💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
15K subscribers
4.48K photos
2.09K videos
162 files
12.6K links
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله

ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ↓↓
Download Telegram
➲የሰለፎችን መንሀጅ አጥብቀህ ያዝ !!
➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱

▪️‏قال العلامة ŘŻ. صالح بن فوزان ‎الفوزان حفظه الله "كلما يتأخر الزمان ŘŞŘ´ŘŞŘŻ الغربة وتك؍ع الفتن ويحتاج المسلمون إلى عناية أك؍ع بمنهج السلف"

➲ዘመን በራቀና በረዘመ ቁጥር

➧እንግዳነት ይበዛል
➧ፊትናም ይጨምራል
➧የዚህን ጊዜ ሙስሊሞች

✅የሰለፎችን (የቀደምቶች) መንሀጅና አካሄድ ላይ ትኩረት ማድረግ ከምንም በላይ ይፈልጋሉ።

📚 حاجة الأمة إلى المنهج السلفي ١٣

https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
خطورة التهاون في الصلاة | لفضيلة الشيخ العلامة صالح اللحيدان رحمه اللّٰه.

📌 رابط القناة للإشتراك 👇👇
https://t.me/https_Asselefya1
Audio
💢ተከታታይ ስለ ረመዷን ዳሰሳ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

የመጃሊሱ ሸህሪ ረመዳን ቂርአት
➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷
◾️በደርሱ የተወሱ ነጥቦች፦
①) ፈትሁ መካ ላይ የተከሰቱ ክስተቶች
②) ነብዩ መካ የከፈቱበት አስደናቂ ሁኔታ
③) የነብዩ አስደናቂ የጦር አመራር ሁኔታ


《ክፍል 4⃣8⃣》
〰〰〰〰〰

🎙 አቡ አብደሏህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/+V9ZPw4j7SHAIsgeQ
https://t.me/+V9ZPw4j7SHAIsgeQ
✍️ጥሩ ጓደኛ ካለህ አጥብቀህ ያዘው!!

💧ኢማሙ ሻፍእይ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ።

✅ለአላህ ብሎ መዋደድና ጓደኛ የመሆን ምሳሌው ልክ እንደ እጅና አይን ምሳሌ ነው። አይን ስታለቅስ እጅ እምባዋን ታብሳለች። እጅ ስትታመም ደግሞ በሷ ህመም አይን ታለቅሳለች። ወደ መልካም የሚመራህና በአላህ ትእዛዝ ላይ የሚያግዝ ጓደኛ ካለህ እንዳይለይህ አጥብቀህ ያዘው። ምክንያቱም በአሁን ሰአት መልካም ጓደኛ ማግኘት በጣም ከባድ ነው። ከመልካም ጓደኛ መለየት ግን በጣም ቀላል ነው።


📖|{حِلْيَةُ الْأَوْلِيَاء ١٠١/٤}

https://t.me/https_Asselefya1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
➲ ጀውዝይ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ።

✅ ለታመመ አካል ለህመሙ ማርና ሌሎች መድሀኒቶች ከሚጠቅሙት በላይ ቁርአን መቅራት ይጠቅመዋል።
📕انظر : التبــصـرة 79

https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
➲ከተውሂድ አርማዎች ➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱ ➧ክፍል ስምንት ➲የተውሒድ ምንነትና እውነታ ➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭ ➧ተውሒድ፡ “ወሐደ” (አንድ አደረገ) ፣“ዩወሒዱ” (አንድ ያደርጋል) ለሚሉት ግሶች ስርወ ቃል ነው፡፡ ተውሒድ ነጠላን የሚጠቁም ስርወ ቃል ነው፡፡የአላህ ተውሒድ አላህን በአምልኮ ብቸኛ ማድረግ ፣ እርሱ በሚለይባቸው ነገሮች ሌሎችን አካላት ከእርሱ ላይ ማጋራትን ማራቆት ማለት ነው፡፡…
➲ከተውሂድ አርማዎች
➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭➭

➭ክፍል ዘጠኝ

➧የተውሂድ ምንነትና እውነታ
➱➱➱➱➱➱➱➱➱➱

➲አንደኛው ተውሒድ አር'ሩቡብያ፡ አላህ በመፍጠርም ፣ ሲሳይ በመስጠትም ፣ ሁሉን ተቆጣጣሪ በመሆኑም ፣ ጸጋን በመስጠቱና ሁሉን በማገለባበጡ ብቸኛ መሆኑንና በእነዚህ ነገሮች ምንም አይነት ተጋሪ የሌለው መሆኑን አምኖ ብቸኛ ማድረግ ማለት ነው፡፡

➲አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጾቹ የሚከተለውን ተናግሯል፡

▪️قُلْ مَن رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ قُلِ اللَّهُ ۚ

“የሰማያትና የምድር ጌታ ማን ነው?” በላቸው፡፡ “አላህ ነው” በል፡፡ አር ረዕድ (16)

◀قُل لِّمَنِ الْأَرْضُ وَمَن فِيهَا إِن كُنتُمْ تَعْلَمُونَ ◆سَيَقُولُونَ لِلَّهِ ۚ قُلْ أَفَلَا تَذَكَّرُونَ ◆قُلْ مَن رَّبُّ السَّمَاوَاتِ السَّبْعِ وَرَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ ◆سَيَقُولُونَ لِلَّهِ ۚ قُلْ أَفَلَا تَتَّقُونَ◆قُلْ مَن بِيَدِهِ مَلَكُوتُ كُلِّ شَيْءٍ وَهُوَ يُجِيرُ وَلَا يُجَارُ عَلَيْهِ إِن كُنتُمْ تَعْلَمُونَ

➲
“ምድርና በውስጧ ያለው ሁሉ የማን ነው? የምታውቁ ብትሆኑ (ንገሩኝ)” በላቸው፡፡ “በእርግጥ የአላህ ነው” ይሉሃል፡፡ “ታዲያ አትገሰጹምን?” በላቸው፡፡“የሰባቱ ሰማያት ጌታና የታላቁ ዐርሽ ጌታ ማን ነው?”በላቸው፡፡ “በእርግጥ አላህ ነው” ይሉሃል፡፡ “እንግዲያ አትፈሩትምን?” በላቸው፡፡ “የነገሩ ሁሉ ግዛት በእጁ የሆነ እርሱ የሚጠብቅ በእርሱ ላይ የማይጠበቅ ማን ነው?የምታውቁ እንደሆናችሁ (መልሱልኝ) በላቸው፡፡ አል ሙእሚኑን፡(84__88)

▪️ذَٰلِكُمُ اللَّهُ رَبُّكُمْ ۖ فَتَبَارَكَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ

“ይሃችሁ ጌታችሁ አላህ ነው፡፡የዓለማትም ጌታ አላህ ላቀ፡፡” ጋፊር፡64

➧ሁለተኛው ክፍል፡ ተውሒዱል አስማእ ወስ'ሲፋት በቁርኣን በሐዲስ በመጡ መልካም ስሞቹና ከፍተኛ የሆኑ መገለጫዎች አላህን ብቸኛ ማድረግ ማለት ነው፡፡

➲አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጾቹ የሚከተለውን ተናግሯል፡

▪️اللَّهُ لَا إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ

“አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ለእርሱ መልካሞች የሆኑ ስሞች አሉት፡፡”
ጦሃ፡(8)
◀قُلِ ادْعُوا اللَّهَ أَوِ ادْعُوا الرَّحْمَٰنَ ۖ أَيًّا مَّا تَدْعُوا فَلَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ ۚ

➧አላህን ጥሩ ወይም አር'ረሕማንን ጥሩ ፤ (ከሁለቱ) ማንኛውንም ብትጠሩ (መልካም ነው)፡፡ ለእርሱ መልካም ስሞች አሉትና” አል ኢስራእ (110)

▪️هُوَ اللَّهُ الَّذِي لَا إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ عَالِمُ الْغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ ۖ هُوَ الرَّحْمَٰنُ الرَّحِيمُ ◆هُوَ اللَّهُ الَّذِي لَا إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ الْمَلِكُ الْقُدُّوسُ السَّلَامُ الْمُؤْمِنُ الْمُهَيْمِنُ الْعَزِيزُ الْجَبَّارُ الْمُتَكَبِّرُ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ ◆هُوَ اللَّهُ الْخَالِقُ الْبَارِئُ الْمُصَوِّرُ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ ۚ يُسَبِّحُ لَهُ مَا فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۖ وَهُوَ الْعَزِيزُ الْحَكِيمُ

➧እርሱ አላህ ነው ፤ ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ ፤ ሩቁንና ቅርቡን ዐዋቂ የሆነ ነው፡፡ እርሱ እጅግ በጣም ርህሩህ በጣም አዛኝ ነው፡፡ እርሱ አላህ ነው፡፡ ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ ፤ ንጉሱ ከጉድለት ሁሉ የጠራው ፣ የሰላም ባለቤቱ ፣ ጸጥታን ሰጭው ፣ ባሮቹን ጠባቂው ፣ አሸናፊው ፣ ሃያሉ ፣ ኩሩው ነው፡፡ አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ፡፡ እርሱ አላህ ፈጣሪው (ከኢምንት) አስገኚው ፣ ቅርጽን አሳማሪው ነው፡፡ ለእርሱ መልካሞች ስሞች አሉት፡፡ በሰማያትና በምድርም ያለው ሁሉ ለእርሱ ያሞግሳል፡፡ እርሱም አሸናፊና ጥበበኛም ነው፡፡”ሐሽር፡(22__24)

〰 〰 〰 〰 〰 〰 〰
◉
◉
◉
◉✍️ኢንሻአላህ ይቀጥላል

تأليف: فضيلة الشيخ عبدالرزاق بن عبد المحسن البدر

【አንብብ! ማንበብ የተሻለ ሰው ያደርጋል】

➧ ወ ደ ቻ ና ላ ች ን ይ ቀ ላ ቀ ሉ ን
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
➴https://t.me/https_Asselefya1
➴https://t.me/https_Asselefya1
Audio
◾️ተከታታይ የቂርአት ፕሮግራም
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰

➡️ ሸርህ አቂደቱል ዋሲጥያ የፈውዛን

➰ክፍል 8⃣9️⃣➰
〰〰〰〰〰

🎙አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
006 ፊርቀቱ አናጂያህ ወጧኢፈቱል መንሱራህ
በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ (አቡ ጁወይሪያ)
♦️አዲስ ተከታታይ የኪታብ ደርስ
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫

▪️كتاب منهاج الفرقة الناجية والطائفة المنصورة

➲ፊርቀቱ አናጂያህ ወጧኢፈቱል መንሱራህ

▪️ክፍል ስድስት
〰〰〰〰〰

♦️የኪታቧን PDF ለማገኘት
➴➴➘➘➷➷➴➴➘➘➷➷➷
https://t.me/https_Asselefya1/3725

🎙በኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ(አቡ ጁወይሪያ)
https://t.me/UstazKedirAhmed
https://t.me/https_Asselefya1
Audio
🔺ሴትነት ወደ ኢልም ይገፋፋል እንጂ ከኢልም አያግድም!!

🔺ኢልም መፈለግ በወንድም በሴትም ላይ ግዴታ ነው!


🔺ኢልም ለሴት ልጂ አስፈላጊነቱ የተዳሰሰበት!!

🔺በኢልም የመጠቁ ሰለፍያቶች የተወሱበት!!


🎙 አቡ አብደሏህ ኢብኑ ኸይሩ

https://t.me/https_Asselefya1
Audio
💢ተከታታይ ስለ ረመዷን ዳሰሳ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

የመጃሊሱ ሸህሪ ረመዳን ቂርአት
➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷➷
◾️በደርሱ የተወሱ ነጥቦች፦
①) መካ ከተከፈተ በኋላ…
②) ቁረይሾች ከተሸነፋ በኋላ…
③) የሰዎች ወደ እስልምና መጉረፍ
…

《ክፍል 4⃣9⃣》
〰〰〰〰〰

🎙 አቡ አብደሏህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/https_Asselefya1
https://t.me/https_Asselefya1
የመጨረሻ የውይይት ጥሪ
~ ~~~~
بسم الله الرحمن الرحيم
ከሆነ ጊዜ ወዲህ ያለው ንትርክ ውል ለማስያዝ ብለን የውይይት ጥሪ ያደረግንላቸው አካላት እስካሁን ድረስ ሰበብ እየደረደሩ ማሰናከሉን ተያይዘውታል። አሁን ደግሞ "ህዝብ ምን ያውቃልና ነው ዳኛ የሚሆነው?" በማለት ለህዝብ ክፍት መሆኑን እየነቀፉ ነው። በጉዳዩ ላይ ግር ያለው ሁሉ ከአሉባልታ ባለፈ በቀጥታ በመከታተል የጠራ አቋም ይይዝ ዘንድ ለህዝብ ክፍት ይሁን አልን እንጂ ህዝብ ዳኛ ሆኖ ነጥብ ይስጠን አላልንም። በዚያ ላይ ካልተግባባን የደረስንባቸውን ነጥቦች በጋራ ፅፈን በጋራ ለምናምንባቸው ዓሊሞች እናቅርባለን ብለናል። አንድ ጫፍ ላይ ሳንደርስ "ዓሊም እናስመጣለን" ወይም "ወደ ውጭ እንሄዳለን" ማለት መሸሻ ሰበብ እንጂ መፍትሄ መሻት አይደለም። ይህን ያክል ጉዳዩ ለታላላቅ ዓሊሞች እንዲቀርብ ብትፈልጉ ኖሮማ ተብዲዕ ውስጥ ከመዋኘታችሁ በፊት ተረጋግታችሁ ትጠብቁ ነበር።
ደግሞስ ከዚህ በፊት ለተለያዩ ወገኖች በግልፅ የውይይት ጥሪ ስናደርግ እንደነበር ይታወቃል። ለምን ያኔ አትነቅፉም ነበር? ጉዳዩ ወደናንተ ሲመጣ ነው ሰበብ የምትደረድሩት?
ለማንኛውም "ውይይቱ በአካል ቢሆን" ስትሉ ለነበራችሁ አካላት ሁሉ! ይሄው ጥያቄያችሁን በበጎ በማየት አንድ እርምጃ ለመቅረብ ወስነናል። ስለዚህ ሁለት ወይም ሶስት ሆነን ወደ ባህርዳር እንሄዳለን፣ ኢንሻአላህ። ይሁን እንጂ በር ዘግተን ከጥቂት ሰዎች ጋር ብቻ የምናወራበት ሁኔታ አይኖርም። በእንዲህ አይነት አካሄድ በተደጋጋሚ ተነድፈናል። ስለዚህ ባህዳር ውስጥ ካሉ መስጂዶች ውስጥ በአንዱ ይመቻች። የፈለገ ይታደምበት ዘንድ በሩ ክፍት ይሁን። ውይይቱን መቅዳትም፣ ቀጥታ ማስተላለፍም ለፈለገ አካል እንዲሁ ክፍት እንዲሆን እንፈልጋለን። ውይይቱን ለመምራትም የውጭ ሰው እንዲሆን አንጠይቅም። እዚያው ባህርዳር ያሉ መሻይኾች (ሸይኽ ዐብደላህ፣ ሸይኽ አሕመድ፣ ሸይኽ ሙሐመድ አወል፣ ኡስታዝ ዩሱፍን ጨምሮ) ይምሩት።
ለመረጃ ያክል ከውስጣችሁ ከኢኽዋን ጋር በግልፅ ውይይት ያደረገ ሰው አውቃለሁ። ይህንን የማነሳው ጥሪያችንን በሆነ ማመሀኛ እንዳትገፉት ነው።

NB፦
~~
በነገራችን ላይ ሰሞኑን በሕሩ የለቀቀውን ድምፅ አልሰማሁትም። የሰሙ ሰዎች ሲነግሩኝ ግን በዚህ መጠን መድረሱ ገርሞኛል። እንዲህ አይነቱን የዙልም አካሄድ ለህዝብ መበተኑ "ለአኺራዬ ያዋጣኛል" ካለ ምርጫው የራሱ ነው። ለጊዜው ግን ለራሴ እየተከላከልኩ ምላሽ በመስጠት ዋናውን የውይይት አጀንዳ ማደብዘዝ አልፈልግም። እቅጩን ስናገር ከውይይቱ ጥሪ ሰበብ እየደረደሩ የሚሸሹት የያዙት አቋም ሆድ የሚያስነፋ እንዳልሆነ ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ነው። ስለዚህ የሚፈልጉት ወይ በተዘጋ ክፍል ውስጥ ወይ ደግሞ ጭፍን ደጋፊ ብቻ ባለበት ቦታ ያለ ጠያቂ፣ ያለ ሞጋች እንደፈለጉ መወንጀል ነው። በዚሁ መልኩ ብቻ ነው የምንቀጥለው ካሉ፣ ለህሊናቸው ካልጎረበጣቸው መንገዱን ጨርቅ ያድርግላቸው። "እናንተ ዘንድ የሌላ እውነት አለን" ካሉ ይሄው ለመታረም ዝግጁ ነን እያልን ነው። እኛ እጅ ለመስጠት ፈቃደኞች ካልሆንም "እውነታቸውን" ገልጠው እንደሚያስቡት በኛ የተሸወዱትን አካላት የሚያተርፉበትን እድል ይጠቀሙበት። የቀደመ አቋሙን የቀየረው ማን እንደሆነ ይለይ። እዚያም እዚህም የምንሰማው የተምይዕ ውንጀላም ተፍረጥርጦ ይውጣ። ይሄ ወደ ሱና በመጣራትና ቢድዐን በመዋጋት ጭንብል የተንሰራፋው ውሸትም ይጋለጥ። ባጭሩ እንገናኝና ወይ አጥፊው ይታረም፤ ወይ ውሸታሙ ይፈር።
~ ሰላም ~