Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
መውሊድ ለምን አላማ እንደተጀመረ ያውቃሉ?
~
መውሊድ በሺዐዎች እንደተጀመረ ቀደም ብየ ገልጬ ነበር። አሁን ደግሞ ለምን አላማ ጀመሩት የሚለውን ባጭሩ እዳስሳለሁ።
በግብፅ የአስዩጥ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት የነበሩት ዶክተር ሐሰን ኢብራሂም ሐሰን እና በሃገሪቱ የትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ትምህርቶች ገምጋሚ የነበሩት ጦሀ አሕመድ ሸረፍ በጋራ በመሆን “አልሙዒዝ ሊዲኒላህ” በሚል ርእስ ስለ“ፋጢሚያዎቹ” ንጉስ ጥልቅ ጥናት በማድረግ አንድ መፅሐፍ አዘጋጅተዋል፡፡ በዚህ መፅሐፍ ውስጥ “አውደ - አመታት እና በዓላት” በሚል ርእስ ስር ያሰፈሩት ሃሳብ “መውሊድ ለምን አላማ ታስቦ ነው የተጀመረው?” ለሚለው ጥያቄ ጥሩ ምላሽ ይሰጣል፡፡ እንዲህ ነበር ያሉት፡-
“(ንጉሱ) አልሙዒዝ በሂጅራ አቆጣጠር የመጀመሪያው ቀን፣ በነብዩ ﷺ መውሊድ ቀን፣ በረጀብ መጀመሪያና አጋማሽ ላይ፣ በሸዕባን መጀመሪያና አጋማሽ ላይ፣ በረመዷን መጀመሪያ ቀን ከሚያስተዳድራቸው ህዝቦች ጋር ይካፈል ነበር፡፡ ይህን የሚያደርገው
* የሱኒ፞ዮቹን ልብ ለማረጋጋት፣
* እንዲሁም በሱኒ፞ዮች መርሆዎችና በሺዐዎች እምነቶች መካከል ያለውን ርቀት ለማጥበብ በማሰብ ነው፡፡
* በተጨማሪም ይሄ አልሙኢዝ ሊዲኒላ፞ህ የንግስና ዘመኑን ያሸበረቀባቸውን እነዚህን በዓላት የኢስማዒሊያ ሺዐ መዝሀብ እምነቶችን ለማሰራጨት ይጠቀምባቸው ነበር፡፡ ለዚህም ነበር የሑሰይንን ዝክር ህያው ለማድረግ የዓሹራእ ቀንን ያከብር የነበረው፡፡ ልክ እንዲሁ የበርካታ አኢማዎችን መውሊድና ስልጣን ላይ ያለውን ገዢ መውሊድ በሚልም (የራሱን ልደት) ያከብር ነበር፡፡
* ልክ በዚህ መልኩ የህዝቦቹን ትኩረት ወደሱ ለመሳብና የኢስማዒሊያ ሺዐ መዝሀብ መሰረታዊ እምነቶችን ለማሰራጨት እነዚህን በዓላት እንደ መዳረሻ ይጠቀምባቸው ነበር፡፡” [አልሙዒዝ ሊዲኒ'ላህ፡ 284]
ስለዚህ መውሊድ የተጀመረው ለፖለቲካዊ ትርፍና የሺዐን እምነት ለማስፋፋት ዓላማ ነው ማለት ነው፡፡ የክርስቲያኖቹ ገና፞፣ ሁዳዴ፣ …፣ የሺዐዎቹ የዓሹራእ በዓል፣ ገዲር ኹም፣ …፣ የእሳት አምላኪ መጁሳዎቹ ነይሩዝ ይከበሩ ከነበሩት በዓላት ውስጥ ነበሩ፡፡ የህዝብን ትኩረት ለመሳብ፣ ቅሬታ ውስጥ ያሉ ሱኒ፞ዮችን ልብ ለማረጋጋት በሂደትም ወደራሱ የሺዐ እምነት ሰዎችን ለማስገባት በማለም ነው፡፡ ቀስ እያለ በጉልበት ወደ ሺዐ እምነት መጣራት እንደተጀመረ ይታወስ፡፡ ስለዚህ አላማቸው ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚመጡትን የህዝብ ግፊቶች በማርገብ ይከተሉት የነበሩትን የኢስማዒሊያ ሺዐ እምነት ማስፋፋት ነበር፡፡ ይሄ ደግሞ ዛሬ ሱፍዮች እንደሚያስቡት “የወሃብዮች” ፕሮፓጋንዳ ሳይሆን ከላይ እንዳየነው የታሪክ አጥኚዎች ድምዳሜ ነው፡፡
የመውሊድ ስርኣቱ ለእኩይ አላማ የታለመ ስለነበርም ነው ሶላሑዲን አልአዩቢይ ሺ0ዎችን አስወግዶ ግብፅን ሲቆጣጠር አስቁሞት የነበረው፡፡ መቼም እሱንም “ወሃቢ ነው” እንደማትሉ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ዳግም የተጀመረው ኋላ በመምሉካውያን ጊዜ ነው፡፡ የመውሊድ ተግባር እንደገና ሲመለስ ሌሎቹ በአላት የሌላ እምነት መሰረት ያላቸው ወይም ሺዐ-ዘመም ስለነበሩ በሱኒ፞ው አለም ገበያ አላገኙም፡፡
ዛሬም የሙስሊሞችን መብት የሚጨፈልቁ የፖለቲካ ኃይሎች አጉል ተቆርቋሪ ሊመስሉ ለመውሊድ የተለየ ሸፋንና ድጋፍ ሲሰጡ ማየት የተለመደ ነው። ብልጥ የሆነ ሰው ሊያስተውል ይገባል። አላህ ማስተዋሉን ይስጠን።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
~
መውሊድ በሺዐዎች እንደተጀመረ ቀደም ብየ ገልጬ ነበር። አሁን ደግሞ ለምን አላማ ጀመሩት የሚለውን ባጭሩ እዳስሳለሁ።
በግብፅ የአስዩጥ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት የነበሩት ዶክተር ሐሰን ኢብራሂም ሐሰን እና በሃገሪቱ የትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ትምህርቶች ገምጋሚ የነበሩት ጦሀ አሕመድ ሸረፍ በጋራ በመሆን “አልሙዒዝ ሊዲኒላህ” በሚል ርእስ ስለ“ፋጢሚያዎቹ” ንጉስ ጥልቅ ጥናት በማድረግ አንድ መፅሐፍ አዘጋጅተዋል፡፡ በዚህ መፅሐፍ ውስጥ “አውደ - አመታት እና በዓላት” በሚል ርእስ ስር ያሰፈሩት ሃሳብ “መውሊድ ለምን አላማ ታስቦ ነው የተጀመረው?” ለሚለው ጥያቄ ጥሩ ምላሽ ይሰጣል፡፡ እንዲህ ነበር ያሉት፡-
“(ንጉሱ) አልሙዒዝ በሂጅራ አቆጣጠር የመጀመሪያው ቀን፣ በነብዩ ﷺ መውሊድ ቀን፣ በረጀብ መጀመሪያና አጋማሽ ላይ፣ በሸዕባን መጀመሪያና አጋማሽ ላይ፣ በረመዷን መጀመሪያ ቀን ከሚያስተዳድራቸው ህዝቦች ጋር ይካፈል ነበር፡፡ ይህን የሚያደርገው
* የሱኒ፞ዮቹን ልብ ለማረጋጋት፣
* እንዲሁም በሱኒ፞ዮች መርሆዎችና በሺዐዎች እምነቶች መካከል ያለውን ርቀት ለማጥበብ በማሰብ ነው፡፡
* በተጨማሪም ይሄ አልሙኢዝ ሊዲኒላ፞ህ የንግስና ዘመኑን ያሸበረቀባቸውን እነዚህን በዓላት የኢስማዒሊያ ሺዐ መዝሀብ እምነቶችን ለማሰራጨት ይጠቀምባቸው ነበር፡፡ ለዚህም ነበር የሑሰይንን ዝክር ህያው ለማድረግ የዓሹራእ ቀንን ያከብር የነበረው፡፡ ልክ እንዲሁ የበርካታ አኢማዎችን መውሊድና ስልጣን ላይ ያለውን ገዢ መውሊድ በሚልም (የራሱን ልደት) ያከብር ነበር፡፡
* ልክ በዚህ መልኩ የህዝቦቹን ትኩረት ወደሱ ለመሳብና የኢስማዒሊያ ሺዐ መዝሀብ መሰረታዊ እምነቶችን ለማሰራጨት እነዚህን በዓላት እንደ መዳረሻ ይጠቀምባቸው ነበር፡፡” [አልሙዒዝ ሊዲኒ'ላህ፡ 284]
ስለዚህ መውሊድ የተጀመረው ለፖለቲካዊ ትርፍና የሺዐን እምነት ለማስፋፋት ዓላማ ነው ማለት ነው፡፡ የክርስቲያኖቹ ገና፞፣ ሁዳዴ፣ …፣ የሺዐዎቹ የዓሹራእ በዓል፣ ገዲር ኹም፣ …፣ የእሳት አምላኪ መጁሳዎቹ ነይሩዝ ይከበሩ ከነበሩት በዓላት ውስጥ ነበሩ፡፡ የህዝብን ትኩረት ለመሳብ፣ ቅሬታ ውስጥ ያሉ ሱኒ፞ዮችን ልብ ለማረጋጋት በሂደትም ወደራሱ የሺዐ እምነት ሰዎችን ለማስገባት በማለም ነው፡፡ ቀስ እያለ በጉልበት ወደ ሺዐ እምነት መጣራት እንደተጀመረ ይታወስ፡፡ ስለዚህ አላማቸው ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚመጡትን የህዝብ ግፊቶች በማርገብ ይከተሉት የነበሩትን የኢስማዒሊያ ሺዐ እምነት ማስፋፋት ነበር፡፡ ይሄ ደግሞ ዛሬ ሱፍዮች እንደሚያስቡት “የወሃብዮች” ፕሮፓጋንዳ ሳይሆን ከላይ እንዳየነው የታሪክ አጥኚዎች ድምዳሜ ነው፡፡
የመውሊድ ስርኣቱ ለእኩይ አላማ የታለመ ስለነበርም ነው ሶላሑዲን አልአዩቢይ ሺ0ዎችን አስወግዶ ግብፅን ሲቆጣጠር አስቁሞት የነበረው፡፡ መቼም እሱንም “ወሃቢ ነው” እንደማትሉ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ዳግም የተጀመረው ኋላ በመምሉካውያን ጊዜ ነው፡፡ የመውሊድ ተግባር እንደገና ሲመለስ ሌሎቹ በአላት የሌላ እምነት መሰረት ያላቸው ወይም ሺዐ-ዘመም ስለነበሩ በሱኒ፞ው አለም ገበያ አላገኙም፡፡
ዛሬም የሙስሊሞችን መብት የሚጨፈልቁ የፖለቲካ ኃይሎች አጉል ተቆርቋሪ ሊመስሉ ለመውሊድ የተለየ ሸፋንና ድጋፍ ሲሰጡ ማየት የተለመደ ነው። ብልጥ የሆነ ሰው ሊያስተውል ይገባል። አላህ ማስተዋሉን ይስጠን።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
❤1
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ከፊሉ ልጅ የለኝም ብሎ ያለቅሳል። ሌላውን ልጁ ያስለቅሰዋል።
ከፊሉ እህት ወንድም የለኝም ብሎ ይከፋዋል። ሌላው በእህት በወንድሞቹ ውስጡ ቆስሏል።
ዱንያ አጃዒቧ አያልቅም። ግማሹ በመከራ፣ ሌላው በጥጋብ ያለቅሳል። "እናቱ የሞተችበትና፣ ገበያ የሄደችበት እኩል ያለቅሳል" በሚለው አገርኛ ብሂል ውስጥ ህመም አለ። መከራ ሁሉ አንድ አይደለም። ከባሰም በላይ ብዙ የባሰ እንዳለ በማስተዋል "አልሐምዱ ሊላህ" እንበል።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
ከፊሉ እህት ወንድም የለኝም ብሎ ይከፋዋል። ሌላው በእህት በወንድሞቹ ውስጡ ቆስሏል።
ዱንያ አጃዒቧ አያልቅም። ግማሹ በመከራ፣ ሌላው በጥጋብ ያለቅሳል። "እናቱ የሞተችበትና፣ ገበያ የሄደችበት እኩል ያለቅሳል" በሚለው አገርኛ ብሂል ውስጥ ህመም አለ። መከራ ሁሉ አንድ አይደለም። ከባሰም በላይ ብዙ የባሰ እንዳለ በማስተዋል "አልሐምዱ ሊላህ" እንበል።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የማለዳ መልእክት (45)
ለኸጢቦች እና ለዱዓቶች
~
የደዕዋ እና የኹጥባ መድረክ የነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መድረክ ነው። የማህበረሰብን ንቃተ ህሊና ለመቀየር፣ ዲኑን ለማስተማር፣ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለማንቃት እጅግ የላቀ ቦታ ነው። ግን እንደሚገባ እየተጠቀምነው ነው ወይ? መድረኩ ነብያዊ አማና ነውና አማናውን እየተወጣን ነው ወይ? ለመድረኩ የሚመጥን አቅምና ዝግጅትስ አለን ወይ? ሐቅን ለመናገር፣ ማህበረሰብን ለመጠበቅ የሰዎችን ስሜትና ፍላጎታቸውን ተከትለን ነው የምንፈሰው ወይስ አላህን በማሰብ፣ ለሐቅ በመቆርቆር፣ ዘላቂ ጥቅምን በማስቀደም በጀግንነት እንጓዛለን? ኃላፊነትን ባለመወጣት ከመጠየቃችን በፊት ከራሳችን ጋር ሂሳብ እንስራ።
1. ወደ ህዝብ ከመቅረባችን በፊት በቂ ዝግጅት እናድርግ፣ አቅማችንን እናዳብር። ሳይዘጋጁ መቅረብ ታዳሚን መናቅ ነው። ቦታውንም ክብር ማሳጣት ነው።
2. መሰረታዊ የኢስላም ርእሶችን ቅድሚያ እንስጥ። አርካኑል ኢማን፣ አርካኑል ኢስላም፣ ተውሒድና ሺርክ፣ ሱናና ቢድዐ፣ ከባኢረ ዙኑብ፣ ስነ ምግባር፣ ኢስላማዊ ቤተሰብ፣ እንደ ኡማ ሊኖረን የሚገባ መተዛዘንና መደጋገፍ፣ ዘረኝነት፣ እንደ ጫትና ሲጋራ ያሉ ጎጂ ሱሶች፣ ወዘተ. የህዝብን ቁጣና ኩርፊያ ሳንፈራ ግን ደግሞ ባማረና በማያስበረግግ መልኩ ደጋግመን እናስተምር።
3. ርእስ መረጣ ላይ የሰዎችን ስሜትና ፍላጎት እየተከተልን አንፍሰስ። ትኩረታችን የሚጠቅማቸውን መስጠት ይሁን። ደዕዋ ሰው መለወጫ እንጂ መዝናኛ መድረክ አይደለም። የሰዎችን ስሜትና ፍላጎት እየተከተለ የሚፈስ አስተማሪ ፈሪና አስመሳይ እንጂ እውነተኛ ተቆርቋሪ አይደለም።
4. እንደ ዘመን በህዝብ ላይ የተጋረጡ አደጋዎች እና ወቅታዊ ክስተቶች ሲኖሩ አቅጣጫ መስጠት ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ በቂ ንቃትና ዝግጅት ይፈልጋል። ንቃትና ዝግጅት ማለት እንግሊዝኛ መቀላቀል አይደለም። በሚዲያ የሰማነውን ዜና ማስተጋባትም አይደለም። የዳዒ ኃላፊነት እንደ ጋዜጠኛ ክስተቶችን ማንልበልና መተንተን አይደለም። መድረኮችን የፖለቲካ መደስኮሪያ እያደረጉ ማርከስ ንቃት አይደለም። ከዳዒ የሚጠበቀው ነገሮችን በኢስላም መነፅር በመመልከት ህዝብን ማረጋጋት፣ ሰዎችን ወደ አላህ መመለስ፣ በወቅታዊ ክስተቶች ከአቅማቸው በላይ በመግባት እንዳይዋጡ ማሳሰብ ነው።
እንዳጠቃላይ ለመድረኩ የሚመጥን ትኩረት እንስጥ፤ አቅም እናዳብር፤ ዝግጅት እናድርግ፤ ጀግንነትን እንላበስ፤ ሐቀኛ ተቆርቋሪነትን ሁሌም እናስብ። ሰላም።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሶፈር 30/1448)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
ለኸጢቦች እና ለዱዓቶች
~
የደዕዋ እና የኹጥባ መድረክ የነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መድረክ ነው። የማህበረሰብን ንቃተ ህሊና ለመቀየር፣ ዲኑን ለማስተማር፣ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለማንቃት እጅግ የላቀ ቦታ ነው። ግን እንደሚገባ እየተጠቀምነው ነው ወይ? መድረኩ ነብያዊ አማና ነውና አማናውን እየተወጣን ነው ወይ? ለመድረኩ የሚመጥን አቅምና ዝግጅትስ አለን ወይ? ሐቅን ለመናገር፣ ማህበረሰብን ለመጠበቅ የሰዎችን ስሜትና ፍላጎታቸውን ተከትለን ነው የምንፈሰው ወይስ አላህን በማሰብ፣ ለሐቅ በመቆርቆር፣ ዘላቂ ጥቅምን በማስቀደም በጀግንነት እንጓዛለን? ኃላፊነትን ባለመወጣት ከመጠየቃችን በፊት ከራሳችን ጋር ሂሳብ እንስራ።
1. ወደ ህዝብ ከመቅረባችን በፊት በቂ ዝግጅት እናድርግ፣ አቅማችንን እናዳብር። ሳይዘጋጁ መቅረብ ታዳሚን መናቅ ነው። ቦታውንም ክብር ማሳጣት ነው።
2. መሰረታዊ የኢስላም ርእሶችን ቅድሚያ እንስጥ። አርካኑል ኢማን፣ አርካኑል ኢስላም፣ ተውሒድና ሺርክ፣ ሱናና ቢድዐ፣ ከባኢረ ዙኑብ፣ ስነ ምግባር፣ ኢስላማዊ ቤተሰብ፣ እንደ ኡማ ሊኖረን የሚገባ መተዛዘንና መደጋገፍ፣ ዘረኝነት፣ እንደ ጫትና ሲጋራ ያሉ ጎጂ ሱሶች፣ ወዘተ. የህዝብን ቁጣና ኩርፊያ ሳንፈራ ግን ደግሞ ባማረና በማያስበረግግ መልኩ ደጋግመን እናስተምር።
3. ርእስ መረጣ ላይ የሰዎችን ስሜትና ፍላጎት እየተከተልን አንፍሰስ። ትኩረታችን የሚጠቅማቸውን መስጠት ይሁን። ደዕዋ ሰው መለወጫ እንጂ መዝናኛ መድረክ አይደለም። የሰዎችን ስሜትና ፍላጎት እየተከተለ የሚፈስ አስተማሪ ፈሪና አስመሳይ እንጂ እውነተኛ ተቆርቋሪ አይደለም።
4. እንደ ዘመን በህዝብ ላይ የተጋረጡ አደጋዎች እና ወቅታዊ ክስተቶች ሲኖሩ አቅጣጫ መስጠት ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ በቂ ንቃትና ዝግጅት ይፈልጋል። ንቃትና ዝግጅት ማለት እንግሊዝኛ መቀላቀል አይደለም። በሚዲያ የሰማነውን ዜና ማስተጋባትም አይደለም። የዳዒ ኃላፊነት እንደ ጋዜጠኛ ክስተቶችን ማንልበልና መተንተን አይደለም። መድረኮችን የፖለቲካ መደስኮሪያ እያደረጉ ማርከስ ንቃት አይደለም። ከዳዒ የሚጠበቀው ነገሮችን በኢስላም መነፅር በመመልከት ህዝብን ማረጋጋት፣ ሰዎችን ወደ አላህ መመለስ፣ በወቅታዊ ክስተቶች ከአቅማቸው በላይ በመግባት እንዳይዋጡ ማሳሰብ ነው።
እንዳጠቃላይ ለመድረኩ የሚመጥን ትኩረት እንስጥ፤ አቅም እናዳብር፤ ዝግጅት እናድርግ፤ ጀግንነትን እንላበስ፤ ሐቀኛ ተቆርቋሪነትን ሁሌም እናስብ። ሰላም።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሶፈር 30/1448)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Forwarded from Kassis Faage
🔴Wakti widirih elle iyyaamal meqe mari gabakalakaay uma mari ambagguk yamaate:
عَنْ مِرْداسٍ الأسْلَمِيِّ رضي الله عنه قالَ قالَ النَّبيُّ ﷺ: يَذْهَبُ الصَّالحُونَ الأوَّلُ فالأولُ، وتَبْقَى حُثَالَةٌ كحُثَالَةِ الشِّعِيرِ أوْ التَّمْرِ، لاَ يُبالِيهمُ اللَّه بالَةً رواه البخاري
Mirdaas Al-aslamiyyi Yalli kaa oggolay, iyyeh : Yallih Nabii(ﷺ) iyyeh: ❝ meqe mari naharsittu naharsittul gexaanaah
(raban) caffali qagurih(casurih) innah, hinnay tamri qagurih innah yan mari keenik
raaqaah, Yalli hebeltô xaagitiyyah ken ma xaagita(Yalli caagid keenit mali)❞ iyye.
[📜 Bukhaari -6434] .
Ta cadiis aaker waktil meqe mari xuguuguluh tii tiya ciggiilak rabaah, ellecaboh caffalik raaqa casurih innah Yallih xaqul tû caddo sinni maray Yalli tuh hangi kah cee waah iyya manguk raaqam neh warisa. Yalli caagid keenit mali yaanam Yallih garil caddo aallewaanaah, uma mara kinnoonum tascasse.
Tah yaanam meqe mari inkinnah mayan yaanam hinna laakin wakti widirih elle iyyaamal kaxxaam daggoowak yamaateeniih, uma mari ambagguk raaqam yascasse.
Ta Cadiisiik lafa le farmo macaay inneh wagitnek: Meqe marih katayyol faxsiisaah, baaxol daggoowan way mangom rabi ken yookomeh gexan way, ken gita katayoona faxximtam kee ken gita sadaanaah Yallih garil burrutume marih loowot gacaanamak takkaawisa.
قال الشيخ ابن عثيمين - رحمه الله - :
( لذلك تجدُ الناسَ يترَدُّون كلَّ عام عن العام الذي قبله.
فيما سبق تجدُ الناس:َ
يتهجَّدون في الليل، ويصومون النهار، ويتصدَّقون من أقواتهم، ويؤثرون على أنفسهم.
أما الآن تجدُ الناسَ تغيروا من سنة إلى أخرى إلى أردى من قبل:
سهرٌ في الليل على غير طاعة الله،
ونوم في النهار أو لهوٌ أو بيعٌ وشراء يشتمل على الغش والكذب والعياذُ بالله.
ومع ذلك يوجدٌ أناسٌ ولله الحمدُ على دينِ اللهِ مستقيمين على ما يبدو، لكنَّ العبرةَ بالعموم والشمول ...
ولذلك يَجِبُ الحذرُ من أن يكونَ الإنسانُ من الحثالةِ التي كحثالةِ الشعير أو التمر،ِ وأن يحرصَ على أمرِ اللهِ حتى لو كان الناسُ قد هلكوا؛ فإنهم إن أصيبوا بالعذابِ العامِّ فإنه يُبعثُ كلُّ إنسانٍ على نيَّتِه يَوْمَ القيامة )
شرح_رياض_الصالحين (٦٣٤/٦)
للشيخ محمد صالح ابن عثيمين رحمه الله
#Join ⤵️⤵️ Telegram channel
https://t.me/Kassisfaage
https://t.me/Kassisfaage
عَنْ مِرْداسٍ الأسْلَمِيِّ رضي الله عنه قالَ قالَ النَّبيُّ ﷺ: يَذْهَبُ الصَّالحُونَ الأوَّلُ فالأولُ، وتَبْقَى حُثَالَةٌ كحُثَالَةِ الشِّعِيرِ أوْ التَّمْرِ، لاَ يُبالِيهمُ اللَّه بالَةً رواه البخاري
Mirdaas Al-aslamiyyi Yalli kaa oggolay, iyyeh : Yallih Nabii(ﷺ) iyyeh: ❝ meqe mari naharsittu naharsittul gexaanaah
(raban) caffali qagurih(casurih) innah, hinnay tamri qagurih innah yan mari keenik
raaqaah, Yalli hebeltô xaagitiyyah ken ma xaagita(Yalli caagid keenit mali)❞ iyye.
[📜 Bukhaari -6434] .
Ta cadiis aaker waktil meqe mari xuguuguluh tii tiya ciggiilak rabaah, ellecaboh caffalik raaqa casurih innah Yallih xaqul tû caddo sinni maray Yalli tuh hangi kah cee waah iyya manguk raaqam neh warisa. Yalli caagid keenit mali yaanam Yallih garil caddo aallewaanaah, uma mara kinnoonum tascasse.
Tah yaanam meqe mari inkinnah mayan yaanam hinna laakin wakti widirih elle iyyaamal kaxxaam daggoowak yamaateeniih, uma mari ambagguk raaqam yascasse.
Ta Cadiisiik lafa le farmo macaay inneh wagitnek: Meqe marih katayyol faxsiisaah, baaxol daggoowan way mangom rabi ken yookomeh gexan way, ken gita katayoona faxximtam kee ken gita sadaanaah Yallih garil burrutume marih loowot gacaanamak takkaawisa.
قال الشيخ ابن عثيمين - رحمه الله - :
( لذلك تجدُ الناسَ يترَدُّون كلَّ عام عن العام الذي قبله.
فيما سبق تجدُ الناس:َ
يتهجَّدون في الليل، ويصومون النهار، ويتصدَّقون من أقواتهم، ويؤثرون على أنفسهم.
أما الآن تجدُ الناسَ تغيروا من سنة إلى أخرى إلى أردى من قبل:
سهرٌ في الليل على غير طاعة الله،
ونوم في النهار أو لهوٌ أو بيعٌ وشراء يشتمل على الغش والكذب والعياذُ بالله.
ومع ذلك يوجدٌ أناسٌ ولله الحمدُ على دينِ اللهِ مستقيمين على ما يبدو، لكنَّ العبرةَ بالعموم والشمول ...
ولذلك يَجِبُ الحذرُ من أن يكونَ الإنسانُ من الحثالةِ التي كحثالةِ الشعير أو التمر،ِ وأن يحرصَ على أمرِ اللهِ حتى لو كان الناسُ قد هلكوا؛ فإنهم إن أصيبوا بالعذابِ العامِّ فإنه يُبعثُ كلُّ إنسانٍ على نيَّتِه يَوْمَ القيامة )
شرح_رياض_الصالحين (٦٣٤/٦)
للشيخ محمد صالح ابن عثيمين رحمه الله
#Join ⤵️⤵️ Telegram channel
https://t.me/Kassisfaage
https://t.me/Kassisfaage
Telegram
Kassis Faage
★Baxaabaxsale diini kassiisitte Qafár afat elle geytoona waytan faage.
Ni faagel arciba!
👉Join us:https://t.me/Kassisfaage
Ni faagel arciba!
👉Join us:https://t.me/Kassisfaage
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የማለዳ መልእክት (46)
~
ከአቡ ሁረ ይረህ - ረዲየላሁ ዐንሁ - ተይዞ ነብያችን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
أكْملُ المؤمنينَ إيمانًا أحسنُهُم خلقًا . وخيارُكُم خيارُكُم لنسائِهِم
"ከምእመናን መካከል ኢማኑ ሙሉ የሆነው ሥነ-ምግባሩ ያማረው ነው። ከእናንተ መካከል በላጮቹ ለሴቶቻቸው (ለባለቤቶቻቸው) መልካም የሆኑት ናቸው።"
[አቡ ዳውድ (4682)፣ ቲርሚዚይ (1162) እና አሕመድ (2/ 472) የዘገቡት ሲሆን ሸይኹል አልባኒይ "ሐሰኑን ሶሒሕ" ብለውታል። (ሶሒሑ ቲርሚዚይ፡ 1162) ]
የራሳችንን ሁኔታ እናጢን፤ የተሻለ ለመሆንም እንጣር።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 01/1448)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
~
ከአቡ ሁረ ይረህ - ረዲየላሁ ዐንሁ - ተይዞ ነብያችን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
أكْملُ المؤمنينَ إيمانًا أحسنُهُم خلقًا . وخيارُكُم خيارُكُم لنسائِهِم
"ከምእመናን መካከል ኢማኑ ሙሉ የሆነው ሥነ-ምግባሩ ያማረው ነው። ከእናንተ መካከል በላጮቹ ለሴቶቻቸው (ለባለቤቶቻቸው) መልካም የሆኑት ናቸው።"
[አቡ ዳውድ (4682)፣ ቲርሚዚይ (1162) እና አሕመድ (2/ 472) የዘገቡት ሲሆን ሸይኹል አልባኒይ "ሐሰኑን ሶሒሕ" ብለውታል። (ሶሒሑ ቲርሚዚይ፡ 1162) ]
የራሳችንን ሁኔታ እናጢን፤ የተሻለ ለመሆንም እንጣር።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 01/1448)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሙስሊም ወንድሞቼ ፣ ጊዜው ሳያልፍ እንንቃ!
ያ አላህ! ጉዳዩ እየከበደና እያሳሰበ መጥቷል። ሀገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ ፊርቆችና አስተሳሰቦች እየተጋለጠች ነው። አንዳንድ ቡድኖችና እንቅስቃሴዎችም በሕዝቡ መካከል እየተስፋፉ ሲሆን፣ በተለይም ወጣቶችንና ሕፃናትን ማነጣጠራቸው እየጨመረ ነው።
በቅርብ ጊዜም ከአህሉስ-ሱና ወልጀማዓ አስተምህሮ ፍፁም የሚለያዩ ቡድኖች፣ ከእነሱም መካከል ሺዓ፣ አሕመዲያ እና ሌሎችም በአንዳንድ አካባቢዎች እየተስፋፉ እንደሚገኙ እናስተውላለን። በተለይም በባቲና በአካባቢዋ የተለያዩ የትምህርትና የዳዕዋ እንቅስቃሴዎች እየተካሄዱ መሆናቸው ትኩረታችንን ይሻል።
በተለይ ልንጠነቀቅ የሚገባን ሕፃናትና ወጣቶች ላይ የሚደረገው ትኩረት ነው። አንዳንድ ወገኖች ትምህርት ቤቶችን፣ ማዕከላትንና የትምህርት ተቋማትን በመክፈት ሕፃናትን ገና ከልጅነታቸው ከ kg ጀምሮ ለማስተማር እየሰሩ ነው።
እንግዲህ ራሳችንን መጠየቅ ይገባናል፦
ልጆቻችን እና ወጣቶች ምን እየተማሩ ነው?
ምን ዓይነት እምነትና አስተሳሰብ እየተቀበሉ ነው?
ትምህርታቸውን የሚከታተልና አቅጣጫ የሚሰጣቸው ማን ነው?
ወንድሞቼና የተከበራችሁ ወገኖቼ ሆይ!
ከሀገራችን ጫፍ እስከ ሌላኛው ጫፍ ድረስ፣ የአህሉስ-ሱና ወልጀማዓ ተከታዮች ሆይ፣ የአካባቢያችን ሰዎች ሆይ፣ በተለይም የባቲ ነዋሪዎች ሆይ!
የልጆቻችን የወጣቶችን የራሳችንንእምነት መጠበቅና የአላህን መጽሐፍ እና የነቢዩን ﷺ ሱና ማስተማር ታላቅ ኃላፊነት ነው።
ይህንንም በዘፈቀደ ግጭት፣ በስድብ ወይም ሌሎችን በማዋረድ ሳይሆን፣ በዕውቀት፣ በጥበብ፣ በትክክለኛ ትምህርት፣ በግንዛቤ ማስጨበጥ እና ማህበረሰባችንን በቁርአን፣ በሱናና በትክክለኛ የእስልምና እምነት ማጠናከር ነው።
ማህበረሰባችንን በቅርብ ልንከታተል፣ ምን እንደሚማሩም ልናውቅ ይገባል። በራሳችን ትምህርት ቤቶችና የእስልምና ማዕከላት ውስጥም ጠንካራና ጠቃሚ ትምህርት እንዲያገኙ ልንጥር ይገባል።
ይህም ቁርአንን፣ ትክክለኛ የአቂዳ ትምህርትን፣ ፊቅህን፣ መልካም ሥነ-ምግባርንና የዓረብኛ ቋንቋን ያካተተ መሆን አለበት።
ሌሎች ሰዎች ቦታውን እንዲይዙ ከፈቀድን በኋላ፣ ሐሳቦቻቸው ስለተስፋፉ ብቻ ማማረር መፍትሔ አይሆንም።
ስለዚህ ኃላፊነታችንን እንወጣ። ማህበረሰባችን ከሌሎች ዘንድ ከመማራቸው በፊት እኛ እናስተምራቸው። የተሳሳቱ አስተሳሰቦችንም በዕውቀት፣ በማስረጃና በጥበብ እንመልስ።
ኢንሻአላህ፣ እነዚህ ቡድኖች ምን እንደሆኑ፣ መሠረታዊ ሐሳቦቻቸውና እምነቶቻቸው ምን እንደሆኑም በማስረጃና በታማኝ ምንጮች ላይ በመመስረት አብራራለሁ፤ ዓላማዬም ሙስሊሙ ስለ ዲኑ በቂ ዕውቀት እንዲኖረውና በጉዳዮች ላይ በግልጽ እውቀት እንዲቆም ነው።
አላህ ሆይ! ሀገራችንንና ማህበረሰባችንን ጠብቅ። እኛንና እነርሱን በቁርአንና በሱና ላይ አጽና። ዑለማዎቻችንን፣ ዳዒዎቻችንንና መምህራኖቻችንን ኃላፊነታቸውን በትክክል እንዲወጡ እርዳቸው። ከቀናው መንገድ የራቁትንም ወደ እውነት ምራቸው።
አላህ ሆይ! የሙስሊሞችን ልጆች ጠብቅ፣ እምነታቸውን ጠብቅ፣ ወደ እውነትና መልካም ሥራ የሚጠሩ ዳዒዎች አድርጋቸው።
አሚን!
=
አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ ሙሐመድ
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
ያ አላህ! ጉዳዩ እየከበደና እያሳሰበ መጥቷል። ሀገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተለያዩ ፊርቆችና አስተሳሰቦች እየተጋለጠች ነው። አንዳንድ ቡድኖችና እንቅስቃሴዎችም በሕዝቡ መካከል እየተስፋፉ ሲሆን፣ በተለይም ወጣቶችንና ሕፃናትን ማነጣጠራቸው እየጨመረ ነው።
በቅርብ ጊዜም ከአህሉስ-ሱና ወልጀማዓ አስተምህሮ ፍፁም የሚለያዩ ቡድኖች፣ ከእነሱም መካከል ሺዓ፣ አሕመዲያ እና ሌሎችም በአንዳንድ አካባቢዎች እየተስፋፉ እንደሚገኙ እናስተውላለን። በተለይም በባቲና በአካባቢዋ የተለያዩ የትምህርትና የዳዕዋ እንቅስቃሴዎች እየተካሄዱ መሆናቸው ትኩረታችንን ይሻል።
በተለይ ልንጠነቀቅ የሚገባን ሕፃናትና ወጣቶች ላይ የሚደረገው ትኩረት ነው። አንዳንድ ወገኖች ትምህርት ቤቶችን፣ ማዕከላትንና የትምህርት ተቋማትን በመክፈት ሕፃናትን ገና ከልጅነታቸው ከ kg ጀምሮ ለማስተማር እየሰሩ ነው።
እንግዲህ ራሳችንን መጠየቅ ይገባናል፦
ልጆቻችን እና ወጣቶች ምን እየተማሩ ነው?
ምን ዓይነት እምነትና አስተሳሰብ እየተቀበሉ ነው?
ትምህርታቸውን የሚከታተልና አቅጣጫ የሚሰጣቸው ማን ነው?
ወንድሞቼና የተከበራችሁ ወገኖቼ ሆይ!
ከሀገራችን ጫፍ እስከ ሌላኛው ጫፍ ድረስ፣ የአህሉስ-ሱና ወልጀማዓ ተከታዮች ሆይ፣ የአካባቢያችን ሰዎች ሆይ፣ በተለይም የባቲ ነዋሪዎች ሆይ!
የልጆቻችን የወጣቶችን የራሳችንንእምነት መጠበቅና የአላህን መጽሐፍ እና የነቢዩን ﷺ ሱና ማስተማር ታላቅ ኃላፊነት ነው።
ይህንንም በዘፈቀደ ግጭት፣ በስድብ ወይም ሌሎችን በማዋረድ ሳይሆን፣ በዕውቀት፣ በጥበብ፣ በትክክለኛ ትምህርት፣ በግንዛቤ ማስጨበጥ እና ማህበረሰባችንን በቁርአን፣ በሱናና በትክክለኛ የእስልምና እምነት ማጠናከር ነው።
ማህበረሰባችንን በቅርብ ልንከታተል፣ ምን እንደሚማሩም ልናውቅ ይገባል። በራሳችን ትምህርት ቤቶችና የእስልምና ማዕከላት ውስጥም ጠንካራና ጠቃሚ ትምህርት እንዲያገኙ ልንጥር ይገባል።
ይህም ቁርአንን፣ ትክክለኛ የአቂዳ ትምህርትን፣ ፊቅህን፣ መልካም ሥነ-ምግባርንና የዓረብኛ ቋንቋን ያካተተ መሆን አለበት።
ሌሎች ሰዎች ቦታውን እንዲይዙ ከፈቀድን በኋላ፣ ሐሳቦቻቸው ስለተስፋፉ ብቻ ማማረር መፍትሔ አይሆንም።
ስለዚህ ኃላፊነታችንን እንወጣ። ማህበረሰባችን ከሌሎች ዘንድ ከመማራቸው በፊት እኛ እናስተምራቸው። የተሳሳቱ አስተሳሰቦችንም በዕውቀት፣ በማስረጃና በጥበብ እንመልስ።
ኢንሻአላህ፣ እነዚህ ቡድኖች ምን እንደሆኑ፣ መሠረታዊ ሐሳቦቻቸውና እምነቶቻቸው ምን እንደሆኑም በማስረጃና በታማኝ ምንጮች ላይ በመመስረት አብራራለሁ፤ ዓላማዬም ሙስሊሙ ስለ ዲኑ በቂ ዕውቀት እንዲኖረውና በጉዳዮች ላይ በግልጽ እውቀት እንዲቆም ነው።
አላህ ሆይ! ሀገራችንንና ማህበረሰባችንን ጠብቅ። እኛንና እነርሱን በቁርአንና በሱና ላይ አጽና። ዑለማዎቻችንን፣ ዳዒዎቻችንንና መምህራኖቻችንን ኃላፊነታቸውን በትክክል እንዲወጡ እርዳቸው። ከቀናው መንገድ የራቁትንም ወደ እውነት ምራቸው።
አላህ ሆይ! የሙስሊሞችን ልጆች ጠብቅ፣ እምነታቸውን ጠብቅ፣ ወደ እውነትና መልካም ሥራ የሚጠሩ ዳዒዎች አድርጋቸው።
አሚን!
=
አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ ሙሐመድ
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
Telegram
አቡ አዩብ ሙሃመድ ሰይድ ሙሃመድ
قال الإمام مالك ((لايصلح آخر هذه الأمة إلا بماصلح به أولها))
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የማለዳ መልእክት (46)
~
ታላቁ ሶሓቢይ ሰዕድ ብኑ አቢ ወቃስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ባስተላለፉት ሐዲሥ የአላህ መልእክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
إن الله يحب العبد التقي الغني الخفي
"አላህ፡ አላህን ፈሪውን፣ በራሱ የተብቃቃውን እና ድብቁን (ዝናን የማይፈልገውን) ባሪያውን ይወዳል።"
ኢማሙ ሙስሊም በሶሒሓቸው ውስጥ ዘግበውታል። [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 2965]
=
ዑለማኦች የአላህን ውዴታ የሚያስገኙትን እነዚህን ሦስት ባሕርያት እንደሚከተለው አብራርተዋቸዋል፦
1. «አል-ተቂይ» (ፈሪሃ-አላህ ያለው / አላህን ፈሪ):-
ይህ ባሪያ የአላህን ትዕዛዛት በመፈጸም እና ክልከላዎቹን በመራቅ የአላህን ትእዛዝ የሚጠብቅ፣ በአላህ ትዕዛዝና ኃጢአትን እንዲሁም አጠራጣሪ ነገሮችን በመራቅ በእርሱ እና በአላህ ቅጣት መካከል ከልላይን የሚያደርግ ነው።
2. «አል-ገኒይ» (ሀብታም / የተብቃቃ):-
«ሀብት/መብቃቃት» በሚለው ትርጉም ላይ በሁለት አቅጣጫ ገልጸውታል፦
* የነፍስና የቀልብ መብቃቃት (ይህ ይበልጥ ጎላ ያለና ተመራጩ ትርጉም ነው)፦
ባሪያው አላህ በወሰነለት እና በሰጠው ሲሳይ የሚረካ፣ በሰዎች እጅ ካለው ነገር ተብቃቅቶ በአላህ ብቻ የሚብቃቃ፣ ቀልቡ በኢማን እና በየቂን (እርግጠኝነት) የሞላ መሆን ነው። ነቢዩም ﷺ፦ «ولكن الغنى غنى النفس» («እውነተኛ ሀብት ማለት ግን የነፍስ (የቀልብ) መብቃቃት ነው») ብለዋል።
* የገንዘብ ሀብት፦
ይህም ሀብቱን በበጎ አድራጎት፣ በመልካም ሥራዎች እና ሰዎችን በመጥቀም ላይ የሚያውል፣ ሀብቱ ከአላህ እገዛ እንዳይዘናጋው የአላህን ሐቅ እየፈጸመ የሚያመሰግን ሀብታም ነው።
3. «አል-ኸፊይ» (ድብቁ / ራሱን የማያገዝፈው):-
* ዝናን፣ ሥልጣንን እና በምድር ላይ ከፍ ማለትን የማይሻ፣ ይልቁንም ጌታውን በመገዛት፣ የራሱን ጉድለቶች በመመልከት እና ራሱን በማረም ላይ ብቻ የተጠመደ ሰው ማለት ነው።
* በተጨማሪም፦ ፍጹም ለአላህ ብቻ ብሎ ለመስራት (ኢኽላስ) እና ይዩልኝ ስሙልኝን (ሪያእ) በመፍራት መልካም ሥራዎቹንና አምልኮቶቹን (እንደ ድብቅ ሶደቃና የሌሊት ሶላት ያሉትን) ሰው እንዳያይበት የሚደብቅ ሰውም በዚህ ውስጥ ይካተታል።
||
(ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 04/1448)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
~
ታላቁ ሶሓቢይ ሰዕድ ብኑ አቢ ወቃስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ባስተላለፉት ሐዲሥ የአላህ መልእክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
إن الله يحب العبد التقي الغني الخفي
"አላህ፡ አላህን ፈሪውን፣ በራሱ የተብቃቃውን እና ድብቁን (ዝናን የማይፈልገውን) ባሪያውን ይወዳል።"
ኢማሙ ሙስሊም በሶሒሓቸው ውስጥ ዘግበውታል። [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 2965]
=
ዑለማኦች የአላህን ውዴታ የሚያስገኙትን እነዚህን ሦስት ባሕርያት እንደሚከተለው አብራርተዋቸዋል፦
1. «አል-ተቂይ» (ፈሪሃ-አላህ ያለው / አላህን ፈሪ):-
ይህ ባሪያ የአላህን ትዕዛዛት በመፈጸም እና ክልከላዎቹን በመራቅ የአላህን ትእዛዝ የሚጠብቅ፣ በአላህ ትዕዛዝና ኃጢአትን እንዲሁም አጠራጣሪ ነገሮችን በመራቅ በእርሱ እና በአላህ ቅጣት መካከል ከልላይን የሚያደርግ ነው።
2. «አል-ገኒይ» (ሀብታም / የተብቃቃ):-
«ሀብት/መብቃቃት» በሚለው ትርጉም ላይ በሁለት አቅጣጫ ገልጸውታል፦
* የነፍስና የቀልብ መብቃቃት (ይህ ይበልጥ ጎላ ያለና ተመራጩ ትርጉም ነው)፦
ባሪያው አላህ በወሰነለት እና በሰጠው ሲሳይ የሚረካ፣ በሰዎች እጅ ካለው ነገር ተብቃቅቶ በአላህ ብቻ የሚብቃቃ፣ ቀልቡ በኢማን እና በየቂን (እርግጠኝነት) የሞላ መሆን ነው። ነቢዩም ﷺ፦ «ولكن الغنى غنى النفس» («እውነተኛ ሀብት ማለት ግን የነፍስ (የቀልብ) መብቃቃት ነው») ብለዋል።
* የገንዘብ ሀብት፦
ይህም ሀብቱን በበጎ አድራጎት፣ በመልካም ሥራዎች እና ሰዎችን በመጥቀም ላይ የሚያውል፣ ሀብቱ ከአላህ እገዛ እንዳይዘናጋው የአላህን ሐቅ እየፈጸመ የሚያመሰግን ሀብታም ነው።
3. «አል-ኸፊይ» (ድብቁ / ራሱን የማያገዝፈው):-
* ዝናን፣ ሥልጣንን እና በምድር ላይ ከፍ ማለትን የማይሻ፣ ይልቁንም ጌታውን በመገዛት፣ የራሱን ጉድለቶች በመመልከት እና ራሱን በማረም ላይ ብቻ የተጠመደ ሰው ማለት ነው።
* በተጨማሪም፦ ፍጹም ለአላህ ብቻ ብሎ ለመስራት (ኢኽላስ) እና ይዩልኝ ስሙልኝን (ሪያእ) በመፍራት መልካም ሥራዎቹንና አምልኮቶቹን (እንደ ድብቅ ሶደቃና የሌሊት ሶላት ያሉትን) ሰው እንዳያይበት የሚደብቅ ሰውም በዚህ ውስጥ ይካተታል።
||
(ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 04/1448)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሰዎች ህይወት እና ንብረት በሌላው ላይ ሐራም ነው!
~
ከአቡ በክረህ (አላህ ይውደድላቸው) ተይዞ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
" إِنَّ دِمَاءَكُمْ وَأَمْوَالَكُمْ وَأَعْرَاضَكُمْ بَيْنَكُمْ حَرَامٌ كَحُرْمَةِ يَوْمِكُمْ هَذَا، فِي شَهْرِكُمْ هَذَا، فِي بَلَدِكُمْ هَذَا "
“ደማችሁ (ሕይወታችሁ)፣ ንብረታችሁ እና ክብራችሁ በእናንተ ላይ እርም (የተከለከለ) ነው፤ ልክ በዚህ ወራችሁ እና በዚህ አገራችሁ ውስጥ ይሄ ቀናችሁ እንዳለው ክብር።”
[ቡኻሪይ (39) ከዘገቡት ሐዲሥ የተወሰደ ነው። ሙስሊምም (2816) ዘግበውታል።]
* ቡኻሪይ (7078) ውስጥ በሚገኝ ሌላ ዘገባ ደግሞ እንዲህ የሚል አለ፦
" وَأَبْشَارَكُمْ، عَلَيْكُمْ حَرَامٌ كَحُرْمَةِ يَوْمِكُمْ هَذَا "
“አካሎቻችሁም እንዲሁ እንደዚህ ቀናችሁ ክብር የተከበሩ ናቸው።”
* በተጨማሪም ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
" لَا تَرْجِعُوا بَعْدِي كُفَّارًا، يَضْرِبُ بَعْضُكُمْ رِقَابَ بَعْضٍ "
“ከኔ በኋላ ከፊላችሁ የከፊሉ አንገት የሚሰይፍ ከሃዲዎች ሆናችሁ አትመለሱ።” [ቡኻሪይ (67 እና 7078] እና ሙስሊም (1679) ዘግበውታል።]
የቃላት መፍቻ፦
=
1. “ይሄ ቀናችሁ” የተባለው ዙልሒጃ አስር ሲሆን የዒደል አድሓ የመጀመሪያው ቀን ነው።
2. “በዚህ ወራችሁ” የተባለው የተከበረው የዙልሒጃ ወር ነው።
3. “በዚህ ሃገራችሁ” የተባለው የተከበረው የአላህ ቤት፣ የተከበረችዋ መካ ለማለት ነው።
ከሐዲሡ የሚወሰዱ ትምህርቶች፦
=
1. የሙስሊሞች ደም ፈፅሞ ሊደፈር የማይገባው እርም እንዲሁም በጣም የተከበረ እንደሆነ፣
2. የሰዎችን ንብረትና ክብር መዳፈር ክልክል እንደሆነ እና
3. የሙስሊም ደሙ፣ ንብረቱ እና ክብሩ ከተከበረው ሃገር፣ ከተከበረው ወር እና ከተከበረው ቀን ክብር በላይ እንደሆነ እንወስዳለን።
ዐብዱላህ ብኑ ዐምር ብኒል ዓስ (አላህ ይውደድላቸው) ባስተላለፉት ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
" وَالَّذِي نَفْسِي بِيَدِهِ لَقَتْلُ مُؤْمِنٍ أَعْظَمُ عِنْدَ اللهِ مِنْ زَوَالِ الدُّنْيَا "
“ነፍሴ በእጁ በሆነችው (ጌታዬ) እምላለሁ! አንድን አማኝ መግደል አላህ ዘንድ ከድፍን ዓለም መጥፋት የከፋ ነው።” [ነሳኢይ (3986) ዘግበውታል።]
* ሙስሊም ያልሆኑ አካላትም እንዲሁ ሊበደሉ አይገባም። ይህንን የሚመለከት ማስረጃ ሌላ ጊዜ አቀርባለሁ፣ ኢንሻአላህ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
~
ከአቡ በክረህ (አላህ ይውደድላቸው) ተይዞ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
" إِنَّ دِمَاءَكُمْ وَأَمْوَالَكُمْ وَأَعْرَاضَكُمْ بَيْنَكُمْ حَرَامٌ كَحُرْمَةِ يَوْمِكُمْ هَذَا، فِي شَهْرِكُمْ هَذَا، فِي بَلَدِكُمْ هَذَا "
“ደማችሁ (ሕይወታችሁ)፣ ንብረታችሁ እና ክብራችሁ በእናንተ ላይ እርም (የተከለከለ) ነው፤ ልክ በዚህ ወራችሁ እና በዚህ አገራችሁ ውስጥ ይሄ ቀናችሁ እንዳለው ክብር።”
[ቡኻሪይ (39) ከዘገቡት ሐዲሥ የተወሰደ ነው። ሙስሊምም (2816) ዘግበውታል።]
* ቡኻሪይ (7078) ውስጥ በሚገኝ ሌላ ዘገባ ደግሞ እንዲህ የሚል አለ፦
" وَأَبْشَارَكُمْ، عَلَيْكُمْ حَرَامٌ كَحُرْمَةِ يَوْمِكُمْ هَذَا "
“አካሎቻችሁም እንዲሁ እንደዚህ ቀናችሁ ክብር የተከበሩ ናቸው።”
* በተጨማሪም ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
" لَا تَرْجِعُوا بَعْدِي كُفَّارًا، يَضْرِبُ بَعْضُكُمْ رِقَابَ بَعْضٍ "
“ከኔ በኋላ ከፊላችሁ የከፊሉ አንገት የሚሰይፍ ከሃዲዎች ሆናችሁ አትመለሱ።” [ቡኻሪይ (67 እና 7078] እና ሙስሊም (1679) ዘግበውታል።]
የቃላት መፍቻ፦
=
1. “ይሄ ቀናችሁ” የተባለው ዙልሒጃ አስር ሲሆን የዒደል አድሓ የመጀመሪያው ቀን ነው።
2. “በዚህ ወራችሁ” የተባለው የተከበረው የዙልሒጃ ወር ነው።
3. “በዚህ ሃገራችሁ” የተባለው የተከበረው የአላህ ቤት፣ የተከበረችዋ መካ ለማለት ነው።
ከሐዲሡ የሚወሰዱ ትምህርቶች፦
=
1. የሙስሊሞች ደም ፈፅሞ ሊደፈር የማይገባው እርም እንዲሁም በጣም የተከበረ እንደሆነ፣
2. የሰዎችን ንብረትና ክብር መዳፈር ክልክል እንደሆነ እና
3. የሙስሊም ደሙ፣ ንብረቱ እና ክብሩ ከተከበረው ሃገር፣ ከተከበረው ወር እና ከተከበረው ቀን ክብር በላይ እንደሆነ እንወስዳለን።
ዐብዱላህ ብኑ ዐምር ብኒል ዓስ (አላህ ይውደድላቸው) ባስተላለፉት ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
" وَالَّذِي نَفْسِي بِيَدِهِ لَقَتْلُ مُؤْمِنٍ أَعْظَمُ عِنْدَ اللهِ مِنْ زَوَالِ الدُّنْيَا "
“ነፍሴ በእጁ በሆነችው (ጌታዬ) እምላለሁ! አንድን አማኝ መግደል አላህ ዘንድ ከድፍን ዓለም መጥፋት የከፋ ነው።” [ነሳኢይ (3986) ዘግበውታል።]
* ሙስሊም ያልሆኑ አካላትም እንዲሁ ሊበደሉ አይገባም። ይህንን የሚመለከት ማስረጃ ሌላ ጊዜ አቀርባለሁ፣ ኢንሻአላህ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor