ታማኝ መረጃ
851 subscribers
1.77K photos
50 videos
108 links
ታማኝ እና አዲስ መረጃዎች ለመግኘት ቻናላችንን ምርጫቹ አድርጉ
Download Telegram
“ህወሃት መስራች መሆኔ የህይወቴ ትልቁ ስህተት ነው” ዶ/ር አረጋዊ በርሀ✔️

“ለዘመናት ትግራይን ያወደመ፤ ለዓመታት ኢትዮጵያዊያን የበላ፣ የከፋፈለ ለብዙ ሰቆቃ ያጋለጠ ህዉሓት የተባለ አረመኔ ድርጅት መስራች መሆኔ ይቆጨኛል ፣ የህይወቴ ትልቁም ስህተት ነዉ” በማለት ዶክተር አረጋዊ በርሀ ተናገሩ።

ህወሃት የትግራይን እናቶች ከልቅሶ አትውጡ ብሎ ጭካኔን ያወጀ፣ እያወጀም ያለ ፤ከስህተቱ የማይማር፣ ስልጣንና ወንበርን የሞት አፋፍ ላይ ተቀምጦ እንኳ በህዝብ ስቃይ የሚመኝ ከንቱ ድርጅች፣ ከኢትዮጵያ ጥንተ ጠላቶች ጋር አብሮ እናቱን የሚዋጋ የዚህ ድርጅት መስራች መሆኔ ሁሌም ይቆጨኛል ሲሉም ዶ/ር አረጋዊ ሀሳባቸውን ገልጿል።
1👍1
ታማኝ መረጃ pinned «https://youtu.be/fhifk206qD8»
ሚስጥረስላሴ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድት እንደማትወክል ተገለፀ📌

የኢሕአፓ እና የትብብሩ ጸሃፊ ሚስጥረስላሴ የሽግግር መንግስት ይቋቋም የሚል አቋምን በሚያንጸባርቀው በነልደቱ አያሌው ስብስብ ጥሪ ላይ በመሳተፍ ሰለማዊ ትግል እንደማትቀጥልበት ምልክት ሰጥታለች።

በትብብር በኩል ከኢሕአፓ ጋር አጋር በሆነው የእናት ፓርቲ አባሉ አቶ ጌትነት በኩል ደሞ “እኛ እንደትብብር የሽግግር መንግስት የሚሉት ቡድኖች ህገ ወጥ በመሆናቸው እንደማንሳተፍ ወስነናል ፤ እዛ ላይ የተሳተፉት የትብብሩ አባላት በግል ፍላጎታቸው ላይ ተመሰርተው ነው የተሳተፉት” በሚል ነቀፌታቸውን አሰምተዋል።

በመሆኑም ይህ የምስጥረ ከጸረ ሰላም ሃይሎች ጋር ያላት ቁርኝት የበረታ መሆኑን የሚያሳይ አካሄድና ከትብብሩ አቋም ውጭ መንቀሳቀስ የፓርቲዋንም ሆነ የትብብሩን ገጽታ የሚያጠለሽ በመሆኑ ምናልባትም ግዜው ካልረፈደ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድት ግለሰቧን ከጸሃፊነቷ ለማንሳት እንደሚንቀሳቀስ ምንም ጥርጥር አይኖረውም ።
በርካታ አመራሮች የተደመሰሱበት ኦፕሬሽን 📌

ደጀኑ ሰራዊታችን በሰሜን ጎጃም ዞን እና በደቡብ ጎንደር ባካሄደው ስምሪት የፅንፈኛ አመራሮችን ከነግበረ አበሮቻቸው በመደምሰስ እና በመማረክ ወጤታማ አፈፃፀም አስመዝግቧል 💪

ሰሜን ጎጃም ዞን በሰሜን ሜጫ ፣ ይልማናዴንሳ ፣ በጎንጂ ቆለላና አዴት ፣ በባህር ዳር ዙርያ እና በደቡብ ጎንደር ወረዳዎች በተካሄደ የተጠና ኦፕሬሽኖች እራሱን ዘመቻና የጦር አዛዥብሎ የሚጠራው ሻለቃ ሸዋነህ ሙልጌታ፣ ሃምሳ አለቃ ዘካርያስ፣ የልዩ ዘመቻ ሃላፊ ይነገር ተገኝ እና በርካታ ታጣቂዎች አብረው መደምሰሳቸው ታውቋል።

እንዲሁም ጌትነት ተፈራ የተባለ የፅንፈኛው ሐኪም እንዲሁም ሰውአለ ምኒችል የተባለ የፅንፈኛው ሎጀስቲክስም ተማርኳል።

በተጨማሪ ፅንፈኛው ከህዝብ ዘርፎ ሲገለገልባቸው የነበሩ አራት ተሽከርካሪዎች በሰራዊቱ ቁጥጥር ስር ውሏል።
👎2👍1
በህወሃት ፍቃድ ትግራይ የገባው ሻዕብያ

ሻዕብያ ትናንት በትግራይ ህዝብ ላይ የፈፀመዉ ዘግናኝ ጭፍጨፍ ሳይበቃዉ ዛሬም በህወሃት ላይ ታዝሎ ወደ ትግራይ በመግባት የትግራይን ህዝብ ከቤት ንብረቱ እያፈናቀለዉ ይገኛል።

ለአብነትም ትላንት (መጋቢት28/2018 ዓ.ም) የኤርትራ ሰራዊት የኤርትራ አዋሳኝ በሆነው በራማ አዲ አርባተ አቅራቢያ በሚገኘው የመርብ ወንዝ ወርቅና ማዕድን በማውጣትና በሌሎች ዘርፎች ላይ ተሰማርተው ኑሯቸውን የሚገፉ የትግራይ ተወላጆችን ንብረታቸውንና ከብቶቻቸውን እየዘረፈ በኃይል ከመኖሪያቸው ማፈናቀሉ ተሰምቷል።

ህወሃት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ደጋግሞ በመጣስ ከሻዕቢያ ጋር በመሆን ጦርነት ቀስቃሽ ድርጊቶች መፈፀሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት በቸልታ ሊመለከቱት አይገባም።
ሹፌር ያገቱ የፅንፈኛው አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ🙌

በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ላይ አርማጭሆ አከባቢ ከጎንደር ወደ ሁመራ ሲጓዝ የነበረ ተሳቢ መኪና ሹፌር የጃዊሳው ቡድን አባላት አግተው ወደ ጫካ የአከባቢው ህዝብ ከረዳቱ ባገኘው መረጃ መሰረት ተባብረው በመውጣት ከእገታው እንዳስለቀቁት እና ከጸጥታ ኃይል ጋር የፅንፈኛው አባላቶች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረጋቸው ታውቋል።

ይህ የህብረተሰቡ ተግባር የፅንፈኛው ተግባር እንደማመረው እና ከእንግዲህ እንደማይታገሰው ማረጋገጫን የሚሰጥ ነው።

ሌሎች ዞኖችም ከዚህ ትምህርት በመውሰድ ከፀጥታ ኃይሉ በጋራ በመስራት የአከባቢውን ሰላም ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል 👍
👍1👎1
ጀነራል አልቡርሃን ለዲሞክራሲያዊ ሽግግር ፍቃደኝነቱን ገልጿል📌

ህዝባዊ ተቃውሞ የተበራከተበትና ተስፋ የቆረጠው ጀነራል አልቡርሃን ወታደራዊ መንግስቱ ዲሞክራሲያዊ ሽግግር ለማድረግ እንዲሁም ስልጣኑን ለህዝብ ለማስረከብ ዝግጁ መሆኑን ይፋ አድርጓል።

ይህ የጀነራሉ ንግግር የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉን መበርታትና ወደ ስልጣን መምጣቱን አይቀሬነት የሚያረጋግጥ ነው።

በተመሳሳይ ደሞ ከፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ በተቃራኒ ቆመወ ለከረሙት ለእነ ኤርትራና ግብጽ ደግሞ ሌላ ስጋትን የሚጭር ውሳኔም ነው።

በተለይ ህወሃት የትግራይ ወጣቶችን ለሱዳኑ ጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን ጦር በገንዘብ በመሸጡ በፈጥኖ ደራሽ ኃይል ውስጥ በጣላትነት ተመዝግቧል።
👍43
ተመልካች ያጣው የባንዳዎች ጭወኃት 📌

በሚልየን የሚቆጠር ህዝብ ያየናል በሚል የኢንተርኔት ሰልፍ ያዘጋጀው የከሰረው ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው እንኳን በሚልየን ሊታይና አስር ሺ የሚደርስ የህዝብ ቁጥር እንኳን ሊያገኝ አልቻለም።

ላለመታየቱ በአንከር ሚድያ ላይ እንደምክንያት ያቀረበው “የኢትዮጵያ ህዝብ ዩቱብ ከማየት ወደ ቲክቶክ ስለዞረ ነው” ነበር ያለው።

እውነታው ግን የኢትዮጵያ ህዝብ በአቋራጭ ስልጣን ለመያዝ ከሚታትሩ ፣ በጠላት ሃገር ተገዝተው አመጽ እና ብጥብጥን ከሚያነሳሱ እንዲሁም የህዝቡንም ሆነ የሃገር ጥቅም አሳልፈው ከሚሰጡት ጎን እንደማይቆሙያሳዩበት መሆኑ ነው ።
👍1
ምሬ ወዳጆ እጅ ለመስጠት ሂደቱን ጀምሯል 🚨

ምሬ ወዳጆ ከስህተቱ ተምሮ ለአማራ ህዝብ ደህንነት እና ሰላም ሲል እጅ ለመስጠት መንገድ መጀመሩ ተሰምቷል።

ካፕቴን ማስረሻ ሰጤ እጅ መስጠቱን እና ወደ ሰላም መምጣቱን ተከትሎ በአስረስ ማረ ትዕዛዝ የፋኖ ታጣቂውን ወንድሙን እንደገደሉበት የሚታወስ ነው።

ታድያ ይህንን ስራቸውን ጠንቅቆ የሚያውቀው ምሬ ወዳጆ እጅ የመስጠት ሃሳብ ላይ ስላለ እሱ ከገባ በኋላ ልጁን እንዳይገድሉበት ልጁን ቀድሞ በሰራዊቱ ቁጥጥር ስር በትላንትናው ዕለት እንዲውል ማድረጉ ታውቋል።

ምሬ ህዝብን ለመታደግ ወደ ሰላም መምጣት የሚደነቅ ነው
4👎2
የጄኔራል ታደሰ ወረደ ሹመት መራዘም እና የፅንፈኛው ዕቅድ📌

የጄነራል ታደሰ ወረደ ስልጣን ተራዘመ የሚለውን ጭምጭምታ ተከትሎ ፅንፈኛው ህወሓት ትላንት (መጋቢት 29/2018 ዓ.ም) የከተማና የወረዳ ምክር ቤቶችን አስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት የፕሪቶሪያ የሰላም ሥምምነት ተጥሷል ሲል የጦርነት ነጋሪቱን ጎስሟል።

ይህም በመሆኑ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፈርሶ ከጦርነቱ በፊት በምርጫ የተመረጠው ሕጋዊ የሆነ መንግስት ይመለስ የሚል ውሳኔ እያስወሰነ መፈንቅለ መንግስቱን እያወጀ እንደሚገኝ ስምተናል።

ይህን ውሳኔውኔም የዓድዋ፣ የዓብይአዲ እና ሓሓይለ ከተማ መስተዳደሮች ተቀብለው ይሁንታ መስጠታቸው ታውቋል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ከሚታይባቸው የምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ሀገር ሆናለች 🤩

ምሥራቅ አፍሪካ እ.ኤ.አ. በ2026 አኅጉራዊ የዕድገት መሪነት እንደሚይዝና ጠንካራ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ የሚታይባቸው ሩዋንዳ፣ ኢትዮጵያና ታንዛኒያ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያ ዋነኛዋ የአካባቢው የዕድገት ኃይል መሆኗን፣ የአፍሪካ ኤክስፖርትና ኢምፖርት ባንክ (አፍሪ ኤግዚም ባንክ) ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።

ኢትዮጵያ ለውጭ ገበያ የምትልካቸውን ቡና፣ ጨርቃ ጨርቅ፣ ቆዳና የማኑፋከቸሪንግ ውጤቶች ላይ ትኩረት በማድረግ የውጭ ገበያ አቅሟን ማሳደግ እንደምትችል ሪፖርቱ አብራርቷል፡፡
የሁለት አሸባሪዎች እቅድ 📌

በወለጋ አካባቢ የሚንቀሳቀሰው ራሱን የወለጋ ቢንዛሞ ብሎ የሚጠራው የጃዊሳዉ ቡድን ክንፍ ታጣቂ የኦሮሞውን አርሶ አደር ከብት እንዲዘርፉ ቤታቸውን እንዲያቃጥሉ ውሳኔ ላይ ደርሷል።

በተመሳሳይ የሸኔው ታጣቂ ደግሞ በአካባቢው ያለውን የአማራውን ሃብት ንብረት እንዲያወድሙ እና የዕርስ በርስ ግጭት በመቀስቀስ ህዝቡን ለማፈናቀል እንደተወያዩ ከውስጥ የወጣው መረጃ ያሳያል።

ሁለቱም አሸባሪዎች በየፊናቸው ተከፋፍለው ኢትዮጵያን ገሀነም ለማድረግ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለማስቆም አስቸኳይ እርምጃ ሊወሰድባቸው ይገባል።
👎1
🚨 ሰበር መረጃ 🚨

የጀነራሉ ስልጣን ለአንድ ዓመት ተራዝሟል ‼️

ጀነራሉ የአስተዳደሩን አመታዊ የግምገማ ሪፖርት ለጠቅላዩና ሌሎች የፌደራል አካላት አቅርበው ባስገመገሙ ማግስት ዛሬ መጋቢት 30 ነው የጀነራሉ ስልጣን ለተጨማሪ አንድ አመት መራዘሙ ይፋ የሆነው ።

ይህን የፌደራል መንግስቱን ውሳኔ ተከትሎም ጀነራሉን አስወግዶ የራሱን ሰው መሾም የሚፈልገው የነ ሞንጆሪኖ ስብስብ ቀጣይ ዕርምጃ ጀነራሉ ወደ መቀለ ከመመለሱ በፊት መፈንቅለ መንግስት መፈጸም ሊሆን እንደሚችል ፣ ሆኖም ስብስቡ ይህን ካደረገ የሚከተለው አጸፋ የከፋ በመሆኑ ምናልባትም እሱን ግምት ውስጥ በማስገባት የሃሳብ ለውጥ ሊያደርግ ይችላል የሚለውም የሚጠበቅ በመሆኑ የቡድኑ ዕርምጃ ላይ ሃምሳ ሃምሳ የሆነ ግምት ተይዟል ።

በመሆኑም ስብስቡ የጀነራሉን ሹመት እየመረረውም ቢሆን የሚውጠው ከሆነና ጀነራሉ በሰላም ወደ መቀሌ ከገቡ ያባከኑትን አንድ ዓመት ዞር ብለው በመገምገም በተጨመረላቸው ተጨማሪ የስልጣን ዘመን እዛ እና እዚህ መርገጣቸውን ትተው ለትግራይ ህዝብ የሚበጀውን ሊያደርጉ ይገባል እንላለን ።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ከሚታይባቸው የምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ሀገር ሆናለች 🤩

ምሥራቅ አፍሪካ እ.ኤ.አ. በ2026 አኅጉራዊ የዕድገት መሪነት እንደሚይዝና ጠንካራ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ የሚታይባቸው ሩዋንዳ፣ ኢትዮጵያና ታንዛኒያ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያ ዋነኛዋ የአካባቢው የዕድገት ኃይል መሆኗን፣ የአፍሪካ ኤክስፖርትና ኢምፖርት ባንክ (አፍሪ ኤግዚም ባንክ) ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።

ኢትዮጵያ ለውጭ ገበያ የምትልካቸውን ቡና፣ ጨርቃ ጨርቅ፣ ቆዳና የማኑፋከቸሪንግ ውጤቶች ላይ ትኩረት በማድረግ የውጭ ገበያ አቅሟን ማሳደግ እንደምትችል ሪፖርቱ አብራርቷል፡፡
የዶክተሮች ግድያ እንደቀጠለ ነው😢

በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ቡሬ ከተማ በሚገኘው “ቡሬ ሆስፒታል” ጠቅላላ የቀዶ ህክምና ሃኪም የሆኑት ዶክተር አበበ መኮንን መጋቢት 27/2018 ዓም የሙህራንን ደም መምጠጥ በለመደው ጽንፈኛው ጃውሳ መገደላቸው ታውቋል።

ፀረ ህዝቡ ስብስብ ከፖለቲካ ጋር ምንም አይነት ንክኪ የሌላቸውን ፍፁም ሰላማዊ ሰዎችን በጭካኔ መ*ግ*ደ*ል የሁልግዜም ተግባሩ ነው።

‎የአማራ ህዝብ ሙህራንን በማጥፋት የአማራን ህዝብ አንገት ማስደፋት የዚህ አረመኔ ቡድን ፍላጎት ነው።
👎1
የኛዎቹ ባንዳዎች ከኢራን መማር አለባቸው ‼️

ኢራናውያን እርስ በርሳቸው የፖለቲካ ልዩነት አላቸው፣ ይሄኛው ጦርነት ከመጀመሩ በፊት እንድያውም መንግስታቸውን ለመቃወም አደባባይ ወጥተውም ነበር።

ሆኖም ግን አሜሪካ ኢራን ጋር በገባችበት ግጭት መሰረተ ልማቶችዋን ለማጋየት ስትዝት ለብሄራዊ ጥቅማቸው እና ለሃገር ሉዓላዊነታቸው ሲሆን ግን ያለልዩነት “እናጋየዋለን” ወደ ተባለው ቦታ ወጥተው ከመንግስታቸው ጎን ቆመው የህይወት መሰዋትነት ለመክፈል በአንድነት ሲቃወሙ ተመልክተናል።

የኛ ሃገር መንግስት ተቃዋሚ እና ተፋላሚው ግን ብሄራዊ ጥቅምን አሳልፈው ለመሸጥ አይደለም ከነግብጽ ከሴይጣንም ጋር እንሰራለን እያለ ያለ ሀፍረት ይፉክራል።

እንዲሁም መንግስት በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ያስፈልገናል ሲል ሶማሊያ ተነካች ኤርትራ ተነካች እያሉ “መች ነው ተጣምረን የምንዋጋው” እያሉ እናት ሃገራቸውን እና ህዝባቸውን ለመበተን ይጣጣራሉ ።
የሻዕቢያን ሴራ የበጠሰው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ርእሰ መሥተዳድር ሹመት መራዘም ✔️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ( ዶ.ር) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ርእሰ መሥተዳድር ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ ሹመት ለአንድ ዓመት አራዝሟል።

ይሄም በተደጋጋሚ ጦርነቱ በህውሃት በኩል እንዳይጀመር ታደሰ እንቅፋት ሆኗል ከስልጣን ይወገድ ሲል የነበረውን የሻዕቢያን ሴራ ሊበጣጠስ ችሏል።

ሻዕቢያ ከህወሓት ጋር የፈጠረው “ፅምዶ” ጥምረት ዕሁን እንዳይሆን የፌደራል መንግስት ውሳኔ ተገቢ ነው።

የትግራይ ህዝብም በዚህ ውሳኔ ደስታኛ እንደሚሆን አያጠያይቅ 🙌
እንደልማዱ የዘመኑን ወጣት ሊበላ የተነሳው ሰልፈኛው ኢህአፓ

ከድሮም የትግል ልምዱ በዋናነት በከተማ ጎዳናዎች ላይ በሚደረጉ የአመፅ ሰልፎች ላይ የተመሰረተው ኢህአፓ ከስሙ ውጭ በርካታ ተሃድሶወችን አድርጌ መጥቻለሁ ይበል እንጂ ከዚህ የአመጽ አባዜው እንዳልተላቀቀ ግን ዛሬ ባደረገው የሰልፍ ጥሪው በጽኑ አረጋግጧል ።

ፓርቲው ያደርግ በነበረው እንቅስቃሴ መነሻነት ደርግ ባደረገው ከፍተኛ ጭፍጨፋ ለአንድ ትውልድ እልቂት ምክንያት መሆኑ የሚነገር ሲሆን ፤ ይሄው ፓርቲም ራሱ በለውጡ ማግስት ታህሳስ 04 ቀን 2012 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ዓመታዊ ጉባኤውን በአዲስ አበባ ባካሄደበት ወቅት በትግል ወቅት በነበረው ሁኔታ ለጠፋው የሰው ህይወትና በንብረት ላይ ለደረሰው ጉዳት የኢትዮጵያ ህዝብን በተለይም ጉዳት የደረሰባቸውን ቤተሰቦችና ግለሰቦች በፕሬዝዳንቱ ወይዘሮ ቆንጂት በኩል በይፋ ይቅርታ መጠየቁና ቀድሞ የተሰራው ስህተት አሁን ላለው ትውልድ ትምህርት እንዲሆን መጠቆሙ የሚዘነጋ አልነበረም ።

ሆኖም ከስህተቱ ያልታረመውና ከበርካታ ጥፋቶች በኋላም ዘመን ጠብቆ እንደቀላል ‘’ ይቅርታ ‘’ በሚል ብቻ ጥፋቱን ማለፍ የለመደው ፓርቲው በቀጥተኛው የምርጫ ሂደት ላይ እየተሳተፈ ባለበት በዚህ ወቅትም የጥፋት አባዜው ተነስቶበት ወጣቱን ሰልፍ በመጥራት ዳግም የጎዳና ላይ አመጹን ለማስኬድ እንቅስቃሴ ጀምሯል ።

ሆኖም ወጣቱ ዘመን እየጠበቀ በስሜት ነድቶ ትውልድን የሚበላና እንደቀላል ህይወትን አስቀጥፎ ‘’ ይቅርታ ‘’ ብቻ ብሎ ለሚያልፈው ለዚህ ፓርቲ ከታሪክ በመማር ጆሮ ሊነፍገውና ራሱን ሊጠብቅ ይገባዋል ።
ከመጋቢት 24ቱ የቀጠለው የኢህአፓ የሰልፍ ጥሪ ‼️

ኢህአፓ የፋኖ ጭራነቱን ደግሞ ደጋግሞ በማስመስከር ላይ ይገኛል ።

ፓርቲው እንደበቀቀን የፋኖን ንግግር እና ውሳኔ እየተከተለ ቃል በቃል በመድገም ተጠምዶ የከረመ ሲሆን ፤ አሁን ደግሞ ይህን የበቀቀንነት አባዜውን ከፍ በማድረግ መጋቢት 24 ፋኖ በአማራ ክልል ብቻ በግዳጅ እንዲካሄድ ያደረገውን የተቃውሞ ሰልፍ ፋኖ ተሰሚነት በማያገኝባቸው ሌሎች ስፍራወች ጭምር በስፋት እንዲሰራጭ ለማስቀጠል ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል ።

ፓርቲው ዛሬ መጋቢት 30 ባወጣው የሰልፍ ጥሪው ሚያዝያ 30/2018 ዓም በመላው ሃገሪቱ በሚገኙ የክልል ከተሞች ሁሉ አመጽ እንዲቀሰቀስ የሚል መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን ፤ በጥሪው ላይ ያስተላለፋቸው መልዕክቶችና በመፈክርነት ይነሳሉ በሚል ያሰፈራቸው ጽሁፎች ፋኖ መጋቢት 24 በግዳጅ በአማራ ክልል ባስወጣው ሰልፍ ላይ ህዝቡን በግዳጅ ያስጨበጣቸው መፈክሮች ራሳቸው መሆናቸው ሁለቱ ሃይሎች ከተማና ጫካ ከመንቀሳቀሳቸው ውጭ ልዩነት የሌላቸው በሽርክና የሚሰሩ የጥፋት ሃይሎች መሆናቸውን በይበልጥ ያረጋገጠ ሁኗል ።
1👎1
ጀነራል ታደሰ ወረደ ስልጣናቸውን ማስጠበቅ ጀምሯል📌

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፈርሶ ከጦርነቱ በፊት በምርጫ የተመረጠው ሕጋዊ የሆነ መንግስት ይመለስ የሚለውን የህወሃት ውሳኔ ጀነራል ታደሰ ወረደ ሹመታቸው መራዘሙን ተከትሎ ውድቅ እያደረጉት ይገኛል።

የፕሪቶሪያ ስምምነት ፈርሷል በሚል ስብስቡ ያቀረበውን ምክረ ሃሳብ ተቀብለው ያጸደቁ የወረዳ ምክር ቤቶች ውሳኔያቸውን እንዲያነሱ አስጠንቅቋል።

እንዲሁም ከዚህ በፊት ከስር ያሉ አስተዳደሮችንና ከንቲባወችን በራሳቸው ይሾሙ ዘንድ ሰጥቷቸው የነበረውን ውክልና መንሳቱን የሚገልጽ መልዕክት ጀነራል ታደሰ ወረደ ወደ ትግራይ መላካቸው ተሰምቷል።

ይህም ጀነራሉ በጭማሪ የስልጣን ግዜያቸው ከህውሃት እግር ስር ከመርመስመስ ይልቅ ለትግራይ ህዝብ የሚበጀውን ለማድረግ እንደቆረጡ ያመላክታል።