#ከትላንት_ሳንማር
ሰው ከሰው ተኳርፎ ዘመኑ ቢታደስ
አሮጌ ዓመት ወርዶ አዲስ ዘመን ቢነግሥ
እድሜ ቁጥር እንጂ ቢደመር ቢቀነስ
እኛ ሳንታረቅ እንቁጣጣሽ ቢደርስ
ፍቅር በሌለበት ውብ ድግስ ቢደገስ
የዶሮ የበጉ የበሬው ደም ቢፈስ
የከንቱ ከንቱ ነው ፍቅር ካልታደሰ
አንዱ የአንዱን ጎጆ ከፍቶ እያፈረሰ
መተሳሰብ ሳይኖር ልባችን ሳይቀና
አዲስ ዓመት መጣ ዞሮን እንደገና
ከትላንት ሳንማር በስህተት ተዘፍቀን
በእንቁጣጣሽ ዜማ እንቁ እንናፍቃለን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ሰው ከሰው ተኳርፎ ዘመኑ ቢታደስ
አሮጌ ዓመት ወርዶ አዲስ ዘመን ቢነግሥ
እድሜ ቁጥር እንጂ ቢደመር ቢቀነስ
እኛ ሳንታረቅ እንቁጣጣሽ ቢደርስ
ፍቅር በሌለበት ውብ ድግስ ቢደገስ
የዶሮ የበጉ የበሬው ደም ቢፈስ
የከንቱ ከንቱ ነው ፍቅር ካልታደሰ
አንዱ የአንዱን ጎጆ ከፍቶ እያፈረሰ
መተሳሰብ ሳይኖር ልባችን ሳይቀና
አዲስ ዓመት መጣ ዞሮን እንደገና
ከትላንት ሳንማር በስህተት ተዘፍቀን
በእንቁጣጣሽ ዜማ እንቁ እንናፍቃለን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤10🔥1
#ስላንቺ_ልንፏቀቅ
ሰወች ሳይገባቼው ሚስጥሩን ሳያቁ :
ከእሷ ምን አይቶ ነው ሲሉ ቢደነቁ:
አንቺ ግን አደራ ውዴ የኔ ፍቅር:
ጆሮሽን አትስጪ ለሚባለው ነገር:
ከጎንሽ ነኝ ዛሬም አርቅም ያንቺ አጋር:
ፍፁም አያውክሽ አሉባልታ ወሬ:
እኔ አልለውጥም ዛሬም ያውነኝ ፍቅሬ:
መከራ ሳይገርፍሽ ክፉ ቀን ሳይመጣ:
እየተሳሳምን ከሰፈር ስንወጣ:
ትዝ ይልሻል ያኔ?????????
አንድ ቁጥር ነበርን ስትቆሚ ከጎኔ:
ተቃቅፈን ስንዘምት በዚሁ ጎዳና:
እንዳላሉን ያኔ ፍቅራቼው ሲያስቀና:
እንዳ ባወሩበት በዛው ምላሳቼው:
አሁን ቢሞክሩ ሊያረጉኝ የራሳቼው:
ውዴ የኔ ፍቅር እኔን ሰሚኝ እማ:
ፈልገሽ ሳትገቢ ለዋጠሽ ጨለማ:
አልሆንህም በቃ ሂድ አትበይ አትፍሪ:
መቼም አልተውሽም አትጠራጠሪ:
እንኳን ትቼሽ ልሄድ ካጠቀብሽ ልርቅ
ቢቻል አጎንብሼ ስላንቺ ልንፏቀቅ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ሰወች ሳይገባቼው ሚስጥሩን ሳያቁ :
ከእሷ ምን አይቶ ነው ሲሉ ቢደነቁ:
አንቺ ግን አደራ ውዴ የኔ ፍቅር:
ጆሮሽን አትስጪ ለሚባለው ነገር:
ከጎንሽ ነኝ ዛሬም አርቅም ያንቺ አጋር:
ፍፁም አያውክሽ አሉባልታ ወሬ:
እኔ አልለውጥም ዛሬም ያውነኝ ፍቅሬ:
መከራ ሳይገርፍሽ ክፉ ቀን ሳይመጣ:
እየተሳሳምን ከሰፈር ስንወጣ:
ትዝ ይልሻል ያኔ?????????
አንድ ቁጥር ነበርን ስትቆሚ ከጎኔ:
ተቃቅፈን ስንዘምት በዚሁ ጎዳና:
እንዳላሉን ያኔ ፍቅራቼው ሲያስቀና:
እንዳ ባወሩበት በዛው ምላሳቼው:
አሁን ቢሞክሩ ሊያረጉኝ የራሳቼው:
ውዴ የኔ ፍቅር እኔን ሰሚኝ እማ:
ፈልገሽ ሳትገቢ ለዋጠሽ ጨለማ:
አልሆንህም በቃ ሂድ አትበይ አትፍሪ:
መቼም አልተውሽም አትጠራጠሪ:
እንኳን ትቼሽ ልሄድ ካጠቀብሽ ልርቅ
ቢቻል አጎንብሼ ስላንቺ ልንፏቀቅ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍2❤1