ግጥም
4.25K subscribers
26 photos
1 video
10 links
በዚህ ቻናል በጣም ምርጥ እና መንፈስን የሚያድሱ ግጥሞች ፣ ተከታታይ ታሪኮች ፣ የኦንላይን ቢዝነስ ቲፖች ይቀርቡበታል

መርጣችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን

Buy Ads https://telega.io/c/gitm_post

ADMIN 👉 @Big_jor
Download Telegram
#ታማሚ_ሀኪም_መድኃኒት

በሽታ ያጠቃው የታወከ ስጋ
ከህመሙ እንዲድን ተንፏቆ ይሄዳል መድኃኒት ፍለጋ
መዳንን የሚሻ ሀኪም ዘንድ ይቀርባል ከመድኃኒት ቀድሞ
ሀኪም ባዘዘለት መድኃኒት መስራት ይድናል ታክሞ
ለፈውስ ነው ብሎ ያገኘውን ሁሉ ከመሰልቀጥ ይፁም
ባኪም ያልታዘዘ መድኃኒት የዋጠ አይድንም በፍፁም
በሽተኛ ትውልድ
ሀኪም ባዘዘልህ በሽታህ ቢሆን ሰድል
መድኃኒቱን ስትይዝ ሃኪሙን አትበድል
ብታውቅማ ኖሮ 
ከመድኃኒት ይልቅ ሀኪም ነው ትልቁ 
ለያዘህ በሽታ መድኃኒት ማወቁ
ብታወቅማ ኖሮ
ከመድኃኒት በፊት ሀኪሙ ነው ውዱ
ፈውስ እንዲሆንህ መድኃኒት አምጦ መዳኒት መውለዱ
መዳኒት ልጅዋ ነው ሀኪሟም እማምላክ
መዳንን ከፈለክ ሁልጊዜም ወደሷ በሽቶችህን ላክ
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
አስታውሰኝ እረጋሳ
👍234👎2👏1
#መቼ_ይፈውሳል

በህይወት ውጥንቅጥ ያኮረፈ ስሜት፣
በሀሰት ጭብጨባ የተደበቀ እውነት፣
በግዜ ወለምታ ጉዳት ያጋጠመው፣
ወጌሻው ማን ይሆን አሽቶ የሚያድነው?
በማስመሰል ዜማ በግፍ ቅኝት ክራር፣
በውብ ቃል አስውበው ቢባል ፍቅር ፍቅር
መቼ ይፈውሳል ቃል ብቻ ቢንጋጋ
በደልን የሚሽር የእውነት ቀን ካልነጋ
የመከፋት ምንጩን ልብ ሆኖ መነሻው
ይቅርታ ብቻ ነው ለመርዙ ማርከሻው
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ስንታየሁ ሀብታሙ
👍167
#ፍቅር_ጥላ_ሲጥል

በገና ቢቀኙ
ሸክላ ቢያዘፍኑ
ክራር ቢጫወቱ…..
ለሚወዱት ምነው
ሙዚቃ ቢያዜሙ
ቃል ቢደረድሩ
ጌጥ ውበት ቢፈጥሩ
ቤት ንብረት ቢሠሩ
አበባ ቢልኩ
ምነው ቢናፍቁ
አገር ቢያቋርጡ
ቢሄዱ ቢርቁ
አመት ቢጠብቁ
ለሚወዱት ምነው?
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገብረ ክርስቶስ ደስታ
👍141
#መሄድሽን_ሳስብ

ያለፉትን ቀኖች
ዳግም አልፌያቸው
.......ከኋላቸው ሄጄ
አንቺን የምትመስል
........አንቺኑ ወድጄ
መኖርን እያሰብኩ
በጣም እስቃለሁ
ለካ...
ወደኋላ መኖር
የህልም እንጀራ ነው፤
ለነገሩ...
ለነገሩ ያው ነው
ካላንቺ መኖሩም
ያው አለመኖር ነው።
ብቻ...
ጩህ... ጩህ... ይለኝና
ዝም ባለ ልቤ
ዝም'ብዬ ጮሀለው
በጠራራ ፀሀይ
ቀኔን አጨልማለሁ፤
ጉድ እኮ ነው ጎበዝ!!
ዝም ብሎ መጮህ
ዝም ብሎ ማውራት
ሰሚ በሌለበት
ሳይጠሩ መጣራት።
ብቻ...
መሄድሽን ሳስብ...
እኔ የማላውቀው
ደርሶ ያላማከረኝ
ቅልስልስ እንባዬ
ባይኔ ስር ይፈሳል
ችሎ ላይመልስሽ
አመለኛው እግሬ
ቁጭ ብሎ ይነሳል፤
ጉድ እኮ ነው ጎበዝ!!
ያላዘዙት እንባ
ካይን አልፎ ሲያነባ
ያላነሱት እግር
ቁጭ ብሎ ሲዳክር፤
ብቻ...
ትንግርት ነው ሁሉ
አንቺ ከሄድሽ ወዲያ
የሚሆነው ሁሉ፤
ግና ምን ዋጋ አለው...
ከኛ ፍቅር በላይ
ከኛ ምኞት በላይ
የሱ ትክክል ነው¡¡
በዝች ግዑዝ አለም...
አንቺ አንቺን ሆነሽ
እኔ እኔን ሆኜ
ጊዜን ብንተውንም
ደራሲና አዘጋጅ
እግዚአብሔር ነውና
ከሱ ውጪ አኖንም።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
አዱኛ አስራት
👍139
#በኪሱ_ልክ_ነው!

የሰካራም ሕጉ ፍርድና ችሎቱ
ሰፈር መረበሹ ወድቆ መነሳቱ
ልኬቱ መስፈርቱ የህይወት ቅኝቱ
በጠጣው መጠን ነው ያለው ልዩነቱ
ግራ ቀኝ ፔንዱለም የሚወዛወዘው
በኪሱ ልኬት ነው ሁሉም የሚሰክረው
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
     ስንታየሁ ሀብታሙ
19👍9
#እሳት_ወይ_አበባ

ይቅር ብቻ አንናገርም፥
እኔና አንቺ አንወያይም፥
ለውይይት አልታደልንም
እንዲያው ዝም እንጂ ዝም.....ዝም፡፡
አበባ አንሆን ወይም እሳት
ተጠምደን በምኞት ቅጣት
ሰመመን ባጫረው መአት
እድሜአችንን እንዳማጥናት....
እሳት አንሆን ወይ አበባ
በሕቅ -እንቅ ስንባባ
ባከነች ልጅነታችን ፥ እየቃተትን ስናነባ፡፡
ፈራን፤ አዎን ፍቅር ፈራን፥
የነፍስን አንደበት ዘጋን፥
የእድሜ ጠብታችንን ምጥ፥ የጣር ፅንሳችንን ልሣን፥
ልጅነት የለገሠንን
በመለኮት የቀባንን
በእሳቱ ያጠመቀንን
የፍቅር አምላክ በጥበቡ፥ በሥልጣን ያላበሰንን
ፈራን፥ አዎን እውነት ፈራን
የስሜት እስትንፋስ ነሳን፡፡
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን
11👍7
#ጥሬ_ጨው

መስለውኝ ነበረ ፣
የበቁ የነቁ
ያወቁ የረቀቁ
የሰው ፍጡሮች ፣
ለካ እነሱ ናቸው ፣
ጥሬ ጨው..ጥሬ ጨው
ጥሬ ጨዋዎች ፣
መፈጨት-መሰለቅ-መደለዝ-መወቀጥ
መታሸት-መቀየጥ
ገና እሚቀራቸው ፣
“እኔ የለሁበትም !”
ዘወትር ቋንቋቸው ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ደበበ ሰይፉ
10👍4
#ኑ_እውሸት_እንስራ !

ዘጠኝ ቁና ውሸት
ከአንድ ቁና እውነት
አሙቀን አቅልጠን
ቀይጠን አላቁጠን
በተዋበ ተንኮል በረቀቀ ሴራ
ኑ! እውሸት እንስራ!
ቅጥፈት ነው እንዳይሉ፤
የእውነት መአዛ ያውዳል በሩቁ
ሀቅም ነው እንዳይሉ፤
መጠርጠር አይቀርም እያደር ሲነቁ!
እስከ ጊዜው ድረስ ...
እስኪተላለቁ እርስ በ'ርስ ተጋጭተው
ወይ እስኪያስተውሉ ከሰመመን ነቅተው ...
ከጓዳቸው ገብተን
የቻልነውን በልተን
ቀሪውን ሸክፈን አርገን በስልቻ
እንጓዝ በስውር እንሂድ ለብቻ
በጊዜ እናምልጥ እንምጠቅ እንብረር፤
አሻራ ሳንተው ...
ክንፋቸውን ሰርቀን ፥ ከአይን እንሰወር!
ዘጠኝ ቁና ውሸት
ከአንድ ቁና እውነት
አሙቀን አቅልጠን
ቀይጠን አላቁጠን
በተዋበ ተንኮል በረቀቀ ሴራ
ኑ! እውሸት እንስራ!!
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
በርናባስ ከበደ
👍182
#የማንችለው_በዛ

በሳቅ መጋረጃ ሀዘን ተደብቆ
ጥርስ ከላይ ከላይ በማስመሰል ስቆ
ልብ እህ እህ ይላል በስቃይ ዋይታ
ለማለፍ ሲያጣጥር ሁሉን በዝምታ።
የደረሰበትን በጥርስ ሳቅ ከልሎ
ውስጥ እረመጥ ፈጀው የማይቻል ችሎ።
ላያስችል አይሰጥም ይባል ነበር ድሮ
የማንችለው በዛ እንጃልኝ ዘንድሮ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
     ስንታየሁ ሀብታሙ
🥰11👍63
#ቀረሽ_እንደዋዛ

እንደ ድመቶቹ
የትም እንደሚያድሩት
እንደ ስልክ እንጨቶች
እንደ ዛፍ ሀረጎች
እንደ ቤት ክዳኖች
ብርድ አቆራመደኝ
ስጠብቅ ስጠብቅ
˝ትመጫለሽ ብዬ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ
የልጅነት አይኔ ሟሟ እንደ በረዶ˝
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር
ትመጫለሽ ብዬ ባዝን ባንጎራጉር
ትወጫለሽ ብዬ በበራፍሽ ብዞር
ብርድ አቆራመደኝ
የመንገድ መብራቶች አይተው አፌዙብኝ
ውርጩ ቀለደብኝ
ጨለማው ሳቀብኝ
አለመምጣትሽን አውቀዋል ያውቃሉ
መስኮቶች ጨልመው
ቤቶች ተቆልፈው
ከተማው ሲተኛ
አይተዋል ያያሉ
አለመምጣትሽን
አውቀዋል ያውቃሉ፡፡
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገብረ ክርስቶስ ደስታ
👍7🔥62
#ተስፋ_ስንት_ያወጣል?

ሰው በሰው ጨክኖ ቀን፡ሲለብስ ጥቀርሻ
ህልሙ የጨለመበት፡ያስሳል መሸሻ

እግሩን፡ተከትሎ
ተስፋን፡አንጠልጥሎ
አዲስ፡ቀንን ስሎ።
በሄደበት መንገድ፡በጀመረው ጉዞ
ወየው ማለት ሆኗል፡ሰው ሬሳውን ይዞ።
ወየው…ወየው…ወየው
ሰውስ ስንቱን፡ አየው።
ተስፋ ስንት ያወጣል፡ምንድነው ተመኑ?
በይሆናል ምኞት፡ስንቶቹ በከኑ።
ስንቶችስ ስመጡ፡ስንትቹ ረገፉ
እነማን ሲሄዱ፡እነማን ተቀጠፉ።
ወይታ ብቻ ሆነ፡ዝም ብሎ ለቅሶ
ለደጋፍ የሚሆን፡ጉልበታችን አንሶ
              በደላችን፡ብሶ
              አቅማችን፡ኮስሶ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
አረጋኸኝ ሙሉ (ዛኪ)
👍72
#ጆሮዬን_መልሺ!

ይመስለኝ ነበረ...
ልቤን የሰወርሽው፥ እንዳያስብ ሌላ
ዓይኔን የጋረድሽው፥በመውደድሽ ጥላ፣...

ይመስለኝ ነበረ ...
ከንፈሬን ያሸግሽው ፥ የሰው እንዳይነካ
አሁን ሳስተውለው ...
ጆሮዬን ጨምረሽ ፥ ወስደሽዋል ለካ!

ዘፈን እንዴት ላድምጥ? ...
ፍቅርን አስቀይሜ ፥ ቃል ኪዳኔን ጥዬ
አምባሰል ነሽ ባቲ ፥ ኧረግ አንቺ ሆዬ!

ክራር ጤና ነሳኝ ...
መሰንቆና ዋሽንት ፥  ከበሮ ድለቃ ...
እንዳውም ይቅርብኝ!  ኃጢኣት ነው ሙዚቃ፨

ለደስታ ካልሆነኝ
                ዝንቱ ከንቱ ውእቱ
ጥርቅም!  ....  ኤ--ታ--ባ--ቱ!!

ዋ! ሞኙ!
ዋ!  እኔ!
ያበጀሁኝ መስሎኝ ፥ ያቀናሁ በቤቴ
ባሳብ ለሚዋልል ፥ ርብሽብሽ ስሜቴ
ፀጥታን ላጣጥም ፥ እፎይ ከማለቴ፣ ...

ናፍቆትን ቀስቅሶ ፥ በንፋስ ጣት ንዝረት
በሽንቁር ሾላኪ ፥ ፉጨት - ርግብግቢት፣...
ጥሩሩን አጥልቆ
ስውር ሰይፉን ታጥቆ፣ ...
ዜመኛው ዝምታሽ ፥ ሊሸርፈኝ ይከንፋል
ትዝታ እንደ ዘፈን ፥ ተጫውቶ መች ያልፋል?!
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
      ✍️ በርናባስ ከበደ
👍102👏2
#ህልፈተ_ዓለም

ደረሰ ይሉናል ዓለም ማለፊያዋ፣

የሰው ነገር ዋ ፣
ጊዜው መቼ ገና ፣
መች ደረሰና።
ሰው ነው በገዛ እጁ የራሱ መፍረሻ
ሌላ .....ነገር ሲሻ
አይበቃኝም ብሎ፣ ሲሰስት ሲሻማ
የሌሎቹን ኣለም፣ ሲናጠቅ ሲቃማ
ይፈጥራል ጦርነት......
ይጠዛጠዛሉ ኣለማት ካለማት።

ከመሬት ጨረቃ ከጨረቃ መሬት
.......ያቶሚኩ ርችት
ይለካል - ይመጣል
የከዋክብት መስመር ጉዟቸው ይናጋል።

እየተፋለሰ ኣንዱ ኮከብ ካንዱ
ኣለማት ሲፈርሱ፣ ኣለማት ሲናዱ
ህልፈት የሚመጣው
ወዮ! ያን ጊዜ ነው።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገብረክርስቶስ ደስታ
5👍2
በትላንት ፈገግታ ዛሬን አየኖርነው
ስንቱን ወጣ ውረድ ችለን ተሻገርነው።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ስንታየሁ ሀብታሙ
👍16
#ተመልሼ_አልመጣም

ከወንጌል ቃል ሁሉ:እግዜር ካስተማረው
ነብስያዬን ገዝቶ:ቀልቤን የማረከው
ከልቡ የሆነ :ይድናል የሚለው !!

ምክንያቱም አለሜ : ምክንያቱም ህመሜ
የእውነትን ካልኖርኩ :እኔ አልድንም ፆሜ
ፀሎትም አይሰምር: አይፈይድም ስግደት
ሰደቃም አያርግ:ይስሙላ ካለበት

እናልሽ:አለሜ :
ከወንጌል ቃል ሁሉ :እግዜር ካስተማረው
ነብስያዬን ገዝቶ:ቀልቤን የማረከው
ከልቡ የሆነ:ይድናል የሚለው!!!

ስለዚህ መሻትሽ:ከልብሽ ከሆነ
በፍቅራችን ቅጠል አንቺም:ትድኛለሽ የኔም ነብስ ዳነ !!
ግና ነብስያዬን:ፍፁም ካልወደድሻት
ውዴ ቀረሽብኝ:አንቺም ቀረሽባት!

ደግሞ ካንቺ እርቄ: ከሸሸሁኝ በጣም
ውዴ ካለሽበት:ተመልሼ አልመጣም
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ዳዊት ጥዑማይ
5👍2👎1👏1
#የሐውልት_ላይ_ፁሁፍ

"ፀሀፊው በምን አረፈ?"
ተብላችሁ ብትጠየቁ
ኑሮውን ስትዘክሩ፣
እንዲህ ብላችሁ መስክሩ
ፀሀፊው ነብይ ነበረ
ብዕሩ ቀለም ተሞልታ
ልቦናው በሀሳብ ታጭቆ
እንዲፅፍ የተፈጠረ
አንጋሹ ቀቢው በርክቶ
ከፍ ከፍ አድራጊው በዝቶ
በእብሪት እንደታበተ
ጥቂት መስመር እንደጫረ
በሆነ መድረክ እግርጌ
ጭብጨባ ጨፍልቆት ሞተ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ቴድሮስ ፀጋዬ
👍8🔥21
አንቺን ነበር የፈለኩት
ላንቺ ነበር የተሳልኩት

ወይ አለችኝ ህልም ብላ
ጋኔል አለች ጨለም ብላ
መቼ ሰማች ወይብላ

የጠራናት ከአመት ቁስል
ሞተን ቆየን መጣሁ ስትል

ደከምኩኝ እስካለሽ
ተብከነከንኩ በየአፍ
ይቅናህ በይኝ እንዳገኝሽ
አልደረስኩም ስንቱን ባልፍ

ደሜን ማነው ያባከነው
ሞቴን ብቻ ሚመነዝር
አንቺን ከእኔ እያራቁ
ቃሉን ደግመው የሚያሰምር
ማነው አንቺን የሚያፈቅር ?
ማነው አንቺን አምኖ ሚያድር
ማነው ላንቺ የሚሰክር ?

ከእኔ ብቻ ዕንባ ዕንባ
ከእኔ ሌላ ህመም አለ?
ወይ'ብላም አጠራኝም
ኮሶ ብቻ መድን ካለ

ኑሮሽን እንድሸከም
ወንድሞቼን ፈለኳቸው
ተከዜ ላይ ጎርፉን ሆነው
ወድቀው ነው ያየኋቸው

ሶስት አይን ጥቁር ያላት
ሀዘን ጫንቃ የበዛባት
ይቺ ሀገር ሀገር ሳትሆን
የሲኦል በር ማለፊያ ናት !
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ግዕዝ ሙላት
👍75👏4
#ፍቅር_እና_ቅናት

እባክህ ፍቅሬ ሆይ እመነኝ አትቅና፤
በሄድሁበት ሁሉ አልረሳህምና፤
አትቅና ውደደኝ ከልቤ ስወድህ፤
እንኮንስ እርቄህ ጎንህ ስር ተኝቸ ትናፍቀኛለህ፤

ስትል ውስጤ እረክቶ ታንጾ መንፈሴ፤
ፍጹም እንዳልቀና ቃል ገባሁ ለራሴ፤

ኳላ ሱስ ሆኖባት…
የኔ በእሷ መቅናት…

አሁን የማትቀና ከቤቴ ስወጣ፤
ስለማትወደኝ ነው አለች ተገልብጣ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
14😁8👍4
#ቶሎ_ቶሎ_ምጪ

ውዴዋ!!! ስሚኝማ ማሬ ፣
እንዴው አትሳቂብኝ ይህን መናገሬ፣
ካንቺ ጋራ ስሆን እኔ ሌላ ሰው ነኝ፣
እንኳን ፖለቲካ ምግብ ትዝ የማይለኝ፣
እናም ስሚኝማ ሁልግዜ ተከሰቺ፣
ፓለቲካ አስጥለሽ ልቤን አስደስቺ፣
በማላውቀው ጉዳይ ገብቼ ስዛክር፣
ልክ አንቺ ስትመጭ ይዘሽልኝ ፍቅር፣
እንኳን የማላውቀው ግሙ ፖለቲካ፣
ምግብንም ይረሳል እጄ ሌላ አይነካ፣
እናም ጥበብዬ የእኔ ፍቅር ሸጋ፣
ቶሎ ቶሎ ምጪ ሌሊቱ እንዲነጋ፣
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ስንታየሁ ሀብታሙ
👍1311🥰3
#በትን_ያሻራህን_ዘር

በጓጥ በስርጓጉጡ
በማጥ በድጡ
እንደ ተንጋለልክ፣እንደ ዘመምክ
ትንፋሽህን እንደቋጠርክ
ልል ቀበቶህን እንዳጠበክ
የተልእኮህን አባዜ
የህይወትህን ቃል ኑዛዜ
ወርውር
የእጅህን ዘገር
በትን !
ያሻራህን ዘር
ይዘኸው እንዳትቀበር።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ደበበ ሰይፉ
👍91🥰1
#ቀቢፀ_ተስፋ

ፍቅረኛ የያዘች ለታ፣
አንጀቴም ይቆርጥልኛል ልቤም ያገኛል እፎይታ።
የሚል ተስፋ ቃል ሰንቄ ጉልበት ለግሶኝ እምነቱ፣
ቀን ቆጥሮ ተምሞ ሲነጉድ ግዜው ደረሰ ሰዓቱ፣
ፍቅረኛም ያዘች ልጅቱ፣
ግና ሚያስተዛዝበው በሷ ላይ የሚጨክነው ከየት ተገኝቶስ አንጀቱ።

ተስፋን ማያጣው ይህ ልቤም አልቆርጥም ብሎኝ ለዘበ፣
ዳግም እንዲም ሲል ሀሰበ።
ፍቅረኛ መያዝን እንደው ማን አረገው ትልቅ ጉዳይ፣
የኔም ፍቅረኛ ነበረች እስኪጠቡን ምድር ሰማይ፣
ባለሀገሩ እስኪያውቅልን እስክትሞቀን ድረስ ፀሀይ።
እኔ እንደሆንኩ ተስፋ አላጣም እሷ እንደሆን ሰርክ አዲስ ነች፣
ከኔም ጋር እንደተጣላች ነገ ከሱም ትጣላለች።

ይብላኝልኝ ገሩ ልቤ እንዳሰበው መቼ ቀና፣
ጆሮ ስሎ ሲጠባበቅ ተለያዩ የሚል ዜና፣
የወጠነው ፈሩ ለቆ እንኳን እሷ ልትጣላ፣
ባለማመን በደመነፍስ ድል ያለውን ሠርጓን በላ።

ያ የካበው የእምነት ጡብ ድንገት ባንዴ ቢናድበት፣
መደበቂያ የሚለው ሰው ጎኑ ቢያጣ ሚገባበት፣
ልቤ ፍቅሯ ስልብ አድርጎት ተስፋን መቁረጥ መች ታደለ፣
ማያባራን ቀቢፅ ተስፋ እንዲ ብሎም አስከተለ።

ይሁን ታግባ ምንም አይደለ፣
አልቆጥርባት እንደበደል።
ባለትዳር የተባሉት ቀን ወር ዓመት ሲደረደር፣
አይቻለሁ ሲሳናቸው ለቃላቸው ታምኖ ማደር።
እኔ እንደሆን ተስፋ አላጣም እሷ እንደሆን ሰርክ አዲስ ነች፣
እኔን እንደተወችኝ እሱንም ትፈታዋለች።

አወየሁ ተላላው ልቤ የገዛ የራሱ ተስፋ ሁሌ እየጣለው ተብትቦ፣
እየጠበቀ ባለበት ፍቺዋን በጉጉት ስቦ፣
አንጀቱን መቁረጥ ተስኖት ነገን ሲጠብቅ በተስፋ፣
ድንገት አግኝቷት አረፈው መንታ ልጆቿን ታቅፋ።

ድጡን ሲያልፈው ከማጡ ጉድባውን ሲዘል ሸለቆ፣
ቀላል ነው ያለው አቅሎት ይባስ በፍቅሯ ተጨንቆ፣
ምፅዓት ሆኖ ቢታየው መለየት በቁም ቢቀብረው፣
እንዲ የሚልን ተስፋ ቃል እንዳዲስ በልቡ አኖረው።

ሴቶች ወልደው ሲስሙ ሲጫናቸው ሀላፊነት፣
ከሩቅ ቀልብን የሚስበው የገፃቸው ጥዑም ውበት፣
ሚያስጎመጀው ተክለ ሰውነት፣
ስለማይከርም እንደፊቱ ያኔ ሸጋ እንደነበረው፣
የባሎችን ፍቅር ስሜት ታዝቤያለሁ ሲቀይረው።

ፍቅሬን ያገባት ባሏም በድንገት ውበቷን ሲያጣው፣
ሌላ ሴትን ከከጀለ ትችላለች ከልቧ ውስጥ የዛን ለታ ልታስወጣው።

እንዲህ እንዲያ የበዛበት፣
ሰበብ አስባብ የሞላበት፣
በቃ አክትሟል የሌለበት፣
ተላላ ነው የኔ እኔነት።

እንደዚሁ ነኝ እኔ በቃ አያልቅብኝ ቀቢፅ ተስፋው፣
አረ አይሆንም ማለት ከብዶኝ በምናልባት እየለፋው፣
ሰው ስከተል ከራሴ ጋር ሳልገናኝ ስንቴ ጠፋው።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ሄኖክ_ብርሃኑ
👍11😢32👏2