እሺ ስላላሺኝ ፍቅሬን ተቀብለሽ
እኔም ወድሃለው ባትይኝ መልሰሽ
አንቺ ባይኖረሽም እንደ እኔ ዓይነት ስሜት
ጨለማ ሳትሆኝ ብርሃን ነሽ ለእኔ ቤት
#ለምን?
ብዙ ሳልደክምብሽ አንዲያው በባዶ ህልም
ተስፋ በማደረግ ዉስጥ እራሴም ሳልደክም
ስለ አዳንሺኝ እኔን ከቶ ከአጉል ምኞት
ብርሃን ነሽ አንቺ ሻማየ እና ማዶት
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍️ገጣሚ_ገላና ዳንዴና
እኔም ወድሃለው ባትይኝ መልሰሽ
አንቺ ባይኖረሽም እንደ እኔ ዓይነት ስሜት
ጨለማ ሳትሆኝ ብርሃን ነሽ ለእኔ ቤት
#ለምን?
ብዙ ሳልደክምብሽ አንዲያው በባዶ ህልም
ተስፋ በማደረግ ዉስጥ እራሴም ሳልደክም
ስለ አዳንሺኝ እኔን ከቶ ከአጉል ምኞት
ብርሃን ነሽ አንቺ ሻማየ እና ማዶት
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍️ገጣሚ_ገላና ዳንዴና
👍9😁4👏2❤1
ለምን ቂምን ላትርፍ ሰውን አስቀይሜ
ለተሰፈረ ቀን ለማይጨምር መኖር
በጥላቻ ስካር እኔ አላጣም ፍቅር።
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍15❤6
#ያልጣዱት_አይበስልም
ፍቅር እንደ ዝናብ ከሰማይ አይወርድም
ያበባ መደብ ነው
በሰው የሚታነፅ ፡ በሰው የሚወድም
ተዘርቶብን እንጅ ፡ ተሰብከን አንወድም።
"ወዳጄ ወዳጄ" የሚያቀነቅኑ
አገር ያቀኑ ለት መች ልብን አቀኑ
ሳይወጡ ሳይወርዱ
ውብ ስራን ከውብ ቃል ፡ ሳያስተባብሩ
ከድሜ እና ከምቾት ቆርሰው ሳይገብሩ
ፍቅር መች ይፈልቃል?
በስብከት በምልጃ በየዋህ ሰዎች ህልም
ያልጣዱት አይበስልም
ያልዘሩት አይበቅልም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍በእውቀቱ ስዪም
ፍቅር እንደ ዝናብ ከሰማይ አይወርድም
ያበባ መደብ ነው
በሰው የሚታነፅ ፡ በሰው የሚወድም
ተዘርቶብን እንጅ ፡ ተሰብከን አንወድም።
"ወዳጄ ወዳጄ" የሚያቀነቅኑ
አገር ያቀኑ ለት መች ልብን አቀኑ
ሳይወጡ ሳይወርዱ
ውብ ስራን ከውብ ቃል ፡ ሳያስተባብሩ
ከድሜ እና ከምቾት ቆርሰው ሳይገብሩ
ፍቅር መች ይፈልቃል?
በስብከት በምልጃ በየዋህ ሰዎች ህልም
ያልጣዱት አይበስልም
ያልዘሩት አይበቅልም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍
👍7👏4❤3
እኔው ለኔ አልቅሼ እኔው ለኔ ስቄ
በውጣ ውረዱ ታሪኬን አድምቄ!!!
ዛሬን አይቻለሁ ትላንትን አልፌ
ጊዜን እየቆጠርኩ ቀናትን ገፍፌ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
በውጣ ውረዱ ታሪኬን አድምቄ!!!
ዛሬን አይቻለሁ ትላንትን አልፌ
ጊዜን እየቆጠርኩ ቀናትን ገፍፌ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
🥰6❤4👍1
#ኑሪልኝ_እህቴ
ክፉ አይንካሽ ውዴ ኑሪልኝ በጤና
የደስታዬ ምስጢር የሂወቴ ፍና
ስከፋም ስደሰት ሁኝልኝ ከጎኔ
የሁልግዜ አጋሬ የመኖሬ ቅኔ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ክፉ አይንካሽ ውዴ ኑሪልኝ በጤና
የደስታዬ ምስጢር የሂወቴ ፍና
ስከፋም ስደሰት ሁኝልኝ ከጎኔ
የሁልግዜ አጋሬ የመኖሬ ቅኔ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍7❤4👏3
#ሙግት
ጊዜ ለሰው ህይወት
ዘበት አይታክተው
እኔም ምላሽ ባጣም
መጠየቄን አልተው።
ኩታ ገጠም ናቸው
አልፋና ኦሜጋ
እንዴት ቀን ይመሻል
በቅጡ ሳይነጋ?
ማን ዘረፈው ጠጉሬን?
ማን አሰረው እግሬን?
ጉልበቴን ምን በላው?
አቅሜን ማን ወረሰው?
ተወልዶ ሳይጨርስ
እንዴት ያረጃል ሰው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍በእውቀቱ ስዪም
ጊዜ ለሰው ህይወት
ዘበት አይታክተው
እኔም ምላሽ ባጣም
መጠየቄን አልተው።
ኩታ ገጠም ናቸው
አልፋና ኦሜጋ
እንዴት ቀን ይመሻል
በቅጡ ሳይነጋ?
ማን ዘረፈው ጠጉሬን?
ማን አሰረው እግሬን?
ጉልበቴን ምን በላው?
አቅሜን ማን ወረሰው?
ተወልዶ ሳይጨርስ
እንዴት ያረጃል ሰው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍
❤16👍9
#ያንተ_ዘር_የቱ_ነው?
ዘር ቁጠር ይለኛል ሰው መሆኑን ትቶ
ገላ አፈር መሆኑን መሞቱን ዘንግቶ
እስኪ በል ንገረኝ ያንተ ዘር የቱ ነው?!
ከተደረደሩት ብሔርህስ ማነው?!
አየህ ሰው ከንቱ ነው አይኖርም ዘላለም
ቋሚ ፈጣሪ እንጅ ቋሚ ብሔር የለም!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ዘር ቁጠር ይለኛል ሰው መሆኑን ትቶ
ገላ አፈር መሆኑን መሞቱን ዘንግቶ
እስኪ በል ንገረኝ ያንተ ዘር የቱ ነው?!
ከተደረደሩት ብሔርህስ ማነው?!
አየህ ሰው ከንቱ ነው አይኖርም ዘላለም
ቋሚ ፈጣሪ እንጅ ቋሚ ብሔር የለም!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_
👍15👏2
" #ከየትኛው_ላይ_ነን?!!!"
ወደፊት መጥተናል? ወይ ሗላ ቀርተናል?
ይኼ የእኔ ትውልድ ግራ ያጋባኛል፤
ድሮ ላይ ነው ስለው ዛሬ ላይ ነኝ ይላል፤
በዛሬ ስሰፍረው ትላንት ላይ ይገኛል ፤
የትኛው ዘመን ላይ ይሆን የቀረነው?
ከአለፈው ከሌለን አሁንን ካልያዝነው?
ከባቢሎን ህዝቦች የባሰ ተቃርኖ፤
እንዲህ የለያየን በሀሳብ በታትኖ፤
ከፊት ነን ከሗላ ወይስ በትላንቱ?
የእኔ ዘመን ትውልድ የቱ ነው እውነቱ?
ወይ በአለፈው አይኖር? ከዛሬም ተጣልቶ፤
ከሁለቱም ሳይሆን መሀል መንገድ ቀርቶ፤
ወዲህ ነው ስትለው ወዲያ ነው እያለ፤
ወዲያ ነው ስትለው ወዲህ ከዘለለ?
የእኔ ዘመን ትውልድ ከየትኛው ላይ ነው?
እንኳንስ ሊያስረዳ ለራሱም ያልገባው፤
የትኛው ላይ ይሆን መንገዱ የጠፋው?
በሀሳብ ተቃርኖ መታረቅ ያቃተው?
ከትላንቱም የለ ከዛሬው የራቀ፤
እንኳንስ ከሌላ ከእራስ ያልታረቀ፤
ምን እንደሚፈልግ ማንስ ምን አወቀ?
ከባለፈው ሳይኖር በአሁን ያልደመቀ፤
ያልገባኝ ያልገባን አንድ ነገር አለ!
ከትላንት ከዛሬም ከየትም የሌለ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ወደፊት መጥተናል? ወይ ሗላ ቀርተናል?
ይኼ የእኔ ትውልድ ግራ ያጋባኛል፤
ድሮ ላይ ነው ስለው ዛሬ ላይ ነኝ ይላል፤
በዛሬ ስሰፍረው ትላንት ላይ ይገኛል ፤
የትኛው ዘመን ላይ ይሆን የቀረነው?
ከአለፈው ከሌለን አሁንን ካልያዝነው?
ከባቢሎን ህዝቦች የባሰ ተቃርኖ፤
እንዲህ የለያየን በሀሳብ በታትኖ፤
ከፊት ነን ከሗላ ወይስ በትላንቱ?
የእኔ ዘመን ትውልድ የቱ ነው እውነቱ?
ወይ በአለፈው አይኖር? ከዛሬም ተጣልቶ፤
ከሁለቱም ሳይሆን መሀል መንገድ ቀርቶ፤
ወዲህ ነው ስትለው ወዲያ ነው እያለ፤
ወዲያ ነው ስትለው ወዲህ ከዘለለ?
የእኔ ዘመን ትውልድ ከየትኛው ላይ ነው?
እንኳንስ ሊያስረዳ ለራሱም ያልገባው፤
የትኛው ላይ ይሆን መንገዱ የጠፋው?
በሀሳብ ተቃርኖ መታረቅ ያቃተው?
ከትላንቱም የለ ከዛሬው የራቀ፤
እንኳንስ ከሌላ ከእራስ ያልታረቀ፤
ምን እንደሚፈልግ ማንስ ምን አወቀ?
ከባለፈው ሳይኖር በአሁን ያልደመቀ፤
ያልገባኝ ያልገባን አንድ ነገር አለ!
ከትላንት ከዛሬም ከየትም የሌለ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_
👍12❤4🔥4
#የኔነሽ
የምጠረጥረው ፥ የማልጠረጥረው
ቄሱ መነኮሱ ፥ ወታደር ደብተራው
ያም የኔነሽ ሲላት፤
ያም የኔነሽ ሲላት፤
ለበለበኝ ፍቅር አቃጠለኝ ቅናት
ወይ ጠንካራ ክንዴ ፥ ጉልበቴ አያስቀራት!
እንዴት የብቻዬ ፥ የግሌ ላድርጋት?
ሰው በጠራት ቁጥር ፥ ባልነቴ ሟሟ
የሰማኒያ ሚስቴ ፥ የኔነሽ ነው ስሟ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደራሲይስማዕክ ወርቁ
የምጠረጥረው ፥ የማልጠረጥረው
ቄሱ መነኮሱ ፥ ወታደር ደብተራው
ያም የኔነሽ ሲላት፤
ያም የኔነሽ ሲላት፤
ለበለበኝ ፍቅር አቃጠለኝ ቅናት
ወይ ጠንካራ ክንዴ ፥ ጉልበቴ አያስቀራት!
እንዴት የብቻዬ ፥ የግሌ ላድርጋት?
ሰው በጠራት ቁጥር ፥ ባልነቴ ሟሟ
የሰማኒያ ሚስቴ ፥ የኔነሽ ነው ስሟ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደራሲ
😁17👍8❤4🔥2
" #ይገለባበጣል "
ጠላቴ አትደሰት ለእኔ ተራ መውደቅ
መነሳቴ አይቀርም ነግ ለኔ በል ይልቅ
ይገለባበጣል ጊዜ ቋሚ አይደለም
ሳይወድቅ የኖረ ሰው እስከዛሬ የለም
የወደቀው ቆሞ የቆመው ይወድቃል
ይልቅ መደጋገፍ ለሁሉም ይበጃል!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ጠላቴ አትደሰት ለእኔ ተራ መውደቅ
መነሳቴ አይቀርም ነግ ለኔ በል ይልቅ
ይገለባበጣል ጊዜ ቋሚ አይደለም
ሳይወድቅ የኖረ ሰው እስከዛሬ የለም
የወደቀው ቆሞ የቆመው ይወድቃል
ይልቅ መደጋገፍ ለሁሉም ይበጃል!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_
👏11👍8
#ልቤ_ክፍት_ይሰንብት
ከራሚ ጠፋ እንጅ ከልባችን ጓዳ
ገብቶ ወጭስ አለ የማያድር እንግዳ
ሳይጠራ ገብቶ ሳይሸኝ ይሄዳል
በዚህ ዘመን ከልብ ማን ይሰነብታል
ገብተው እየወጡ የልቤ በር ሰፍቷል
እያደር ማገሩ የጠበቀው ላልቷል!
እኔን የናፈቀኝ ከራሚ ሰው ነበር
ቃሉ የሚፀና የሚያድር ለፍቅር
ገብታችሁ አትውጡ አይባል ሰው በግድ
ሳይጋበዝ መጥቶ ሳይሸኙት ለሚሄድ
ለካስ ይከብድ ነበር ከልብ ሰው ማልመድ
ከማይዘልቅ ተጓዥ ጋር ከንቱ ነው መዋደድ
ድግስ አትደግሱ አብዝታችሁ ለሰው
ቁርስ በልቶ ምሳ ውሎ ለማይደግመው
አይዘጋ በሩ ልቤስ ክፍት ይሰንብት
አንድ ቀን ከመጣ ከራሚ ሰው ድንገት
ይመላለሱበት አይዘጋም በሩ
ቢወጡም ቸኩለው ቢጓዙ ሳያድሩ
ድንገት እንዳያጣኝ ከራሚ ሲመጣ
ልቤ ክፍት ክረም ሁሉም ገብቶ ይውጣ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ከራሚ ጠፋ እንጅ ከልባችን ጓዳ
ገብቶ ወጭስ አለ የማያድር እንግዳ
ሳይጠራ ገብቶ ሳይሸኝ ይሄዳል
በዚህ ዘመን ከልብ ማን ይሰነብታል
ገብተው እየወጡ የልቤ በር ሰፍቷል
እያደር ማገሩ የጠበቀው ላልቷል!
እኔን የናፈቀኝ ከራሚ ሰው ነበር
ቃሉ የሚፀና የሚያድር ለፍቅር
ገብታችሁ አትውጡ አይባል ሰው በግድ
ሳይጋበዝ መጥቶ ሳይሸኙት ለሚሄድ
ለካስ ይከብድ ነበር ከልብ ሰው ማልመድ
ከማይዘልቅ ተጓዥ ጋር ከንቱ ነው መዋደድ
ድግስ አትደግሱ አብዝታችሁ ለሰው
ቁርስ በልቶ ምሳ ውሎ ለማይደግመው
አይዘጋ በሩ ልቤስ ክፍት ይሰንብት
አንድ ቀን ከመጣ ከራሚ ሰው ድንገት
ይመላለሱበት አይዘጋም በሩ
ቢወጡም ቸኩለው ቢጓዙ ሳያድሩ
ድንገት እንዳያጣኝ ከራሚ ሲመጣ
ልቤ ክፍት ክረም ሁሉም ገብቶ ይውጣ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_
❤9👍4😁2👏1
#ልብና_መስታወት
አንዳችም ሳይጨምር ፥ አንዳችም ሳይቀንስ፤
በተሰጠው መጠን ለሁሉም ሲመልስ፤
ከትዝታ ገጹ ምንም ሳይጽፍበት፤
መስታወት ብቻ ነው ኑሮን ያወቀበት።
ልብ ግን አቃተው!
በመጣው ሲደሰት በሄደው ሲከፋ፤
ውለታ ሲደምር ቅያሜ ሲያጠፋ፤
ከሚስጥር ሆድ እቃው ነገር ሲያመሰኳ፤
ቀለም አልባ ሆነ- ይቅርታችን መልኳ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍በረከት በላይነህ
አንዳችም ሳይጨምር ፥ አንዳችም ሳይቀንስ፤
በተሰጠው መጠን ለሁሉም ሲመልስ፤
ከትዝታ ገጹ ምንም ሳይጽፍበት፤
መስታወት ብቻ ነው ኑሮን ያወቀበት።
ልብ ግን አቃተው!
በመጣው ሲደሰት በሄደው ሲከፋ፤
ውለታ ሲደምር ቅያሜ ሲያጠፋ፤
ከሚስጥር ሆድ እቃው ነገር ሲያመሰኳ፤
ቀለም አልባ ሆነ- ይቅርታችን መልኳ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍
👍8
#ተራርቆ_ከእውነት
ነፃነትን ሸጦ ገንዘብን ፍለጋ
በረከሰ ስደት በረከሰ ዋጋ
ህሊናን ለውጦ በሆድ አቆማዳ
እውነትን አስይዞ መግባት ትልቅ እዳ
ጎተራው ላይሞላ መሶቡ ላይፋፋ
ለኩርማን እንጀራ በውሸት ሲለፋ
አወይ ሰው ምስኪኑ ከትላንት አይማር
ውዱን እየሸጠ ለርካሽ የሚኖር
እርካታ ሳይኖረው ባለው ሳይደሰት
ሆዱ ይመራዋል ተራርቆ ከእውነት
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ነፃነትን ሸጦ ገንዘብን ፍለጋ
በረከሰ ስደት በረከሰ ዋጋ
ህሊናን ለውጦ በሆድ አቆማዳ
እውነትን አስይዞ መግባት ትልቅ እዳ
ጎተራው ላይሞላ መሶቡ ላይፋፋ
ለኩርማን እንጀራ በውሸት ሲለፋ
አወይ ሰው ምስኪኑ ከትላንት አይማር
ውዱን እየሸጠ ለርካሽ የሚኖር
እርካታ ሳይኖረው ባለው ሳይደሰት
ሆዱ ይመራዋል ተራርቆ ከእውነት
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👏8❤4👍4
#እባካችሁ_ተውኝ!!!
እንኳን የሰው ሀጢአት ደርቤ ሊቀለኝ
የእራሴንም አልቻልኩ እያንገዳገደኝ
የእኔ ነውር በዝቶ ከብዶኝ እያያችሁ
የሌላውን ሸክም ደርብ ማለታችሁ
በየትኛው አቅሜ ችዬ ልሸከመው
ሁሉም የስራውን በግሉ ይቻለው
ሰው የእራሱን በደል እያለባበሰ
የሌላውን ሀጢአት ቆሞ እየቀደሰ
ሲበርደው ይኖራል ፀጋውን ተገፎ
በሰው ጉዳይ ገብቶ እያደር ወፍፎ
እባካችሁ ተውኝ የእኔም አቅቶኛል
ከአቅሜ በላይ በዝቶ ዘንድሮስ ከብዶኛል
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
እንኳን የሰው ሀጢአት ደርቤ ሊቀለኝ
የእራሴንም አልቻልኩ እያንገዳገደኝ
የእኔ ነውር በዝቶ ከብዶኝ እያያችሁ
የሌላውን ሸክም ደርብ ማለታችሁ
በየትኛው አቅሜ ችዬ ልሸከመው
ሁሉም የስራውን በግሉ ይቻለው
ሰው የእራሱን በደል እያለባበሰ
የሌላውን ሀጢአት ቆሞ እየቀደሰ
ሲበርደው ይኖራል ፀጋውን ተገፎ
በሰው ጉዳይ ገብቶ እያደር ወፍፎ
እባካችሁ ተውኝ የእኔም አቅቶኛል
ከአቅሜ በላይ በዝቶ ዘንድሮስ ከብዶኛል
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_
👍15😭4❤2👏1
#ባልተቋጨ_ፍቅር
ያልረሳውን እውነት የረሳ ለመምሰል
ስንቱ ይታገላል ትዝታን ለማቅለል
በልቡ ማህደር ፍቅርን ተሸክሞ
በውሸት ፈገግታ እራሱን አስታሞ
ዛሬን አስመስሎ ለትላንት የሚኖር
ብዙ አለ ታማሚ ባልተቋጨ ፍቅር
በልቡ እያነባ በጥርሱ እየሳቀ
ደስተኛ መስሎ ግን የተጨነቀ
ምዕራፍ ባጣ ታሪክ እልባት በሌለው
በትላንት ትዝታ ዛሬን የሚኖረው
በውሸት ፈገግታ የሚወዛወዘው
ስንት አለ ባለበት እሱን ቤት ይቁጠረው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ያልረሳውን እውነት የረሳ ለመምሰል
ስንቱ ይታገላል ትዝታን ለማቅለል
በልቡ ማህደር ፍቅርን ተሸክሞ
በውሸት ፈገግታ እራሱን አስታሞ
ዛሬን አስመስሎ ለትላንት የሚኖር
ብዙ አለ ታማሚ ባልተቋጨ ፍቅር
በልቡ እያነባ በጥርሱ እየሳቀ
ደስተኛ መስሎ ግን የተጨነቀ
ምዕራፍ ባጣ ታሪክ እልባት በሌለው
በትላንት ትዝታ ዛሬን የሚኖረው
በውሸት ፈገግታ የሚወዛወዘው
ስንት አለ ባለበት እሱን ቤት ይቁጠረው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_
❤6👍5🔥4👏2🥰1
#ተራ_ነሽ_ለልቤ
እንደ ዛሬው ሳትሆኝ ክፋት ሳትማሪ
አውቄያለሁ ብለሽ ዘርንም ሳትቆጥሪ
በንጹሕ ልቦናሽ ሰው በመሆን ቅኔ
እወድሽ ነበረ አልወደሽም እኔ።
ስልጣኔ መስሎሽ እርቃን እውቀት ይዘሽ
ልብሽ ሲደነድን ክብርሽም ሲሟሽሽ
ጠላሁሽ ከልቤ በርካሽ ጸባይሽ
ተራ ነሽ ለልቤ የልቤን ልንገርሽ
ያኔ! ግን በእውነቱ ልብሽ የከበረ
ሰው የማክበር ዜማሽ ሰውነት ነበረ
አንደበትሽ ማርማር ለእግዚአብሔር ያደረ
ያ " ሁሉ ቀረና ዘምኛለሁ ብለሽ ቅሉም ተሰበረ
አሁን አልወድሽም የለሽም ከሆዴ
ስልጣኔሽ ሁሉ የቂል ሆኗል ውዴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
እንደ ዛሬው ሳትሆኝ ክፋት ሳትማሪ
አውቄያለሁ ብለሽ ዘርንም ሳትቆጥሪ
በንጹሕ ልቦናሽ ሰው በመሆን ቅኔ
እወድሽ ነበረ አልወደሽም እኔ።
ስልጣኔ መስሎሽ እርቃን እውቀት ይዘሽ
ልብሽ ሲደነድን ክብርሽም ሲሟሽሽ
ጠላሁሽ ከልቤ በርካሽ ጸባይሽ
ተራ ነሽ ለልቤ የልቤን ልንገርሽ
ያኔ! ግን በእውነቱ ልብሽ የከበረ
ሰው የማክበር ዜማሽ ሰውነት ነበረ
አንደበትሽ ማርማር ለእግዚአብሔር ያደረ
ያ " ሁሉ ቀረና ዘምኛለሁ ብለሽ ቅሉም ተሰበረ
አሁን አልወድሽም የለሽም ከሆዴ
ስልጣኔሽ ሁሉ የቂል ሆኗል ውዴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍10❤3🥰1
#ፖለቲካ_አልባ_ስንኝ
ዳሌሽ ያንቺ ነው? ንገሪኝ በሞቴ
ሰው ሰራሽ ከሆነ እንዳትገቢ ቤቴ
ከደረትሽ ገዝፈው የተወደሩቱ
ከጦር በላይ ሾለው የተቀሰሩቱ
ሁለቱ መንትዮች እውነት ያንቺ ናቸው?
ንገሪኝ ሳትፈሪ ዘመኑ ፎርጅድ ነው።
ከዐይኖችሽ ሽፋሽፍት የተንጨባረሩት
ከከንፈርሽ ዳርዳር ደምቀው የሚታዩት
ጸጉርሽን አስንቀው የሚንዘናፈሉት
ውዴ የማናቸው? እውነቱን እናውራ
ከተፈጥሮ በላይ ምን አለ ሚያኮራ?
አትመሪ አልልም መድመቅሽን አልጠላም
የማን እንደሆኑ ማወቅ ግን አይከፋም።
ተፈጥሮን አስንቀው ባንቺ የነገሡ
ማንነት ያስናቁ ማን ናቸው? እነርሱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
ዳሌሽ ያንቺ ነው? ንገሪኝ በሞቴ
ሰው ሰራሽ ከሆነ እንዳትገቢ ቤቴ
ከደረትሽ ገዝፈው የተወደሩቱ
ከጦር በላይ ሾለው የተቀሰሩቱ
ሁለቱ መንትዮች እውነት ያንቺ ናቸው?
ንገሪኝ ሳትፈሪ ዘመኑ ፎርጅድ ነው።
ከዐይኖችሽ ሽፋሽፍት የተንጨባረሩት
ከከንፈርሽ ዳርዳር ደምቀው የሚታዩት
ጸጉርሽን አስንቀው የሚንዘናፈሉት
ውዴ የማናቸው? እውነቱን እናውራ
ከተፈጥሮ በላይ ምን አለ ሚያኮራ?
አትመሪ አልልም መድመቅሽን አልጠላም
የማን እንደሆኑ ማወቅ ግን አይከፋም።
ተፈጥሮን አስንቀው ባንቺ የነገሡ
ማንነት ያስናቁ ማን ናቸው? እነርሱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👏12👍3❤2❤🔥1👎1🥰1
#ጀሮ_ባጣ_ሀገር
አድማጭ በሌለበት በነጠፈ ጀሮ
በስንኝ ቋጠሮ የሚያሰሙ እሮሮ
ዜማው ቢሽሞነሞን ቃላቱ ተመርጦ
ክራሩ ቢሰደር በዋሽንት አጊጦ
አድማጭ በሌለበት ብሶት ቢደረደር
ጀሮ ዋጋ ላይሰጥ ምላስ ቢቀባጥር
ቅኔ ምን ሊፈይድ ዜማስ ምን አባቱ!!!
ሰሚ በሌለው ቤት መባከን ነው ከንቱ
ከበሮ ቢደለቅ መሰንቆ ቢያነባ ዋሽንት እህ እህ ቢል
የስንኝ ቋጠሮ ከዜማው ቃል ቢጥል
ሁሉም ተዋህደው ተስማምተው ቢገጥሙ
ጀሮ ባጣ ሀገር ትርፉ ነው ድካሙ ❤
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
አድማጭ በሌለበት በነጠፈ ጀሮ
በስንኝ ቋጠሮ የሚያሰሙ እሮሮ
ዜማው ቢሽሞነሞን ቃላቱ ተመርጦ
ክራሩ ቢሰደር በዋሽንት አጊጦ
አድማጭ በሌለበት ብሶት ቢደረደር
ጀሮ ዋጋ ላይሰጥ ምላስ ቢቀባጥር
ቅኔ ምን ሊፈይድ ዜማስ ምን አባቱ!!!
ሰሚ በሌለው ቤት መባከን ነው ከንቱ
ከበሮ ቢደለቅ መሰንቆ ቢያነባ ዋሽንት እህ እህ ቢል
የስንኝ ቋጠሮ ከዜማው ቃል ቢጥል
ሁሉም ተዋህደው ተስማምተው ቢገጥሙ
ጀሮ ባጣ ሀገር ትርፉ ነው ድካሙ ❤
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_
👍9❤3🥰2
#በእንባ_የራሰ_ፍትፍት
ቀበሌ ሂድና ፥ ድህነት አስመስክር
ይላል አሉ ሃብታም ፥ መፅውቶ ሲሰክር
እማኝ ጥራ ይላል ፤ ቀበሌ በተራው
እማኙ ሲመጣ ፤ ይንዛዛል ወረፋው
አሹቅ ከጨበጠ...
ከነዳይ መዳፋ ላይ ፥ ሹም እየዘገነ
"ድሃ!" መባል እንኳን ፥ ገንዘብ ላለው ሆነ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍በርናባስ ከበደ
ቀበሌ ሂድና ፥ ድህነት አስመስክር
ይላል አሉ ሃብታም ፥ መፅውቶ ሲሰክር
እማኝ ጥራ ይላል ፤ ቀበሌ በተራው
እማኙ ሲመጣ ፤ ይንዛዛል ወረፋው
አሹቅ ከጨበጠ...
ከነዳይ መዳፋ ላይ ፥ ሹም እየዘገነ
"ድሃ!" መባል እንኳን ፥ ገንዘብ ላለው ሆነ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍
👍12👏6
#ዝኑፋ_ወቀሳ
ይለኛል ታዛቢ...
"በእኛ ተረማምዶ - ስኬቱን ሸመተ፤
ሲመቸው ፣ ሲደላው - ትቶን ሰነበተ!"
ይለኛል ታዛቢ...
"አቅፈን አሳድገን - ከሰው መሐል ለየን፤
አለፈለትና - ዞር ብሎም አያዬን!"
እኔ ግን እላለሁ...
"ስህተት የለብኝም፤
ያለፍኩበት ሁሉ አላሻገረኝም፤
የረገጥኩት ሁሉ አልተሸከመኝም!"
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በረከት በላይነህ
ይለኛል ታዛቢ...
"በእኛ ተረማምዶ - ስኬቱን ሸመተ፤
ሲመቸው ፣ ሲደላው - ትቶን ሰነበተ!"
ይለኛል ታዛቢ...
"አቅፈን አሳድገን - ከሰው መሐል ለየን፤
አለፈለትና - ዞር ብሎም አያዬን!"
እኔ ግን እላለሁ...
"ስህተት የለብኝም፤
ያለፍኩበት ሁሉ አላሻገረኝም፤
የረገጥኩት ሁሉ አልተሸከመኝም!"
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በረከት በላይነህ
❤10👍2👏1