብ መጥታ ተማጸነችው::
አብሯት ወደ ዋሻዋ ቢሔድ ልጆቿ በሙሉ ዓይነ ሥውራን
ሆነው አገኛቸው::
እርሱም ወደ መሬት ምራቁን እትፍ ብሎ በጭቃ ለውሶ
ቢቀባቸው የሁሉም ዐይናቸው በርቷል::

+ስለ ውለታውም ጅቢቱ የበግ ቆዳ እየጐተተች አምጥታ
ሰጥታዋለች:: (ከሰው ልጅ በቀር እንስሳት ውለታን
አይረሱምና) ቅዱስ
መቃርስም ለወትሮው ባዶው መሬት (አፈር) ላይ ይተኛ
የነበረው ከዚያ ቀን በኋላ በአጐዛው ላይ የሚተኛ ሁኗል::

+በሃገሩ እስክንድርያም ለ2 ዓመታት ዝናብ በመጥፋቱ
ሕዝቡ ተጨንቆ ነበርና "ናልን" ሲሉ መልዕክት ላኩበት::
እርሱ መጥቶ
ሲጸልይም መብረቅ የቀላቀለ ዝናብ ጣለ:: ዝናቡም ያለ
ማቆም ለ2 ቀናት በመዝነቡ ሕዝቡ ፈርተው "አባታችን ስለ
ኃጢአታችን
እንዳንጠፋ ለምንልን?" አሉት:: እርሱም በጸሎቱ
(በፈጣሪው ኃይል) እንደ ወደዱት ዝናቡን አቁሞላቸዋል::

+የአባ መቃርስን ዜና ሕይወትና ተአምራት ተናግሬ
አልፈጽመውም:: ግን አንዲት ብቻ ላክል:: ሁሌ ሳስበው
ስለሚገርመኝም
ነው::

+ብዙዎቻችን የጌታችን ሥጋና ደም አንቀበልም:: ለምን
ያከበርነውና የፈራነው አስመስለን ኃጢአትን ለመጥገብ
ቦታን (
አጋጣሚን) ስለምንፈልግ:: በተቃራኒው ደግሞ
አንዳንዶቻችን መለኮት የተዋሐደውን የጌታ ሥጋና ደም
እንደ ተርታ ነገር (ያለ
ጥንቃቄ) ስንቀበል ይታያል:: 2ቱም ግን ስሕተት ነው::

+ፈርተን (ፍርሃቱ ጤነኛ ባይሆንም) ስለ ራቅን በፍርድ ቀን
ማምለጥ አንችልም:: "ሥጋየን ያልበላ: ደሜንም ያልጠጣ
የዘለዓለም ሕይወት የለውም" ይለናልና:: (ዮሐ. 6:52)

+በድፍረት ለምንቀበልም ሥጋው እሳት ሁኖ እንዳይበላን:
ደሙም ባሕር ሆኖ እንዳያሰጥመን ልናከብረው ይገባናል::
"ሳይገባው
ከጌታ ሥጋና ደም የተቀበለ የጌታ ሥጋ ዕዳ አለበት"
ይለናልና:: (1ቆሮ. 11:27)

<< ታዲያ የሚሻለው ለሁላችንም ንስሃ ገብቶ: በፍርሃት
ሆኖ መቅረቡ ነው:: >>

+ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና አባ መቃርስ ወደ በርሃ
እንደ ገባ ሥጋ ወደሙን ተቀብሎ ነበር:: ቅዱሱ ይህንን
እያሰበ
ለ60 ዓመታት ምራቁን ሳይተፋ ኑሯል:: ለዚያ አይደል
አበው "ብታከብሩት ያከብራቹሃል" ያሉት::

+ሊቃውንቱም ይህንን ሲያደንቁ:-
"ኢታስተማስልዎ ለቁርባን ከመ ሕብስት ዕራቆ::
አኮኑ ሥጋ መለኮት ዘይትላጸቆ::
መቃርዮስ አብ ዕበየ ቁርባን ለአጠይቆ::
ድኅረ ተወክፈ በአሚን እንበለ ያብዕ ናፍቆ::
መጠነ ዓመታት ስሳ ኢተፍአ ምራቆ::" ብለዋል::

+ቅዱስ መቃርስም በ100 ዓመቱ በ5ኛው ክ/ዘመን
መጀመሪያ አካባቢ በዚህች ቀን ዐርፏል::

❖ጌታችን ከክብሩ: ከበረከቱ አይለየን::

=>ግንቦት 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አባ መቃርስ ገዳማዊ
2.እናታችን ቅድስት ሰሎሜ ኢትዮዽያዊት
3.አባ ይስሐቅ ጻድቅ
4.ቅድስት ዲላጊና 4 ሴት ልጆቿ (ሰማዕታት)
5.ቅዱስ ዳናስዮስ ሰማዕት
6.ቅዱስ በንደላዖስ ሰማዕት (የታላቁ ኤስድሮስ አባት)
7.አባ አሞን ጻድቅ (ዽዽስናን አልፈልግም ብሎ የሸሸ አባት)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም
2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን
3.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል
4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
7.ቅድስት ሰሎሜ
8.አባ አርከ ሥሉስ
9.አባ ጽጌ ድንግል
10.ቅድስት አርሴማ ድንግል

=>+"+ ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘለዓለም ሕይወት አለው:: እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሳዋለሁ:: ሥጋዬ እውነተኛ መብል: ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና:: ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል:: እኔም በርሱ እኖራለሁ:: +"+ (ዮሐ. 6:53-56)

   <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
«ወደ እግዚአብሔር የምንጸልየው፥ መረጃ ወይም መመሪያ ልንሰጠው ሳይሆን፥ ወደ እርሱ እንድንቀርብና ከእርሱ ጋር ኅብረት ያለን እንድንሆን ነው።»
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

❖ ግንቦት 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ

=>በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከሐዋርያት ቀጥሎ የቅዱስ
አትናቴዎስን ያሕል ስለ ሃይማኖት የተዋጋ ቅዱስ ፈልጐ
ማግኘት አይቻልም::

❖ቅዱስ አትናቴዎስ ማን ነው?

+ቅዱስ አትናቴዎስ በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት
በዘመነ ሰማዕታት መጠናቀቂያ በ300 አካባቢ(296)
እስክንድርያ
ግብፅ ውስጥ ነው የተወለደው:: ወላጆቹ አረማውያን
በመሆናቸው ክርስትናን አልተማረም ነበር::

+ሕጻን እያለ ለጭዋታ ከቤቱ ሲወጣ የክርስቲያን ልጆች
ሃይማኖታዊ ጨዋታ ሲጫወቱ ተመለከተ:: ሊቀላቀላቸው
ቢፈልግም
ክርስቲያን ባለመሆኑ ከለከሉት:: አትናቴዎስም ክርስቲያን
ልሁንና አጫውቱኝ ብሏቸው እሺ ስላሉት ሕጻናቱ ዕጣ
ተጣጣሉ::

+ላንዱ ቄስ: ላንዱም ዲያቆን መሆን ሲደርሳቸው
ለአትናቴዎስ ፓትርያርክ መሆን ስለ ደረሰው ሌሎቹ ሕጻናት
ይሰግዱለት ጀመር::
በአጋጣሚ ሕጻናቱ ይሕንን ሁሉ ሲያደርጉ የወቅቱ
ፓትርያርክ ቅዱስ እለ እስክንድሮስ በመገረም ያያቸው
ነበርና ለሕጻኑ
አትናቴዎስ ትንቢት ተናገረለት::

+ከዚያም የአትናቴዎስ አባቱ ሲሞት ሊቀ ዻዻሳቱ ከእናቱ
ወስዶ አጥምቆ: የሚገባውን መንፈሳዊ ትምሕርት ሁሉ
በልቡናው ላይ
ቀረጸበት:: ከዚሕ በኋላ ዲቁናን ሹሞ አስተምር አለው::
ምንም ሕጻን ቢሆንም ከሊቅነቱ: ከአመላለሱና ከአንደበቱ
ጣፋጭነት
የተነሳ የሰማው ሁሉ ይደነቅ ነበር:: ጸጋ እግዚአብሔር
በእርሱ ላይ አድራለችና::

+ቅዱስ አትናቴዎስ ሊቀ ዲቁና በተሾመ ወራት አርዮስ
ቤተ ክርስቲያንን በመረበሹ ኒቅያ ላይ 318ቱ ሊቃውንት
ሲሰበሰቡ
ጸሐፊ አድርገው ሾሙት:: በጊዜውም በዕድሜ የስንት
ጊዜ ትልቁ የሚሆነውን አርዮስን ተከራክሮ ምላሽ
አሳጣው::

ቅዱስ
አትናቴዎስ ከሊቃውንቱ ጋር ሆኖ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ
ወልደ አምላክ: እግዚአብሔር መሆኑን በአደባባይ
መሠከረ:: ጸሎተ
ሃይማኖትንም ያረቀቀው እርሱ ነው::

+ከዚሕ በኋላ የእስክንድርያ (የግብፅ) 20ኛ ፓትርያርክ
ሆኖ ተሾመ:: ቤተ ክርስቲያንን በመልካም እረኝነት ለ48
ዓመታት
ሲመግብ ብዙ መከራዎችን ተቀበለ:: ለ5 ጊዜ ከመንበሩ
አፈናቅለው ወደ በርሃ ሲያግዙት በስደት ከ15 ዓመታት
በላይ
አሳልፏል::

+በተሰደደባቸው ቦታዎች መከራን እየተቀበለ ያላመኑትን
አሳምኗል:: በጎቹ እንዳይባዝኑበት ደግሞ በጦማር
(በደብዳቤ)
ይጠብቃቸው ነበር:: ዛሬ በሃይማኖተ አበው የምናገኘው
ቃለ ሃይማኖት በዚሕ ዘመን የተጻፈ ነው::

+በወቅቱ የነበረው ንጉሥ (ትንሹ ቆስጠንጢኖስ) የአባቱን
(ታላቁ ቆስጠንጢኖስን) ዕረፍት ተከትሎ ነገሠ::

+ወዲያውም አርዮሳዊ መናፍቅ ሆነ:: ሃይማኖታቸው የቀና
አባቶችንም ያሳድድ ገባ:: ከአበው ቅዱሳን መካከል ግን
የዚህ
መከራ ቀዳሚው ገፈት ቀማሽ ታላቁ ሊቅ ቅዱስ
አንትናቴዎስ ነበር::

+በተለይ አንድ ጊዜ ንጉሡ ቅዱሱን ወደ በርሃ አግዞ:
መናፍቅ ዻዻስ በግብጽ ሹሞ: ብዙ ክርስቲያኖችን በግፍ
ሲያስገድል:
ቅዱሱን ለ6 ዓመታት አሰቃየው:: የወገኖቹ (የልጆቹን)
ስቃይ የሰማው ቅዱስ አትናቴዎስ ግን በድፍረት ወደ ቤተ
መንግስት
ገብቶ ተናገረው::

+2 አማራጭን አቅርቦ "ወይ ግደለኝና እንደ አባቶቼ
ሰማዕት ልሁን: ካልሆነ ግን ወደ መንጐቼ (ምዕመናን)
መልሰኝ" አለው::
መናፍቁ ንጉሥም ቢገድለው ብጥብጥ እንደሚነሳ
ስለሚያውቅ በስልት ሊያጠፋው ወሰነ::

+ቀዛፊ: መቅዘፊያ: ምግብና ውሃ በሌላት ጀልባ ውስጥ
ከቶም ሜዲትራኒያን ባሕር ውስጥ ጣለው:: ድንገት ግን
ከሰማይ
ጌታችን መላእክቱን አስከትሎ ወረደ::

+ሚካኤልና ገብርኤል ባሕሩን እየቀዘፍ: ሌሎች መላእክት
እየመገቡት በዚህች ቀን እስክንድርያ (ግብጽ) አድርሰውት
ተሠውረዋል:: ሕዝቡም በታላቅ ሐሴት እየዘመሩ
አባታቸውን ተቀብለውታል::

+ሐዋርያዊው ቅዱስ ስለ ኦርቶዶክስ ተዋግቶ: ብዙ
ስቃይንም ተቀብሎ በ373 ዓ/ም አካባቢ አርፏል:: ቤተ
ክስርቲያን
☞"ሊቀ
ሊቃውንት:
☞ርዕሰ ሊቃውንት:
☞የቤተ ክርስቲያን
(የምዕመናን) ሐኪም (Doctor of the Church):
☞ሐዋርያዊ" ብላ
ታከብረዋለች::

=>አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሊቁ በረከት አይለየን::
በምልጃውም ሃይማኖታችንን ይጠብቅልን::

=>ግንቦት 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
2.የባሕታውያን አለቃ ታላቁ አባ ሲኖዳ (ጽንሰቱ)
3.ቅዱስ ዮሐንስ ጻድቅ (ሃብቱን: ንብረቱን: ልብሱን
ሳይቀር መጽውቶ ራቁቱን የተገኘ ደግ ሰው ነው)
4.አባ ሐርስዮስ ገዳማዊ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)

=>+"+ ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብጹዐን ናቸው:: መንግስተ
ሰማያት የእነርሱ ናትና:: ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ
በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ
ብጹዓን ናችሁ:: ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ
ይበላችሁ:: ሐሴትም አድርጉ:: ከእናንተ በፊት የነበሩ
ነቢያትን እንዲሁ አሳደዋቸዋልና:: +"+ (ማቴ. 5:10)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/kaletsidkzm
Forwarded from 𝚜𝚊𝚖𝚛𝚒-19
ለዝክረ ቅዱስ ያሬድ የሚዘመሩ መዝሙራት
††† እንኳን ለእናታችን ቅድስት እሌኒ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† እሌኒ ንግሥት †††

††† ቅድስት እሌኒ የታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ እናቱና እግዚአብሔር ለበጐ አገልግሎት የጠራት ቡርክት ሴት (ንግሥት) ናት::
ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
የቅድስቲቱ ሃገረ ሙላዷ ሮሃ (ሶርያ) አካባቢ ነው:: ነገዷ ከእሥራኤል ዝርዋን እንደሆነም ይነገራል:: ጣልያኖች "Helena" : በእንግሊዝኛው "Helen" ይሏታል:: እኛ ደግሞ "እሌኒ" እንላታለን:: ትርጓሜው "ጥሩ ምንጭ" : አንድም "ውብና ደግ ሴት" ማለት ነው::

ቅድስት እሌኒ በመልካም ክርስትና አድጋ እንደ ቤተ ክርስቲያን መተርጉማን ተርቢኖስ የሚባል ነጋዴ አግብታ ነበር:: ወቅቱም ዘመነ ሰማዕታት ነበር:: በማይሆን ነገር ጠርጥሮ ባሕር ላይ ጥሏት ንጉሥ ቁንስጣ አግኝቷታል:: እርሱም የበራንጥያ (የኋላዋ ቁስጥንጥንያ) ንጉሥ ነበር::

ቅድስት እሌኒ ከቁንስጣ የተባረከ ልጅን ወለደች:: ቆስጠንጢኖስ አለችው:: በልቡናው ፍቅርን : ርሕራሄን : መልካምነትን እየዘራች አሳደገችው:: ቅዱሱ አባቱ በሞተ ጊዜ ተተክቶ ነገሠ::

ቅድስት እሌኒንም ንግሥት አደረጋት:: ያንን የአርባ ዓመት ግፍ በአዋጅ አስቀርቶ ለክርስቲያኖች ነፃነትን : ክብርን በይፋ ሰጠ:: አንድ : ሁለት ብለን የማንቆጥረውን ውለታ ለምዕመናን ዋለ:: ከነዚህ መልካም ምግባራቱ ጀርባ ታዲያ ቅድስት እናቱ ነበረች::

ቅድስት እሌኒ ጾምን : ጸሎትን ከማዘውተሯ ባሻገር አጽመ ሰማዕታትን ትሰበስብ : አብያተ ክርስቲያንን ታሳንጽ : ለነዳያንም ትራራ ነበር:: በኢየሩሳሌምና አካባቢው ብቻ ከሰማንያ በላይ አብያተ መቃድስ አሳንጻለች:: እነዚህንም በወርቅና በእንቁ ለብጣቸዋለች::

በዘመኗ መጨረሻም የጌታችንን ቅዱስ ዕፀ መስቀል ከተቀበረበት አውጥታ ለዓለም በረከትን አስገኝታለች::

እናታችን ቅድስት እሌኒ እንዲህ በቅድስና ተመላልሳ በሰማንያ ዓመቷ በ330ዎቹ አካባቢ ዐርፋለች:: ቤተ ክርስቲያናችንም ስለ ቅድስናዋና ውለታዋ በዓል ሠርታ : ታቦት ቀርፃ ስታከብራት ትኖራለች::

††† ከቅድስት እናታችን ምልጃና በረከት አምላካችን ያድለን::

††† ግንቦት 9 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት እሌኒ ንግሥት
2.ቅዱስ ስልዋኖስ

††† ወርኀዊ በዓላት
1.አባ በርሱማ ሶርያዊ (ለሶርያ መነኮሳት ሁሉ አባት)
2.አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ (ኢትዮጵያዊ)
3.ሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ ቅዱሳን ሊቃውንት (ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ)
4.የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
5.አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ (ኢትዮጵያዊ)
6.ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ (ዓለመ ብፁዐንን ያየ አባት)

††† "ነገር ግን ለበጐ ነገር ጥበበኞች : ለክፉትም የዋሆች እንድትሆኑ እወዳለሁ:: የሰላምም አምላክ ሰይጣንን ከእግራችሁ በታች ፈጥኖ ይቀጠቅጠዋል:: የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን::" †††
(ሮሜ. ፲፮፥፲፱)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

https://t.me/kaletsidkzm