ግጥም
4.25K subscribers
24 photos
1 video
8 links
በዚህ ቻናል በጣም ምርጥ እና መንፈስን የሚያድሱ ግጥሞች ፣ ተከታታይ ታሪኮች ፣ የኦንላይን ቢዝነስ ቲፖች ይቀርቡበታል

መርጣችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን

Buy Ads https://telega.io/c/gitm_post

ADMIN 👉 @Big_jor
Download Telegram
#ጓደኛ

ከልብህ ውሰጥ ጠልቆ ስቃይ ካልተረዳ
የጓደኛ መብዛት  አንተን ምን ሊረዳ?
ከሚግተለተለው ከሺህ ሳቅ አድማቂ
ከልብ የሚረዳ አንድ ሰው ነው በቂ።
@gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍22
ችየበት ነው እንጂ ሀዘንን መደበቅ
በማሽላ ዘዴ እያረሩን መሳቅ
እንደኔ የከፋው ማን ይሆን ዘንድሮ
በጥርሱ የሚኖር ከልቡ ሃዘን ቀብሮ።
@gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍84
#አዎ_ፍቅር_የለም

በዝሙት ህሊና በክህደት እይታ
በእምነት አልባ ቅኔ በጥቅመኞች ኩታ
ከሆነ ልኬቱ የሚዛኑም ክብደት
በእርግጥ ፍቅር የለም ሲረክስ ሰውነት
ፍቅርን በፍቅር ለሚለካ ደግሞ
የእውነት ፍቅር አለ ደጋግሞ ደጋግሞ።
@gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍63🔥3
ጉልበትም ውበትም በግዜ ይረግፋል
መልካም ስራ ብቻ ዘመን ይሻገራል
የከንቱ ከንቱ ነው ቁመና ደም ግባት
በጎነት ይኖራል ሲመሰክር እውነት።
@gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
3
#ተወደደ_ጆሮ

እኔው ለእኔ ብቻ ዝምታዬን ልስማ
መቼም ዘመኑ ነው ቢጮሁ አይሰማ
ተናግሬ ሰሚ አድማጭ በሌለበት
ዝምታ ወርቅ ነው እስኪነጋ እውነት
ላድምጠው እራሴን የብቻዬን ቅኔ
መልሱን እየመለስኩ እኔው ቆሜ ለኔ
ዝምታ አይሰማም አትበሉ ዘንድሮ
መናገር ከንቱ ነው ተወደደ ጆሮ
@gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
12👏1
ህሊናዬን ሼጬ በጮማ ከማድር
እፍኝ ቆሎ ስጡኝ ይበቃል ለመኖር
ሀሰትን ተናግሮ ከሚኖር አግስቶ
መኖር መታደል ነው እፍኝ ንፍሮ በልቶ።
@gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍12🔥1
#ነፍስ_ይማር

እውነት ታማ ነበር በወሸት ተጎድታ
መዳን ስላልቻለች ተቀበረች ሞታ
ነፍስ ይማር ይላታል የገደላት ሀሰት
ይኼኔ ነው እኮ ሁለት ግዜ መሞት
በዳይ አዛኝ መስሎ ገድሎ ካለቀሰ
በገደለው ቀብር እንባን ካፈሰሰ
በነፍስ ይማር ንፍሮ በደል ከተሻረ
ሁሉም በዳይ ቆሞ ሟችን ከቀበረ
የሞት ሞት ያኔ ነው የሟች ዳግም መሞት
በእውነት መቃብር ላይ ከነገሠች ሀሰት።
  @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍14❤‍🔥5🔥3
ቀን አይጥልም እያልኩ አልከራከርም
የዘንድሮ ዝናብ አያጉረመርምም
ድንገት እየጣለ ስንቱን አበስብሷል
መጠለያን አጥቶ የሚወድቀው በዝቷል።
@gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍103
#እንደዚህ_ነው_ለካ!

የእራስ ምስል ገዝፎ ሌላን አኮስሶ
ሲወጠር ልባችን ትቢት እብሪት ለብሶ
በሌሎች ማንነት እራስን ፍለጋ
የእኛ ይመስለናል የሌሎቹ ዋጋ
ከተሰጠን ተመን ከተፈጥሮ ጸጋ
የእራስ ባልሆነ ዓለም ከፍታ ፍለጋ
መባዘን መኳተን በሌሎቹ ዱካ
ልካችን የጠፋን እንደዚህ ነው ለካ
ድመትን ነብር ነሽ ጀግና ነሽ እያሏት
ምስሏን አስረስተው የሌላትን ሰጧት።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍73
መቼ አነሰን እና የሰው ሰራሽ ችግር
በተፈጥሮ አደጋ ቀጣኸን እግዚአብሔር?
አንተ እንኳን ተው ማረን እንደ ሰው አትክፋ
ገጠሩን አትቅጣው ከተሜው ባጠፋ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍9👏31
#አንድ_ነገር_አለ

አንድ ነገር አለ ያልገባን እውነታ
የተጋረደብን በጫጫታ ኩታ
መረዳት ያልቻልነው የሰውነት ጥጉ
ከፍታው ዝቅታው ውርደቱ ማዕረጉ
በሀቅ ያልተቃኘ ያልገባን ግርታ
አንድ ነገር አለ ያልታየን እውነታ
ወደ ነፈሰበት የሚስብ አስልቶ
ከሰውኛ ስሌት የሚጥል ጎትቶ
መግነጢሳዊ ሀይል ለእኛ ያልታወቀን
በዘር ዛር አዙሪት የሚያንቀጠቅጠን
ያልታወቀን ህመም ያልታየን በሽታ
አንድ ነገር አለ ያልገባን እውነታ
የግርግር ዓለም ረባሽ ውካታ
የእራስ አቋም ነጥቆ በሰው የሚስመራ
ባልገባን በገባን ዘወትር የሚያስወራ
እወነትን አስትቶ ከሀቅ የሚያጣላ
በሆነ ባልሆነው ትውልድ የሚበላ
ለማወቅ ያልጣርነው ሊገባን ያልቻለ
ማየት ያልፈለግነው አንድ ነገር አለ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
3👏3❤‍🔥1
በበጋው ተገኝተሽ በክረምቱ መጥፋት
ምን አለ ብለሽ ነው ከዚህ በላይ ቅጣት
ያንችስ ክፋት በዛ የጭካኔሽ ጥልቀት
ፍች ይጠየቃል ወይ አሁን በዚህ ክረምት።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍8😁53
#አንዳንድ_ሀዘን_አለ

አቅምን ሲነሳ ሃዘን ልብ ሰብሮ
ይነበባል ጎልቶ በፊት ላይ ተሰምሮ
የሚታየው እንባ በፊትሽ ገንፍሎ
መነሻው ልብ ነው ገደቡን ፈንቅሎ
አንዳንድ ሀዘን አለ በእንባ የማይወጣ
ባልጠበቅነው ቅጽበት በድንገት ሲመጣ
በውስጥ ተዳፍኖ ልብን የሚያቃጥል
አንዳንድ ሀዘን አለ በለቅሶ የማይቀል።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
🥰6👍31
አንቺም በሰው ግፊት እኔም በሰው ጣልቃ
ትዳርን መስርተን ለአንቱታ ልንበቃ
ጀመርነው መንገዱን በእልልታ በሆታ
ካለው ተበድረን በድግስ በፌሽታ!
ግና ምን ያደርጋል ያጋቡን ጎትጉተው
ተፋቱ ይሉናል ዛሬም ጣልቃ ገብተው።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
12👍4👏2
#ጭጭ!!!#እንበል!!!

በምላስ ጋጋታ ችግር ካልተፈታ
እስኪ እንሞክረው ደግሞ በዝምታ
መጮኽ መንጫጫቱ ከሌለው ቁም ነገር
ዝምታ ይታወጅ ጭጭ እንበል እንደ አገር
ሁሉም ተናጋሪ ጸጥ! ቢል ላንድ አፍታ
እመኑኝ ይጮሃል ድምጽ አለው ዝምታ
ነገርን ካለወጥን በጩኸት ኡኡታ!!!
መፍትሄው ወይ ይሆን ወይ? የሁሉም ዝምታ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👏85👍2🔥1
ብዙ ዓመታት ወስዶ ቢገነባ  ሀሰት
ይናዳል በቅጽበት በሴኮንዶች እውነት
እልፍ አላፍ ተከታይ ሀሰት ቢያሰልፍም
አንድ እውነት ሲመጣ መበተኑ አይቀርም።
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍84👏2
#እኔ_ያንተ_ምስኪን

ለኔ መምጣትህ ነው የሚታየኝ ዞሮ
መቅረትህ ቢበዛም ዓመታት ተቆጥሮ
ትመጣለህ እያልኩ መቅረትህ ሳይረታኝ
የሴትነት እድሜ መንጎድ ሳያሰጋኝ
በቃል ተጠፍሬ በፍቅርህ ውለታ
እጠብቅሀለሁ ጠዋት ሳልል ማታ
እንዲህ ነው ሳትለኝ ወጥተህ እንደ ዘበት
ቀናት በሳምንታት ሳምንታት በወራት ወራትም በዓመታት
በተፈጥሮ ህጉ ቦታ ሲቀይሩ
ዓለምን ደጋግመው በተራ ሲዞሩ
እኔ ያንተ ምስኪን ከአስቀመጥከኝ ቦታ
በመምጣትህ ናፍቆት አለሁ በትዝታ
መቅረትህ ቢበዛም በዓመታት ተቆጥሮ
ለእኔ መምጣትህ ነው የሚታየኝ ዞሮ።
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👏6👍532
ከግርግር ዓለም ከብዙ ጫጫታ
ግርማ ሞገስ አለው ያስፈራል ዝምታ
ውል ከሌለው ጩኸት ከውሸት ፈግግታ
ልብን ይማርካል ይደምቃል ዝምታ!!!
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍8🥰2
#የስንቱ_ዝምታ

የምላስ ጋጋታ ጀሮን ባይጋርደው
ይደመጥ ነበረ ዝምታም ቃል አለው
በህሊና ከሳሽ በልብ ዳኝነት
የዝምታ ችሎት የተሰየመ እለት
ሁሉም ተናጋሪ ጸጥ! ቢል ላንድ አፍታ
እመኑኝ ይጮሃል ድምጽ አለው ዝምታ
የተፈጥሮ ችሎት በልብ ሚዛን ቢረግጥ
ዓለም ለሴኮንዶች መናገርን ቢል ጸጥ
ያኔ ይደመጣል ቃል አለው ዝምታ
ገለል ሲልለት የምላስ ውካታ
ጆሮ ባይጋረድ በቃላት ጋጋታ
መጮኽ በጀመረ የስንቱ ዝምታ
የሰው ልጅ ቢኖረው ስድስተኛ ህዋስ
ይሰማው ነበረ ዝምታችን ሲፈስ።
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍64👏2
በማሽቃበጥ ትሪ እንጀራ ብንበላ
ሰው ታዘበን እንጂ ሆዳችን መች ሞላ
የማስመሰል ጉርሻ እራብ ላያስታግስ
ስም ነው ያተረፍነው በስስት ስንጎርስ።
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
👍63
#በተስፋ_የማልባት

ወተቷን ባልቀምስም ባትደርስ ለችግሬ፤
ላም አለኝ ከሰማይ ገዛሁ ተበድሬ፤
ጥገት የሆነች ናት ወተቷን የማላይ፤
በተስፋ የማልባት እያየሁ ወደ ላይ፤
ምራቅ የምታሱጥ እርጎ ቅቤ የማትሰጥ፤
ከደመና እርቃ ከላይ የምትቀመጥ፤
ላም አለች በስሜ ከቶ ማትዳሰስ፤
ለረሀብ ለችግሬ ለዛሬ የማትደርስ።
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገጣሚ_ስንታየሁ ሀብታሙ
12👍3👏3🥰2