“ስለዚህ ሂዱና ሕዝቦችን ሁሉ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤”
ማቴዎስ 28:19 NASV
ይሄ ነው የተጠራንለት፤ ከአማኝነት የላቀው ተልዕኮ፡፡
#higher_missions
#discipleship_motivations
ማቴዎስ 28:19 NASV
ይሄ ነው የተጠራንለት፤ ከአማኝነት የላቀው ተልዕኮ፡፡
#higher_missions
#discipleship_motivations
❤3
“የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን መሪዎቻችሁን አስቡ፤ የኑሯቸውን ፍሬ ተመልከቱ፤ በእምነታቸውም ምሰሏቸው። ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንት፣ ዛሬም ለዘላለምም ያው ነው።”
ዕብራውያን 13:7-8 NASV
የዕብራውያን ጸሃፊ የእግዚአብሔር ቃል ያስተማሯችሁን ሰዎች እነርሱ ክርስቶስን እንደሚመስሉ (የማይመስሉትን አይጨምርም) ምሰሏቸው(ጳውሎስ እኔ ክርስቶስን እንደሚመስል እነን ምሰሉኝ እንዳለው ማለት ነው) ፡፡ ክርስቶስ ትላንትም ዛሬም ያው ነው፤ አልተቀየረም ለዘላለምም አይቀየርም፡፡ ክርስቶስ ሌላ መገለጫ የለውም አንደውኑ እስከዘላለም ተገልጧል እያለን ነው፡፡
ዕብራውያን 13:7-8 NASV
የዕብራውያን ጸሃፊ የእግዚአብሔር ቃል ያስተማሯችሁን ሰዎች እነርሱ ክርስቶስን እንደሚመስሉ (የማይመስሉትን አይጨምርም) ምሰሏቸው(ጳውሎስ እኔ ክርስቶስን እንደሚመስል እነን ምሰሉኝ እንዳለው ማለት ነው) ፡፡ ክርስቶስ ትላንትም ዛሬም ያው ነው፤ አልተቀየረም ለዘላለምም አይቀየርም፡፡ ክርስቶስ ሌላ መገለጫ የለውም አንደውኑ እስከዘላለም ተገልጧል እያለን ነው፡፡
❤4
ከእኔ የተማራችሁትን ማንኛውንም ነገር አድርጉ
“ከእኔ የተማራችሁትን ወይም የተቀበላችሁትን፣ የሰማችሁትን ወይም ያያችሁትን ማንኛውንም ነገር አድርጉ፤ የሰላም አምላክም ከእናንተ ጋራ ይሆናል።”
ፊልጵስዩስ 4:9 NASV
ጳውሎስ ይህንን ያለው የፊልጵስዩስ መልክት ስጨርስ አከባቢ ነው፡፡ እንግድህ እርሱ ሲያደርግ የነበረውን ሁሉንም፤ ማለትም መድረክ ላይም ከመድረግ ውጭም ያደረገውን በሙሉ አድርጉ እያላቸው ነው፡፡
ጥያቄው እኛስ ዛሬ እንደ ጳውሎስ እንደዚህ በድፍረት ከእኔ ያያችሁትን ማንኛውንም ነገር አድረጉ የማለት ድፍረቱ አለን ወይ ነው? መቸም ጳውሎስ እንደእኛ ሰው ነው፤ ነገር ግን እንደዚህ በድፍረት የሚናገረው በትክክል የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ስለሆነ ነው፡፡ በዚህም እርግጠኛ ነው፡፡
ይሄ ለእኛ ጥሩ challenge ነው፡፡ ለምንመራቸው ሰዎች ክርስቶስን ወይም ጳውሎስን ወይም በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያለን ገጸባህሪ ሳይሆን እራሳችንን ነው ማሳየት ያለብን፡፡ እኔ እንደማደርገው አድርጉ፤ እንደ እኔ ሁኑ ነው ማለት ያለብን፡፡
ዛሬ ከጳውሎስ ህይወት የምንማረው ደቀ መዝሙር ሆነን ደቀ መዝሙር ማድረግ እንደሚገባን ነው፡፡ ደቀ መዝሙር የምናደርገው ደግሞ በማውራት ብቻ ሳይሆን አድርጎ በማሳየት ጭምር ነው፡፡
ይህንን ምሳሌ እንድንከተል ጸጋው ያስፈልገናል፤ የእግዚአብሔር ጸጋ ይብዛልን፡፡
“ከእኔ የተማራችሁትን ወይም የተቀበላችሁትን፣ የሰማችሁትን ወይም ያያችሁትን ማንኛውንም ነገር አድርጉ፤ የሰላም አምላክም ከእናንተ ጋራ ይሆናል።”
ፊልጵስዩስ 4:9 NASV
ጳውሎስ ይህንን ያለው የፊልጵስዩስ መልክት ስጨርስ አከባቢ ነው፡፡ እንግድህ እርሱ ሲያደርግ የነበረውን ሁሉንም፤ ማለትም መድረክ ላይም ከመድረግ ውጭም ያደረገውን በሙሉ አድርጉ እያላቸው ነው፡፡
ጥያቄው እኛስ ዛሬ እንደ ጳውሎስ እንደዚህ በድፍረት ከእኔ ያያችሁትን ማንኛውንም ነገር አድረጉ የማለት ድፍረቱ አለን ወይ ነው? መቸም ጳውሎስ እንደእኛ ሰው ነው፤ ነገር ግን እንደዚህ በድፍረት የሚናገረው በትክክል የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ስለሆነ ነው፡፡ በዚህም እርግጠኛ ነው፡፡
ይሄ ለእኛ ጥሩ challenge ነው፡፡ ለምንመራቸው ሰዎች ክርስቶስን ወይም ጳውሎስን ወይም በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያለን ገጸባህሪ ሳይሆን እራሳችንን ነው ማሳየት ያለብን፡፡ እኔ እንደማደርገው አድርጉ፤ እንደ እኔ ሁኑ ነው ማለት ያለብን፡፡
ዛሬ ከጳውሎስ ህይወት የምንማረው ደቀ መዝሙር ሆነን ደቀ መዝሙር ማድረግ እንደሚገባን ነው፡፡ ደቀ መዝሙር የምናደርገው ደግሞ በማውራት ብቻ ሳይሆን አድርጎ በማሳየት ጭምር ነው፡፡
ይህንን ምሳሌ እንድንከተል ጸጋው ያስፈልገናል፤ የእግዚአብሔር ጸጋ ይብዛልን፡፡
“በልዑል መጠጊያ የሚኖር፣ በሁሉን ቻይ አምላክ ጥላ ሥር ያድራል። እግዚአብሔርን፣ “መጠጊያዬ፣ ምሽጌ፣ የምታመንብህ አምላኬ” እለዋለሁ።”
መዝሙር 91:1-2 NASV
#discipleship_motivations #higher_missions
#daily_pasture
#የእለት_ስንቅ
መዝሙር 91:1-2 NASV
#discipleship_motivations #higher_missions
#daily_pasture
#የእለት_ስንቅ
“ለእኔ፣ መኖር ክርስቶስ ነው፤ ሞትም ማትረፍ ነው።”
ፊልጵስዩስ 1:21 NASV
ይላል የክርስቶስ ደቀመዝሙር የሆነ ሰው፡፡
#discipleship_motivations
#higher_missions
ፊልጵስዩስ 1:21 NASV
ይላል የክርስቶስ ደቀመዝሙር የሆነ ሰው፡፡
#discipleship_motivations
#higher_missions
“በዚህ ጊዜ አንቺ ዝም ብትዪ፣ ለአይሁድ ርዳታና ትድግና ከሌላ ስፍራ ይመጣላቸዋል፤ አንቺና የአባትሽ ቤት ግን ትጠፋላችሁ፤ ደግሞስ አንቺ ንግሥት ለመሆን የበቃሽው ለዚህ ጊዜ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?””
አስቴር 4:14 NASV
ዛሬ ያለንበት ቦታ ያለነው ለምንድን ነው? እግዚአብሔር ለሆነ አላማ አስቀምጦን ይሆን ብለን አስበን እናውቃለን? የጌታ ደቀመዝሙር የሆነ ሰው እንዲህ ያስባል፡፡
#discipleship_motivations
#higher_mission
#daily_pasture
አስቴር 4:14 NASV
ዛሬ ያለንበት ቦታ ያለነው ለምንድን ነው? እግዚአብሔር ለሆነ አላማ አስቀምጦን ይሆን ብለን አስበን እናውቃለን? የጌታ ደቀመዝሙር የሆነ ሰው እንዲህ ያስባል፡፡
#discipleship_motivations
#higher_mission
#daily_pasture
ቃል
“በመጀመሪያ ቃል ነበረ፤ ቃልም ከእግዚአብሔር ጋራ ነበረ፤ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። እርሱም በመጀመሪያ ከእግዚአብሔር ጋራ ነበረ። ሁሉ ነገር በርሱ ተፈጥሯል፤ ከተፈጠረው ሁሉ ያለ እርሱ የተፈጠረ ምንም የለም። ሕይወት በርሱ ነበረች፤ ይህች ሕይወት የሰው ብርሃን ነበረች።”
ዮሐንስ 1:1-4 NASV
ይህ ቃል ወደ ዘፍጥረት አንድ ይጠቁመናል፡፡ በዚያ ምዕራፍ እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር ከሰው ውጭ በቃሉ(በክርስቶስ) ነው የሰራው፡፡ እርሱ ቃል እራሱ የሰው ብርሃን ነበር ይለናል ዮሐንስ፤ ይህ ማለት በእርሱ በክርስቶስ የሄደ ብቻ ወደ እውነት ወይም ቀጥተኛው (orthodox) ህይወት መድረስ ይችላል ማለት ነው፡፡ ከእርሱ ውጭ ብርሃን የለም ብርሃን ከሌለ መድረሻ የለም እያለን ነው ሐዋርያው፡፡
በእርሱ ብርሃን ተመርተን ከዘላለም ህይወት መድረስ እንድንችል ፀጋው ይርዳን፡፡
#higher_mission
#daily_pasture
#discipleship_motivations
“በመጀመሪያ ቃል ነበረ፤ ቃልም ከእግዚአብሔር ጋራ ነበረ፤ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። እርሱም በመጀመሪያ ከእግዚአብሔር ጋራ ነበረ። ሁሉ ነገር በርሱ ተፈጥሯል፤ ከተፈጠረው ሁሉ ያለ እርሱ የተፈጠረ ምንም የለም። ሕይወት በርሱ ነበረች፤ ይህች ሕይወት የሰው ብርሃን ነበረች።”
ዮሐንስ 1:1-4 NASV
ይህ ቃል ወደ ዘፍጥረት አንድ ይጠቁመናል፡፡ በዚያ ምዕራፍ እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር ከሰው ውጭ በቃሉ(በክርስቶስ) ነው የሰራው፡፡ እርሱ ቃል እራሱ የሰው ብርሃን ነበር ይለናል ዮሐንስ፤ ይህ ማለት በእርሱ በክርስቶስ የሄደ ብቻ ወደ እውነት ወይም ቀጥተኛው (orthodox) ህይወት መድረስ ይችላል ማለት ነው፡፡ ከእርሱ ውጭ ብርሃን የለም ብርሃን ከሌለ መድረሻ የለም እያለን ነው ሐዋርያው፡፡
በእርሱ ብርሃን ተመርተን ከዘላለም ህይወት መድረስ እንድንችል ፀጋው ይርዳን፡፡
#higher_mission
#daily_pasture
#discipleship_motivations
“በሰዎች ሁሉ ላይ ከደረሰው የተለየ ፈተና አልደረሰባችሁም፤ እግዚአብሔር ታማኝ ነው፤ ስለዚህ ከምትችሉት በላይ እንድትፈተኑ አይተዋችሁም፤ ነገር ግን በምትፈተኑበት ጊዜ ፈተናውን መታገሥ እንድትችሉ፣ መውጫ መንገዱን ያዘጋጅላችኋል።”
1 ቆሮንቶስ 10 : 13 NASV
“The temptations in your life are no different from what others experience. And God is faithful. He will not allow the temptation to be more than you can stand. When you are tempted, he will show you a way out so that you can endure.”
1 Corinthians 10 : 13 NLT
#discipleship_motivations
#higher_mission
#daily_pasture
1 ቆሮንቶስ 10 : 13 NASV
“The temptations in your life are no different from what others experience. And God is faithful. He will not allow the temptation to be more than you can stand. When you are tempted, he will show you a way out so that you can endure.”
1 Corinthians 10 : 13 NLT
#discipleship_motivations
#higher_mission
#daily_pasture
“እንደማያፍርና የእውነትን ቃል በትክክል እንደሚያስረዳ የተመሰከረለት ሠራተኛ፣ ራስህን በእግዚአብሔር ፊት ልታቀርብ ትጋ። እግዚአብሔርን ከማያስከብር ከንቱ ልፍለፋ ራቅ፤ በዚህ ነገር የተጠመዱ ሰዎች ከእግዚአብሔር እየራቁ ይሄዳሉና።”
2 ጢሞቴዎስ 2:15-16 NASV
ጵውሎስ እራስን ለእግዚአብሔር ስለማቅረብ ሮማውያንን ራሳቸውን እንዲያቀርቡ ሲያሳስባቸው ነበር። አሁን ደግሞ ጥሞተዎስን በተመሳሳይ እንደተመሰከረለት የቅሉ ሰባኪ ራሱን ለእግዚአብሔር እንዲያቀርብ፣ ወይም ራሱን እንከን የሌለበት ለማድረግ እንዲሰራ ያሳስበዋል። እርሱም እንዴት እንደሚቻል ሲያስረዳ እግዚአብሔርን ከማያስከብር ንግግር ራሱን በማራቅ ቁጥብ በመሆን እንደሆነ ያረጋግጥለታል። በነገራችን ላይ የተመሰከረለት ሲል በሰዎች የተመሰከረለት ነው እያለ ያለው።
እኛስ ዛሬ ቁጥብ ህይወት በመምራት እንደተመሰከረለት ሰራተኛ ራሳችንን እያቀረብን ነው፡፡ ይሄ አቀራረብ የተወሰነ ዋጋ መክፈልን ይጠይቃል፡፡ ይህንን የማናደርግ ከሆነስ ለማድረግ ዝግጁ ነን?
#daily_pasture #discipleship_motivations #higher_mission
2 ጢሞቴዎስ 2:15-16 NASV
ጵውሎስ እራስን ለእግዚአብሔር ስለማቅረብ ሮማውያንን ራሳቸውን እንዲያቀርቡ ሲያሳስባቸው ነበር። አሁን ደግሞ ጥሞተዎስን በተመሳሳይ እንደተመሰከረለት የቅሉ ሰባኪ ራሱን ለእግዚአብሔር እንዲያቀርብ፣ ወይም ራሱን እንከን የሌለበት ለማድረግ እንዲሰራ ያሳስበዋል። እርሱም እንዴት እንደሚቻል ሲያስረዳ እግዚአብሔርን ከማያስከብር ንግግር ራሱን በማራቅ ቁጥብ በመሆን እንደሆነ ያረጋግጥለታል። በነገራችን ላይ የተመሰከረለት ሲል በሰዎች የተመሰከረለት ነው እያለ ያለው።
እኛስ ዛሬ ቁጥብ ህይወት በመምራት እንደተመሰከረለት ሰራተኛ ራሳችንን እያቀረብን ነው፡፡ ይሄ አቀራረብ የተወሰነ ዋጋ መክፈልን ይጠይቃል፡፡ ይህንን የማናደርግ ከሆነስ ለማድረግ ዝግጁ ነን?
#daily_pasture #discipleship_motivations #higher_mission
“ፍቅር ይህ ነው፤ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው ሳይሆን እርሱ እንደ ወደደንና ስለ ኀጢአታችን ማስተስረያ ይሆን ዘንድ ልጁን መላኩ ነው። ወዳጆች ሆይ እግዚአብሔር እንዲህ ከወደደን፣ እኛም እርስ በእርሳችን መዋደድ ይገባናል።”
1 ዮሐንስ 4:10-11 NASV
ዮሐንስን የሚወደው እንቅጩን ስለምናገር ነው፤ በተለይ በተግባራዊ እምነት ጉዳይ፡፡ ስለፍቅር ስናገር 'ይገባናል' አለ ግዴታ አለብን ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ለእኛ በልጁ ለምናምን መውደድ ምርጫ አይደልም እርሱ ያለቅድሜ ሁኔታ እንደወደደን እኛም ሌሎችን እንዲሁ መውደድ ይገባናል፡፡
ጸጋው ይብዛልን!
#higher_mission
#discipleship_motivations
1 ዮሐንስ 4:10-11 NASV
ዮሐንስን የሚወደው እንቅጩን ስለምናገር ነው፤ በተለይ በተግባራዊ እምነት ጉዳይ፡፡ ስለፍቅር ስናገር 'ይገባናል' አለ ግዴታ አለብን ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ለእኛ በልጁ ለምናምን መውደድ ምርጫ አይደልም እርሱ ያለቅድሜ ሁኔታ እንደወደደን እኛም ሌሎችን እንዲሁ መውደድ ይገባናል፡፡
ጸጋው ይብዛልን!
#higher_mission
#discipleship_motivations
❤2
“ድነት በሌላ በማንም አይገኝም፤ እንድንበት ዘንድ ለሰዎች የተሰጠ ከዚህ ስም በቀር ሌላ ስም ከሰማይ በታች የለምና።””
ሐዋርያት ሥራ 4:12 NASV
ለመዳን የተሰጠን አንድ Original ስም ብቻ ነው፤ እርሱም ኢየሱስ ነው፡፡ የቀሩት high copy ናቸው፡፡ ስለዚህ ከእነዚህ አስመሳይ ስሞች መጠንቀቅ ያሻናል፡፡
ጸጋው ይርዳን!
#discipleship_motivation
#discipleship_motivations
#daily_pasture
ሐዋርያት ሥራ 4:12 NASV
ለመዳን የተሰጠን አንድ Original ስም ብቻ ነው፤ እርሱም ኢየሱስ ነው፡፡ የቀሩት high copy ናቸው፡፡ ስለዚህ ከእነዚህ አስመሳይ ስሞች መጠንቀቅ ያሻናል፡፡
ጸጋው ይርዳን!
#discipleship_motivation
#discipleship_motivations
#daily_pasture
“ወንድሞቼ ሆይ፤ ነጻ እንድትሆኑ ተጠርታችኋል፤ ነጻነታችሁን ግን ሥጋዊ ምኞታችሁን መፈጸሚያ አታድርጉት፤ ይልቁንም አንዱ ሌላውን በፍቅር ያገልግል።”
ገላትያ 5:13 NASV
ነጻነት ሁሌም መዘዝ አለው። የሆነ ነገር ነጻ ከሆነ በጥንቃቄ አይያዝም፤ የነጻ ውሃ፣ ምግብ፣ የመሳሰሉትን ማሰብ እንችላለን። በእርግጥ ርካሽ ከሆነም ይቃጣናል እንደንጻ ባይሆንም። ጳውሎስ ይህንን ስለተረዳ እንዲህ ይለናል። ነጻነታችንን ለማይገባው አንጠቀም። በጣም ግልጽ እና አንገብጋቢ፤ ጸጋው ይርዳን!
#discipleship_motivation
#daily_pasture
ገላትያ 5:13 NASV
ነጻነት ሁሌም መዘዝ አለው። የሆነ ነገር ነጻ ከሆነ በጥንቃቄ አይያዝም፤ የነጻ ውሃ፣ ምግብ፣ የመሳሰሉትን ማሰብ እንችላለን። በእርግጥ ርካሽ ከሆነም ይቃጣናል እንደንጻ ባይሆንም። ጳውሎስ ይህንን ስለተረዳ እንዲህ ይለናል። ነጻነታችንን ለማይገባው አንጠቀም። በጣም ግልጽ እና አንገብጋቢ፤ ጸጋው ይርዳን!
#discipleship_motivation
#daily_pasture
“ንቁ፤ በእምነት ጽኑ፤ በርቱ፤ ጠንክሩ። የምታደርጉትን ሁሉ በፍቅር አድርጉ።”
1 ቆሮንቶስ 16:13-14 NASV
ጳውሎስ የመጀመሪያው የቆሮንቶስን መልዕክት ሲጨርስ ነበር ይህን የተናገረው፡፡ በመጨረሻም እንደማለት ነው፤ ንቁ እምነታችሁን ለማጥፋት የሚፈልጉ ሃይላትን እንዲታውቁ፤ በእምነታችሁ ጽኑ ብዙ የሚያሰናክሉ ነገሮች ቢኖሩም እናንተ ግን ጽኑ (እንዲጸና የሚነገረው ጽናቱ ለተፈተነ ሰው ነው)፤ በርቱ ለመንቃት እንዲሁም ለመጽናት ብርታት ይጠይቃል፤ ጠንክሩ በቦታ ለመቆየት እንዲሁም ለመጽናት ጥንካሬ ያሻል፡፡
የምናደርገውን ሁሉ ደግሞ በፍቅር እንድናደርግ ይመከራል፤ ምክንያቱም ፍቅር የሁሉም ነገር ማሰርያ ነው፡፡ ያለፍቅር የምናደርገው ነገር መጨረሻው ጥሩ እንደማይሆን ሁሉ በፍቅር የምናድርገው ነገር ውጤቱ ሁልጊዜም ጥሩ ይሆናል፡፡
#discipleship_motivation
#higher_mission
1 ቆሮንቶስ 16:13-14 NASV
ጳውሎስ የመጀመሪያው የቆሮንቶስን መልዕክት ሲጨርስ ነበር ይህን የተናገረው፡፡ በመጨረሻም እንደማለት ነው፤ ንቁ እምነታችሁን ለማጥፋት የሚፈልጉ ሃይላትን እንዲታውቁ፤ በእምነታችሁ ጽኑ ብዙ የሚያሰናክሉ ነገሮች ቢኖሩም እናንተ ግን ጽኑ (እንዲጸና የሚነገረው ጽናቱ ለተፈተነ ሰው ነው)፤ በርቱ ለመንቃት እንዲሁም ለመጽናት ብርታት ይጠይቃል፤ ጠንክሩ በቦታ ለመቆየት እንዲሁም ለመጽናት ጥንካሬ ያሻል፡፡
የምናደርገውን ሁሉ ደግሞ በፍቅር እንድናደርግ ይመከራል፤ ምክንያቱም ፍቅር የሁሉም ነገር ማሰርያ ነው፡፡ ያለፍቅር የምናደርገው ነገር መጨረሻው ጥሩ እንደማይሆን ሁሉ በፍቅር የምናድርገው ነገር ውጤቱ ሁልጊዜም ጥሩ ይሆናል፡፡
#discipleship_motivation
#higher_mission
👏3
“የርኅራኄ አባት፣ የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ። እኛ ራሳችን ከእግዚአብሔር በተቀበልነው መጽናናት፣ በመከራ ያሉትን ማጽናናት እንድንችል፣ እርሱ በመከራችን ሁሉ ያጽናናናል።”
2 ቆሮንቶስ 1:3-4 NASV
ሐዋሪያው ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ሁለተኛውን ደብዳቤ ስጽፍ በመጽናናት ይጀምራል፡፡ ከምንም በላይ የመጽናናት ሁሉ ምንጭ የሆነውን እንዲሁም በመከራ ሁሉ ያጽናናቸውን እግዚአብሔርን በማመስገን ይጀምርና እነርሱ የተጽናኑት ለሌችን ለማጽናናት እንደሆነ በመናገር በጣም ቁልፍ መሪህ ያነሳል፡፡ እኛ የምንጽናናው ሌሎችን ለማጽናናት ነው፡፡ ይሄ ማለት የተጽናናን ሰዎች በሙሉ የማጽናናት አቅሙም ሆነ አላፊነቱን አለን ማለት ነው፡፡
#daily_pasture
#higher_mission
#discipleship_motivation
2 ቆሮንቶስ 1:3-4 NASV
ሐዋሪያው ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ሁለተኛውን ደብዳቤ ስጽፍ በመጽናናት ይጀምራል፡፡ ከምንም በላይ የመጽናናት ሁሉ ምንጭ የሆነውን እንዲሁም በመከራ ሁሉ ያጽናናቸውን እግዚአብሔርን በማመስገን ይጀምርና እነርሱ የተጽናኑት ለሌችን ለማጽናናት እንደሆነ በመናገር በጣም ቁልፍ መሪህ ያነሳል፡፡ እኛ የምንጽናናው ሌሎችን ለማጽናናት ነው፡፡ ይሄ ማለት የተጽናናን ሰዎች በሙሉ የማጽናናት አቅሙም ሆነ አላፊነቱን አለን ማለት ነው፡፡
#daily_pasture
#higher_mission
#discipleship_motivation
🙏2
ኤፌ። 2:10፣
10
እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይንኩ።
https://cherinat.wixsite.com/highermission/post/discovering-your-life-purpose
10
እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይንኩ።
https://cherinat.wixsite.com/highermission/post/discovering-your-life-purpose
Highermission
Discovering Your Life Purpose
"For we are His workmanship, created in Christ Jesus for good works, which God prepared beforehand, that we should walk in them." Ephesians 2:10In a world overflowing with distractions and expectations, the search for life purpose can feel overwhelming.…
❤2👏1