Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አሳሳቢ የክረምት መልእክቶች
~
1. ልጆች የተሻለ ሰፊ ጊዜ የሚያገኙበት ጊዜ እንደመሆኑ ቁርኣን እንዲቀሩ፣ ኪታቦችን እንዲማሩ መስራት ይገባል።
2. በቅጡ የሚለበስ የሌላቸው ወገኖችን በዚህ በብርድ ወቅት ካለን ብናካፍል ትልቅ ሶደቃ ነው።
3. በየጎዳናውና ጉሊቱ ትናንሽ ነገሮችን ለመሸጥ ኩርምት ብለው የተቀመጡ እናቶችን የያዙትን በመግዛት፣ ከተቻለ ከዚያም አለፍ ብሎ ማገዝ ብዙ ሰዎች የሚዘነጉት ሶደቃ ነው።
4. ለቀጣይ የትምህርት ዓመት አቅመ ደካማ ተማሪዎችን በማሰብ ያለፉ ተማሪዎችን የደምብ ልብሶች (ዩኒፎርም) መሰብሰብ እና አስተባብሮ ደብተር በመግዛት ላይ በየአካባቢው ብንረባረብ ትልቅ ስራ ነው። አገሩን የሚወድ አገር ተረካቢ ትውልድ ላይ ይሰራል።
5. ብዙ የሀገራችን አካባቢዎች በዚህ ክረምት ዝናብ በመጥፋቱ ህዝብ ጭንቅ ላይ ነው። አጥብቀን ዱዓእ እናድርግ።
6. ዝናብ ባለበት አካባቢ ያላችሁ ኢማሞችና ኸጢቦች በሶላታችሁም፣ በኹጥባችሁም ታዳሚውን እያሰባችሁ፣ ወቅቱን እያገናዘባችሁ ፈጽሙ። በናንተ ያፈፃፀም ችግር ሰው ዝናብ እንዳይመታው ተጠንቀቁ። ከላይ የተዘረዘሩትን ነጥቦች እና መሰል ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ለማህበረሰብ ግንዛቤ ስጡ። ኹጥባ ማለት ማህበረሰብን መቀየሪያ ሁነኛ መድረክ ነውና እየተጠቀማችሁበት መሆናችሁን ገምግሙ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
~
1. ልጆች የተሻለ ሰፊ ጊዜ የሚያገኙበት ጊዜ እንደመሆኑ ቁርኣን እንዲቀሩ፣ ኪታቦችን እንዲማሩ መስራት ይገባል።
2. በቅጡ የሚለበስ የሌላቸው ወገኖችን በዚህ በብርድ ወቅት ካለን ብናካፍል ትልቅ ሶደቃ ነው።
3. በየጎዳናውና ጉሊቱ ትናንሽ ነገሮችን ለመሸጥ ኩርምት ብለው የተቀመጡ እናቶችን የያዙትን በመግዛት፣ ከተቻለ ከዚያም አለፍ ብሎ ማገዝ ብዙ ሰዎች የሚዘነጉት ሶደቃ ነው።
4. ለቀጣይ የትምህርት ዓመት አቅመ ደካማ ተማሪዎችን በማሰብ ያለፉ ተማሪዎችን የደምብ ልብሶች (ዩኒፎርም) መሰብሰብ እና አስተባብሮ ደብተር በመግዛት ላይ በየአካባቢው ብንረባረብ ትልቅ ስራ ነው። አገሩን የሚወድ አገር ተረካቢ ትውልድ ላይ ይሰራል።
5. ብዙ የሀገራችን አካባቢዎች በዚህ ክረምት ዝናብ በመጥፋቱ ህዝብ ጭንቅ ላይ ነው። አጥብቀን ዱዓእ እናድርግ።
6. ዝናብ ባለበት አካባቢ ያላችሁ ኢማሞችና ኸጢቦች በሶላታችሁም፣ በኹጥባችሁም ታዳሚውን እያሰባችሁ፣ ወቅቱን እያገናዘባችሁ ፈጽሙ። በናንተ ያፈፃፀም ችግር ሰው ዝናብ እንዳይመታው ተጠንቀቁ። ከላይ የተዘረዘሩትን ነጥቦች እና መሰል ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ለማህበረሰብ ግንዛቤ ስጡ። ኹጥባ ማለት ማህበረሰብን መቀየሪያ ሁነኛ መድረክ ነውና እየተጠቀማችሁበት መሆናችሁን ገምግሙ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ያ ሁሉ ወጣት እንደ ቅጠል ረግፎ፣ ካለፈው ከደረሰው እንደ መማር ዛሬም ጠበንጃ መወልወል አሳዛኝ ነገር ነው። ክፉ ልክፍት! ደም የማይጠግብ አእምሮ!! የወጣቶች በአጭር መቀጨት፣ የእናቶች በሀዘን መሰበር፣ የአዛውንቶች ያለ ጧሪ ቀባሪ መቅረት፣ የሃገር መቆርቆዝ የማያስደነግጠው ልብ ከጠላት በላይ ጨካኝ ነው። ሰው ሌሎች ላይ ከደረሰው፣ ከጎረቤቱ ይማራል። እሱ ቢቀር እንዴት በራስ ላይ ከደረሰው መማር ያቅታል?!
ለማንኛውም ወጣት ሆይ! ለራስህ እወቅበት። በስምህ የሚምለው ሁሉ ተቆርቁሮልህ እንዳይመስልህ። ጀግና ጀግና የሚልህ ጀግና ስለሆንክ አይደለም። እየሸነገለህ ነው። ራሱንም ቤተሰቡንም ከእሳቱ አርቆ ነው አንተን የሚማግደው። ካንተ ሞት በኋላ ልጅህን፣ እናትህን ዞሮ አያይም። ግፋ ቢል ነገ ካንተ ሞት በኋላ የሰማእታት ሀውልት ብሎ የድንጋይ ክምር ቢያቆምልህ ነው። ይሄ ላንተም ለቤተሰብህም የሚጠቅመው ነገር የለም። ህዝብ ማደንዘዣ፣ ሌላ እልቂት ማቀጣጠያ እንጂ የሚፈይደው አንዳች ነገር የለም። ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
ለማንኛውም ወጣት ሆይ! ለራስህ እወቅበት። በስምህ የሚምለው ሁሉ ተቆርቁሮልህ እንዳይመስልህ። ጀግና ጀግና የሚልህ ጀግና ስለሆንክ አይደለም። እየሸነገለህ ነው። ራሱንም ቤተሰቡንም ከእሳቱ አርቆ ነው አንተን የሚማግደው። ካንተ ሞት በኋላ ልጅህን፣ እናትህን ዞሮ አያይም። ግፋ ቢል ነገ ካንተ ሞት በኋላ የሰማእታት ሀውልት ብሎ የድንጋይ ክምር ቢያቆምልህ ነው። ይሄ ላንተም ለቤተሰብህም የሚጠቅመው ነገር የለም። ህዝብ ማደንዘዣ፣ ሌላ እልቂት ማቀጣጠያ እንጂ የሚፈይደው አንዳች ነገር የለም። ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Forwarded from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
ልብህን ለማን እንደምትሰጥ እወቅ!
የዱኑያ ምሽት ላይ እንደመሆናችንና የመሲሐድ'ደጃል መምጫም እንደመቃረቡ ዲኑ ላይ የሚጫወቱና እራሳቸው ተደናብረው ኡማውን የሚያደናብሩ ሰዎች በዝተዋል።
ማህበራዊ ሚዲያውም የራሱ ጥሩ ጎን እንዳለው ሁሉ ሰዎችን ማሳሳትና ግራ ማጋባት ላይ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል።
መችና ከማን የሸሪዓህ እውቀት እንደተማሩ የማይታወቅ ሰዎች በካሜራ (በስልክና ኮምፒዩተር) መስኮት ብቅ እያሉ የፈለጉትን ሐላል፣ የፈለጉትን ሐራም ብለው ያለ በቂ እውቀት በስሜትና በግምት በመናገር ብዙ አላዋቂዎችን ያሳስታሉ።
ከዚህም አልፎ ገና አዲስ ወደ ኢስላም የገቡ ወንድምና እህቶች እራሳቸው እንኳ ዲኑን በትክክልና በጥልቀት ሳይረዱ መደበኛ አስተማሪ ሆነው ቀርበው ኢስላምና ሙስሊሞችን ወክለው ሲናገሩና ሲከራከሩም ይታያል !!
ይህ በጣም ይገርማል፤ ያሳዝናልም! ይበልጥ የሚገርመው ደግሞ እንደዚህ ዓይነት ሰዎችን እንደ ትልቅ አዋቂ ቆጥረው የሚከተሏቸውና ልባቸውን የሚሰጧቸው ሰዎች ሁኔታ ነው!!
ኢስላማዊ እውቀት የዲኑ/የእምነቱ አንድ አካል ነው፤ ከኔ ይሻላል ከሚሉት ሁሉ (ከየትም፣ ከማንም) እውቀትን ዝም ብሎ መቀበል እምነትን ሊያበላሽ፣ ማንነትና አስተሳሰብን ሊቀይር ይችላልና
ምላስና ድፍረት ስላለው ብቻ ራሱን በራሱ ጊዜ አስተማሪ አድርጎ የቀረበን ሁሉ ከመስማትና ከመከተል እንጠንቀቅ!!
ለአካላዊ ጤናችን ሃኪም ከምንመርጠው በላይ ለልብና ለእምነታችን መሪና መካሪ እንምረጥ።
ትልቁ መሲሐድ'ደጃል ከመምጣቱ በፊት ለሱ መንገድ የሚያመቻቹ ብዙ ትናንሽ ደጃሎች እንዳሉ ተነግሯል።
ቂያማ ሲቃረብ ሸይጣን በሰው ተመስሎ አስተማሪ ሆኖ እንደሚቀርብም ተገልጿልና ልብህን ለማን እንዳምትሰጥ/ጪ፣ የሸሪዓህ እውቀትን ከማን እንደምትቀስም/ሚ ጠንቅቀህ/ሽ እወቅ/ቂ።
የሸሪዓህ እውቀትን ከምንጩ ያልወሰደና በዑለሞች ያልተመሰከረለት የዩቱበር፣ የቲክቶከርና ፌስቡከር ... መጫወቻ እንዳትሆን/ኚ!!
ኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም
ዛዱል-መዓድ
©: ኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም
የዱኑያ ምሽት ላይ እንደመሆናችንና የመሲሐድ'ደጃል መምጫም እንደመቃረቡ ዲኑ ላይ የሚጫወቱና እራሳቸው ተደናብረው ኡማውን የሚያደናብሩ ሰዎች በዝተዋል።
ማህበራዊ ሚዲያውም የራሱ ጥሩ ጎን እንዳለው ሁሉ ሰዎችን ማሳሳትና ግራ ማጋባት ላይ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል።
መችና ከማን የሸሪዓህ እውቀት እንደተማሩ የማይታወቅ ሰዎች በካሜራ (በስልክና ኮምፒዩተር) መስኮት ብቅ እያሉ የፈለጉትን ሐላል፣ የፈለጉትን ሐራም ብለው ያለ በቂ እውቀት በስሜትና በግምት በመናገር ብዙ አላዋቂዎችን ያሳስታሉ።
ከዚህም አልፎ ገና አዲስ ወደ ኢስላም የገቡ ወንድምና እህቶች እራሳቸው እንኳ ዲኑን በትክክልና በጥልቀት ሳይረዱ መደበኛ አስተማሪ ሆነው ቀርበው ኢስላምና ሙስሊሞችን ወክለው ሲናገሩና ሲከራከሩም ይታያል !!
ይህ በጣም ይገርማል፤ ያሳዝናልም! ይበልጥ የሚገርመው ደግሞ እንደዚህ ዓይነት ሰዎችን እንደ ትልቅ አዋቂ ቆጥረው የሚከተሏቸውና ልባቸውን የሚሰጧቸው ሰዎች ሁኔታ ነው!!
ኢስላማዊ እውቀት የዲኑ/የእምነቱ አንድ አካል ነው፤ ከኔ ይሻላል ከሚሉት ሁሉ (ከየትም፣ ከማንም) እውቀትን ዝም ብሎ መቀበል እምነትን ሊያበላሽ፣ ማንነትና አስተሳሰብን ሊቀይር ይችላልና
ምላስና ድፍረት ስላለው ብቻ ራሱን በራሱ ጊዜ አስተማሪ አድርጎ የቀረበን ሁሉ ከመስማትና ከመከተል እንጠንቀቅ!!
ለአካላዊ ጤናችን ሃኪም ከምንመርጠው በላይ ለልብና ለእምነታችን መሪና መካሪ እንምረጥ።
ትልቁ መሲሐድ'ደጃል ከመምጣቱ በፊት ለሱ መንገድ የሚያመቻቹ ብዙ ትናንሽ ደጃሎች እንዳሉ ተነግሯል።
ቂያማ ሲቃረብ ሸይጣን በሰው ተመስሎ አስተማሪ ሆኖ እንደሚቀርብም ተገልጿልና ልብህን ለማን እንዳምትሰጥ/ጪ፣ የሸሪዓህ እውቀትን ከማን እንደምትቀስም/ሚ ጠንቅቀህ/ሽ እወቅ/ቂ።
የሸሪዓህ እውቀትን ከምንጩ ያልወሰደና በዑለሞች ያልተመሰከረለት የዩቱበር፣ የቲክቶከርና ፌስቡከር ... መጫወቻ እንዳትሆን/ኚ!!
ኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም
ዛዱል-መዓድ
©: ኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
መውሊድ ለምን አላማ እንደተጀመረ ያውቃሉ?
~
መውሊድ በሺዐዎች እንደተጀመረ ቀደም ብየ ገልጬ ነበር። አሁን ደግሞ ለምን አላማ ጀመሩት የሚለውን ባጭሩ እዳስሳለሁ።
በግብፅ የአስዩጥ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት የነበሩት ዶክተር ሐሰን ኢብራሂም ሐሰን እና በሃገሪቱ የትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ትምህርቶች ገምጋሚ የነበሩት ጦሀ አሕመድ ሸረፍ በጋራ በመሆን “አልሙዒዝ ሊዲኒላህ” በሚል ርእስ ስለ“ፋጢሚያዎቹ” ንጉስ ጥልቅ ጥናት በማድረግ አንድ መፅሐፍ አዘጋጅተዋል፡፡ በዚህ መፅሐፍ ውስጥ “አውደ - አመታት እና በዓላት” በሚል ርእስ ስር ያሰፈሩት ሃሳብ “መውሊድ ለምን አላማ ታስቦ ነው የተጀመረው?” ለሚለው ጥያቄ ጥሩ ምላሽ ይሰጣል፡፡ እንዲህ ነበር ያሉት፡-
“(ንጉሱ) አልሙዒዝ በሂጅራ አቆጣጠር የመጀመሪያው ቀን፣ በነብዩ ﷺ መውሊድ ቀን፣ በረጀብ መጀመሪያና አጋማሽ ላይ፣ በሸዕባን መጀመሪያና አጋማሽ ላይ፣ በረመዷን መጀመሪያ ቀን ከሚያስተዳድራቸው ህዝቦች ጋር ይካፈል ነበር፡፡ ይህን የሚያደርገው
* የሱኒ፞ዮቹን ልብ ለማረጋጋት፣
* እንዲሁም በሱኒ፞ዮች መርሆዎችና በሺዐዎች እምነቶች መካከል ያለውን ርቀት ለማጥበብ በማሰብ ነው፡፡
* በተጨማሪም ይሄ አልሙኢዝ ሊዲኒላ፞ህ የንግስና ዘመኑን ያሸበረቀባቸውን እነዚህን በዓላት የኢስማዒሊያ ሺዐ መዝሀብ እምነቶችን ለማሰራጨት ይጠቀምባቸው ነበር፡፡ ለዚህም ነበር የሑሰይንን ዝክር ህያው ለማድረግ የዓሹራእ ቀንን ያከብር የነበረው፡፡ ልክ እንዲሁ የበርካታ አኢማዎችን መውሊድና ስልጣን ላይ ያለውን ገዢ መውሊድ በሚልም (የራሱን ልደት) ያከብር ነበር፡፡
* ልክ በዚህ መልኩ የህዝቦቹን ትኩረት ወደሱ ለመሳብና የኢስማዒሊያ ሺዐ መዝሀብ መሰረታዊ እምነቶችን ለማሰራጨት እነዚህን በዓላት እንደ መዳረሻ ይጠቀምባቸው ነበር፡፡” [አልሙዒዝ ሊዲኒ'ላህ፡ 284]
ስለዚህ መውሊድ የተጀመረው ለፖለቲካዊ ትርፍና የሺዐን እምነት ለማስፋፋት ዓላማ ነው ማለት ነው፡፡ የክርስቲያኖቹ ገና፞፣ ሁዳዴ፣ …፣ የሺዐዎቹ የዓሹራእ በዓል፣ ገዲር ኹም፣ …፣ የእሳት አምላኪ መጁሳዎቹ ነይሩዝ ይከበሩ ከነበሩት በዓላት ውስጥ ነበሩ፡፡ የህዝብን ትኩረት ለመሳብ፣ ቅሬታ ውስጥ ያሉ ሱኒ፞ዮችን ልብ ለማረጋጋት በሂደትም ወደራሱ የሺዐ እምነት ሰዎችን ለማስገባት በማለም ነው፡፡ ቀስ እያለ በጉልበት ወደ ሺዐ እምነት መጣራት እንደተጀመረ ይታወስ፡፡ ስለዚህ አላማቸው ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚመጡትን የህዝብ ግፊቶች በማርገብ ይከተሉት የነበሩትን የኢስማዒሊያ ሺዐ እምነት ማስፋፋት ነበር፡፡ ይሄ ደግሞ ዛሬ ሱፍዮች እንደሚያስቡት “የወሃብዮች” ፕሮፓጋንዳ ሳይሆን ከላይ እንዳየነው የታሪክ አጥኚዎች ድምዳሜ ነው፡፡
የመውሊድ ስርኣቱ ለእኩይ አላማ የታለመ ስለነበርም ነው ሶላሑዲን አልአዩቢይ ሺ0ዎችን አስወግዶ ግብፅን ሲቆጣጠር አስቁሞት የነበረው፡፡ መቼም እሱንም “ወሃቢ ነው” እንደማትሉ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ዳግም የተጀመረው ኋላ በመምሉካውያን ጊዜ ነው፡፡ የመውሊድ ተግባር እንደገና ሲመለስ ሌሎቹ በአላት የሌላ እምነት መሰረት ያላቸው ወይም ሺዐ-ዘመም ስለነበሩ በሱኒ፞ው አለም ገበያ አላገኙም፡፡
ዛሬም የሙስሊሞችን መብት የሚጨፈልቁ የፖለቲካ ኃይሎች አጉል ተቆርቋሪ ሊመስሉ ለመውሊድ የተለየ ሸፋንና ድጋፍ ሲሰጡ ማየት የተለመደ ነው። ብልጥ የሆነ ሰው ሊያስተውል ይገባል። አላህ ማስተዋሉን ይስጠን።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
~
መውሊድ በሺዐዎች እንደተጀመረ ቀደም ብየ ገልጬ ነበር። አሁን ደግሞ ለምን አላማ ጀመሩት የሚለውን ባጭሩ እዳስሳለሁ።
በግብፅ የአስዩጥ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት የነበሩት ዶክተር ሐሰን ኢብራሂም ሐሰን እና በሃገሪቱ የትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ትምህርቶች ገምጋሚ የነበሩት ጦሀ አሕመድ ሸረፍ በጋራ በመሆን “አልሙዒዝ ሊዲኒላህ” በሚል ርእስ ስለ“ፋጢሚያዎቹ” ንጉስ ጥልቅ ጥናት በማድረግ አንድ መፅሐፍ አዘጋጅተዋል፡፡ በዚህ መፅሐፍ ውስጥ “አውደ - አመታት እና በዓላት” በሚል ርእስ ስር ያሰፈሩት ሃሳብ “መውሊድ ለምን አላማ ታስቦ ነው የተጀመረው?” ለሚለው ጥያቄ ጥሩ ምላሽ ይሰጣል፡፡ እንዲህ ነበር ያሉት፡-
“(ንጉሱ) አልሙዒዝ በሂጅራ አቆጣጠር የመጀመሪያው ቀን፣ በነብዩ ﷺ መውሊድ ቀን፣ በረጀብ መጀመሪያና አጋማሽ ላይ፣ በሸዕባን መጀመሪያና አጋማሽ ላይ፣ በረመዷን መጀመሪያ ቀን ከሚያስተዳድራቸው ህዝቦች ጋር ይካፈል ነበር፡፡ ይህን የሚያደርገው
* የሱኒ፞ዮቹን ልብ ለማረጋጋት፣
* እንዲሁም በሱኒ፞ዮች መርሆዎችና በሺዐዎች እምነቶች መካከል ያለውን ርቀት ለማጥበብ በማሰብ ነው፡፡
* በተጨማሪም ይሄ አልሙኢዝ ሊዲኒላ፞ህ የንግስና ዘመኑን ያሸበረቀባቸውን እነዚህን በዓላት የኢስማዒሊያ ሺዐ መዝሀብ እምነቶችን ለማሰራጨት ይጠቀምባቸው ነበር፡፡ ለዚህም ነበር የሑሰይንን ዝክር ህያው ለማድረግ የዓሹራእ ቀንን ያከብር የነበረው፡፡ ልክ እንዲሁ የበርካታ አኢማዎችን መውሊድና ስልጣን ላይ ያለውን ገዢ መውሊድ በሚልም (የራሱን ልደት) ያከብር ነበር፡፡
* ልክ በዚህ መልኩ የህዝቦቹን ትኩረት ወደሱ ለመሳብና የኢስማዒሊያ ሺዐ መዝሀብ መሰረታዊ እምነቶችን ለማሰራጨት እነዚህን በዓላት እንደ መዳረሻ ይጠቀምባቸው ነበር፡፡” [አልሙዒዝ ሊዲኒ'ላህ፡ 284]
ስለዚህ መውሊድ የተጀመረው ለፖለቲካዊ ትርፍና የሺዐን እምነት ለማስፋፋት ዓላማ ነው ማለት ነው፡፡ የክርስቲያኖቹ ገና፞፣ ሁዳዴ፣ …፣ የሺዐዎቹ የዓሹራእ በዓል፣ ገዲር ኹም፣ …፣ የእሳት አምላኪ መጁሳዎቹ ነይሩዝ ይከበሩ ከነበሩት በዓላት ውስጥ ነበሩ፡፡ የህዝብን ትኩረት ለመሳብ፣ ቅሬታ ውስጥ ያሉ ሱኒ፞ዮችን ልብ ለማረጋጋት በሂደትም ወደራሱ የሺዐ እምነት ሰዎችን ለማስገባት በማለም ነው፡፡ ቀስ እያለ በጉልበት ወደ ሺዐ እምነት መጣራት እንደተጀመረ ይታወስ፡፡ ስለዚህ አላማቸው ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚመጡትን የህዝብ ግፊቶች በማርገብ ይከተሉት የነበሩትን የኢስማዒሊያ ሺዐ እምነት ማስፋፋት ነበር፡፡ ይሄ ደግሞ ዛሬ ሱፍዮች እንደሚያስቡት “የወሃብዮች” ፕሮፓጋንዳ ሳይሆን ከላይ እንዳየነው የታሪክ አጥኚዎች ድምዳሜ ነው፡፡
የመውሊድ ስርኣቱ ለእኩይ አላማ የታለመ ስለነበርም ነው ሶላሑዲን አልአዩቢይ ሺ0ዎችን አስወግዶ ግብፅን ሲቆጣጠር አስቁሞት የነበረው፡፡ መቼም እሱንም “ወሃቢ ነው” እንደማትሉ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ዳግም የተጀመረው ኋላ በመምሉካውያን ጊዜ ነው፡፡ የመውሊድ ተግባር እንደገና ሲመለስ ሌሎቹ በአላት የሌላ እምነት መሰረት ያላቸው ወይም ሺዐ-ዘመም ስለነበሩ በሱኒ፞ው አለም ገበያ አላገኙም፡፡
ዛሬም የሙስሊሞችን መብት የሚጨፈልቁ የፖለቲካ ኃይሎች አጉል ተቆርቋሪ ሊመስሉ ለመውሊድ የተለየ ሸፋንና ድጋፍ ሲሰጡ ማየት የተለመደ ነው። ብልጥ የሆነ ሰው ሊያስተውል ይገባል። አላህ ማስተዋሉን ይስጠን።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
❤1
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ከፊሉ ልጅ የለኝም ብሎ ያለቅሳል። ሌላውን ልጁ ያስለቅሰዋል።
ከፊሉ እህት ወንድም የለኝም ብሎ ይከፋዋል። ሌላው በእህት በወንድሞቹ ውስጡ ቆስሏል።
ዱንያ አጃዒቧ አያልቅም። ግማሹ በመከራ፣ ሌላው በጥጋብ ያለቅሳል። "እናቱ የሞተችበትና፣ ገበያ የሄደችበት እኩል ያለቅሳል" በሚለው አገርኛ ብሂል ውስጥ ህመም አለ። መከራ ሁሉ አንድ አይደለም። ከባሰም በላይ ብዙ የባሰ እንዳለ በማስተዋል "አልሐምዱ ሊላህ" እንበል።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
ከፊሉ እህት ወንድም የለኝም ብሎ ይከፋዋል። ሌላው በእህት በወንድሞቹ ውስጡ ቆስሏል።
ዱንያ አጃዒቧ አያልቅም። ግማሹ በመከራ፣ ሌላው በጥጋብ ያለቅሳል። "እናቱ የሞተችበትና፣ ገበያ የሄደችበት እኩል ያለቅሳል" በሚለው አገርኛ ብሂል ውስጥ ህመም አለ። መከራ ሁሉ አንድ አይደለም። ከባሰም በላይ ብዙ የባሰ እንዳለ በማስተዋል "አልሐምዱ ሊላህ" እንበል።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የማለዳ መልእክት (45)
ለኸጢቦች እና ለዱዓቶች
~
የደዕዋ እና የኹጥባ መድረክ የነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መድረክ ነው። የማህበረሰብን ንቃተ ህሊና ለመቀየር፣ ዲኑን ለማስተማር፣ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለማንቃት እጅግ የላቀ ቦታ ነው። ግን እንደሚገባ እየተጠቀምነው ነው ወይ? መድረኩ ነብያዊ አማና ነውና አማናውን እየተወጣን ነው ወይ? ለመድረኩ የሚመጥን አቅምና ዝግጅትስ አለን ወይ? ሐቅን ለመናገር፣ ማህበረሰብን ለመጠበቅ የሰዎችን ስሜትና ፍላጎታቸውን ተከትለን ነው የምንፈሰው ወይስ አላህን በማሰብ፣ ለሐቅ በመቆርቆር፣ ዘላቂ ጥቅምን በማስቀደም በጀግንነት እንጓዛለን? ኃላፊነትን ባለመወጣት ከመጠየቃችን በፊት ከራሳችን ጋር ሂሳብ እንስራ።
1. ወደ ህዝብ ከመቅረባችን በፊት በቂ ዝግጅት እናድርግ፣ አቅማችንን እናዳብር። ሳይዘጋጁ መቅረብ ታዳሚን መናቅ ነው። ቦታውንም ክብር ማሳጣት ነው።
2. መሰረታዊ የኢስላም ርእሶችን ቅድሚያ እንስጥ። አርካኑል ኢማን፣ አርካኑል ኢስላም፣ ተውሒድና ሺርክ፣ ሱናና ቢድዐ፣ ከባኢረ ዙኑብ፣ ስነ ምግባር፣ ኢስላማዊ ቤተሰብ፣ እንደ ኡማ ሊኖረን የሚገባ መተዛዘንና መደጋገፍ፣ ዘረኝነት፣ እንደ ጫትና ሲጋራ ያሉ ጎጂ ሱሶች፣ ወዘተ. የህዝብን ቁጣና ኩርፊያ ሳንፈራ ግን ደግሞ ባማረና በማያስበረግግ መልኩ ደጋግመን እናስተምር።
3. ርእስ መረጣ ላይ የሰዎችን ስሜትና ፍላጎት እየተከተልን አንፍሰስ። ትኩረታችን የሚጠቅማቸውን መስጠት ይሁን። ደዕዋ ሰው መለወጫ እንጂ መዝናኛ መድረክ አይደለም። የሰዎችን ስሜትና ፍላጎት እየተከተለ የሚፈስ አስተማሪ ፈሪና አስመሳይ እንጂ እውነተኛ ተቆርቋሪ አይደለም።
4. እንደ ዘመን በህዝብ ላይ የተጋረጡ አደጋዎች እና ወቅታዊ ክስተቶች ሲኖሩ አቅጣጫ መስጠት ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ በቂ ንቃትና ዝግጅት ይፈልጋል። ንቃትና ዝግጅት ማለት እንግሊዝኛ መቀላቀል አይደለም። በሚዲያ የሰማነውን ዜና ማስተጋባትም አይደለም። የዳዒ ኃላፊነት እንደ ጋዜጠኛ ክስተቶችን ማንልበልና መተንተን አይደለም። መድረኮችን የፖለቲካ መደስኮሪያ እያደረጉ ማርከስ ንቃት አይደለም። ከዳዒ የሚጠበቀው ነገሮችን በኢስላም መነፅር በመመልከት ህዝብን ማረጋጋት፣ ሰዎችን ወደ አላህ መመለስ፣ በወቅታዊ ክስተቶች ከአቅማቸው በላይ በመግባት እንዳይዋጡ ማሳሰብ ነው።
እንዳጠቃላይ ለመድረኩ የሚመጥን ትኩረት እንስጥ፤ አቅም እናዳብር፤ ዝግጅት እናድርግ፤ ጀግንነትን እንላበስ፤ ሐቀኛ ተቆርቋሪነትን ሁሌም እናስብ። ሰላም።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሶፈር 30/1448)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
ለኸጢቦች እና ለዱዓቶች
~
የደዕዋ እና የኹጥባ መድረክ የነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መድረክ ነው። የማህበረሰብን ንቃተ ህሊና ለመቀየር፣ ዲኑን ለማስተማር፣ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለማንቃት እጅግ የላቀ ቦታ ነው። ግን እንደሚገባ እየተጠቀምነው ነው ወይ? መድረኩ ነብያዊ አማና ነውና አማናውን እየተወጣን ነው ወይ? ለመድረኩ የሚመጥን አቅምና ዝግጅትስ አለን ወይ? ሐቅን ለመናገር፣ ማህበረሰብን ለመጠበቅ የሰዎችን ስሜትና ፍላጎታቸውን ተከትለን ነው የምንፈሰው ወይስ አላህን በማሰብ፣ ለሐቅ በመቆርቆር፣ ዘላቂ ጥቅምን በማስቀደም በጀግንነት እንጓዛለን? ኃላፊነትን ባለመወጣት ከመጠየቃችን በፊት ከራሳችን ጋር ሂሳብ እንስራ።
1. ወደ ህዝብ ከመቅረባችን በፊት በቂ ዝግጅት እናድርግ፣ አቅማችንን እናዳብር። ሳይዘጋጁ መቅረብ ታዳሚን መናቅ ነው። ቦታውንም ክብር ማሳጣት ነው።
2. መሰረታዊ የኢስላም ርእሶችን ቅድሚያ እንስጥ። አርካኑል ኢማን፣ አርካኑል ኢስላም፣ ተውሒድና ሺርክ፣ ሱናና ቢድዐ፣ ከባኢረ ዙኑብ፣ ስነ ምግባር፣ ኢስላማዊ ቤተሰብ፣ እንደ ኡማ ሊኖረን የሚገባ መተዛዘንና መደጋገፍ፣ ዘረኝነት፣ እንደ ጫትና ሲጋራ ያሉ ጎጂ ሱሶች፣ ወዘተ. የህዝብን ቁጣና ኩርፊያ ሳንፈራ ግን ደግሞ ባማረና በማያስበረግግ መልኩ ደጋግመን እናስተምር።
3. ርእስ መረጣ ላይ የሰዎችን ስሜትና ፍላጎት እየተከተልን አንፍሰስ። ትኩረታችን የሚጠቅማቸውን መስጠት ይሁን። ደዕዋ ሰው መለወጫ እንጂ መዝናኛ መድረክ አይደለም። የሰዎችን ስሜትና ፍላጎት እየተከተለ የሚፈስ አስተማሪ ፈሪና አስመሳይ እንጂ እውነተኛ ተቆርቋሪ አይደለም።
4. እንደ ዘመን በህዝብ ላይ የተጋረጡ አደጋዎች እና ወቅታዊ ክስተቶች ሲኖሩ አቅጣጫ መስጠት ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ በቂ ንቃትና ዝግጅት ይፈልጋል። ንቃትና ዝግጅት ማለት እንግሊዝኛ መቀላቀል አይደለም። በሚዲያ የሰማነውን ዜና ማስተጋባትም አይደለም። የዳዒ ኃላፊነት እንደ ጋዜጠኛ ክስተቶችን ማንልበልና መተንተን አይደለም። መድረኮችን የፖለቲካ መደስኮሪያ እያደረጉ ማርከስ ንቃት አይደለም። ከዳዒ የሚጠበቀው ነገሮችን በኢስላም መነፅር በመመልከት ህዝብን ማረጋጋት፣ ሰዎችን ወደ አላህ መመለስ፣ በወቅታዊ ክስተቶች ከአቅማቸው በላይ በመግባት እንዳይዋጡ ማሳሰብ ነው።
እንዳጠቃላይ ለመድረኩ የሚመጥን ትኩረት እንስጥ፤ አቅም እናዳብር፤ ዝግጅት እናድርግ፤ ጀግንነትን እንላበስ፤ ሐቀኛ ተቆርቋሪነትን ሁሌም እናስብ። ሰላም።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሶፈር 30/1448)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Forwarded from Kassis Faage
🔴Wakti widirih elle iyyaamal meqe mari gabakalakaay uma mari ambagguk yamaate:
عَنْ مِرْداسٍ الأسْلَمِيِّ رضي الله عنه قالَ قالَ النَّبيُّ ﷺ: يَذْهَبُ الصَّالحُونَ الأوَّلُ فالأولُ، وتَبْقَى حُثَالَةٌ كحُثَالَةِ الشِّعِيرِ أوْ التَّمْرِ، لاَ يُبالِيهمُ اللَّه بالَةً رواه البخاري
Mirdaas Al-aslamiyyi Yalli kaa oggolay, iyyeh : Yallih Nabii(ﷺ) iyyeh: ❝ meqe mari naharsittu naharsittul gexaanaah
(raban) caffali qagurih(casurih) innah, hinnay tamri qagurih innah yan mari keenik
raaqaah, Yalli hebeltô xaagitiyyah ken ma xaagita(Yalli caagid keenit mali)❞ iyye.
[📜 Bukhaari -6434] .
Ta cadiis aaker waktil meqe mari xuguuguluh tii tiya ciggiilak rabaah, ellecaboh caffalik raaqa casurih innah Yallih xaqul tû caddo sinni maray Yalli tuh hangi kah cee waah iyya manguk raaqam neh warisa. Yalli caagid keenit mali yaanam Yallih garil caddo aallewaanaah, uma mara kinnoonum tascasse.
Tah yaanam meqe mari inkinnah mayan yaanam hinna laakin wakti widirih elle iyyaamal kaxxaam daggoowak yamaateeniih, uma mari ambagguk raaqam yascasse.
Ta Cadiisiik lafa le farmo macaay inneh wagitnek: Meqe marih katayyol faxsiisaah, baaxol daggoowan way mangom rabi ken yookomeh gexan way, ken gita katayoona faxximtam kee ken gita sadaanaah Yallih garil burrutume marih loowot gacaanamak takkaawisa.
قال الشيخ ابن عثيمين - رحمه الله - :
( لذلك تجدُ الناسَ يترَدُّون كلَّ عام عن العام الذي قبله.
فيما سبق تجدُ الناس:َ
يتهجَّدون في الليل، ويصومون النهار، ويتصدَّقون من أقواتهم، ويؤثرون على أنفسهم.
أما الآن تجدُ الناسَ تغيروا من سنة إلى أخرى إلى أردى من قبل:
سهرٌ في الليل على غير طاعة الله،
ونوم في النهار أو لهوٌ أو بيعٌ وشراء يشتمل على الغش والكذب والعياذُ بالله.
ومع ذلك يوجدٌ أناسٌ ولله الحمدُ على دينِ اللهِ مستقيمين على ما يبدو، لكنَّ العبرةَ بالعموم والشمول ...
ولذلك يَجِبُ الحذرُ من أن يكونَ الإنسانُ من الحثالةِ التي كحثالةِ الشعير أو التمر،ِ وأن يحرصَ على أمرِ اللهِ حتى لو كان الناسُ قد هلكوا؛ فإنهم إن أصيبوا بالعذابِ العامِّ فإنه يُبعثُ كلُّ إنسانٍ على نيَّتِه يَوْمَ القيامة )
شرح_رياض_الصالحين (٦٣٤/٦)
للشيخ محمد صالح ابن عثيمين رحمه الله
#Join ⤵️⤵️ Telegram channel
https://t.me/Kassisfaage
https://t.me/Kassisfaage
عَنْ مِرْداسٍ الأسْلَمِيِّ رضي الله عنه قالَ قالَ النَّبيُّ ﷺ: يَذْهَبُ الصَّالحُونَ الأوَّلُ فالأولُ، وتَبْقَى حُثَالَةٌ كحُثَالَةِ الشِّعِيرِ أوْ التَّمْرِ، لاَ يُبالِيهمُ اللَّه بالَةً رواه البخاري
Mirdaas Al-aslamiyyi Yalli kaa oggolay, iyyeh : Yallih Nabii(ﷺ) iyyeh: ❝ meqe mari naharsittu naharsittul gexaanaah
(raban) caffali qagurih(casurih) innah, hinnay tamri qagurih innah yan mari keenik
raaqaah, Yalli hebeltô xaagitiyyah ken ma xaagita(Yalli caagid keenit mali)❞ iyye.
[📜 Bukhaari -6434] .
Ta cadiis aaker waktil meqe mari xuguuguluh tii tiya ciggiilak rabaah, ellecaboh caffalik raaqa casurih innah Yallih xaqul tû caddo sinni maray Yalli tuh hangi kah cee waah iyya manguk raaqam neh warisa. Yalli caagid keenit mali yaanam Yallih garil caddo aallewaanaah, uma mara kinnoonum tascasse.
Tah yaanam meqe mari inkinnah mayan yaanam hinna laakin wakti widirih elle iyyaamal kaxxaam daggoowak yamaateeniih, uma mari ambagguk raaqam yascasse.
Ta Cadiisiik lafa le farmo macaay inneh wagitnek: Meqe marih katayyol faxsiisaah, baaxol daggoowan way mangom rabi ken yookomeh gexan way, ken gita katayoona faxximtam kee ken gita sadaanaah Yallih garil burrutume marih loowot gacaanamak takkaawisa.
قال الشيخ ابن عثيمين - رحمه الله - :
( لذلك تجدُ الناسَ يترَدُّون كلَّ عام عن العام الذي قبله.
فيما سبق تجدُ الناس:َ
يتهجَّدون في الليل، ويصومون النهار، ويتصدَّقون من أقواتهم، ويؤثرون على أنفسهم.
أما الآن تجدُ الناسَ تغيروا من سنة إلى أخرى إلى أردى من قبل:
سهرٌ في الليل على غير طاعة الله،
ونوم في النهار أو لهوٌ أو بيعٌ وشراء يشتمل على الغش والكذب والعياذُ بالله.
ومع ذلك يوجدٌ أناسٌ ولله الحمدُ على دينِ اللهِ مستقيمين على ما يبدو، لكنَّ العبرةَ بالعموم والشمول ...
ولذلك يَجِبُ الحذرُ من أن يكونَ الإنسانُ من الحثالةِ التي كحثالةِ الشعير أو التمر،ِ وأن يحرصَ على أمرِ اللهِ حتى لو كان الناسُ قد هلكوا؛ فإنهم إن أصيبوا بالعذابِ العامِّ فإنه يُبعثُ كلُّ إنسانٍ على نيَّتِه يَوْمَ القيامة )
شرح_رياض_الصالحين (٦٣٤/٦)
للشيخ محمد صالح ابن عثيمين رحمه الله
#Join ⤵️⤵️ Telegram channel
https://t.me/Kassisfaage
https://t.me/Kassisfaage
Telegram
Kassis Faage
★Baxaabaxsale diini kassiisitte Qafár afat elle geytoona waytan faage.
Ni faagel arciba!
👉Join us:https://t.me/Kassisfaage
Ni faagel arciba!
👉Join us:https://t.me/Kassisfaage