🙏16❤2
#ከመሄድሽ_በፊት
ካንች ቃል ከወጣ ትተሽኝ ለመሄድ
ልብሽ ከወሰነ ከጀመረ መንገድ
ቅሪም አልልሽም
አላስገድድሽም
መንገድሽ ጨርቅ ይሁን ክፉም አይግጠምሽ
ህይወትሽ አይጉደል ኑሮሽ ይስመርልሽ
ከእኔ የተሻለ አዛኝ ሰውን ይስጥሽ
ግን ውዴ ነገ ብትመለሽ.....
አንችን እየጠበኩ ላይሆን ስለሚችል
🚶♀➡️ ከመሄድሽ በፊት....
አርቀሽ አስቢ ተስፋን ፊት አትንሻት
ስሜትን ኮንኚው በእርጋታ ዳኝነት
ለወሬ ጆሮ አትስጭ ምቀኛን አትስሚ
በዛሬ ስሜትን ለነገ አትጨልሚ
በትዕግስት መድሀኒት ኑሮሽን አክሚ
🚶♀➡️ከመሄድሽ በፊት.....
ስላለፈው ኑሮ ስላለፈው ፍቅር
ትዝታን ጠይቂው " ልሂድ? ወይስ ልቅር? "
መልሱን ይነግርሻል
ያኔ ይገባሻል
መቼም ተምረሻል
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ካንች ቃል ከወጣ ትተሽኝ ለመሄድ
ልብሽ ከወሰነ ከጀመረ መንገድ
ቅሪም አልልሽም
አላስገድድሽም
መንገድሽ ጨርቅ ይሁን ክፉም አይግጠምሽ
ህይወትሽ አይጉደል ኑሮሽ ይስመርልሽ
ከእኔ የተሻለ አዛኝ ሰውን ይስጥሽ
ግን ውዴ ነገ ብትመለሽ.....
አንችን እየጠበኩ ላይሆን ስለሚችል
🚶♀➡️ ከመሄድሽ በፊት....
አርቀሽ አስቢ ተስፋን ፊት አትንሻት
ስሜትን ኮንኚው በእርጋታ ዳኝነት
ለወሬ ጆሮ አትስጭ ምቀኛን አትስሚ
በዛሬ ስሜትን ለነገ አትጨልሚ
በትዕግስት መድሀኒት ኑሮሽን አክሚ
🚶♀➡️ከመሄድሽ በፊት.....
ስላለፈው ኑሮ ስላለፈው ፍቅር
ትዝታን ጠይቂው " ልሂድ? ወይስ ልቅር? "
መልሱን ይነግርሻል
ያኔ ይገባሻል
መቼም ተምረሻል
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤25👏6👍2🥰1
የመኖር ፈተና ምንም ቢያንገዳግድ
አታካችም ቢሆን መውጣት እና መውረድ
ነብሴን ልታደጋት ህይወቴን ዘክሬ
ሞቴም ትንሳኤ ነው በህያው መኖሬ
እኔስ ላይቀር ማለፌ
ነበርን አትርፌ
ለመሞት አልኖርም
ለመኖር ነው ሞቴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ መኮንን
አታካችም ቢሆን መውጣት እና መውረድ
ነብሴን ልታደጋት ህይወቴን ዘክሬ
ሞቴም ትንሳኤ ነው በህያው መኖሬ
እኔስ ላይቀር ማለፌ
ነበርን አትርፌ
ለመሞት አልኖርም
ለመኖር ነው ሞቴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ መኮንን
❤16👏2
#ሚስቴ_እና_ሰበቧ!
ለስጋዋ ስትኖር
-- ነፍሷን አሞኝታ
አገኘዃትና
-- ስትሳም ተኝታ
ምነው ምን በደልኩሽ?
-- ብዬ ስጠይቃት
እግሯ ስር ወድቄ
-- በእንባ ስማጸናት
እንደለመደችው
-- ሰበብ አዘጋጅታ
አንተ መስለኸኝ ነው
-- አለችኝ ተነስታ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ለስጋዋ ስትኖር
-- ነፍሷን አሞኝታ
አገኘዃትና
-- ስትሳም ተኝታ
ምነው ምን በደልኩሽ?
-- ብዬ ስጠይቃት
እግሯ ስር ወድቄ
-- በእንባ ስማጸናት
እንደለመደችው
-- ሰበብ አዘጋጅታ
አንተ መስለኸኝ ነው
-- አለችኝ ተነስታ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
😁37👏4❤2🥰1
#ጥላችን_አይደለም
በህይወት ጎዳና ፈጥነን ስንራመድ
ወይም በዝግታ በሀሳብ ስንሄድ
ስንቆም የሚቆመው ሲመሽ የማናየው
ጥላችን አይደለም ለካስ ሞታችን ነው!
የሚከታተለን በእርምጃችን መጠን
ስንፈጥን ስንዘገይ ሁሌ ሚከተለን
ጥላችን አይደለም የምስላችን ቅኔ
ሞታችን ነው ባይ ነኝ እንደገባኝ እኔ
ሲመሽ ተደብቆ ሲነጋ ተገልጦ
ስንተኛ ተኝቶ ስንሮጥ እሮጦ
የያዝነውን ይዞ ስንበላ በልቶ
ሁልግዜም አብሮን ነው ሞታችን አድብቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
በህይወት ጎዳና ፈጥነን ስንራመድ
ወይም በዝግታ በሀሳብ ስንሄድ
ስንቆም የሚቆመው ሲመሽ የማናየው
ጥላችን አይደለም ለካስ ሞታችን ነው!
የሚከታተለን በእርምጃችን መጠን
ስንፈጥን ስንዘገይ ሁሌ ሚከተለን
ጥላችን አይደለም የምስላችን ቅኔ
ሞታችን ነው ባይ ነኝ እንደገባኝ እኔ
ሲመሽ ተደብቆ ሲነጋ ተገልጦ
ስንተኛ ተኝቶ ስንሮጥ እሮጦ
የያዝነውን ይዞ ስንበላ በልቶ
ሁልግዜም አብሮን ነው ሞታችን አድብቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍17❤5🥰1👏1
" #ይስጥሽ"
ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ
ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ
ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ
ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤
ይስጥሽ ከፀጉሬ ከአናቴ ላይ ዘግኖ
ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ
አወይ ፀጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ
ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ
እቴ.....
ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ
ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ
ከዓይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ
እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ።
እቴ....
እጄን ብትፈልጊ እግሬን ብትፈልጊ
አንገቴን ደረቴን
ተሰጥኦ ሀሳቤን
ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ
እግዜር ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ
ያስቀርልኝ ዓይኔን
አንቺን ማየት ብቻ
ያኖረኛል እኔን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ
ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ
ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ
ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤
ይስጥሽ ከፀጉሬ ከአናቴ ላይ ዘግኖ
ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ
አወይ ፀጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ
ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ
እቴ.....
ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ
ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ
ከዓይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ
እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ።
እቴ....
እጄን ብትፈልጊ እግሬን ብትፈልጊ
አንገቴን ደረቴን
ተሰጥኦ ሀሳቤን
ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ
እግዜር ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ
ያስቀርልኝ ዓይኔን
አንቺን ማየት ብቻ
ያኖረኛል እኔን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤18👏7🔥2
#የኔን_ቀን_ገድዬ
የደላኝ መስዬ
ብሶቴን አምቄ
ወደ ውስጤ አልቅሼ
ቀን ብገፋ ስቄ
የኔ ባል ሞኝ ነው
ፍቅር ይሰጠኛል
ስጠላው አያውቅም
ብለሽ አምተሽኛል
በዚህ እኩይ አለም
አምላክ ፊት ቀርቤ
እኔ ለታማሁኝ
ደጁ ተንበርክኬ
የኔን ቀን ገድዬ
ለሷ እጨነቃለሁ
ይቅር በላት እያልኩ
ስፀልይ አድራለሁ
አታውቀውምና
እሷ የኔን ነገር
ከመኖር ያለፈ
እንዴት እንደምኖር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
የደላኝ መስዬ
ብሶቴን አምቄ
ወደ ውስጤ አልቅሼ
ቀን ብገፋ ስቄ
የኔ ባል ሞኝ ነው
ፍቅር ይሰጠኛል
ስጠላው አያውቅም
ብለሽ አምተሽኛል
በዚህ እኩይ አለም
አምላክ ፊት ቀርቤ
እኔ ለታማሁኝ
ደጁ ተንበርክኬ
የኔን ቀን ገድዬ
ለሷ እጨነቃለሁ
ይቅር በላት እያልኩ
ስፀልይ አድራለሁ
አታውቀውምና
እሷ የኔን ነገር
ከመኖር ያለፈ
እንዴት እንደምኖር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤21🥰2🔥1👏1
#ታውቂያለሽ_አይደለ?
ስላንቺ በማሰብ
ዘመኔ ማለፉን
አንቺን በመናፈቅ
እምባየ ማለቁን
አሻግሬ ሳይሽ
እይኔ መደብዘዙን
ኮቴሽን በማድመጥ
ጆሮየ መድከሙን
ታውቂያለሽ አይደለ
ቆሜ ስጠብቅሽ
ቆየኝ ባልሽኝ ስፍራ
በረዶና ዝናብ
በላየ እንዳባራ
እንቅልፍ አልባ
ቀናት በኔ እንደነጎዱ
ጀምበር ከጨረቃ እንደተዋሀዱ
አውቃለሁ አታውቂም አንዳቹንም ነገር
እኔ መውደድ እንጂ አልችልም መናገር፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዘላለም ምህረቱ
ስላንቺ በማሰብ
ዘመኔ ማለፉን
አንቺን በመናፈቅ
እምባየ ማለቁን
አሻግሬ ሳይሽ
እይኔ መደብዘዙን
ኮቴሽን በማድመጥ
ጆሮየ መድከሙን
ታውቂያለሽ አይደለ
ቆሜ ስጠብቅሽ
ቆየኝ ባልሽኝ ስፍራ
በረዶና ዝናብ
በላየ እንዳባራ
እንቅልፍ አልባ
ቀናት በኔ እንደነጎዱ
ጀምበር ከጨረቃ እንደተዋሀዱ
አውቃለሁ አታውቂም አንዳቹንም ነገር
እኔ መውደድ እንጂ አልችልም መናገር፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዘላለም ምህረቱ
❤15👍6🔥5👏2🥰1
#ቃል_ብዬ_ጠራሁሽ
ስላንች ለመፃፍ ብእር እቀርፅና
ቀለሙን አቅልሜ ፈቅፍቄ ብራና
ፊደልና ቃላት እንደልጅ እያማጥኩ
ሀረግ እየመዘዝኩ ምሳሌ እየጠቀስኩ
ቃል ባጣው ልሳኔ ስፅፍ ውዬ አድሬ
ገልጨሽ ሳይበቃኝ ትደርቃለች ብእሬ
ደግሞ ተመልሼ................
ደሜን አንጠፍጥፌ ቀለሙን አቀለምኩ
አጥንቴን ፈቅፍቄ ላንች ብእር ቀረፅኩ
ብእሬን በደሜ ነክሬ ሳወጣው
አንችን እገልፅበት ቅንጣት ቃላት አጣው
ለካንስ ቃልዬ!!!
በፍቅር ነሁልሎ መንፈስ ከደከመ
ናፍቆት አገርጥቶት ልብ ከታመመ
እንኳን ቃል ተዋቅሮ ቅኔ ሊመሰጠር
ደግሞ ስንኝ ሁኖ ግጥም ሊደረደር
ደህና አደርክ ሲባል ለእግዚአብሄር ይመስገን
አንደበት ቃል ያጣል ሲመርቁት ለአሜን
ለዛ ነው ቃልዬ!!!
መግለጫ ቃል ባጣ እልፍ ዘመን ሙሉ
የብራናዬ ገፅ ግራ ገብቶት ውሉ
እየደጋገምኩኝ የፃፍኩት አንድ ቃል
እ
ን
ዲ
ህ
ብቻ ይላል
ሌላ ቃል ተገኝቶ
ወይ ልሳንህ ፈቶ
ህቡእ በሆነ ቃል እስከምትገልፃት
ቃልህ እሷ ነችና ቃሌ ብለህ ጥራት
እናም አንች ቃሌ ነሽ ሀረግና ስንኝ
ካጠገቤ ሁነሽ ሰርክ የምትርቢኝ
እናም የኔ ንግስት
ገፅሽን አድምቄ በልቤ መዝገብ ላይ
ቃሌ ብዬ ፃፍኩሽ ቃል አጣው ቃሌ ላይ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ስላንች ለመፃፍ ብእር እቀርፅና
ቀለሙን አቅልሜ ፈቅፍቄ ብራና
ፊደልና ቃላት እንደልጅ እያማጥኩ
ሀረግ እየመዘዝኩ ምሳሌ እየጠቀስኩ
ቃል ባጣው ልሳኔ ስፅፍ ውዬ አድሬ
ገልጨሽ ሳይበቃኝ ትደርቃለች ብእሬ
ደግሞ ተመልሼ................
ደሜን አንጠፍጥፌ ቀለሙን አቀለምኩ
አጥንቴን ፈቅፍቄ ላንች ብእር ቀረፅኩ
ብእሬን በደሜ ነክሬ ሳወጣው
አንችን እገልፅበት ቅንጣት ቃላት አጣው
ለካንስ ቃልዬ!!!
በፍቅር ነሁልሎ መንፈስ ከደከመ
ናፍቆት አገርጥቶት ልብ ከታመመ
እንኳን ቃል ተዋቅሮ ቅኔ ሊመሰጠር
ደግሞ ስንኝ ሁኖ ግጥም ሊደረደር
ደህና አደርክ ሲባል ለእግዚአብሄር ይመስገን
አንደበት ቃል ያጣል ሲመርቁት ለአሜን
ለዛ ነው ቃልዬ!!!
መግለጫ ቃል ባጣ እልፍ ዘመን ሙሉ
የብራናዬ ገፅ ግራ ገብቶት ውሉ
እየደጋገምኩኝ የፃፍኩት አንድ ቃል
እ
ን
ዲ
ህ
ብቻ ይላል
ሌላ ቃል ተገኝቶ
ወይ ልሳንህ ፈቶ
ህቡእ በሆነ ቃል እስከምትገልፃት
ቃልህ እሷ ነችና ቃሌ ብለህ ጥራት
እናም አንች ቃሌ ነሽ ሀረግና ስንኝ
ካጠገቤ ሁነሽ ሰርክ የምትርቢኝ
እናም የኔ ንግስት
ገፅሽን አድምቄ በልቤ መዝገብ ላይ
ቃሌ ብዬ ፃፍኩሽ ቃል አጣው ቃሌ ላይ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤10👏3👍1🔥1🥰1
#ዘርን_ለማስቆጠር
እንጋባ አትበይኝ ግራ ገብቶኝ ሳለ፤
ተጋቦቶ ለመውለድ ነፃነት የት አለ?
ወልዶ ለመከበረ ጋብቻ ቅዱስ ነው፤
የሚወለደው ልጅ መኖሪያ ከሌለው!
በይ እስኪ ንገሪኝ? አንቺ ግራ ጎኔ፤
በነፃነት አድጎ ሰው በመባል ቅኔ፤
በኢትዮጵያዊነት ካልኮራ ዓይኔ በዐይኔ፤
ለመሳቀቅማ አይበቃም ወይ የእኔ።
ሀገርን ሳልሰራ ሰው መሆን ሳይቀድም፤
ዘርን ለማስቆጠር እኔስ ልጅ አልወልድም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
እንጋባ አትበይኝ ግራ ገብቶኝ ሳለ፤
ተጋቦቶ ለመውለድ ነፃነት የት አለ?
ወልዶ ለመከበረ ጋብቻ ቅዱስ ነው፤
የሚወለደው ልጅ መኖሪያ ከሌለው!
በይ እስኪ ንገሪኝ? አንቺ ግራ ጎኔ፤
በነፃነት አድጎ ሰው በመባል ቅኔ፤
በኢትዮጵያዊነት ካልኮራ ዓይኔ በዐይኔ፤
ለመሳቀቅማ አይበቃም ወይ የእኔ።
ሀገርን ሳልሰራ ሰው መሆን ሳይቀድም፤
ዘርን ለማስቆጠር እኔስ ልጅ አልወልድም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤10👏7👍1
#ፍቅር_አለቀሰ
ፍቅርን ስፈልገው ቀናቶች አለፉ
ፈለግኩት ፈለግኩት ድካም ሆነ ትርፉ
አጋጣሚ ሆኖ ተደብቆ አየሁት
አላምን ስላልኩኝ ምክንያቱን ጠየኩት
"ፍቅር አንተው ነህ ወይ?" ብዬ ብጠይቀው
ምንም መልስ ሳይመልስ እንባ ተናነቀው
ግራ ገባኝና ባግራሞት አየሁት
ቆይ ፍቅር ደስታ ነው ሲባል ሰምቻለሁ
ታድያ ያንተ ለቅሶ ከየት የመጣ ነው?
ፍቅርም መለሰልኝ አይኑን መሬት ተክሎ
መናገር ጀመረ ቃላትን ቀጣጥሎ
"ደስታማ ደስታ ነኝ ላወቀው ሚስጥሬን
ከደስታም በላይ ነኝ ከተረዱኝ እኔን
ያስለቀሰኝ ነገር ሆድ ሆዴን ያስባሰው
በኔ ስም መነገድ መቸ አቆመ ሰው
አፈቀርኩሽ ብሎ ሲዋሻት በኔ ስም
ማሬ ውዴ ብላ ከድታው ስትሄድ እሷም
በኔ ሲጫወቱ የሀሰት ጨዋታ
በኔ ሲባልጉ በኔ ስም ሲምታታ
በውሸት ዓለም ሆነው በኔ ስም ሲጠሩ
እንዴት አላነባ ካልረባ ነገሩ"
ብሎ መለሰልኝ ፍቅር በቀስታ
አንገቱን ቢያስደፉው የሀሰት ጨዋታ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ፍቅርን ስፈልገው ቀናቶች አለፉ
ፈለግኩት ፈለግኩት ድካም ሆነ ትርፉ
አጋጣሚ ሆኖ ተደብቆ አየሁት
አላምን ስላልኩኝ ምክንያቱን ጠየኩት
"ፍቅር አንተው ነህ ወይ?" ብዬ ብጠይቀው
ምንም መልስ ሳይመልስ እንባ ተናነቀው
ግራ ገባኝና ባግራሞት አየሁት
ቆይ ፍቅር ደስታ ነው ሲባል ሰምቻለሁ
ታድያ ያንተ ለቅሶ ከየት የመጣ ነው?
ፍቅርም መለሰልኝ አይኑን መሬት ተክሎ
መናገር ጀመረ ቃላትን ቀጣጥሎ
"ደስታማ ደስታ ነኝ ላወቀው ሚስጥሬን
ከደስታም በላይ ነኝ ከተረዱኝ እኔን
ያስለቀሰኝ ነገር ሆድ ሆዴን ያስባሰው
በኔ ስም መነገድ መቸ አቆመ ሰው
አፈቀርኩሽ ብሎ ሲዋሻት በኔ ስም
ማሬ ውዴ ብላ ከድታው ስትሄድ እሷም
በኔ ሲጫወቱ የሀሰት ጨዋታ
በኔ ሲባልጉ በኔ ስም ሲምታታ
በውሸት ዓለም ሆነው በኔ ስም ሲጠሩ
እንዴት አላነባ ካልረባ ነገሩ"
ብሎ መለሰልኝ ፍቅር በቀስታ
አንገቱን ቢያስደፉው የሀሰት ጨዋታ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤20👏9✍2🔥2🥰1
ጭር አለ ከተማው ጭር አለ መንገዱ
ያ ስምንተኛው ሽህ ተገለጠ ጉዱ
ሰው ሁሉ ተሳቆ ፈርቶት አንዱን አንዱ
እስከዚህ አይሎ ሰው ከሰው ሽሽቱ
ክተት ብሎ ገባ ሁሉም በየቤቱ
ጭር አለ መንገዱ ጭር አለ ከተማው
ክፉ ዘር ሲበዛ ይህን ነው የምንሰማው
እንለያይ ብለን ስንጮህ ስንፎክር
በዘር ተለያይተን አንዱ አንዱን ሲያባርር
ታሪክ እያዛባን ነገር ስንመነዝር
ኮሮና እብዱ መጣ እንደ ከብት የሚያጉር።
እንለያይ ብለን ይሄው ተለያየን
መሸሽ ጀምረናል ሰውን ሰው እያየን።
ሕሊናችን ሞቶ መለያየት ወደን
ሰው ሰውን ሸሸ በባይረስ ተገደን
ያ ስምንተኛው ሽህ ተገለጠ ጉዱ
ጭር አለ ከተማው ጭር አለ መንገዱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ መምህር ግርማ
ያ ስምንተኛው ሽህ ተገለጠ ጉዱ
ሰው ሁሉ ተሳቆ ፈርቶት አንዱን አንዱ
እስከዚህ አይሎ ሰው ከሰው ሽሽቱ
ክተት ብሎ ገባ ሁሉም በየቤቱ
ጭር አለ መንገዱ ጭር አለ ከተማው
ክፉ ዘር ሲበዛ ይህን ነው የምንሰማው
እንለያይ ብለን ስንጮህ ስንፎክር
በዘር ተለያይተን አንዱ አንዱን ሲያባርር
ታሪክ እያዛባን ነገር ስንመነዝር
ኮሮና እብዱ መጣ እንደ ከብት የሚያጉር።
እንለያይ ብለን ይሄው ተለያየን
መሸሽ ጀምረናል ሰውን ሰው እያየን።
ሕሊናችን ሞቶ መለያየት ወደን
ሰው ሰውን ሸሸ በባይረስ ተገደን
ያ ስምንተኛው ሽህ ተገለጠ ጉዱ
ጭር አለ ከተማው ጭር አለ መንገዱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ መምህር ግርማ
👍3❤2🫡2
ነድፋኛለች ብዬ - በውበቷ ምትሃት፣
በይፋ ከስሼ- ፍርድ እንዳላቀርባት
ለካስ እሷ ራሷ - መፅሐፍ ገላጭ ናት
ከፊት እሷን መሳይ - የጠይም ወላላ፣
በድንቡሽ ብርጭቆ - ወይን እየተሞላ፣
እሱን እየጠጡ -
ለሰስ ባለ ዜማ - እየተመሰጡ
ደግሞ በመሃሉ - እየተቃበጡ
ፍቅር ፍቅር ብቻ - እየመሰጠሩ፣
ዓለምን ረስተው - ምናለ ቢኖሩ፣
ጨለምለም ባለ የብርሃን ድባብ ውስጥ፤
እልም ብሎ መጥፋት - ጭልጥ ብሎ ቅልጥ፤
በልቤ ትርታ - በነፍስ ቋንቋዬ፣
እየደባበስኳት - ምነ ባዜምኩላት - አንቺ ሆዬ ብዬ፤
በይፋ ከስሼ- ፍርድ እንዳላቀርባት
ለካስ እሷ ራሷ - መፅሐፍ ገላጭ ናት
ከፊት እሷን መሳይ - የጠይም ወላላ፣
በድንቡሽ ብርጭቆ - ወይን እየተሞላ፣
እሱን እየጠጡ -
ለሰስ ባለ ዜማ - እየተመሰጡ
ደግሞ በመሃሉ - እየተቃበጡ
ፍቅር ፍቅር ብቻ - እየመሰጠሩ፣
ዓለምን ረስተው - ምናለ ቢኖሩ፣
ጨለምለም ባለ የብርሃን ድባብ ውስጥ፤
እልም ብሎ መጥፋት - ጭልጥ ብሎ ቅልጥ፤
በልቤ ትርታ - በነፍስ ቋንቋዬ፣
እየደባበስኳት - ምነ ባዜምኩላት - አንቺ ሆዬ ብዬ፤
❤8👏2🔥1
#ስጠብቅሽ_ልኑር
ቀናቶች ቢረዝሙ ቢቆጠሩ አመታት
ግዜ ቢለያየን ቢያልፉብን ዘመናት
ከልብሽ ብጠፋም ከትዉስታሽ ጓዳ
በስቃይ ታስሬ በናፍቆት ብጎዳ
ህልሜም ባይሳካ የሆዴን ባላገኝ
በደስታየ ዘመን ባይተዋር ቢያረገኝ
ግዴለም ችላለሁ ሁሉን ነገር ችዬ
እጠብቅሻለሁ ልቤን አባብዬ
የሀሳብ በረዶ ይጠለቅ በአናቴ
ይደንዝዝ አካሌ ይድከሙ ጉልበቴ
ትመጪ እንደሁ እያልኩ በተስፋ ልጠብቅ
እልፍ ግዜ ይለፍ ወዜ ሁሉ ይድቀቅ
ምን ያደርግልኛል ካንች ወድያ ኑሮ
ፍቅርሽ ይበቃኛል የስንቅሽ ቋጠሮ
በትዝታሽ ዋሻ እራሴን ደብቄ
በምናቤ ስየ ፍቅርሽን ሰንቄ
እጠብቅሻለሁ በተሰጠኝ እድሜ
ባንች ናፍቆት ፍቅር ካልሞትኩኝ ታምሜ
.....አዎ...
ስጠብቅሽ ልኑር ሳለሁ በህይዎቴ
ፍቅርም ባንች ይብቃኝ ይምከን ፍላጎቴ ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ናቲ ጥላሁን
ቀናቶች ቢረዝሙ ቢቆጠሩ አመታት
ግዜ ቢለያየን ቢያልፉብን ዘመናት
ከልብሽ ብጠፋም ከትዉስታሽ ጓዳ
በስቃይ ታስሬ በናፍቆት ብጎዳ
ህልሜም ባይሳካ የሆዴን ባላገኝ
በደስታየ ዘመን ባይተዋር ቢያረገኝ
ግዴለም ችላለሁ ሁሉን ነገር ችዬ
እጠብቅሻለሁ ልቤን አባብዬ
የሀሳብ በረዶ ይጠለቅ በአናቴ
ይደንዝዝ አካሌ ይድከሙ ጉልበቴ
ትመጪ እንደሁ እያልኩ በተስፋ ልጠብቅ
እልፍ ግዜ ይለፍ ወዜ ሁሉ ይድቀቅ
ምን ያደርግልኛል ካንች ወድያ ኑሮ
ፍቅርሽ ይበቃኛል የስንቅሽ ቋጠሮ
በትዝታሽ ዋሻ እራሴን ደብቄ
በምናቤ ስየ ፍቅርሽን ሰንቄ
እጠብቅሻለሁ በተሰጠኝ እድሜ
ባንች ናፍቆት ፍቅር ካልሞትኩኝ ታምሜ
.....አዎ...
ስጠብቅሽ ልኑር ሳለሁ በህይዎቴ
ፍቅርም ባንች ይብቃኝ ይምከን ፍላጎቴ ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ናቲ ጥላሁን
❤15🥰2
#ስሞት_አታልቅሱ!
ጎርፍ በላዬ ሲሄድ ዝም ካላችሁኝ፤
ምጠጣው አጥቸ ከንፍሬ እንዲህ ደርቆ ካላጠጣችሁኝ፤
ስትበሉ እያየሁ ወስፍቴ እየጮከ ካላበላችሁኝ፤
ምለብሰው አጥቸ እንዲህ ስንቀጠቀጥ፤
ልብስክን በሳጥን ቆልፈህ ካስቀመጥህ፤
ለምን ትጮሀለህ?፤
ለምን ታነባለህ?፤
ለምንስ ደረትክን ትደቁሰዋለህ?፤
"ማን ገደለው?" ቢሉህ እስኪ ማን ትላለህ?፤
እንባ ምን ሊጠቅመኝ እንባ ምን ሊፈይድ?፤
ያለቀሰ ሳይሆን በቁም ሚረዳ ነው ባምላክ የሚወደድ፤
እናልህ ወገኔ...
ደረትክን አትድቃ ሙሾው ገደል ይግባ፤
ገለከኝ አታልቅስ ይቅርብኝ ያዞ እንባ።
ከልብ ካዘናችሁ በነፍሴ ድረሱ፤
እናተ ገላችሁ ስሞት አታልቅሱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ጎርፍ በላዬ ሲሄድ ዝም ካላችሁኝ፤
ምጠጣው አጥቸ ከንፍሬ እንዲህ ደርቆ ካላጠጣችሁኝ፤
ስትበሉ እያየሁ ወስፍቴ እየጮከ ካላበላችሁኝ፤
ምለብሰው አጥቸ እንዲህ ስንቀጠቀጥ፤
ልብስክን በሳጥን ቆልፈህ ካስቀመጥህ፤
ለምን ትጮሀለህ?፤
ለምን ታነባለህ?፤
ለምንስ ደረትክን ትደቁሰዋለህ?፤
"ማን ገደለው?" ቢሉህ እስኪ ማን ትላለህ?፤
እንባ ምን ሊጠቅመኝ እንባ ምን ሊፈይድ?፤
ያለቀሰ ሳይሆን በቁም ሚረዳ ነው ባምላክ የሚወደድ፤
እናልህ ወገኔ...
ደረትክን አትድቃ ሙሾው ገደል ይግባ፤
ገለከኝ አታልቅስ ይቅርብኝ ያዞ እንባ።
ከልብ ካዘናችሁ በነፍሴ ድረሱ፤
እናተ ገላችሁ ስሞት አታልቅሱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤14🔥1
#ምን_ተሰማሽ_ውዴ?
ውብነትሽም ፈክቶ ደምቀሽ በደስታ፣
መጠውለግ እንዳለ ተዘናግተሽ ለአፍታ፣
በፍካትሽ ኮርተሽ እብሪት አንቀባሮሽ፣
ነገሽን በመርሳት ዛሬን ተመክተሽ፣
መጸውለግ ሲመጣ ጊዜውን ጠብቆ፣
ወዝሽ ላይሰነብት ላይሸኝሽ አርቆ፣
ሁሉን በውበትሽ፣
ስንቱን በፈገግታሽ፣
ሴሰኛን በዳሌሽ፣
ገፍትረሽ በጡትሽ፣
ሰካራም በጠላሽ፣
ቅብጥብጥ! ሲያረግሽ፣
አስቀሽ አላግጠሽ ውበት አመፃድቆሽ
ምን ተሰማሽ? ውዴ ዛሬ ሲሸሽ ጥሎሽ!?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ውብነትሽም ፈክቶ ደምቀሽ በደስታ፣
መጠውለግ እንዳለ ተዘናግተሽ ለአፍታ፣
በፍካትሽ ኮርተሽ እብሪት አንቀባሮሽ፣
ነገሽን በመርሳት ዛሬን ተመክተሽ፣
መጸውለግ ሲመጣ ጊዜውን ጠብቆ፣
ወዝሽ ላይሰነብት ላይሸኝሽ አርቆ፣
ሁሉን በውበትሽ፣
ስንቱን በፈገግታሽ፣
ሴሰኛን በዳሌሽ፣
ገፍትረሽ በጡትሽ፣
ሰካራም በጠላሽ፣
ቅብጥብጥ! ሲያረግሽ፣
አስቀሽ አላግጠሽ ውበት አመፃድቆሽ
ምን ተሰማሽ? ውዴ ዛሬ ሲሸሽ ጥሎሽ!?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍10❤4🥰1
#የንስር_እድሜ_ይስጥሽ
ይታደስ አካልሽ - በሺ አመት ዘመንሽ፣
ከርጅና ‘ሚመለስ - የንስር እድሜ ይስጥሽ፣
እዉነተኛዋ ሰው - ካምላኬ ቀጥለሽ፣
የህይወቴ ህይወት - እማ የምወድሽ፣
የኑሮየ ድምቀት - ድንቅ ስጦታ ነሽ::
የመኖሬ ምክኒያት - ምንጯ የህይወቴ፣
የሃሴት የፍቅር - የሰላም ሙላቴ፣
ቀድመሺኝ የመጣሽ - ገፀ በረከቴ፣
ደስታሽ ደምቆ ይብራ - በ ጉሙ ህ-ይወቴ
እማ ዉዷ እናቴ! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . .
መጠማት መራብሽ - ማጣት መራቆትሽ፣
ከሰው በታች ሆነሽ - ክብርሽን ማጣትሽ፣
እማየ ለኔ ነው - ለደካማዉ ልጂሽ፣
ከቶ በምን ቋንቋ - በምን ቃል ልግለፅሽ? እንዴት ልመልሰዉ - በዝቶብኛል ፍቅርሽ!
ይታደስ አካልሽ - በሺ አመት ዘመንሽ!
ከርጅና ሚመለስ - የንስር እድሜ ይስጥሽ!
ከዚህ በላይ እማ - ምን ቃል አለኝ ልጅሽ! . . . . . . . . . . . . . . .
እማ! . . .እማ!
ጭንቀትሽ ተጥሎ - ሸክምሽ ተንከባሎ፣
አለም ላንቺ ክብር ጎንበስ ቀና ብሎ፣
መቸገርሽ ቀርቶ - ቤትሽ ጓዳሽ ሞልቶ፣ ፊትሽ በፈገግታ - በደስታ አብርቶ፣
ጉድለትሽ ድካምሽ- እንግልትሽ ቀርቶ፣
የህይወትሽ ብርሃን - ይታይ ለአለም ፈክቶ፣
በረከት ረድኤቱን - አምልቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ይታደስ አካልሽ - በሺ አመት ዘመንሽ፣
ከርጅና ‘ሚመለስ - የንስር እድሜ ይስጥሽ፣
እዉነተኛዋ ሰው - ካምላኬ ቀጥለሽ፣
የህይወቴ ህይወት - እማ የምወድሽ፣
የኑሮየ ድምቀት - ድንቅ ስጦታ ነሽ::
የመኖሬ ምክኒያት - ምንጯ የህይወቴ፣
የሃሴት የፍቅር - የሰላም ሙላቴ፣
ቀድመሺኝ የመጣሽ - ገፀ በረከቴ፣
ደስታሽ ደምቆ ይብራ - በ ጉሙ ህ-ይወቴ
እማ ዉዷ እናቴ! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . .
መጠማት መራብሽ - ማጣት መራቆትሽ፣
ከሰው በታች ሆነሽ - ክብርሽን ማጣትሽ፣
እማየ ለኔ ነው - ለደካማዉ ልጂሽ፣
ከቶ በምን ቋንቋ - በምን ቃል ልግለፅሽ? እንዴት ልመልሰዉ - በዝቶብኛል ፍቅርሽ!
ይታደስ አካልሽ - በሺ አመት ዘመንሽ!
ከርጅና ሚመለስ - የንስር እድሜ ይስጥሽ!
ከዚህ በላይ እማ - ምን ቃል አለኝ ልጅሽ! . . . . . . . . . . . . . . .
እማ! . . .እማ!
ጭንቀትሽ ተጥሎ - ሸክምሽ ተንከባሎ፣
አለም ላንቺ ክብር ጎንበስ ቀና ብሎ፣
መቸገርሽ ቀርቶ - ቤትሽ ጓዳሽ ሞልቶ፣ ፊትሽ በፈገግታ - በደስታ አብርቶ፣
ጉድለትሽ ድካምሽ- እንግልትሽ ቀርቶ፣
የህይወትሽ ብርሃን - ይታይ ለአለም ፈክቶ፣
በረከት ረድኤቱን - አምልቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤11🥰1
ማን በገላገለኝ? የእጄን ሠዓት ሠብሮ
በምናልባት አገር
በምናልባት ኑሮ
የመጣው ይምጣ እንጂ
ማን ያቅዳል ደፍሮ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
በምናልባት አገር
በምናልባት ኑሮ
የመጣው ይምጣ እንጂ
ማን ያቅዳል ደፍሮ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
👍11❤1
#ወዴት_ነሽ?
የት ብዬ ልፈልግ ወዴት ነሽ ሄዋኔ፣
የአጥንቴ ክፋይ የሰራሽ ከጎኔ፣
ከበረሀው ካለሽ ንገሪኝ መጣለው፣
አሸዋ ንዳዱን ይሁን ችለዋለው፣
ውሀ ጥም ረሀቡን ባንቺ ረሳዋለው፣
ቆላም ሁኚ ደጋ ጥሪኝ እዘልቃለው፣
ቤተመንግስት ሆኚም ብቻ አለው በዪኝ፣
አልፌ ገባለው ህጉ እንኳ ቢያግደኝ፣
እንደ ወንጀለኛ በእስር ቢያስቀጣኝ፣
ይገደል ተብሎ ሞት ቢፈረድብኝ፣
አንዴ ልይሽ እንጂ ይህ አያሳስበኝ፣
ስፈልግሽ ስውል ሰርክ እያካለልኩሽ፣
ባክኜ እንዳልቀር ጥሪኝ አለው ብለሽ፣
ሄደሽም ከሆነ ወደመጣሽበት፣
መኖርሽ ካበቃ ከፍጥረታት ህይወት፣
ንገሪኝ መጣለው ውዴ ካለሽበት፣
አፈር ከጋረደው ከአካልሽ ቅሪት፣
ደራሲው እንዳለው ፍቅርን እስከ ሞት፣
እኔም ነፍሴ ትለፍ ቁጭ ብዬ ካንቺ ሀውልት፣
ጠቁሚኝ ስፍራሽን ወዴት ነሽ የት ልምጣ፣
አቀበቱን ልውረድ ሽቅቡንም ልውጣ፣
ልቤ ለብቻውን ሚያረገውን አጣ፣
አንቺንም እንደኔ ብቻነት ከጎዳሽ፣
አብሬሽ እንድኖር ንገሪኝ ወዴት ነሽ፣
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
የት ብዬ ልፈልግ ወዴት ነሽ ሄዋኔ፣
የአጥንቴ ክፋይ የሰራሽ ከጎኔ፣
ከበረሀው ካለሽ ንገሪኝ መጣለው፣
አሸዋ ንዳዱን ይሁን ችለዋለው፣
ውሀ ጥም ረሀቡን ባንቺ ረሳዋለው፣
ቆላም ሁኚ ደጋ ጥሪኝ እዘልቃለው፣
ቤተመንግስት ሆኚም ብቻ አለው በዪኝ፣
አልፌ ገባለው ህጉ እንኳ ቢያግደኝ፣
እንደ ወንጀለኛ በእስር ቢያስቀጣኝ፣
ይገደል ተብሎ ሞት ቢፈረድብኝ፣
አንዴ ልይሽ እንጂ ይህ አያሳስበኝ፣
ስፈልግሽ ስውል ሰርክ እያካለልኩሽ፣
ባክኜ እንዳልቀር ጥሪኝ አለው ብለሽ፣
ሄደሽም ከሆነ ወደመጣሽበት፣
መኖርሽ ካበቃ ከፍጥረታት ህይወት፣
ንገሪኝ መጣለው ውዴ ካለሽበት፣
አፈር ከጋረደው ከአካልሽ ቅሪት፣
ደራሲው እንዳለው ፍቅርን እስከ ሞት፣
እኔም ነፍሴ ትለፍ ቁጭ ብዬ ካንቺ ሀውልት፣
ጠቁሚኝ ስፍራሽን ወዴት ነሽ የት ልምጣ፣
አቀበቱን ልውረድ ሽቅቡንም ልውጣ፣
ልቤ ለብቻውን ሚያረገውን አጣ፣
አንቺንም እንደኔ ብቻነት ከጎዳሽ፣
አብሬሽ እንድኖር ንገሪኝ ወዴት ነሽ፣
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤10👏3👍1👌1
#ከትላንት_ሳንማር
ሰው ከሰው ተኳርፎ ዘመኑ ቢታደስ
አሮጌ ዓመት ወርዶ አዲስ ዘመን ቢነግሥ
እድሜ ቁጥር እንጂ ቢደመር ቢቀነስ
እኛ ሳንታረቅ እንቁጣጣሽ ቢደርስ
ፍቅር በሌለበት ውብ ድግስ ቢደገስ
የዶሮ የበጉ የበሬው ደም ቢፈስ
የከንቱ ከንቱ ነው ፍቅር ካልታደሰ
አንዱ የአንዱን ጎጆ ከፍቶ እያፈረሰ
መተሳሰብ ሳይኖር ልባችን ሳይቀና
አዲስ ዓመት መጣ ዞሮን እንደገና
ከትላንት ሳንማር በስህተት ተዘፍቀን
በእንቁጣጣሽ ዜማ እንቁ እንናፍቃለን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ሰው ከሰው ተኳርፎ ዘመኑ ቢታደስ
አሮጌ ዓመት ወርዶ አዲስ ዘመን ቢነግሥ
እድሜ ቁጥር እንጂ ቢደመር ቢቀነስ
እኛ ሳንታረቅ እንቁጣጣሽ ቢደርስ
ፍቅር በሌለበት ውብ ድግስ ቢደገስ
የዶሮ የበጉ የበሬው ደም ቢፈስ
የከንቱ ከንቱ ነው ፍቅር ካልታደሰ
አንዱ የአንዱን ጎጆ ከፍቶ እያፈረሰ
መተሳሰብ ሳይኖር ልባችን ሳይቀና
አዲስ ዓመት መጣ ዞሮን እንደገና
ከትላንት ሳንማር በስህተት ተዘፍቀን
በእንቁጣጣሽ ዜማ እንቁ እንናፍቃለን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤6🔥1