ግጥም
4.83K subscribers
23 photos
1 video
10 links
በዚህ ቻናል በጣም ምርጥ እና መንፈስን የሚያድሱ ግጥሞች ፣ ተከታታይ ታሪኮች ፣ የኦንላይን ቢዝነስ ቲፖች ይቀርቡበታል

መርጣችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን

Buy Ads https://telega.io/c/gitm_post

ADMIN 👉 @Big_jor
Download Telegram
Channel created
#እኔነት_ሲለካ
በዝምታ ቅኔ በማስተዋል ዜማ
ከግርግር እርቀት በብቻ ከተማ
እራሴን ፍለጋ ውስጤን ስፈትሸው
ለካስ ባዶ በርሜል ጫጫታ ብቻ ነው
በተፈጥሮ ሚዛን እኔነት ሲለካ
መመለስን ትቶ መጠየቅ ሲተካ
ሁሉም ከንቱነቱን ይረዳል ከእራሱ
ከስጋው ባሻገር ሲታወሰው ነፍሱ
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
👍82
እያስተዋልን እንጂ የጊዜውን ነገር
እናውራ ካልንማ ስንት አለ የሚነገር።
ያየነውን ሁሉ በሆድ ይፍጀው ዜማ
በማለፋችን ነው የኖርነው እኛማ።
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
🔥6
#የእኔና_አንቺ_ታሪክ
ከሽህ ጦር አለቃ ከሽህ መውዜር ጓንዴ
የእኔና አንቺ ፍቅር ይማርካል ውዴ
ዘርሽን ሳልጠይቅ ዘሬን ሳታጣሪ
በልቤ ውሰጥ ገብተሽ ፍቅርን ስታበሪ
በሰውነት ሚዛን አክብረሽ ስትከብሪ
ስወድሽ ስቶጅኝ ሳኮራሽ ስትኮሪ!
ከሽህ ታንክ ጋጋታ ከሽህ መድፍ ማጓራት
እኔና አንቺ ውዴ ማርኮናል ሰውነት
ከዘር ዛር እርቀን በልባችን ጀልባ
ቀጥፌ ስሰጥሽ የፍቅርን አበባ
ሰውነቴ ገዝቶሽ ሰው መሆንሽ ገብቶኝ
እኔነቴ ማርኮሽ አንችነትሽ ገዝቶኝ!!!
በእቅድ ከሚመራ ከብዙ ጦር ልቆ
የእኔና አንቺ ታሪክ ይነበባል ደምቆ
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
2🥰2
#መነሳቴ_ላይቀር

ከትላንት ውድቀቴ ከአለፈው ተምሬ
ልበል ዳዴ ዳዴ ችዬ ልቁም በእግሬ
ጠላቴ አትደሰት ወድቆ ቀረ ብለህ
የእኔ ከስር መቅረት አንተን ለማይጠቅምህ
በእግዚአብሔር እርዳታ መነሳቴ ላይቀር
አብዝተህ አትሳቅ እንባባል ይቅር!!!
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
2🔥1👏1
" በተራ ልጠጣው"

ስከር ስከር አለኝ ያሻህን ተናገር
ሰው መቸም ጀግና ነው በጠላው ሲሰክር
ከጠጁም ደጋግም አንጋጥ በብርሌ
በፔንድሎም ዜማ ይደንስ አካሌ
ሆድ ያባውን ጌሾ ፈንቅሎ ካወጣው
ከጠላው ከጠጁ በተራ ልጠጣው።
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
👍2😁2
#የከንቱ_ከንቱ_ነው

ስንት ነው ሂሳቡ? የነፍሳችን ዋጋ
የጌታ ቀን ደርሶ ሲመጣ ፍለጋ
በየትኛው ሚዛን በየቱ ተሰፍሮ?
ይከፈለን ይሆን ዋጋው ተደምሮ?
ህይወታችን ሙሉ በበደል ሲጣፋ
የግፋችን ስፍረት ቀን በቀን ሲሰፋ
የትኛው ቅንነት የትኛው ሰው ይሆን?
አምላክ ፊት ለመቆም እኔ አለሁ የሚለን?
ፈራሁ በበኩሌ ዋጋዬን ሳሰላው
የስራዬን ክብደት ቆሜ ዝመዝነው
አጣሁ ጥሩ ነገር ለአምላክ የሚነገር
የከንቱ ከንቱ ነው ህይወቴ ሲሰፍር።
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
👍3🥰3
#ምግባር_ባይኖረኝም

ጌታ ቶሎ ምጣ አምላክ ቶሎ ድረስ
ዓለም ብሶባታል የንጹህ ደም ማፍሰስ
ለጽድቅ የሚያበቃ ምግባር ባይኖረኝም
ይምጣ የፍርድ ቀን አሁን ግድ የለኝም
የግፍ ዘመን ሆኗል ግዜው እጅግ ከፍቶ
የበደል ጽዋችን ገደብ አልፎ ሞልቶ!!!
ሀገር የደም መሬት አኬልዳማ ሆና
ሰው እድሜ ይመኛል ዛሬም እንደገና
ምን ሊበጀኝ መኖር ምን ሊረባኝ እድሜ
የግፍ ግፍ ለመቁጠር በግፍ ዓለም ቆሜ
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
😢2👍1🥰1
#ማን_ያስተምረናል?

ገድሎ መፈክርን ተክነንበታል፣
ታግሶ ማለፍን ማን ያስተምረናል?
ምህረት እንጂ ለሰው የቸገረው ዛሬ፣
ገድሎ ሸላይማ መቺ አጣች ሀገሬ።
የበደለን ምረን ይቅርታ አለማወቅ፣
ውርሳች ነው ዛሬም በግፍ መተላለቅ።
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
👍1😢1
" ነጎደ!!! በረረ!!! "

ዙፋኑ ተሰርቶ በቂም ውርስ ጥላቻ
መሪው ቢቀያየር ወጥ ላይሆን ጉልቻ
የሚጣፍጥ ፍትህ የሚያረካ ሰላም
ሁሌም እንዳማረን የመቻቻል ቀለም
እንኳንስ በጥንቱ ታሪክ በሰነደው
በእኛ እድሜም ብዙ አየን ወጥቶ በወረደው
ስንቱን ስንሾም ስንሽር ትውልድ ተገብሮ
መኖር እያቃተን አብሮ ተከባብሮ!!!
ከጥንቱም እያነስን የጥንቱን እየናቅን
ሙት ወቃሽ ሙት አንጋሽ ሁለት ሀሳብ ይዘን
ይኸው የእኛ እድሜ እንኳን ነጎደ በረረ
ለውጥም ሳናመጣ ቅሉም ተሰበረ!!!
ስንት መሪ ቆጥረን ስንት ትውልድ ቀብረን
ዛሬም የማንማር መላው የጠፋን ነን።
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
ስንታየሁ ሀብታሙ
👏1
መኖር ትርጉም ካጣ ከተብከነከነ
ከህይወት ተኳርፎ እዲው ከመነነ
አለም ባዶ ሁና ከቆረጥክ ተስፋ
ከጎንህ ሰው ካጣህ አዝነህ ስትከፋ
ዛሬ ነገ አደለም አለው አዲስ ተስፋ
ብትወድቅም ጠንክረህ ለመነሳት ልፋ
የእውነት ቀን ላንተ አለ የብርሀን መንገድ
በመውደቅም መሀል መነሳትን ልመድ
ሰው እንደው ጥፍር ነው የሰውነት ባዳ
ስሞ የሚሸጥህ ልክ እንደ ይሁዳ።
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
5👍1
#አልቻለም_ሊወለድ

የእናት ውለታዋን መጣኝ ቃል ፍለጋ
ሊቃውንት ተማክረው ቢሉ ቆላ ደጋ
አዲስ ዜማ ቅኔ ገላጭ ቃል የላቸው
እናት ከማለት ውጭ መጥራት ተሳናቸው
ሽህ ዘመናት መጥቶ ሽህ አዋቂ ቢሄድ
ከእናት በላይ ቃላት አልቻለም ሊወለድ
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
4👍3
#አብረህ_አትርመጥመጥ

ከትርምስ ዓለም ጋጋታ ከሞላው
እየተጋፋፋ ከሚዘላለፈው
ጥቂት ፈቀቅ በል እራስህን አድምጥ
የአንተነህ ዋጋ በሌሎች አይዋጥ
ጡዘቱ ከናረው ጠብቆ ከከረረው
መናገር ብቻ እንጂ ማድመጥ ከሰለቸው
ጥቂት ፈቀቅ በል ጥቂት እፎይ ምረጥ
ከሚተራመሰው አብረህ አትርመጥመጥ
ከልብህ ዋጋ ጋር እራስህን አድምጥ
ከተፈጥሮ ጋራ ሀሳብ ተለዋወጥ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
5👍1
#ችግር_የለም_አትበል

የሀገር ካዝና ጎድሎ ያንተ ስለሞላ
ሚሊዮን ጦም አድሮ ግለሰብ ቢበላ
እንዴት ይመዘናል በጥቂቶች ጥጋብ
ይፋለስ የለም ወይ በብዙዎች ራብ
ህዝብ ተቸግሮ አንተ ሽህ ብትከምር
አይሆንህም ጤና አትዝረፍ ከሀገር
ችግር የለም አትበል ቤትህ ስለሞላ
ሚሊዮን ጦም ያድራል እራቱን ሳይበላ
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
1👍1👏1
#አፋቅሮ_ያስማማን

በጥላቻ ኖረን ዘርን ከምንቆጥር
አፈር ያስማማናል ሞተን እንፋቀር
መግባባት ከአቃተን በህይወት እያለን
ሞታችን ይምጣና አፋቅሮ ያስማማን።
አሁን በዚህ ዘመን መኖሮ ለማን ሊበጅ
የተጣላ ሁሉ በአፈር ፍቅር ይወዳጅ።
@gitm_post
♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
👍61