ግዜ አንደበት ኖሮት ብሶቱን ቢናገር
ተበዳይ በሰው ልጅ እኔ ነኝ ይል ነበር
እራሳቸው ከፍተው ዘመን ለሚከሱ
ሰው ነው ተጠያቂ ነበር ግዜ መልሱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ተበዳይ በሰው ልጅ እኔ ነኝ ይል ነበር
እራሳቸው ከፍተው ዘመን ለሚከሱ
ሰው ነው ተጠያቂ ነበር ግዜ መልሱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍10
#የጠላ_ስባቱ
አንቺው ጠላ ጠምቀሽ አስክረሽ አስክረሽ
ትዳር ስጠይቅሽ ሰካራም አልወድም ለምን ትይኛለሽ?
የቀመምሽው አንቺ በብቅል በጌሾ
ሰካራም አይደለም ለካ አንቺ ነሽ ዋሾ
እርሱማ ይጠጣል የልቡን ሊናገር
ሰካራም ከሌለ መች ታምራለች ሀገር
ማስከር አይደለም ወይ የጠላ ስባቱ
አጠማመቅሽ ነው ያሶደደሽ እቱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
አንቺው ጠላ ጠምቀሽ አስክረሽ አስክረሽ
ትዳር ስጠይቅሽ ሰካራም አልወድም ለምን ትይኛለሽ?
የቀመምሽው አንቺ በብቅል በጌሾ
ሰካራም አይደለም ለካ አንቺ ነሽ ዋሾ
እርሱማ ይጠጣል የልቡን ሊናገር
ሰካራም ከሌለ መች ታምራለች ሀገር
ማስከር አይደለም ወይ የጠላ ስባቱ
አጠማመቅሽ ነው ያሶደደሽ እቱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍21❤8
በቅን ሰው ልቦና በቅን ሰው አንደበት
ሲነገር ደስ ይላል ማርማር ይላል እውነት
በአስመሳዮች ምላስ መሀላ ሲሰደር
ሀሰት መሆኑን ነው የሌለው ቁምነገር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ሲነገር ደስ ይላል ማርማር ይላል እውነት
በአስመሳዮች ምላስ መሀላ ሲሰደር
ሀሰት መሆኑን ነው የሌለው ቁምነገር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍12
#ጥላችን_አይደለም
በህይወት ጎዳና ፈጥነን ስንራመድ
ወይም በዝግታ በሀሳብ ስንሄድ
ስንቆም የሚቆመው ሲመሽ የማናየው
ጥላችን አይደለም ለካስ ሞታችን ነው!
የሚከታተለን በእርምጃችን መጠን
ስንፈጥን ስንዘገይ ሁሌ ሚከተለን
ጥላችን አይደለም የምስላችን ቅኔ
ሞታችን ነው ባይ ነኝ እንደገባኝ እኔ
ሲመሽ ተደብቆ ሲነጋ ተገልጦ
ስንተኛ ተኝቶ ስንሮጥ እሮጦ
የያዝነውን ይዞ ስንበላ በልቶ
ሁልግዜም አብሮን ነው ሞታችን አድብቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
በህይወት ጎዳና ፈጥነን ስንራመድ
ወይም በዝግታ በሀሳብ ስንሄድ
ስንቆም የሚቆመው ሲመሽ የማናየው
ጥላችን አይደለም ለካስ ሞታችን ነው!
የሚከታተለን በእርምጃችን መጠን
ስንፈጥን ስንዘገይ ሁሌ ሚከተለን
ጥላችን አይደለም የምስላችን ቅኔ
ሞታችን ነው ባይ ነኝ እንደገባኝ እኔ
ሲመሽ ተደብቆ ሲነጋ ተገልጦ
ስንተኛ ተኝቶ ስንሮጥ እሮጦ
የያዝነውን ይዞ ስንበላ በልቶ
ሁልግዜም አብሮን ነው ሞታችን አድብቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👏19❤1
እንዴው ያንተ ስራ እንዴው ያንተ ነገር
ምን ቃል ይገልጸዋል ከመደነቅ በቀር
አበቃልህ ሲለኝ ሰይጣን በሹክሹክታ
ፈጥነህ ትደርሳለህ እኔ እንደበረታ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ምን ቃል ይገልጸዋል ከመደነቅ በቀር
አበቃልህ ሲለኝ ሰይጣን በሹክሹክታ
ፈጥነህ ትደርሳለህ እኔ እንደበረታ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
🥰12👍4💯2
#ግጥምና_ገጣሚ
የብዙ ሀሳብ ሸክም በጥቂት አብራርቶ
በስንኝ በቀለም በፊደል ቤት መትቶ
ግጥም ይናገራል ቃላት ሳያበዛ
በቅኔ እያስዋበ በዜማ እያዋዛ
ገጣሚ ስሜቱን
ደስታ ሀዘኑን
ቁጥብ ቃል አምጦ
እንባ ሳቁን ውጦ
በጥቂት ስንኞች ይናገራል ብዙ
የእርሱ ሽልማቱ ብዕር ነው አልማዙ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
የብዙ ሀሳብ ሸክም በጥቂት አብራርቶ
በስንኝ በቀለም በፊደል ቤት መትቶ
ግጥም ይናገራል ቃላት ሳያበዛ
በቅኔ እያስዋበ በዜማ እያዋዛ
ገጣሚ ስሜቱን
ደስታ ሀዘኑን
ቁጥብ ቃል አምጦ
እንባ ሳቁን ውጦ
በጥቂት ስንኞች ይናገራል ብዙ
የእርሱ ሽልማቱ ብዕር ነው አልማዙ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍7❤2👏2
የሰው ልጅ መለኪያው ካልሆነ ምግባሩ
አይድንም ከሀጢአት ቢሸሸግ በዘሩ
መጽደቅ መኮነኑ በሰራው ስራ ነው
የሁሉም መጠሪያ ሰው ሰውነቱ ነው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
አይድንም ከሀጢአት ቢሸሸግ በዘሩ
መጽደቅ መኮነኑ በሰራው ስራ ነው
የሁሉም መጠሪያ ሰው ሰውነቱ ነው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
🥰15👍3
#ቅበጭ_እንደ_ልብሽ
በጫንቃዬ ለዋልሽ ሸክሙ ላልከበደኝ
ቅብጠትሽ የመጨ እኔን ከተመቸኝ
ምን አርጊ ይሉሻል? ቢሉሽም ተያቸው
በእራሴ ትክሻ ምን ቁርጥ አርጓቸው?
ቅበጭ እንደ ልብሽ ደስ ይበልሽ በርቺ
ተከፍተሽ ሳይሽ ነው የሚጨንቀኝ ላንቺ
ምን ይሉኝ አትበይ ካሉሽም ተያቸው
እነርሱን ካልነካሽ ምን ጥልቅ አርጓቸው?
እንኳንስ ጫንቃዬን ልቤንም ወስደሻል
ገና እጨምራለሁ ላንቺ እኮ ያንስሻል
ብቻ አደራ ውዴ ከሌላ አትቅበጭ
በእኔ ሰውነት ላይ ሰክነሽ ተቀመጭ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
በጫንቃዬ ለዋልሽ ሸክሙ ላልከበደኝ
ቅብጠትሽ የመጨ እኔን ከተመቸኝ
ምን አርጊ ይሉሻል? ቢሉሽም ተያቸው
በእራሴ ትክሻ ምን ቁርጥ አርጓቸው?
ቅበጭ እንደ ልብሽ ደስ ይበልሽ በርቺ
ተከፍተሽ ሳይሽ ነው የሚጨንቀኝ ላንቺ
ምን ይሉኝ አትበይ ካሉሽም ተያቸው
እነርሱን ካልነካሽ ምን ጥልቅ አርጓቸው?
እንኳንስ ጫንቃዬን ልቤንም ወስደሻል
ገና እጨምራለሁ ላንቺ እኮ ያንስሻል
ብቻ አደራ ውዴ ከሌላ አትቅበጭ
በእኔ ሰውነት ላይ ሰክነሽ ተቀመጭ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍10❤5🥰4
#በግድ_ፈገግ_በሉ
ሳይወዱ እየሳቁ ሰዎች ከተነሱ
እኛስ ምን ይለና ብንማር ከእነርሱ
ውስጣችን አኩርፎ ጥርሳችን ይፈግግ
ኑ ፎቶ እንነሳ አትያዙ ጥግ ጥግ
ሰብሰብ እንበልና የውሸት እንሳቅ
እኛም እንደ ሰዎች ውስጥን በመደበቅ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ሳይወዱ እየሳቁ ሰዎች ከተነሱ
እኛስ ምን ይለና ብንማር ከእነርሱ
ውስጣችን አኩርፎ ጥርሳችን ይፈግግ
ኑ ፎቶ እንነሳ አትያዙ ጥግ ጥግ
ሰብሰብ እንበልና የውሸት እንሳቅ
እኛም እንደ ሰዎች ውስጥን በመደበቅ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
❤11👍2
#ስንቱ_ቀልጦ_ቀረ
በኩርማን እንጀራ ሰው እየተሸጠ
ከህሊና ይልቅ ሆድ እየበለጠ
ስንቱ እውነትን ክዶ ከሐሰት ተጋባ
በማስመሰል ለቅሶ ያአዞ እንባ እያነባ
ጭንቅላቱ ጎድሎ ሆዱን እየመሞላ
ከስግብግቦች ጋር በጋራ አየበላ
ስንቱ ቀልጦ ቀረ እውነት እየካደ
ከኩርማንም አልፎ ጮማ እየለመደ
ሆዱ እየሞላለት ህሊናው ሲከሰው
በፍርድ አደባባይ ሰው መሆን ሲወቅሰው
ስንቱ ቀልጦ ቀረ በግፍ መርከብ ገብቶ
ሆዱን እየሞላ ህሊናው ተራቁቶ!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
በኩርማን እንጀራ ሰው እየተሸጠ
ከህሊና ይልቅ ሆድ እየበለጠ
ስንቱ እውነትን ክዶ ከሐሰት ተጋባ
በማስመሰል ለቅሶ ያአዞ እንባ እያነባ
ጭንቅላቱ ጎድሎ ሆዱን እየመሞላ
ከስግብግቦች ጋር በጋራ አየበላ
ስንቱ ቀልጦ ቀረ እውነት እየካደ
ከኩርማንም አልፎ ጮማ እየለመደ
ሆዱ እየሞላለት ህሊናው ሲከሰው
በፍርድ አደባባይ ሰው መሆን ሲወቅሰው
ስንቱ ቀልጦ ቀረ በግፍ መርከብ ገብቶ
ሆዱን እየሞላ ህሊናው ተራቁቶ!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍5❤4
እኔው ለኔ አልቅሼ እኔው ለኔ ስቄ
በውጣ ውረዱ ታሪኬን አድምቄ!!!
ዛሬን አይቻለሁ ትላንትን አልፌ
ጊዜን እየቆጠርኩ ቀናትን ገፍፌ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
በውጣ ውረዱ ታሪኬን አድምቄ!!!
ዛሬን አይቻለሁ ትላንትን አልፌ
ጊዜን እየቆጠርኩ ቀናትን ገፍፌ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
❤7🔥4👍3🥰2👏1
"#ጀግና_ምን_አባቱ " 😂
ጀግና በመፈለግ ዘመን አትቁጠሪ
አጠገብሽ አለሁ እኔ ያንቺ ፈሪ
ጥሎሽ ከሚሄደው ሞት እያሸተተ
እያልሽ ከምትሰጊ ዛሬ ነገ ሞተ
እኔ እሻልሻለሁ የአጠገብሽ ፈሪ
በፎከረ ቁጥር ከምትደነብሪ
ጀግና ባል አይሆንም ሀገሩ ናት ሚስቱ
ተረጋግቶ አይተኛም አይገደው ህይወቱ
ይልቅ ነይ ልቀፍሽ ጋደም በይ ከጎኔ
ጀግና ምን አባቱ አለሁልሽ እኔ ¡።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ጀግና በመፈለግ ዘመን አትቁጠሪ
አጠገብሽ አለሁ እኔ ያንቺ ፈሪ
ጥሎሽ ከሚሄደው ሞት እያሸተተ
እያልሽ ከምትሰጊ ዛሬ ነገ ሞተ
እኔ እሻልሻለሁ የአጠገብሽ ፈሪ
በፎከረ ቁጥር ከምትደነብሪ
ጀግና ባል አይሆንም ሀገሩ ናት ሚስቱ
ተረጋግቶ አይተኛም አይገደው ህይወቱ
ይልቅ ነይ ልቀፍሽ ጋደም በይ ከጎኔ
ጀግና ምን አባቱ አለሁልሽ እኔ ¡።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👏10😁7❤5👍4
#አንተ_ብቻ_ሙት
የሚያኗኑር እንጂ የሌለው ዘንድሮ ፤
ቀባሪማ ሞልቷል በነፍስ ይማር ንፍሮ ፤
ብቻ አንተ ሙት እንጂ አታጣም ቀባሪ ፤
ሞልቷል አፈር መላሽ እልፍ አስተባባሪ ፤
ስትኖር ፊት አክብዶ ስትሞት ደረት ደቂ ፤
አንተን አያሳስብህ ለቅሶህን አድማቂ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
የሚያኗኑር እንጂ የሌለው ዘንድሮ ፤
ቀባሪማ ሞልቷል በነፍስ ይማር ንፍሮ ፤
ብቻ አንተ ሙት እንጂ አታጣም ቀባሪ ፤
ሞልቷል አፈር መላሽ እልፍ አስተባባሪ ፤
ስትኖር ፊት አክብዶ ስትሞት ደረት ደቂ ፤
አንተን አያሳስብህ ለቅሶህን አድማቂ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍12❤4
እንደ ሸማኔ መወርወሪያ ለሚፈጥነው እድሜ
በጥላቻ አልኖርም ክፋት ተሸክሜ!!!!
በይቅርታ ፀበል በፍቅር ተጠምቄ
ልሙት በንስሐ በደሌን አውቄ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
በጥላቻ አልኖርም ክፋት ተሸክሜ!!!!
በይቅርታ ፀበል በፍቅር ተጠምቄ
ልሙት በንስሐ በደሌን አውቄ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍16
#እንዲህም_ያምረኛል
የእራሴ ቀብር ቀን ጥሩንባ ማሰማት
ለቀስተኛው መሀል አብሮ ደረት መምታት
ማንበብ ህይወት ታሪክ ውሸት የሌለበት
ከድንኳን ውስጥ ቆሜ እድርተኛ መጥራት
በእራሴ ቀብር ላይ እንዲህ ይዳዳኛል
ሞቴን ቆሞ ማየት አለቅጥ ያምረኛል
አልቃሽ አሽሟጣጩን ካልታዘብክ ይለኛል
ያሁን በሽተኛ እንዲህ ያሰኘኛል
የማያምር ነገር በድንገት ያምረኛል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
የእራሴ ቀብር ቀን ጥሩንባ ማሰማት
ለቀስተኛው መሀል አብሮ ደረት መምታት
ማንበብ ህይወት ታሪክ ውሸት የሌለበት
ከድንኳን ውስጥ ቆሜ እድርተኛ መጥራት
በእራሴ ቀብር ላይ እንዲህ ይዳዳኛል
ሞቴን ቆሞ ማየት አለቅጥ ያምረኛል
አልቃሽ አሽሟጣጩን ካልታዘብክ ይለኛል
ያሁን በሽተኛ እንዲህ ያሰኘኛል
የማያምር ነገር በድንገት ያምረኛል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
😁10👍7🥰4❤2😎2
ሁሉም የድርሻውን ቂም እያወረሰ
በዘር ዛር ጥንቆላ ተግቶ እየረከሰ
ተስፋ ላጣ ትውልድ ሀገር አስረክቦ
በጥላቻ ሰክሯል ፍቅር ግን ተርቦ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
በዘር ዛር ጥንቆላ ተግቶ እየረከሰ
ተስፋ ላጣ ትውልድ ሀገር አስረክቦ
በጥላቻ ሰክሯል ፍቅር ግን ተርቦ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👏5❤3👍1
#መጽሐፉ_ፊቱ_ነው
የህይወት ቀለሙ ባይሳል በሸራ
ከሰው ፊት ተጽፏል እውነትን ሊያወራ
በእድሜ ብዕር ቀለም በገጽ የታተመ
ያሳለፈው እውነት በስሎ የቀለመ
የህይወት ታሪኩ መጽሐፉ ፊቱ ነው
ከልብ መርምሮ ጠልቆ ላስተዋለው
ወጥቶ የወረደው የህይወት ድካሙ
የሰው የእውነት ገጹ እድሜው ነው ቀለሙ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
የህይወት ቀለሙ ባይሳል በሸራ
ከሰው ፊት ተጽፏል እውነትን ሊያወራ
በእድሜ ብዕር ቀለም በገጽ የታተመ
ያሳለፈው እውነት በስሎ የቀለመ
የህይወት ታሪኩ መጽሐፉ ፊቱ ነው
ከልብ መርምሮ ጠልቆ ላስተዋለው
ወጥቶ የወረደው የህይወት ድካሙ
የሰው የእውነት ገጹ እድሜው ነው ቀለሙ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍6❤2
የተመረቃችሁ ከፊት እኛን ምሩ
ጥላቻን ንቃችሁ ፍቅር አስተምሩ
ሰላም ሰላም በሉ ኬር ይሁን ሀገሩ
ተመስገን ማለት ነው ዋናዉ ቁም ነገሩ
ስራ እንኳን ቢጠፋ በእግዚአብሔር ተማሩ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ጥላቻን ንቃችሁ ፍቅር አስተምሩ
ሰላም ሰላም በሉ ኬር ይሁን ሀገሩ
ተመስገን ማለት ነው ዋናዉ ቁም ነገሩ
ስራ እንኳን ቢጠፋ በእግዚአብሔር ተማሩ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍9🔥5🥰2👏1😭1