ግጥም
4.25K subscribers
26 photos
1 video
10 links
በዚህ ቻናል በጣም ምርጥ እና መንፈስን የሚያድሱ ግጥሞች ፣ ተከታታይ ታሪኮች ፣ የኦንላይን ቢዝነስ ቲፖች ይቀርቡበታል

መርጣችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን

Buy Ads https://telega.io/c/gitm_post

ADMIN 👉 @Big_jor
Download Telegram
#ናፍቆት

መለሎ ቁመናሽ ቀጭን ወገብሽ
ኮራ ያለ ዳሌሽ ጉች ጉች ጡትሽ
ኧረ እንዴት ከረሙ አንችስ ደህና ነሽ?
       እኔ በበኩሌ በጣም ደህና ነኝ
       ግን ለደብዳቤዬ መልስ ሳላገኝ
       ባነቺ ናፍቆት ብቻ ሞቼ እንዳትቀብሩኝ
ቢሮዬ ስገባ ስብሰባ ስቀመጥ
አሳቤ ኮብሎ ወዳንቺ ዘንድ ሲሮጥ
ሥጋቴ በዛና ጀመርኩኝ መደንገጥ
       በሰው በደብዳቤ የላክሁት መልዕክት
       ደርሶሽ ነው ዝም ያልሽው ወይስ ረሱት
       እኔ እምሰቃየው በዝናሽ መጥፋት
ከፋም ተናግሬሽ በነገር መሐል
አስቀይሜሽ ከሆንኩ ፈጽሜ በደል
ባይሆን ለይቅርታሽ ካሳውን ልክፈል
        ይቅር ግድ የለኝም ያለፈውስ ይለፍ
        በሽታ እንዳይዘኝ አብጄም እንዳልከንፍ
        ለዚች ለደብዳቤ ቶሎ መልስሽ ይጻፍ
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
    ደራሲ ታደለ ብጡል
👍141👏1
#ከዛሬ_ላይ_ጣለን

በሰቀቀን ዜማ በብሶት ተሰልቶ ፣
የእድሜ ቁጥር ገደብ ሳንኖረው ሞልቶ ፣
የኖርን የመሰለን እድሜያችን የራቀ፣
በጭንቀት ተባዝቶ ሳይኖር አለቀ!!!
በስጋም አልደላን በነፍስም አልታደልን፤
የህይወት አዙሪት ከዛሬ ላይ ጣለን።
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍21🥰1
#ወድቄ_ተሰበርኩ

አተኩሮ ሲያየኝ ቀዝቃዛ መሰልኩት
አፈፍ ቢያረገኝ እጁን ቀዘቀዝኩት
       ሽንጤን ጨበጥ አርጎ አንገቴን አቅንቶ
       ዓይን ዓይኔን እያዬ አፍ ከንፈሬን ከፍቶ
ሳም-ላስ ቢያደርገኝ ዕውነት ቀዝቃዛ ነኝ
የሱ ከንፈር መሞቅ እኔን ግን ገረመኝ
       ከዚህማ ወዲያ ምኑ ይጠየቃል
       ቃናዬ ተስማምቶት ምራቄን ይውጣል
ደጋግሞ ሲስመኝ ሲመጠኝ ሲልሰኝ
ሰውነቴ ሲቀል አቅም ሳጣ ተሰማኝ
       ፍላጎት ምኞቱ ሞልቶለት ሲረካ
       ገልበጥ ቀና አድርጎ ገላዬን ሲነካ
ድንገት ሳያስበው ገፍተር ሲያደርገኝ
ወድቄ ተሰበርኩ የመጠጥ ጠርሙስ ነኝ
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ደራሲ ታደለ ብጡል
👍13👎3👏21
#ከራስህ_ተስማማ

ስትናገር ፎካሪ
ዝም ስትል ፈሪ
ዓለም ስም አታጣ
ለአንተ ስታወጣ
ክፉም ጥሩም ስራ
ዝም በልም አውራ
ስም ትሰጥሃለች
እንዲህ ነው እያለች
አንተ እርሷን አተስማ
ከእራስህ ተስማማ
ዛሬ ከላይ ሰቅላ ነገ ለምታወርድ
ከሰውነት ክብርህ አንተ ብቻ አትውረድ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👏20👍52🔥2
#ሐዘኔ_ከበደ

አፈር ፈጭተን ስናድግ እዚያ እኛ መንደር
ገደብ ባልነበረው ተሳስረን በፍቅር
እጅ ለጅ ተያይዘን ስንሸረሸር
ምን ብለሽኝ ነበር? ምን ብዬሽ ነበር?
         በዛፎች ከለላ አዝግመን ስንሔድ
         የአበቦች ሽታ መዓዛው ሲያውድ
         እንኳን ጠላትና ሲቀና ዘመድ
         ተጋብተን ለመኖር ወልደን ለመክበድ
ምኞት ሕልማችንን ያኔ ያቀድነውን
ልንፈጽም ካልቻልን ቃል የገባነውን
ዛሬ ቀዝቀዝ ካለ ያ ሁሉ ፍቅራችን
በጣም ያሳዝናል ሰዎች መሆናችን
         በወፎች ጫጫታ ልቤ ተመስጦ
         ያንችም ልብ እንደኔ ኔው በሃሳብ ተውጦ
         በፍቅር ትኩሳት አካላችን ቀልጦ
         ጉድ እንዳልተባለ ሚሥጥሩ ተገልጦ
የጋለው ፍቀራችን ዛሬ ከበረደ
ደንዳናው ልባችን ለመናድ ከራደ
ፍቅርን ያመነ ሰው መሆኑን ያበደ
በእውን ተረዳሁት ሐዘኔ ከበደ
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ደራሲ ታደለ ብጡል
👍91🔥1👏1
#አንድ_ነገር_አለ!

አንድ ነገር አለ ያልገባን እውነታ
የተጋረደብን በጫጫታ ኩታ
መረዳት ያልቻልነው የሰውነት ጥጉ
ከፍታው ዝቅታው ውርደቱ ማዕረጉ
በሀቅ ያልተቃኘ ያልገባን ግርታ
አንድ ነገር አለ ያልታየን እውነታ
ወደ ነፈሰበት የሚስብ አስልቶ
ከሰውኛ ስሌት የሚጥል ጎትቶ
መግነጢሳዊ ሀይል ለእኛ ያልታወቀን
በዘር ዛር አዙሪት የሚያንቀጠቅጠን
ያልታወቀን ህመም ያልታየን በሽታ
አንድ ነገር አለ ያልገባን እውነታ
የግርግር ዓለም ረባሽ ውካታ
የእራስ አቋም ነጥቆ በሰው የሚያስመራ
ባልገባን በገባን ዘወትር የሚያስወራ
እወነትን አስትቶ ከሀቅ የሚያጣላ
በሆነ ባልሆነው ትውልድ የሚበላ
ለማወቅ ያልጣርነው ሊገባን ያልቻለ
ማየት ያልፈለግነው አንድ ነገር አለ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍122👏1
#ኑዛዜ

ቀበሮ ነኝ እኔ ዘመድ አልጠጋ
አንደበቴ እሾህ ነው ሁሉን የሚወጋ
     አውሬ ነኝ ተኩላ ነኝ ነገር አነፍናፊ
     ስድ ነኝ ጠበኛ አጉል ተናዳፊ
     ይሉኝታ የሌለኝ ሁሉን ነገር አጥፊ
ዋሾ ነኝ ቀጠፊ እንዲሁም ሴሰኛ
እርጉም ነኝ ክፉ ነኝ አጉል ቀናተኛ
አፈጀሁ አረጀሁ በመሆን ምቀኛ
     ነብር ነኝ ጭራቅ ነኝ የሰው ደም የምመጥ
     አታልላለሁኝ ወዳጅ ዘመድ ሳልመርጥ
     አምናለሁ በሰይጣን ከመላዕክት ይበልጥ
እሰው ቤት እየዞርኩ ቅራሪ ሳጣራ
ካንዱ ተቀብዪ ለሌላው ሳወራ
ጨረስኩት ዕድሜዬን ቁምነገር ሳልሠራ
     ክፋቴ ብዙ ነው አላውቅም ቁጥሩን
     በግምት ይበልጣል ከአንድ ሚሊዮን
     የኔ መጨረሻ ኧረ ምን ይሆን?
ደከመኝ ታከተኝ መሆን ማን ዘራሽ
እንዳልሰርቅ እንዳልገል ደግሞም አንዳልዋሽ
አጣሁኝ መድኃኒት ኧረ የት ልሽሽ?
     መልሱን የምታውቁ እኔን ያልሆናችሁ
     ከእውነተኛው መንገድ ከቶ ያልራቃችሁ
     አካፍሉኝ ምስጢሩን ለነፍስ ብላችሁ!
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ደራሲ ታደለ ብጡል
👍9👏3
#አዎ_ፍቅር_የለም

በዝሙት ህሊና በክህደት እይታ
በእምነት አልባ ቅኔ በጥቅመኞች ኩታ
ከሆነ ልኬቱ የሚዛኑም ክብደት
በእርግጥ ፍቅር የለም ሲረክስ ሰውነት
ፍቅርን በፍቅር ለሚለካ ደግሞ
የእውነት ፍቅር አለ ደጋግሞ ደጋግሞ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍113
#ስልክ_ተደወለ

ስልክ ተደወለ
መላልሶ አቃጨለ
       እኔ አነሳዋለሁ ብላ ሮጠች ሒሩት
       እጮኛዋ መስሏት ይህች የኔ እኅት
ስልኩ ጭርር ብሎ ሲደውል ቆየና
እቴ ስታነሳው ዝም አለ እንደገና
        ከዚያ እቴ አለች ማንን ፈላጊ ነው
        ፍቀረኛዬ ይሆን አሁን የደወለው?
ብላ ብትጠይቅ ወንድሜ እንዲህ አለ
የለም የኔ ፍቅር ነች የኔዋ አምሳለ!
        እማማም በተራ እነሱ አይደሉም
        አለች ማኅበረተኞቼ ሳይሆኑ አይቀሩም
አባቴም በፊናው የኔ ጓደኞች
ናቸው የደወሉት ምን ሆነሻል አንች?
        ብለው በጭቅጭቅ አፍ ላፍ ሲካፈቱ
        ለኔ ነው ለኔ ነው ብለው ሲሟገቱ
ያ! ያቃጨለው ስልክ መልሶ ጭጭ እስኪል
ከጎረቤት ሔጄ የነበርኩ ስደውል
        በጠቡ መሐከል በጣልቃ ገብቼ
        እኔ ነኝ የደወልኩ አልኩኝ ዘመዶቼ
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ደራሲ ታደለ ብጡል
😁22👍71
#ሰው_ሊሆነኝ

የብቼኝነቴ ማስታገሻ
የመከፋቴ ቅኔ መርሻ
ትዝታሽ ነው ቅርብ ወዳጄ
የማይጠፋው ዘወትር ደጄ
ሊጠይቀኝ
ሊያስታውሰኝ
የማይሰለች ተመላላሽ አስታዋሼ
ሰውን ሳጣ ሰው ሊሆነኝ ቅኔ ሞክሼ
የሚተጋ የማይረሳኝ ነግቶ ሲመሽ
አለኝ ክብር አለኝ ሞገስ ለትዝታሽ።
ወረት አያውቅ ማግኘት ማጣት
የሚጋራኝ ተካፋዬ የእኔን እውነት
ትዝታ ነው ዘር የሌለው
የእርሱ መስፈርት ሰው መሆን ነው።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👏11👍6
#የቆሰለው_ልቤ

የቆሰለው ልቤ እያለኝ አልችል
ዓይኖቼ እንባ ሲያዝሉ እኔ ስታገል
     በፍጹም ጭካኔ ፍቅሬን ስለጣልሽ
     ተመቸሽ ወይ አሁን ደስ አለሽ ደላሻ
በረዶ እንኳን ሳይጥል ውርጩ ሳይወረዛ
ቁሩ ሳይጠነክር ምድር ሳይሞላው ጤዛ
     ስምሽን ስሰማ ሳስብ ፍቅርሽን
     እንዘፈዘፋለሁ በብርድ በሐዘን
ሃሳብ ተለዋውጠን ምስጢር ተወያይተን
በክፉ በደግ ቀን እንደዚያ ተስማምተን
        አሁን ብንለያይ እንባ ብንራጭ
       ማነው ደስ የሚለው፣ ማነው የሚቆጭ?
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢʰᵃʳᵉ
ደራሲ ታደለ ብጡል
👍7👏3
#ምላስ_ሲዘረጉ_ምላስ_አትዘርጋ

በዝምታ ቅኔ በልጠህ ካልተውካቸው
ተናግሮ አናጋሪ ነገር ጎታች ናቸው
ይጩሁ ይንጫጩ ይበዱ በጋራ
አንተ ግን ዝም በል ሲናገሩ አታውራ
በዝምታ ፈረስ በችሎ ማለፍ ሕግ
የእራስህን እውነት አንተ እራስህ ፈልግ
በሀሜት አረቄ ዘወትር ከሚሰክሩ
እራስህን አግልል ተዋቸው ይዛክሩ
ዝምታህ ይቅጣቸው በፀፀት አለንጋ
ምላስ ሲዘረጉ ምላስ አትዘርጋ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍24👏9👎1
#በፍቅርሽ_አልሙት

ከልቤ ማፍቀሬን ተናግሬሽ በአፌ
ይህኑ ለማብሰር በእጆቼ አቅፌ
         ከንፈሬ ከንፈርሽን የሙጥኝ እያለ
         ዓይኔ ሲስለመለም ሰውነቴ ጋለ
ጋለ ሰውነቴ ልቤ አለ ድውድው
ምን እንደነካኝም ምኑንም ሳላውቀው
         ሰውነቴን ስቼ መውደቅ ተዝለፍልፌ
         የባጡን የቆጡን እንዲህ መለፍለፌ
እብደት ነው ጤንነት እንዲህ ያለ ነገር
ወይስ ማብሰሬ ነው ላንች ያለኝን ፍቅር
          እንኮይ ከንፈሮችሽ
          ዛጎሎች ዓይኖችሽ
ክፍት ክድን ሲሉ ለጥቅሻ ለሳቅ
ነጉላ አደረጉኝ ምንም የማላውቅ
          የቀጭኔ ጸጉርሽ ሎሚ ተረከዝ
          ተገትሬ እንድቀር አረጉኝ ፍዝዝ
መለየት አቀቶኝ ካንች እራቅ ብዬ
ጥላሽን ስከተል ሳላገኝሽ ውዬ
           ስበር አልነበረም ታዛቢ እንደሚለው
           በገዛማ ጣቴ ዓይኔ ሊወጣ ነው
አካልሽ በሙሉ ሆነብኝ መተት
ኧረ አንድ በይኝ በፍቅርሽ አልሙት፤
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
    ደራሲ ታደለ ብጡል
11👍6👎1🔥1👏1
#ሞራልና_ሆድ

የሞራል ጥያቄ በሆድ ከተረታ
ውጤቱ ሌላ ነው ይሻላል ዝምታ
አዕምሮን አስይዞ በእንጀራ በዳቦ
ህሊናዬስ ይላል በሀሰት ተከቦ!!!
ሆድ እየተራበ ሞራል ጸንቶ ላይኖር
እራሱን ይዋሻል ሰው ጦሙን ላያድር።
          @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍6😭4🥰1
#ይገርማል

የሰው ልጅ በለቅሶ መወለዱን ማብሰር
እያደገ ሲሄድ በቋንቋ መናገር
      ከዚያም በዕድሜው ጉዞ ውጣና ውረድ
      ሲመላለስበት ወልዶ ሲዋለድ
ከቆየ በኋላ ለውስን ዘመናት
ጸጥ በሚልበት ቀን በለቅሶ መሸኘት
       ገሀድ ሁኖ ሳለ ይህን መሰል ዕጣ
        መጨነቅ መጠበብ ምን ፋይዳ ሊያመጣ
ለገንዘብ ሲገዛ ተስገብግቦ ሲኖር
በጣም ያሳዝናል ሰው የሚባል ፍጡር
        ዋሽቶ ተስገብግቦ በዓለም መኖሩ
        በጣም ይገርመኛል ከቶ አለማፈሩ
ስለዚህ ፍጡራን የሰው ልጅች ሁሉ
ደግ ደጉን ጎዳና ይምረጡ በሙሉ
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ደራሲ ታደለ ብጡል
8👍4
#ከታች_ቆላ_አድኝኝ

ትመጫለሽ ቢሉኝ ታጅበሽ በአበባ
እንደመስቀሏ ወፍ መስከረም ሲጠባ
እጠብቅሻለሁ ክረምቱን ታግሼ
እንዳይበርደኝ ከላይ ጓሳየን ለብሼ
በሰማይ ግም ግምታ በጉም ተከብቤ
እህል መች ሊርበኝ ናፍቆት ነው እራቤ
ውርጩን ተቋቁሜ መምጣትሽን ስናፍቅ
ወንዝ ይጎድላል ቢሉ ፀደይን ስጠብቅ
ሀምሌና ነሐሴ ወራቱ እረዘመ
ልቤ በናፍቆትሽ እያደር ታመመ
ወንዙን አልዳፈር ዋና ጠፍቶብኛል
እንደሙሴ ከፍሎ ማን ያሻግረኛል
እርግጥ ነው አይፈራም ፍቅር የያዘው ሰው
ቢልኩት እንቢ አይልም ውሃም አያግደው
ና የሚል ቃል ይውጣ ልምጣ ተሻግሬ
ወንዝሽም ወንዜ ነው  ሀገርሽ ሀገሬ
ወዳንች ስመጣ ከደጋ ጎርፍ ይብላኝ
ዋናተኛ ይዘሽ ከታች ቆላ አድኝኝ
መስከረም ይጠባል ጠብቃት አትበሉኝ
በሸክምም ቢሆን ዛሬ ወንዝ አሻግሩኝ
ሳላያት እንዳልሞት ክረምቱ በርትቶ
በቃሬዛ ልድረስ እግሬም ተጎትቶ
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍85👏2
#እንዲያው_ዝም

ወድሻለሁ ማለት አይጠቅም አይበቃ፤
ፍቅሬ ነሽ ማለትም አይጠቅም አይበቃ !
ነፍሴ ነሽ ማለትም ልቤን አያርሰው 
የፍቅራችን' ነገር ዝም ነው ዝም ነው ።

ምን ላርገው መውደዴን ለመግለጽ በሙሉ?
ልሳምሽ ልቀፍሽ ፤ ላልቅስ ወይ ላመሉ ?

እግርሽን' ልሳም ወይ ፤ ልስገድልሽ ወይ?
ዓዋጅ ልናገረው ፡ በያደባባይ?
ወረቀት ልጻፍ' ወይ ፤ ልላክ' ወይ' ደብዳቤ ፡ እያንዳንዱን ቃላት ወልጄ ከልቤ!
ገንዘቤን ልስጥሽ ወይ ላይቆጨኝ መክሰሬ?
ልታረድ ልሰዋ ለፍቅርሽ ለፍቅሬ?

ይህ ሁሉ ከንቱ ነው
የልብ' አያደርስም።
በቃል' ወይ' በሥራ ፍቅር አይገለጽም።
ይሻላል መሰለኝ እንዲያው ዝም እንዲያው ዝም፤
እንዲያው በደፈና እንደ ሃይማኖት
ፍቅሬን ማወቅሽን ማመን መረዳት።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
መንግስቱ ለማ
👍8👏1
#የት_ነበሩ?!!

ይታየናል ባዮች ሳይበቁ የበቁ
መከራ ሲመጣ እንዴት አላወቁ?
የዘመን ነብያት ትንቢት ተናጋሪ
የቤት የመኪናው ሲደርሳቸው ጥሪ
ምነው ሰው ማለቁን ያልነገሩን ቀድመው?
በለመዱት ድፍረት አምላክን አናግረው።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👏13👍6
#ሐዘንሽ_አመመኝ

ውል አልነበረንም የፍቅር ቀጠሮ
ቃልም አላኖርንም በወግ ተቀምሮ፤
እኔ አንቺን እንዳላይ
አንቺ እኔን እንዳታይ አምባችን ተቃጽሮ
ዕጣችን ተካሮ፤
ቀለምሽ ከዐይኔ አሻራሽ ከጣቴ ባይጠፋ ተማትሮ
(እትብት እምብርት ሁኖ እንዲኖር ደድሮ)
ይኸው አካሄደን በድንገት ዘንድሮ።
የገጽሽ ብርሃን ቢጠይም ፀዳሉ
ድምፅሽ ቢቀጥንብኝ ቢሠልብኝ ቃሉ
ወዘናሽ ቢማስን ዛሬ ያለውሉ
በእጆችሽ ጨበጠኝ ሐዘንሽ ሥዕሉ
ሐዘንሽ አመመኝ
ብሶትሽ ጠቀሰኝ።
ጀንበር ነሽ አበባ ሕይወት ተስፋ ዘቦ
ፋሲካ ዕንቁጣጣሽ ማኅሌተ ገንቦ
ብዬ ያወደስኩበት ታዘበኝ ዘመኔ የትላንታት ቀኔ
ዛሬ ሊጮህብኝ ቅኔ እንዳይደል እውኔ፤
ሐዘንሽ አመመኝ
ብሶትሽ ጠቀሰኝ።
የገደል ማሚቶን ታዘብኳት ተኝታ
በጩኽትሽ ማየል አኩርፋና ታክታ
ላንቃዋ ይታየኛል ደም ለብሶ ደም ጐርሶ
ቃልሽ ያለፈበት በጭንቅ ተለውሶ፤
ሐዘንሽ አመመኝ
ብሶትሽ ጠቀሰኝ።
ጽጌሬዳይቱ ንቦችሽ አለቁ ሰዎችሽ ደቀቁ
ጨፌ ላይ ተኝተው ባድማ ላይ ነቁ፤
ዐዋይን ሰማኋት ስታለቅስ በይፋ
ከጐጆሽ ስትወጣ ትቢያዋን አራግፋ፤
ሐዘንሽ አመመኝ
ብሶትሽ ጠቀሰኝ።
አላውቅልሽ ብዬ አታውቂልኝ ብዬ
እምነትሽን ጥዬ ፍቅርሽን ገድዬ
አኩርፌሽ ስቀመጥ ያው እንደ ባላንጣ
ይኸው ነጭ ማተብሽ ሊያስታርቀን መጣ፤
ሐዘን ነው ውበትሽ ውበት ነው ፍቅርሽ
ብርሃን – ጥለት አልቦ ከል ነጠላሽ
ዐይኔን የገለጠው ጥቁር ጨለማሽ፤…
ሐዘንሽ አመመኝ
ብሶትሽ ጠቀሰኝ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ፦ ደበበ ሰይፉ
👍11👏2
#ከአዳም_ያልመጣ

ለወንድና ለሴት ለአዳም ልጆች
ሔዋን በበኩሏ እናታቸው ነች
      ብለን ብንገምት ብንገመግም
      አዳምና ሔዋን በአገኙት መርገም
አዳም እርሻውን ሲያርስ ሔዋን ስትፈትል
ማን ነበረች ልዕልት ማን ነበረ ልዑል
      መኳንንት መሳፍንት ከየት ተፈጠሩ
      ከአዳም ያልመጣ ግንዱስ የትነው ዘሩ?
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
     ደራሲ ታደለ ብጡል
👍13
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM