#በእንባ_የራሰ_ፍትፍት
ቀበሌ ሂድና ፥ ድህነት አስመስክር
ይላል አሉ ሃብታም ፥ መፅውቶ ሲሰክር
እማኝ ጥራ ይላል ፤ ቀበሌ በተራው
እማኙ ሲመጣ ፤ ይንዛዛል ወረፋው
አሹቅ ከጨበጠ...
ከነዳይ መዳፋ ላይ ፥ ሹም እየዘገነ
"ድሃ!" መባል እንኳን ፥ ገንዘብ ላለው ሆነ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍በርናባስ ከበደ
ቀበሌ ሂድና ፥ ድህነት አስመስክር
ይላል አሉ ሃብታም ፥ መፅውቶ ሲሰክር
እማኝ ጥራ ይላል ፤ ቀበሌ በተራው
እማኙ ሲመጣ ፤ ይንዛዛል ወረፋው
አሹቅ ከጨበጠ...
ከነዳይ መዳፋ ላይ ፥ ሹም እየዘገነ
"ድሃ!" መባል እንኳን ፥ ገንዘብ ላለው ሆነ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍
👍12👏6
#ዝኑፋ_ወቀሳ
ይለኛል ታዛቢ...
"በእኛ ተረማምዶ - ስኬቱን ሸመተ፤
ሲመቸው ፣ ሲደላው - ትቶን ሰነበተ!"
ይለኛል ታዛቢ...
"አቅፈን አሳድገን - ከሰው መሐል ለየን፤
አለፈለትና - ዞር ብሎም አያዬን!"
እኔ ግን እላለሁ...
"ስህተት የለብኝም፤
ያለፍኩበት ሁሉ አላሻገረኝም፤
የረገጥኩት ሁሉ አልተሸከመኝም!"
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በረከት በላይነህ
ይለኛል ታዛቢ...
"በእኛ ተረማምዶ - ስኬቱን ሸመተ፤
ሲመቸው ፣ ሲደላው - ትቶን ሰነበተ!"
ይለኛል ታዛቢ...
"አቅፈን አሳድገን - ከሰው መሐል ለየን፤
አለፈለትና - ዞር ብሎም አያዬን!"
እኔ ግን እላለሁ...
"ስህተት የለብኝም፤
ያለፍኩበት ሁሉ አላሻገረኝም፤
የረገጥኩት ሁሉ አልተሸከመኝም!"
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በረከት በላይነህ
❤10👍2👏1
#ውሻሽን_እሰሪው
አንችን ስመለከት እንቅፋት መትቶኛል
መምጫሽን ስጠብቅ ፀሐይ አጥቁሮኛል
ባጥር ላይሽ ብዬም ውሻችሁ ነክሶኛል
ያውም ክፉ ውሻ...
መምጫው ሳይታወቅ አድብቶ ሚያጠቃ
ገዳይ መሬት ጥሎ የሚለውስ ጭቃ
እችን ስንጥር እግሬን ከአፉ አስገብቶ
አንከባሎኝ ሄዷል እመሬት ጎትቶ
ውሻሽን እሰሪው...
ይህን ሀይለኝነት ከማንስ ተማረ አሳዳጊው አንቺ
አትንኩኝ የምትይ አመል የነፈገሽ ለሰው ማትመቺ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍አቤል ሽመልስ
አንችን ስመለከት እንቅፋት መትቶኛል
መምጫሽን ስጠብቅ ፀሐይ አጥቁሮኛል
ባጥር ላይሽ ብዬም ውሻችሁ ነክሶኛል
ያውም ክፉ ውሻ...
መምጫው ሳይታወቅ አድብቶ ሚያጠቃ
ገዳይ መሬት ጥሎ የሚለውስ ጭቃ
እችን ስንጥር እግሬን ከአፉ አስገብቶ
አንከባሎኝ ሄዷል እመሬት ጎትቶ
ውሻሽን እሰሪው...
ይህን ሀይለኝነት ከማንስ ተማረ አሳዳጊው አንቺ
አትንኩኝ የምትይ አመል የነፈገሽ ለሰው ማትመቺ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍
❤10👍2
#ለሰውነቱ_ክብር
ሰው ኑሮን ለመኖር ሌት ተቀን መዋተት
መውጣት መውረድና እድሜ ሙሉ መልፋት
ፍዳ ነው ፍዳ ነው የሰው ልጆች ሕይወት
ሲያገኙ መደሰት ሲያጡ መሸማቀቅ
ተለምዶ መሆኑ በገሀድ ሲታወቅ
ታድያ ዘመናይ ሰው ለምን ይንደላቀቅ?
ይኸን ውጣ ውረድ የኑሮ ሚዛን
ማሰብ መመራመር መረዳት ሐቁን
ማስተካከል ያሻል በማመጣጠን
ይኸ የዓለም ጣጣ እንዲስተካከል
ምሁር መኃይሙ ሳይነጣጠል
ለሰውነቱ ክብር ሊሰጥ ይገባል
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደራሲ ታደለ ብጡል
ሰው ኑሮን ለመኖር ሌት ተቀን መዋተት
መውጣት መውረድና እድሜ ሙሉ መልፋት
ፍዳ ነው ፍዳ ነው የሰው ልጆች ሕይወት
ሲያገኙ መደሰት ሲያጡ መሸማቀቅ
ተለምዶ መሆኑ በገሀድ ሲታወቅ
ታድያ ዘመናይ ሰው ለምን ይንደላቀቅ?
ይኸን ውጣ ውረድ የኑሮ ሚዛን
ማሰብ መመራመር መረዳት ሐቁን
ማስተካከል ያሻል በማመጣጠን
ይኸ የዓለም ጣጣ እንዲስተካከል
ምሁር መኃይሙ ሳይነጣጠል
ለሰውነቱ ክብር ሊሰጥ ይገባል
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደራሲ ታደለ ብጡል
👍4
#በሰው_ልብ_ከተማ
ስቆ ማለፍ እንጅ ዘንድሮን ለከርሞ
በፈገግታ ዜማ ብሶትን አስታሞ
የሌለንን ትተን ባለን ካልተደሰትን
ጊዜውስ ሞክሯል አዙሮ ሊጥለን
የሳቃችን ሚዜ ሀዘናችን ሆኖ
በጥርሳችን ጋቢ ከውስጥ ተከድኖ
ሳቃችን ሙሽራ ሐዘናችን ሚዜ
አብረው እየበሉ ሳቅና ትካዜ
ጥርሳችን ቢስቅም ሐዘንን ሸሽጎ
ጥርስ እየደመቀ መከራን ሚዜ አርጎ
ደስታና ሐዘን አብረው እቁብ ጣሉ
በሰው ልብ ድንኳን ድግስ እየበሉ
በስቃይ ከተማ ድርሻቸውን ይዘው
የፈረቃ ስልጣን ስፍራቸውን ወስደው
ይፈራረቃሉ በሰው ልብ አዳራሽ
ችሎትን ዘርግተው በሌለበት ከሳሽ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ስቆ ማለፍ እንጅ ዘንድሮን ለከርሞ
በፈገግታ ዜማ ብሶትን አስታሞ
የሌለንን ትተን ባለን ካልተደሰትን
ጊዜውስ ሞክሯል አዙሮ ሊጥለን
የሳቃችን ሚዜ ሀዘናችን ሆኖ
በጥርሳችን ጋቢ ከውስጥ ተከድኖ
ሳቃችን ሙሽራ ሐዘናችን ሚዜ
አብረው እየበሉ ሳቅና ትካዜ
ጥርሳችን ቢስቅም ሐዘንን ሸሽጎ
ጥርስ እየደመቀ መከራን ሚዜ አርጎ
ደስታና ሐዘን አብረው እቁብ ጣሉ
በሰው ልብ ድንኳን ድግስ እየበሉ
በስቃይ ከተማ ድርሻቸውን ይዘው
የፈረቃ ስልጣን ስፍራቸውን ወስደው
ይፈራረቃሉ በሰው ልብ አዳራሽ
ችሎትን ዘርግተው በሌለበት ከሳሽ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_
👍13👏9
#በምናልባት_ኑሮ
አይቦዝን አንቀልባው
አይሞላም ጉድጓዱ
ሺሆች ሞተው ቢያድሩ
ሺሆች ተወለዱ
ይመሻል ይነጋል
ያው እንደልማዱ፤
መሬት ባህር ሆኖ ፥ ድሃን ሰለቀጠው
ትልልቁ ቪላ ፥ ትንሹን ቤት ዋጠው
በመስታወት ጫካ ፥ በጡብ በብረት ደን
አየሁ ባደባባይ ፥ ሰው በሰው ሲታደን፤
ማን በገላገለኝ ፥ የጄን ሰዓት ሰብሮ
በምናልባት አገር ፥ በምናልባት ኑሮ
የመጣው ይምጣ እንጅ ፥ ማን ያቅዳል ደፍሮ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
አይቦዝን አንቀልባው
አይሞላም ጉድጓዱ
ሺሆች ሞተው ቢያድሩ
ሺሆች ተወለዱ
ይመሻል ይነጋል
ያው እንደልማዱ፤
መሬት ባህር ሆኖ ፥ ድሃን ሰለቀጠው
ትልልቁ ቪላ ፥ ትንሹን ቤት ዋጠው
በመስታወት ጫካ ፥ በጡብ በብረት ደን
አየሁ ባደባባይ ፥ ሰው በሰው ሲታደን፤
ማን በገላገለኝ ፥ የጄን ሰዓት ሰብሮ
በምናልባት አገር ፥ በምናልባት ኑሮ
የመጣው ይምጣ እንጅ ፥ ማን ያቅዳል ደፍሮ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤10👍4🔥4🥰1
#ታማሁኝ_በፍቅር
የዘንድሮማ ሰው ማውራት ያውቅበታል
ልቡን ወስደዋለች ብሎ ያዋሽካል
ሐሜተኞች አሙኝ ደካማ ነው ብለው
መልካም ልጅ ባፈቅር ድካሜ እምን ላይ ነው
ኃጢአት አደለም ወይ ወንጀል ማፍቀር
እስቲ ተውኝ ሰዎች በሰላም ልኑር
ለኑሮ መዋተት መውጣትና መውረድ
መቺ አነሰኝና በፍቅር ልዋረድ
ይኸ ሀሜታቸው እንዳይሆን እውነት
ተይ አታንገላችኝ በፍቅርሽ አልሙት
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደሪሲ ታደለ ብጡል
የዘንድሮማ ሰው ማውራት ያውቅበታል
ልቡን ወስደዋለች ብሎ ያዋሽካል
ሐሜተኞች አሙኝ ደካማ ነው ብለው
መልካም ልጅ ባፈቅር ድካሜ እምን ላይ ነው
ኃጢአት አደለም ወይ ወንጀል ማፍቀር
እስቲ ተውኝ ሰዎች በሰላም ልኑር
ለኑሮ መዋተት መውጣትና መውረድ
መቺ አነሰኝና በፍቅር ልዋረድ
ይኸ ሀሜታቸው እንዳይሆን እውነት
ተይ አታንገላችኝ በፍቅርሽ አልሙት
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደሪሲ ታደለ ብጡል
👍11
#አንቺ_ምን_አለብሽ
ባልጠበቀ ስንኝ በላላ ቋጠሮ
ውበትሽን ለመግለጽ ስጭር እንደ ዶሮ
ቤት መታ ቤት ደፋ እያልኩኝ ለእራሴ
ስደክም ስባክን ስትጨነቅ ነፍሴ
አንቺ ምን አለብሽ ተኝተሽ አልሚ
ክረምቱን በሙቀት ሳይበርድሽ ክረሚ
ብዙ አድናቂ ያለሽ ሲጭር የሚያነጋ
ውበትሽን አወዳሽ የገጣሚ መንጋ
ቃላትን አዋቅሮ ይጭራል ይጽፋል
ውበትሽን ለመግለጽ ስንኝ ይቋጥራል
አንቺ ተኝተሻል አይገድሽ አይሞቅሽ
ይብላኝ ለማይተኛው ቆሞ ለሚያልምሽ
በክረምቱ ቆፈን ብርድ እያነዘረው
ሲያስብሽ አዳሪው እልፍ አላፍ ጫሪ ነው
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ባልጠበቀ ስንኝ በላላ ቋጠሮ
ውበትሽን ለመግለጽ ስጭር እንደ ዶሮ
ቤት መታ ቤት ደፋ እያልኩኝ ለእራሴ
ስደክም ስባክን ስትጨነቅ ነፍሴ
አንቺ ምን አለብሽ ተኝተሽ አልሚ
ክረምቱን በሙቀት ሳይበርድሽ ክረሚ
ብዙ አድናቂ ያለሽ ሲጭር የሚያነጋ
ውበትሽን አወዳሽ የገጣሚ መንጋ
ቃላትን አዋቅሮ ይጭራል ይጽፋል
ውበትሽን ለመግለጽ ስንኝ ይቋጥራል
አንቺ ተኝተሻል አይገድሽ አይሞቅሽ
ይብላኝ ለማይተኛው ቆሞ ለሚያልምሽ
በክረምቱ ቆፈን ብርድ እያነዘረው
ሲያስብሽ አዳሪው እልፍ አላፍ ጫሪ ነው
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍13👏2
#ነጠብጣብ_ሀሳቦች
ሰማይ ከሚመክን ይፀንስ መከራ
ያርግፍ" ያርግፍ" ያርግፍ" መዓት እያፈራ
የሣት ዛፍ ባለበት ሰደድ ላያስፈራ።
ከሐምሌት ጋር ሞቷል ፣ የማመንታት ዓለም
ከሆኑ በኋላ፣ አለመሆን የለም፤
ሸክም ፀጋ ሆኗል ፀጋህን አትግፋ
በጠባብ ዓለም ውስጥ ትከሻህን አስፋ።
አንድ ህልም እንደ ጠጅ፣ እየደጋገሙ
ንግር፣ ትንቢት ሳይሆን ታሪክ እያለሙ
ተኝቶ መነሳት
አቤት ሲያቅለሸልሽ
ጌታ ሆይ አትንሳት
ነፍሴን እንቆቅልሽ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገጣሚበእውቀቱ ስዩም
ሰማይ ከሚመክን ይፀንስ መከራ
ያርግፍ" ያርግፍ" ያርግፍ" መዓት እያፈራ
የሣት ዛፍ ባለበት ሰደድ ላያስፈራ።
ከሐምሌት ጋር ሞቷል ፣ የማመንታት ዓለም
ከሆኑ በኋላ፣ አለመሆን የለም፤
ሸክም ፀጋ ሆኗል ፀጋህን አትግፋ
በጠባብ ዓለም ውስጥ ትከሻህን አስፋ።
አንድ ህልም እንደ ጠጅ፣ እየደጋገሙ
ንግር፣ ትንቢት ሳይሆን ታሪክ እያለሙ
ተኝቶ መነሳት
አቤት ሲያቅለሸልሽ
ጌታ ሆይ አትንሳት
ነፍሴን እንቆቅልሽ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገጣሚ
👍6🔥1
#ዋ!
ዓይኔ ወደደሽ ስልሽ
አይኑን አጥፋው ብለሽ ገባሽ አሉ
ስለት
ምኞትሽ ሰመረ አይኖቼ ጠፉልሽ ይኸው እንደዘበት።
ግን መች ተውሻለው
በልቤ ብሩህ ዓይን ዛሬም አይሻለው።
ደሞ እንደዚህ ስልሽ አትወጅኝምና
ልቡንም አጥፋልኝ ብለሽ ትሳይና
ፀሎት ያልቅብሻል እሞትብሻለሁ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገጣሚበረከት በላይነህ
ዓይኔ ወደደሽ ስልሽ
አይኑን አጥፋው ብለሽ ገባሽ አሉ
ስለት
ምኞትሽ ሰመረ አይኖቼ ጠፉልሽ ይኸው እንደዘበት።
ግን መች ተውሻለው
በልቤ ብሩህ ዓይን ዛሬም አይሻለው።
ደሞ እንደዚህ ስልሽ አትወጅኝምና
ልቡንም አጥፋልኝ ብለሽ ትሳይና
ፀሎት ያልቅብሻል እሞትብሻለሁ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገጣሚ
❤13👍6🤯1
#መራራቅ
ቅዠታም አዳሩን
ጨፍጋጋ ውሎዉን
ዝብርቅርቅ ተስፋውን
ደረቅ ትዝታውን...
በይሉኝታ ኮፈን እየጠቀለለ
ከጥርሱ ሲጥለው
ተቀባይ ይሻማል ሳቅ እየመሰለው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገጣሚበረከት በላይነህ
ቅዠታም አዳሩን
ጨፍጋጋ ውሎዉን
ዝብርቅርቅ ተስፋውን
ደረቅ ትዝታውን...
በይሉኝታ ኮፈን እየጠቀለለ
ከጥርሱ ሲጥለው
ተቀባይ ይሻማል ሳቅ እየመሰለው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገጣሚ
👍9🥰6👌2
#ምሥጢር
ምሥጢር ነው ያልከውን ለሌላ ሰው መንገር
መሆኑን ተረዳ በገዛጅ መታሰር
ግን ምሥጢር ለባዕድ እስካልተነገረ
ምሥጢርህ ምሥጢር ነው ባንተው ከታሠረ
ምሥጢርህን ሌላ ሰው ካየና ከሰማው
ያባከንከው ምሥጢር ላንተ ዘብጥያህ ነው
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደሪሲ ታደለ ብጡል
ምሥጢር ነው ያልከውን ለሌላ ሰው መንገር
መሆኑን ተረዳ በገዛጅ መታሰር
ግን ምሥጢር ለባዕድ እስካልተነገረ
ምሥጢርህ ምሥጢር ነው ባንተው ከታሠረ
ምሥጢርህን ሌላ ሰው ካየና ከሰማው
ያባከንከው ምሥጢር ላንተ ዘብጥያህ ነው
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደሪሲ ታደለ ብጡል
👍9😁1
ተቃቅፈን ስንሄድ ለሚያገላግሉ
ጉንጭሽን ስስምሽ ነከሳት ለሚሉ
ከፍቅራችን ይልቅ ጸብ ለናፈቃቸው
ከራስሽ ተጣልተሽ...
የወሬ ማድመቂያ ሰበብ አትሁኛቸው
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገጣሚአቤል ሽመልስ
ጉንጭሽን ስስምሽ ነከሳት ለሚሉ
ከፍቅራችን ይልቅ ጸብ ለናፈቃቸው
ከራስሽ ተጣልተሽ...
የወሬ ማድመቂያ ሰበብ አትሁኛቸው
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገጣሚ
👏10👍4❤3🔥2
#አልቻልኩም
(አብሮ መሰደድ)
የልቤ ሰመመን የፍቅሬ ትዝታ
የዓይኖቼ ብሌን የሕይወቴ አለኝታ
አኔን ከጠላሽኝ ከናቅሽ ፍቅሬን
ከመሔዴ በፊት ስሚማ እሮሮዬን
ልዝብ አንደበትሽ ታጋሽ ተፈጥሮሽ
አስተዋይ አእምሮሽ ንጹሕ ልቦናሽ
ተባብሮ ከዓይኖችሽ ከውበትሽ ጋር
ልቤን ማርኮ ወስዶ አሰረው በፍቅር
ኮኮብ ዓይኖችሽን ጉብል ጉንጮችሽን
የቀጭኔ ጭራ መሳይ ጸጉሮችሽን
ለጋ ከንፈርሽን ወለላ እንደማር
ንብረቴ ለማድረግ ምኞቴ ነበር
አይቻልም ካልሽኝ ማቀፍ ሽንጥሽን
እኔ አልፈቅድም ካልሽኝ መሳም ከንፈርሽን
ፍቅሬን መግለጥ ካልቻልኩ የልቤን መንገር
በሰላም እናብቃው መጣላት ይቅር
እንሰነባበት ነውና መጓዜ
ጻፊልኝ ቢቻልሽ ትዝ ባልኩሽ ጊዜ
ስለተለበለብኩ በፍቅርሽ ንዳድ
አልቻልኩም ለመኖር አብሮ መሰደድ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደራሲ ታደለ ብጡል
(አብሮ መሰደድ)
የልቤ ሰመመን የፍቅሬ ትዝታ
የዓይኖቼ ብሌን የሕይወቴ አለኝታ
አኔን ከጠላሽኝ ከናቅሽ ፍቅሬን
ከመሔዴ በፊት ስሚማ እሮሮዬን
ልዝብ አንደበትሽ ታጋሽ ተፈጥሮሽ
አስተዋይ አእምሮሽ ንጹሕ ልቦናሽ
ተባብሮ ከዓይኖችሽ ከውበትሽ ጋር
ልቤን ማርኮ ወስዶ አሰረው በፍቅር
ኮኮብ ዓይኖችሽን ጉብል ጉንጮችሽን
የቀጭኔ ጭራ መሳይ ጸጉሮችሽን
ለጋ ከንፈርሽን ወለላ እንደማር
ንብረቴ ለማድረግ ምኞቴ ነበር
አይቻልም ካልሽኝ ማቀፍ ሽንጥሽን
እኔ አልፈቅድም ካልሽኝ መሳም ከንፈርሽን
ፍቅሬን መግለጥ ካልቻልኩ የልቤን መንገር
በሰላም እናብቃው መጣላት ይቅር
እንሰነባበት ነውና መጓዜ
ጻፊልኝ ቢቻልሽ ትዝ ባልኩሽ ጊዜ
ስለተለበለብኩ በፍቅርሽ ንዳድ
አልቻልኩም ለመኖር አብሮ መሰደድ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደራሲ ታደለ ብጡል
👍14
#ዝምታም_ይጮኻል
የምላስ ጋጋታ ጀሮን ባይጋርደው
ይደመጥ ነበረ ዝምታም ቃል አለው
በህሊና ከሳሽ በልብ ዳኝነት
የዝምታ ችሎት የተሰየመ እለት
ሁሉም ተናጋሪ ጸጥ! ቢል ላንድ አፍታ
እመኑኝ ይጮሃል ድምጽ አለው ዝምታ
የተፈጥሮ ችሎት በልብ ሚዛን ቢረግጥ
ዓለም ለሴኮንዶች መናገርን ቢል ጸጥ
ያኔ ይደመጣል ቃል አለው ዝምታ
ገለል ሲልለት የምላስ ውካታ
ጆሮ ባይጋረድ በቃላት ጋጋታ
መጮኽ በጀመረ የስንቱ ዝምታ
የሰው ልጅ ቢኖረው ስድስተኛ ህዋስ
ይሰማው ነበረ ዝምታችን ሲፈስ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
የምላስ ጋጋታ ጀሮን ባይጋርደው
ይደመጥ ነበረ ዝምታም ቃል አለው
በህሊና ከሳሽ በልብ ዳኝነት
የዝምታ ችሎት የተሰየመ እለት
ሁሉም ተናጋሪ ጸጥ! ቢል ላንድ አፍታ
እመኑኝ ይጮሃል ድምጽ አለው ዝምታ
የተፈጥሮ ችሎት በልብ ሚዛን ቢረግጥ
ዓለም ለሴኮንዶች መናገርን ቢል ጸጥ
ያኔ ይደመጣል ቃል አለው ዝምታ
ገለል ሲልለት የምላስ ውካታ
ጆሮ ባይጋረድ በቃላት ጋጋታ
መጮኽ በጀመረ የስንቱ ዝምታ
የሰው ልጅ ቢኖረው ስድስተኛ ህዋስ
ይሰማው ነበረ ዝምታችን ሲፈስ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍9👏6❤4🥰2
#መዋሸክ
ምን ያለ ዘመን ነው ዘመነ ብልሹ
መዋሸት ብቻ ነው ትልቁም ትንሹ
ባገራችን ባህል በአገራችን ልምድ
አስነዋሪ ነበር መዋሸክ መልመድ
ግን የዘመኑ ሰው ልማድ ያደረገው
ትንሹም ትልቁም ሰውን ማማትን ነው
ለዚች ላጭር ዕድሜ መቶ ለማትሞላ
እንዴት ሰው ይኖራል ሰውን እያጣላ?
የመዋሽክና የሐሜት ዘይቤ
አያስፈልገኝም ይራቅ ካጠገቤ
ብሎ የሚል ወጣት ወይም አረጋዊ
ምነዋ በኖረ በሐቅ ኢትዮጵያዊ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደራሲ ታደለ ብጡል
ምን ያለ ዘመን ነው ዘመነ ብልሹ
መዋሸት ብቻ ነው ትልቁም ትንሹ
ባገራችን ባህል በአገራችን ልምድ
አስነዋሪ ነበር መዋሸክ መልመድ
ግን የዘመኑ ሰው ልማድ ያደረገው
ትንሹም ትልቁም ሰውን ማማትን ነው
ለዚች ላጭር ዕድሜ መቶ ለማትሞላ
እንዴት ሰው ይኖራል ሰውን እያጣላ?
የመዋሽክና የሐሜት ዘይቤ
አያስፈልገኝም ይራቅ ካጠገቤ
ብሎ የሚል ወጣት ወይም አረጋዊ
ምነዋ በኖረ በሐቅ ኢትዮጵያዊ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደራሲ ታደለ ብጡል
👏6👍4❤3🙏3
#ቅደሙኝ_አልኳቸው
ብዙ ሰው በዋይታ
ጥቂቱ በእልልታ
ዓለምን ተጋርተው
ሳቅና እንባን አዝለው
እየተገፋፉ መንገዱ ጠቧቸው
ሁሉንም በግዜ ሞቱ ሲጠራቸው
ተከትለን ሲሉኝ ቅደሙኝ አልኳቸው
እኔ ከሞት ተራ የምቀር መስሏቸው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ብዙ ሰው በዋይታ
ጥቂቱ በእልልታ
ዓለምን ተጋርተው
ሳቅና እንባን አዝለው
እየተገፋፉ መንገዱ ጠቧቸው
ሁሉንም በግዜ ሞቱ ሲጠራቸው
ተከትለን ሲሉኝ ቅደሙኝ አልኳቸው
እኔ ከሞት ተራ የምቀር መስሏቸው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_
🔥13👍6😁4❤2
#እድሜ_ለሷ
አየሁ ራቁቷን
ውበቷን
እሳቷን
ልቤ በጣም ፈራ ድፍረቴ መከነ
ከጭኖቼ መሐል ድንኳን ተደኮነ
ና ትላለች ባይኗ
ሚሳኤል ጡቶቿን ተፊቴ ደግና
ፈራሁ ጠፋኝ አቅም
ከራዲዮኔ ውጭ ጡት ጠምዝዤ አላውቅም።
ከምኔው አቀፍኳት ከንፈሬስ እራሰ
ቋሚው ብቻ ቀርቶ ድንኳኔ ፈረሰ
ከምኔው እሳቷን አቀፍኩት እስክነድ
እንዴት በዚህ ፍጥነት ተሰራሁ እንደወንድ
በውበቷ ገዳም ገባሁኝ ምናኔ
አጎንባሹ ቀናሁ ለቀሪ ዘመኔ
ፍቅሯን በገሞራ ለውሳ ቀይጣ
ወንድ አርጋ ሸኘችኝ ሰራችኝ አቅልጣ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
አየሁ ራቁቷን
ውበቷን
እሳቷን
ልቤ በጣም ፈራ ድፍረቴ መከነ
ከጭኖቼ መሐል ድንኳን ተደኮነ
ና ትላለች ባይኗ
ሚሳኤል ጡቶቿን ተፊቴ ደግና
ፈራሁ ጠፋኝ አቅም
ከራዲዮኔ ውጭ ጡት ጠምዝዤ አላውቅም።
ከምኔው አቀፍኳት ከንፈሬስ እራሰ
ቋሚው ብቻ ቀርቶ ድንኳኔ ፈረሰ
ከምኔው እሳቷን አቀፍኩት እስክነድ
እንዴት በዚህ ፍጥነት ተሰራሁ እንደወንድ
በውበቷ ገዳም ገባሁኝ ምናኔ
አጎንባሹ ቀናሁ ለቀሪ ዘመኔ
ፍቅሯን በገሞራ ለውሳ ቀይጣ
ወንድ አርጋ ሸኘችኝ ሰራችኝ አቅልጣ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤16👎3🔥3❤🔥2👍1
#ቀረሽ_እንደዋዛ
እንደ ፡ ድመቶቹ...
የትም ፡ እንደሚያድሩት
እንደ ፡ ስልክ ፡ እንጨቶች፣
እንደ ፡ ዛፍ ፡ ሀረጎች
እንደ ፡ ቤት ፡ ክዳኖቸ
ብርድ ፡ አቆራመደኝ ~ ስጠብቅ ፡ ስጠብቅ
ትመጫለሽ ፡ ብዬ...
ሳይ ፡ ማዶ ፡ ሳይ ፡ ማዶ ፣
የልጅነት ፡ ዐይኔ ፡ ሟሟ ፡ እንደ ፡ በረዶ፣
ትመጫለሽ ፡ ብዬ ፡ ደቂቃ ፡ ስቆጥር፣
ትመጫለሽ ፡ ብዬ ፡ ባዝን ፡ ባንጎራጉር፣
ትወጫለሽ ፡ ብዬ ፡ በበራፍሽ ፡ ብዞር፣
ብርድ ፡ አቆራመደኝ፣
የመንገድ ፡ መብራቶች ፡ አይተው ፡ አፌዙብኝ፣
ውርጩ ፡ ቀለደብኝ፣
ጨለማው ፡ ሳቀብኝ።
አለመምጣትሽን ፡ አውቀዋል ፡ ያውቃሉ፣
መስኮቶች ፡ ጨልመው፣
ቤቶች ፡ ተቆልፈው...
ከተማው ፡ ሲተኛ ፡ አይተዋል ያያሉ፣
አለመምጣትሽን አውቀዋል ያውቃሉ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ገጣሚገብረክርስቶስ ደስታ
እንደ ፡ ድመቶቹ...
የትም ፡ እንደሚያድሩት
እንደ ፡ ስልክ ፡ እንጨቶች፣
እንደ ፡ ዛፍ ፡ ሀረጎች
እንደ ፡ ቤት ፡ ክዳኖቸ
ብርድ ፡ አቆራመደኝ ~ ስጠብቅ ፡ ስጠብቅ
ትመጫለሽ ፡ ብዬ...
ሳይ ፡ ማዶ ፡ ሳይ ፡ ማዶ ፣
የልጅነት ፡ ዐይኔ ፡ ሟሟ ፡ እንደ ፡ በረዶ፣
ትመጫለሽ ፡ ብዬ ፡ ደቂቃ ፡ ስቆጥር፣
ትመጫለሽ ፡ ብዬ ፡ ባዝን ፡ ባንጎራጉር፣
ትወጫለሽ ፡ ብዬ ፡ በበራፍሽ ፡ ብዞር፣
ብርድ ፡ አቆራመደኝ፣
የመንገድ ፡ መብራቶች ፡ አይተው ፡ አፌዙብኝ፣
ውርጩ ፡ ቀለደብኝ፣
ጨለማው ፡ ሳቀብኝ።
አለመምጣትሽን ፡ አውቀዋል ፡ ያውቃሉ፣
መስኮቶች ፡ ጨልመው፣
ቤቶች ፡ ተቆልፈው...
ከተማው ፡ ሲተኛ ፡ አይተዋል ያያሉ፣
አለመምጣትሽን አውቀዋል ያውቃሉ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ገጣሚ
👏8❤6👍4🔥1