Higher Mission Ministries (HMM)
140 subscribers
32 photos
6 links
This is the official channel of higher mission ministries. On this channel you will get motivation, idea about life purpose and missions. follow us for more insights on Life purpose. we will share timely news and informations too.
Download Telegram
“Jesus said to the Jews who believed in him, “You are truly my disciples if you remain faithful to my teaching. Then you will know the truth, and the truth will set you free.”
John 8 : 31 - 32 CEB
Knowledge of him #truth will set us free. And that knowledge comes from #remaining in him, which is true #discipleship.

#discipleship_motivations.
Channel photo updated
#love
“Love is #patient, love is #kind. It does not #envy, it does not #boast, it is not #proud. It does not #dishonor others; it is not #self-seeking; it is not easily #angered; it keeps no #record of wrongs. Love does not delight in #evil but rejoices with the #truth. It always #protects, always #trusts, always #hopes, always #perseveres. Love never #fails.
1Cor. 13:4-87 NIV

#love love love!
#discipleship_inspirational
Discipleship is a lifetime journey. Like the natural process, spiritual life starts with being #born again. No one is born as an adult; we all start as infants and grow. In other words, #discipleship is the growth process. We grow to the fullness of Christ, as the Bible says.
So, what stage of growth are you at? Is your growth average? How healthy is your spirit?
Think about such questions.
#discipleship_motivations
Absolutely, prayer is simply not a matter of words. It involves approaching God with complete honesty and humility.
Forwarded from 4 one (Aman €bo)
"እውነተኛ ጸሎት የሚለካው በርዝመቱ አይደለም። እንደ እግዚአብሔር ሃሳብ ካልሆነ፣ በምርጥ ቃላት ከታጀበ የረዥም ጊዜ መነብነብ ይልቅ፣ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የወጣች አንዲት የምጥ ጩኸት የእግዚአብሔርን ልብ የሚሞላ የከበድ ጸሎት ልትሆን ትችላለች"
@one_died_for_all
@one_died_for_all
@one_died_for_all
“Now those who #belong to #Christ Jesus have #crucified the #flesh with its passions and desires.”
Galatians 5:24 CSB

If we are true disciples of Christ, we will #crusify our flash with its desires.
#discipleship_inspirational
“እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፤ ሰውነታችሁን ቅዱስና እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሕያው መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፤ ይህም እንደ ባለ አእምሮ የምታቀርቡት አምልኳችሁ ነው።”
ሮሜ 12:1 NASV
#discipleship_inspirational
“Finally, brothers, whatever is true, whatever is #honorable, whatever is #just, whatever is #pure, whatever is #lovely, whatever is #commendable, if there is any #excellence, if there is anything worthy of #praise, @THINK about these things.”
Philippians 4:8 ESV
#discipleship_motivations
#Do your #best to #present_yourself to #God as one #approved, a #worker who #does_not need to be #ashamed and who correctly handles the #word of #truth.”
2 Timothy 2:15 NIV
"ዛሬ ብዳዊት ከተማ #ምድኅን ተወልዶላችኋልና፤ እርሱም ጌታ ክርስቶስ ነው።" ሉቃ. 2:11። የተወለደው የዛሬ ሁለት ሺህ አመት ቢሆንም #ዛሬም አዳኛችን ነው። መልካም የጌታችን ልደት መትሰቢያ በዓል ይሁንላችሁ። 🎄
"...እናንተ ግን የድካማችሁን ዋጋ ስለምታገኙ በርቱ፤ እጃችሁም አይላላ።" 2ዜና 15:7

እግዚአብሔር የመሪህ አምላክ ነው። በእርሱ ዘንድ በንጻ መድከም የለም፤ ሁሌም ድካም ያስከፍላል። ስለዚህ በእርሱ ፊት የምትተጉ የምትደክሙ ደስ በርቱ፣ ጽኑም በመጨረሻው ዋጋችሁን እግዚአብሔር ይከፍላል።
#የእለት_ስንቅ #Daily_pasture #discipleship_motivations
" ሰው #በአንደበቱ ፍሬ ሆዱ ይጠግባል፤ በከንፈሩም ምርት ይረካል። #አንደበት የሞትና የሕይወት ኀይል አላት፤ የሚወድዷትም ፍሬዋን ይበላሉ።" ምሳሌ 18:20-21

#አንደበት በጣም ወሳኝ የህይወታችን ክፍል ናት። ራሳችንን ለመግለጽ ወይም እኛን ለማሳየት የአንበሳውን ድርሻ የሚጫወት #አንደበት ነው፤ ለምሳሌ ማን እንደሆንን፣ ምን እንደምንወድ፣ ምን እንደምችል፣ ስለሌሎች ያለን አመለካከት እና የመሳሰሉ ነገሮችን በመናገር ሰዎች ስለእኛ ያላቸውን አመለካከት እንገነባለን። ይህም የሚያሳየው በሌሎች ዘንድ ራሳችንን ለመሳል/ ለማስተዋወቅ አንደበት ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ #አንደበትን መግታት/ መቆጣጠር ቀላል አይደለም። ራስን መግዛት #አንደበት መግዛትን ይጨምራል፤ ይህንን ደግሞ ማድረግ ካልቻልን ደግሞ ለብዙ ችግር ልያጋልጠን ይችላል። የምንረካውም ሆነ የምንጠግበው #በአንደበታችን ፍሬ ስለሆነ #በአንደበታችን ለምንዘራው ነገር በጣም መጠንቀቅ ያስፈልገናል፤ ሰው የሚዘራውን ያንኑ ያጭዳልና።
#በአንደበታችን ህይወት ከዘራን ህይወትን እናጭዳለን፤ ሞትን ከዘራን እንዲሁ። ስለዚህ ልክ እንደልባችን ምናልባትም ከልብም በላይ #ለአንደበታችን መጠንቀቅ አለብን። ምክንያቱም #አንደበት ከእኛም አልፎ ሌሎችን ልጎዳ የሚችል ስለሆነ።

"#አንደበት የሞትና የሕይወት ኀይል አላት፤ የሚወድዷትም ፍሬዋን ይበላሉ።"
#Daily_pasture #discipleship_motivations #የእለት_ስንቅ
ለዘላለም በእግዚአብሔር መታመን
“በአንተ ላይ ታምናለችና፣ በአንተ የምትደገፈውን ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ። በእግዚአብሔር ለዘላለም ታመኑ፤ ጌታ እግዚአብሔር የዘላለም ዐለት ነውና።”
ኢሳይያስ 26:3-4 አ.መ.ት

እግዚአብሔር በርሱ የሚታመኑትን ያውቃልና በመከራ ቀን እንደሚደርስላቸው በሰላም እንደሚጠብቃቸው መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። ስለዚህ ለዘላለም በማንኛውም ሁኔታ በእርሱ እንታመን፤ እግዚአብሔር በችግር ጊዜ ብቻ የምንሮጥበት አይደለም፣ በደስታ ጊዜም ልንታመነው የሚገባ ነው እርሱ ታማኝ አለት ነውና። የዚያን ጊዜ ነፍሳችን ፍጹም ሰላም ታገኛለች።
#discipleship_motivations #daily_pasture #የእለት_ስንቅ
#ቃሉን ሰምቶ ማመን ይገባል

“እውነት እላችኋለሁ፤ #ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።”
ዮሐንስ 5:24 NASV

ኢየሱስ #ቃሉ እውነት እርሱም እውነት እንደሆነ ይናገራል፡፡ ኢየሱስ ከዚህ ቁጥር ከፍ ብሎ አብ መፍረድን ለወልድ(ለእርሱ) እንደሰጠ ይናገራል፡፡ ስለዚህ እንዲፈርድ የተሰየመውን ከአመንን ማንም አይፈድብንም፤ #ቃሉ እንደሚለውም በጭራሽ ለፍርድ አንቀርብም ማለት ነው፡፡ ምክንያቱ ዳኛው ራሱ ስለሆነ ጉዳዩን ወደፍርድ ቤት ሳይደርስ ያስቆመዋል፡፡ ይህ ግን የሚሆነው ቃሉን ሰምተን ላመንን ሰዎች ብቻ ነው፡፡ ምንን? እርሱ ወልድ ወይም ጌታ እንደሆነ፡፡ ስለዚህ #ቃሉን መስማት ብቻ ሳይሆን ማመንም ይጠበቃል ማለት ነው፤ #ቃሉ እውነት ስለሆነ፡፡

#የእለት_ስንቅ #discipleship_motivations #discipleship_inspirational #daily_pasture
ዋናው የሰንበት እረፍት ገና ይቀረናል

“ስለዚህ የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ ገና ቀርቶለታል፤ ምክንያቱም ወደ እግዚአብሔር ዕረፍት የሚገባ ሁሉ፣ እግዚአብሔር ከሥራው እንዳረፈ፣ እርሱም ደግሞ ከሥራው ያርፋል።”
ዕብራውያን 4:9-10 NASV

እያሱ እስራኤላውያንን አሳርፏል፤ ነገር ግን እረፍቱ ሙሉ አልነበርም በማለት ገና ለእነርሱም ታለቁ እረፍት/ሰንበት እንደሚቀርላቸው ይናገርና ለእግዚአብሔር ህዝብ ግን እረፍት ገና ይቀራል በማለት የደመድማል፡፡ እዚህ ላይ የተገለጸው እረፍት “Noah/ኖህ” የሀጥአት እረፍት ሳይሆን “Sabbath/ ሰንበት” ከሁሉም ነገር (ከጉልበት ስራ እስከ ሀጥአት) የሚናርፍበት እረፍት ነው፡፡ ይህም ዘላለማዊው የእግዚአብሔር እረፍት ነው፡፡ ይህም እረፍት እኛ የእግዚአብሔር ህዝብ ፍጹም የሆነ ሁሉን አቀፍ እረፍት የምናደርግበት ጊዜ፡፡ ይህንን ጊዜ በጉጉትና በናፍቆት እንጠብቃለን፡፡
#የእለት_ስንቅ
#discipleship_motivations
#daily_pasture
Forwarded from Cherinet N. Yatasa
“በጎ ስጦታና ፍጹም በረከት ሁሉ ከላይ፣ ከሰማይ ብርሃናት አባት ይወርዳሉ፤ በርሱ ዘንድ መለዋወጥ፣ ከመዞር የተነሣ የሚያርፍ ጥላም የለም።”
ያዕቆብ 1:17 NASV

እግዚአብሔር ምህረቱን አብዝቶልን ባለልጅ አደረገን። ስሟንም እርሱ ምሮናልና "ምህረት ቸርነት" ብለናታል።
1
በጎ ስጦታና ፍጹም በረከት ከእግዚአብሄር ብቻ

“በጎ ስጦታና ፍጹም በረከት ሁሉ ከላይ፣ ከሰማይ ብርሃናት አባት ይወርዳሉ፤ በርሱ ዘንድ መለዋወጥ፣ ከመዞር የተነሣ የሚያርፍ ጥላም የለም።”
ያዕቆብ 1:17 NASV

ብዙ አይነት ስጦታዎች አሉ፡፡ ከእነዚህ መካከል ግን በጎ የሆኑት እንዲሆን ከበረከትም ፍጹም የሆነ በረከት ከእግዚአብሄር (Exclusive) የሆኑ ናቸው፡፡ ማንም ምንም ሊባርክ ወይም ሊሰጥ ይችላል፤ ነገር ግን ፍጹም የሆነን አይደለም፡፡ ይህ ከእግዚአብሄር ብቻ ነው የሚመጣው፡፡
በረከት እንደሰጭው ማንነት ነው፡፡ እግዚአብሄር ብቻ በባህሪው ፍጹም ስለሆነ እርሱ ብቻ ነው ፍጹም የሆነ ስጦታና በረከት እንደፍቃዱ ሊሰጥ የሚችለው፡፡ በሌላ አባባል ከእግዚአብሄር የምንቀበለው በረከት ብቻ ነው ሁሌም ፍጹም የሚሆነው ሌላው ግን ባለብዙ እንከን ነው፡፡ ደስታውም አጭር ነው፡፡ ስለዚህም ለፍጹም እና ዘላቂ ደስታ የእርሱን በረከት እንደፈቃዱ እንጠብቅ፡፡

#የእለት_ስንቅ
#daily_pasture
#discipleship_motivations
መልካም የሆነውን እንጂ ክፉውን አትምሰል፡፡

“ወዳጅ ሆይ፤ መልካም የሆነውን እንጂ ክፉውን አትምሰል። መልካም የሆነውን የሚያደርግ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው። ክፉ የሚያደርግ ግን እግዚአብሔርን አላየውም።”
3 ዮሐንስ 1:11 NASV

ሶስተኛዉ የዮሃንስ ምልክት የተጻፈጽ ጋዮስ ለሚባል ሰው ሲሆን ዋናው ሀሳብም አገልጋዮችን እንዲቀበል ስለመጠየቅ ነው፡፡ ዮሐንስ ለጋዮስ በግል የጻፈለት ሲሆን ቤተክርስትያን እንዳትቀበል የሚያደርግ አንድ ዲዮጥራጥስ የሚባል ሰው እንዳለ እና እርሱም የዚያን ሰው ክፉ ስራ እንዳይከተልም ያሳስበዋል፡፡
ዮሐንስ ወዳጁን ጋዮስን ሲመክረው ክፉ ማድረግ እግዚአብሔርን አለማወቅ እንደሆነና ዲዮጥራጥስ በቤተክርስትያን በይፋ ስላደረገ ይህንን መከተል እንደሌለበት ይነግረዋል፡፡ ዲዮጥራጥስ መሪ መሆን የሚወድ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ሰው ቢሆንም እግዚአብሔርን እንደማያውቅና ጋዮስም ሊከተለው እንደማይገባ ያሳስባል፡፡
በቤተክርስትያን ብዙ አይነት ሰዎችን እናገኛለን፤ ሁሉንም በቅንነት ከሚቀበሉ ደግ ሰዎችን እስከ ሁሉንም ነገር ክፉ የሚያስመሱ እንደ ዲዮጥራጥስ አይነት ሰዎችን፡፡ ነገር ግን እኛ የተጠራነው እግዚአብሔርን ለመምሰል እንጂ ሰዎችን ለመምሰል/ ለመከተል አይደለም፡፡
እግዚአብሔርን ማወቃችን የሚለካበት ቀላሉ ሚዛን መልካም ስራ ነው፡፡ ዮሐንስ ሲያብራራ እግዚአብሔርን አይቶ/ አውቆ ክፉ የሚያደርግ ሰው የለም ይላል፡፡ ስለዚህ እንደጥቁር እና ነጭ ወይ ታውቃለህ ወይ አታውቅም ነው፡፡
በፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ እንዳለው ቃሉ ፍሬያችን ነው የሚገልጠን ማለት ነው፡፡
1🔥1
ከተመካን አይቀር በድካማችን

“እርሱ ግን፣ '#ጸጋዬ ይበቃሃል፤ ኀይሌ ፍጹም የሚሆነው በድካም ጊዜ ነውና' አለኝ። ስለዚህ የክርስቶስ ኀይል በእኔ ያድር ዘንድ፣ ይበልጥ ደስ እያለኝ በድካሜ እመካለሁ። ስለ ክርስቶስ በድካም፣ በስድብ፣ በመከራ፣ በስደትና በጭንቀት ደስ የምሠኘው ለዚህ ነው፤ ስደክም ያን ጊዜ ብርቱ ነኝና።”
2 ቆሮንቶስ 12:9-10 NASV

ሐዋሪያው ጳውሎስ ከላይ ‌እርሱ ስለራሱ እንደማይመካ ያትትና ትምክቱን ለመግታት ጌታ እንደሚጠቀምበት ስለሚያምነው የስጋ መውጊያው ይናገራል፡፡ ጌታም ሁሌ #ጸጋዬ ይበቃሃል እንዲሁም ሀይሌ በድካምህ ጎልቶ ይታያል እንደሚለው በማከል ከድካሙ በቀር እንደማይመካ ይናገራል፡፡

ሐዋሪያው ጥሩ ሃላብ ያነሳል ብመካ ብዙ ትምክህት እንዳለው እና በባዶ እንዳልሆነ፤ ነገር ግን ይህ የግሉ ሳይሆን #የጸጋው ስራ ስለሆነ ሰዎች በእሱ እንዲያውቁት እንደማይፈልግ፡፡ ሊታይ የሚገባው እርሱ ሳይሆን ጌታ እንደሆነ ያምናል፡፡