ግጥም
5.24K subscribers
23 photos
1 video
7 links
በዚህ ቻናል በጣም ምርጥ እና መንፈስን የሚያድሱ ግጥሞች ፣ ተከታታይ ታሪኮች ፣ የኦንላይን ቢዝነስ ቲፖች ይቀርቡበታል

መርጣችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን

Buy Ads https://telega.io/c/gitm_post

ADMIN 👉 @Big_jor
Download Telegram
#ታገስ_ተስፋ_አትቁረጥ

እኩል ተሰልፎ ከብርቱካን ማሳ
እንቧይ ከደረሰው እጣውን ሲያነሳ
ፈተናው ነውና የህይወት ጎዳና
ሌላ እጣ መሞከር መፋቅ እንደገና
እንቧይ በማግኘቱ ህይወትን ከመርገም
ነገን እያሰበ  ተግቶ መደጋገም
ዛሬ በሞከረው ነገን ከማጨለም
ሌላ ሰልፍ ፈልጎ እድልን ማለምለም
ለወርቅ ተሰልፎ መዳብ የወሰደ
ተስፋውን ሰንቆ እየተራመደ
በትጋት ጎዳና ዘወትር የሚተጋ
አይቀርም ይወስዳል አለው የወርቅ ዋጋ
ግዜው ሊያስተምረው መዳብ እየሰጠ
የትግስቱን ውጤት በእንቁ እየለወጠ
የጥረቱን ፍሬ ያጭዳል አዝመራውን
ዛሬን በመታገስ ከሰራ ነገውን!!!
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ስንታየሁ ሀብታሙ
12🔥4
"ከጎራው ዘልቄ ፣ እስኪ ልነጋገር
ያለሰው ቢወዱት ምን ያደርጋል አገር
ሕንጻ መች ሆነና ፣ የድንጋይ ክምር
የእኔ ውብ ከተማ
መንገድ መች ሆነና ፣ የድንጋይ አጥር
የእኔ ውብ ከተማ ፣ የእኔ ውብ አገር
የሰው ልጅ ልብ ነው
የሌለው ዳርቻ ፣ የሌለው ድንበር
ሕንጻው ምን ቢረዝም ፣ ምን ቢጸዳ ቤቱ
መንገዱ ቢሰፋ ፣ ቢንጣለል አስፋልቱ
ሰው ሰው ካልሸተተ ፣ ምንድን ነው ውበቱ ?"
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
በዓሉ ግርማ
14👏8👍2
#ልንገርሽ_ጨረቃ

በገጣሚ ብዕር በስንኝ ቋጠሮ
በዜማ ቀማሪ በድምጽ እንጉርጉሮ
እየተሞላቀቅሽ በአፍቃሪ ደብዳቤ
በሰአሊ ቀለም በሸራ ላይ ድቤ
አሞጋሽ ሲበዛ በስምሽ ዘማሪ
ፀሀይ ልሁን አትበይ ጨረቃ ተይ ፍሪ
ደራሲ ነው እንጂ ብዕር አንጠፍጥፎ
በሰው ህሊና ላይ ያተመሽ አግዝፎ
ሰአሊው ነው እንጂ ውበትሽን አድምቆ
የሌለሽ ማንነት ከፀሀይ ላይ ሰርቆ
ገጣሚ ነው እንጂ በስንኝ ቋጠሮ
ዜመኛው በዋሽንት በድምጽ እንጉርጉሮ
አንቺን ያገዘፉሽ በሌለሽ ከፍታ
በምናብ አስውበው በፍቅረኞች ኩታ
የተራ ተራ ነሽ ልንገርሽ ጨረቃ
ፀሀይ ትበልጣለች እጅግ ብዙ ልቃ
በአሞጋሽ ግርግር በዘፋኝ እስክስታ
በጨለማ አድናቂ ሲሰጥሽ ከፍታ
ፀሀይ ነኝ አትበይ አቅምሽን እወቂ
በሰው ህሊና ላይ ገዝፈሽ አትድመቂ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ስንታየሁ ሀብታሙ
13👍5🌚2🔥1👏1🙏1
#አይደለም_ምኞቴ

ባገኘሁት ሰበብ እጭንሽ ስር መግባት
መጭመቅ ዳሌና ባት
ነፍስያን ጨቁኖ በስሜት መግባባት፤

አይደለም ምኞቴ….
እንደ ኮርማ በሬ እላይሽ ላይ መውጣት
ፍትወቴን ማስታገስ ግለቴን መወጣት
እነዚህን ሁሉ …
አላስብም ጭራሽ አላስብም ቅንጣት፤

ልንገርሽ አይደለ?
የመንፈሴን መሻት የልቤን መመኘት
ከነፍስሽ ዜማ ጋ ዜማየን መቃኘት፤

የደማ ስሜቴን …
በሀሳቦችሽ ማከም በቃሎችሽ መግራት
ከጎንሸ ቁጭ ብዬ…
ምትዪኝን መስማት ሚሰማኝን ማውራት፤

አየሽ …
ካካላችን በፊት ነፍሳችን ከጋለ
ከልባችን ግድም ፍቅር ከበቀለ
አልስገበገብም …
ገላሽ ላይ ደርሳለሁ ገላሽ ሁሌም አለ!

አዎ …
አስገድጄሽ ሳይሆን ፤
ፍቅሬ አሸንፎሽ ገላሽን ስትሰጪኝ
ያኔ ነው እንደ ማር የምትጣፍጪኝ!
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
እዮብ ዘ ማርያም
መነሻ ሀሳብ :- በዕውቀቱ ስዩም!
12🥰4👏3🔥1
#ሰው_ማልመድ_ይከብዳል!

ሰው ማመን ብጀምር አምናን እረስቼ፣
የደረሰብኝን ሁሉንም ዘንግቼ፣
ዘንድሮም ደገመኝ ጣለኝ ሰው ማመኔ፣
እኔም አልተማርኩኝ ወይ አልል ለምኔ፣
ጀርባ ይሰጡኛል ፊት ግን ይነሱኛል፣
ልቤን ይሰብሩና ፈጥነው ይርቁኛል፣
ሳልጠራቸው መጥተው ተመልሰው ሄዱ፣
እነ ወረት ዜማው መርጋት መች ለመዱ፣
ለካስ መስሎኝ ነበር እኔ የምገፋቸው፣
ከጀርባ በመቆም የወዘወዝኳቸው፣
እነርሱ ዘንድሮም አይረጋ ልባቸው፣
ለቅቤ የማይደርሱ የቸኮሉ ናቸው፣
ሳይላኩ ወዴት፣
ሳይጠሩም አቤት፣
ብለው ይመጡና ሄዱ ሳይሸኙ፣
እንደጠዋት ጤዛ ቀን ላይ ላይገኙ፣
እኔስ መስሎኝ ነበር ሰው ማልመድ ያቃተኝ፣
እንደቀትር ጥላ ስቀርብ በመራቅ ስርቀው ቢቀርበኝ፣
እንኳን እኔ ፍጡር ተፈጣሪን ላለምድ፣
ልባችን ደንድኗል ፈጣሪ እንኳን ቢወርድ፣
ሰው አልምድ አትበሉኝ ሰው ማልመድ፣ ይከብዳል፣
አንድ ክንድ ሲቀርቡት አርባ ክንድ ይርቃል!!!
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ስንታየሁ ሀብታሙ
18👍2👏1
#ተመኘሁሽ

እንዳሁኑ ሳይሆን፣ የተፈጥሮ ዉበት
መዓዛ ጠረኑን፣ ሁሉን ወሰድሽበት
በራስሽ ወዘና፣ሁሌም የምትፈኪዉ
ቻፕስቲክ፣ሊፕስቲክ፣ኮስሞቲክስ ማታዉቂዉ

የት ሄድሽ ሄዋኔ.....???!
ፍቅርን ባንደበትሽ፣ የማታስመስይዉ
ከልብሽ የሚፈልቅ፣ፈገግታ ምትቸሪዉ
የተጠና ቃላት፥ከአፍሽ የማይወጣ
ገና በዓይን ጥቅሻ፥ቀልቤን በአንችማጣ

እኔ እኮ እንደዚህ ነኝ፥ብለሽ ማትፎክሪ
በገፅሽ ድንቅ ፀዳል፥ከሩቅ የምትጠሪ
ፀባይና ዉበት፣የተሰጠሽ ላንቺ
በሁሉ ነገርሽ፣ለሰዉ ምትመቺ

የት ሄድሽብኝ  ሄዋኔ.....???!
ካለሽበት ልምጣ፣ አንዴ ተዋወቂኝ
ሁለንተናነትሽን፣ ባክሽ ለእኔ ስጭኝ
የምትፈልጊዉን፣አይነት ወንድ ልሁንልሽ
የእኔ መሆንሽን ልወቅ፣ብቸኛ አልሁንብሽ

ካንች ጋራ ሁኘ ፣  ፍቅርን ላጣጥመዉ
ያለሽበት ቦታ፣መገኛሽ ከየት ነዉ..???!!

    'ካሁኑ ናፈቅሽኝ'
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
      ✍🏽 B.J
12🔥1🥴1
#አልሞትም

ስሚ
እኔ በዚህ አለም ፤ብዙ ብሰቃይም
አንድ ሀሙስ የቀረዉ ፤መስየ ብታይም
አምሮቴን ሳላገኝ ፣ ሱሴን ሳላከትም
ከመሬት ከርስ ዉስጥ ፤ ገላየን አልከትም

አልሞትም
ማንም ባልደፈረዉ መንገድ ሳላከትም
እንደ ንጉስ አይዙር ግማሽ ቀን ሳልነግስ
በጠገበዉ ሳልስቅ፣ለራበዉ ሳልደግስ

አልሞትም
ዝማሜን ሳላዉቅ ያንደበቴን ግድብ
ዙፋን ላይ ሳልሸና ጌቶችን ሳልሰድብ
ከድሀዉ ሳላብር ካገሬዉ ሳልወግን
ከምድር በረከት ድርሻየን ሳልዘግን

አልሞትም

ስሚ

ልቤ እንደምኞቱ ቢያገኝ እንደምርጫዉ
ያላማየ ማብቂያ አንቺ ነሽ መቋጫው
እና
አገሬን ለቅቄ ልብሽ ላይ ሳልከትም
በዉብ ከንፈርሽ ላይ ከንፈሬን ሳላትም
አልሞትም።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   በእዉቀቱ ስዩም
18👍1🔥1🥰1😁1🥴1
#እናቴ_ትሙት_አንላቀቅም!

“ሰማህ የኔ ውድ . . .
ሳፈቅርህ ከልቤ ባንተ ተረትቼ
ስላንተው ስባክን አቅሌን ነፍሴን ስቼ
በክንድህ እያሟሟህ ባፍህ እያቀለጥከኝ
ከማያውቁት ዓለም ወስደህ እየከተትከኝ
ነፍሴን አስክረሃት በሀሴት ዳንኪራ
እንዳልቆም እንዳልሄድ ያላንተ እንዳልሰራ
አድርገህ ጠፍረህ እንዲህ አሳስረኸኝ
እሄዳለሁ ብትል ከመንገድ ጥለኸኝ
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
እኔ በፍቅር ቀልድ አላውቅም!”
ስትይኝ ፈራለሁ
አንዳንዴም ኮራለሁ
አንዴ ደስ ይለኛል
አንዳንዴ ይጨንቀኛል።

“እየውልህ ውዴ . . .
እኔማ ስወድህ ሁኚ ያልከኝን ሆኜ
የኔን ዓለም ትቼ ባንተ ዓለም መንኜ
ጠቅልዬ ግብቼ ከገዳምህ ዋሻ
በስምህ ፀልዬ ሃጢያቴን ማስረሻ
እንደሆነ መቼም አንተም ታውቀዋለህ
ከቶ ያልሰጠውህ ኧረ እንደው ምን አለህ
ታዲያ ሁሉን ወስደህ ባዶዬን ቀርቼ
ኑሮዬን በሞላ አንተው ላይ ገንብቼ
ስታውቀው እንዳልኖር አንተን ተለይቼ
እሄዳለሁ ብትል ድንገት አንቺን ትቼ
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
እኔ በህወት ቀልድ አላውቅም!”
ስትይኝ ፈራለሁ
አንዳንዴም ኮራለሁ
አንዴ ደስ ይለኛል
አንዳንዴ ይጨንቀኛል።

ሰማሽ የኔ እመቤት . . .
እውነት አንቺን ርቄ
እምነትሽን ፍቄ
በፍቅርሽ ቀልጄ
ሌላ ሴት ለምጄ
ምኖር ይመስልሻል ?!
እውነት እውነት እውነት
በእውነት ተሳስተሻል !
ደግሞ ፉከራሽን ዛቻሽን ፈርቼ
እንዳይመስልሽ ውዴ እኔስ ተረትቼ!
ይልቅ እኔም አልኩሽ . . .
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
ካንቺስ ወዲያ ሴት አላውቅም።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
አብዲ ሰዒድ
21🔥2👏1
#እኔ_እወድሻለሁ

ብዙ ሺህ ዘመናት
እልፍ አእላፍ ሌሊት
ሚሊዮን መሰለኝ
ፍቅሬ አንቺን ስወድሽ
ቀኑ እረዘመብኝ።
እኔ እወድሻለሁ
የሠማይ መሬቱን
የባህር ስፋቱን
የዓለም ዳርቻ የርቀቱን ያህል
እንደ ፅጌ-ረዳ
እንደ አደይ አበባ
እንደ ሎሚ ሽታ።
እንደ እጣን ጢስ እንጨት፣ እንደ ከርቤ ብርጉድ፣
እኔ እወድሻለሁ፣ አበባ እንዳየ ንብ።
እንደ ቢራቢሮ ጫካ እንደሚያስሰው
ፍቅርሽን በፍቅሬ በፍቅርሽ ልቅመሰው
ማር ወለላ ነሽ ከረሜላ ስኩዋር
አማርኛ አይበቃም፤
ወይ ጉድ!
በአለም ቋንቋ ሁሉ ቢወራ ቢነገር፤
እኔ እወድሻለሁ
እንደ ማታ ጀንበር።
እንደ ጨረቃ ጌጥ፣ እንደ ንጋት ኮከብ፣
እኔ እማልጠግብሽ
ስወድሽ፣ ስወድሽ፣ ስወድሽ፣ ስወድሽ።
ጡት እንዳየ ህፃን ወተት እንዳማረው
ጠጋ በይ ዘመዴ አፍሽ ህይወቴ ነው።
ጣይ እንዳየ ቅቤ
ገላዬ ገላሽን ሲነካ የሚያልቀው፣
አፈር መሬት ትቢያ ውሃ እንደሚበላው፣
ፍቅሬ አንቺን ስወድሽ
ብዙ ሺህ ዘመናት
እልፍ አእላፍ ሌሊት
ውዴ እወድሻለሁ፣
ዓይኖችሽን በዓይኔ ተዳክሜ እያየሁ
ስወድሽ ስወድሽ
እኔ እወድሻለሁ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ገብረክርስቶስ ደስታ
17🔥2
#በማይከፈት_ቤት!

ተሻለህ አትበሉኝ ዛሬም ብሶብኛል
ወይ አልሞት አልድንም ስቃይ ያኖረኛል
በሰቀቀን እንባ በሐዘን ዜማ ስልት
ግራ በተጋባ ትርጉም አልባ ቅኝት
ክራሬን ስገርፈው ብሶት እያዜመ
የአምናው በሽታየ ዘንድሮም ከረመ
ግርፉ ሲሰለቸኝ ብደረድረውም ቅኝቱን ቀይሬ
ከተለከፈበት የሗሊት አዙሪት ቆሞ ቀርቷል እግሬ
እንኳንስ መራመድ መንፏቀቅ ብርቁ ነው
በትዝታ አለንጋ በመለየት ጅራፍ የተገረፈ ሰው
ዳዴ ማለት አይችል ግፋ ቢል መንፏቀቅ
በታመነ ልቡ የናፍቆት ከበሮ ቀን በቀን መደለቅ
ክራሬን ስበሩት ድንገት ከተሻለኝ
ዋሽንቱን ሰንጥቁት ሳጣው  ከቀለለኝ
በገና ማሲንቆ አደራ እንዳተሰብሩ
ካምላክ እንድታረቅ ይልቅስ ደርድሩ
አምና ዝናብ ጥሎ እህል በቅሎ ነበር
የኔ ልብ ግን ዘርቶ ድርቅ ያጠቃው ፍቅር
ከውስጥ በተዘጋ በማይከፈት ቤት
ለብቻው ነው ዛሬም በስቃይ አዙሪት
ይኸ ሰው ምን ነካው ሲሉ እየሰማሁኝ
ከንፈር እያስመጠጥኩ በህይወት አለሁኝ
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ስንታየሁ ሀብታሙ
13🔥8👍3
#ትቀሪያለሽ_ብየ...

ግድየለሽምና ፥ ከልብ ላፈቀረሽ
ሶስቴ ተቀጣጥረን፥ አራት ጊዜ ቀረሽ።

ዛሬም እንደ ወትሮው፥ ትቀሪያለሽ ብየ
እድል የላከውን፥ እጣ የሚመስል፤ እጦት ተቀብየ፥
አበባ ሳልቀጥፍ
አልጋ ሳላነጥፍ
ሙታንታየን ሳልጥፍ
በትራስጌየ ላይ ፎቶሽን ሳለጥፍ፥

ትቀሪያለሽ ብየ፥

በመስታውቴ ፊት
ከልብ አስቀይሜ
አንድ እፍኝ ነጭ ሽንኩርት
እንደ ተልባ ቅሜ
አየሩን መርዤ፥ ህዋሴን አክሜ፤

ትቀሪያለሽ ብየ፥
ጥፍሬን ሳልከረክም
በመቀስ ሳልንደው፥ የጉያየን ሸክም

ትቀሪያለሽ ብየ
ጀንበርን ቀድሜ፤ ቤቴ ተከትቼ
ግቤን ያለ ረዳት፥ በጊዜ መትቼ
የከሸፈ ትውልድ አንሶላ ላይ ትቼ
ልተኛ ስዘጋጅ፥ እፎይ ብየ አርፌ
ከወደ በራፌ
“ውዴ! ደርሻለሁ፥ የሚል ድምጽሽ መጣ”
ከመግባትሽ በፊት፥ እኔ በየት ልውጣ?
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
በእውቀቱ ስዩም
😁159👍8🔥1😭1
#ምንጩ_ሀዘናችን

በሳቃችን ግዜ የሚፈሰው እንባ፣
  ቀድሞ በልባችን በሃዘን ባይገባ፣
በደስታችን ቀን ከቶ ከየት ነበር?
ምንጩ ሀዘናችን ከውስጥ ባይቀበር፣
  የሰው ልጅ ልብ በል አስተውል በጥልቀት፤
  ጎርፍ ሆኖ የሚፈሰው ስሜትህ ሲደሰት፤
ቀስ እያለ ገብቶ የተጠራቀመው፥
በደስታ ሰበብ ድንገት የሚፈሰው፣
  የብዙ ሀዘን ውጤት የትላንት ጥርቅም፣
  እርሱ እንጂ ውጤቱ ደስታህ አይደለም።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ስንታየሁ ሀብታሙ
👍134
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
👍148🎃1
#እፈልግሻለሁ

የ'መንጋው  እረኛ
ላንዲት ግልገል ብሎ እንደሄደው ያ'ኔ፣
ካ'ስራ ሁለ'ት አጥንቴ ዛሬ አ'ንቺ ብትጎ'ይ…
ፈላጊሽ ነኝ እ'ኔ …።
የ'ወደድኩሽ ለ'ታ ልቤ የዳዊት ነው
ጉልበቴ የ'ሶምሶም፣
ጨለማና ንጋት  አይችሉም ከ'ፊቴ…
ባ'ንቺ ፍቅር ስቆም ።
ሰ'ላሜ ነው ፍቅርሽ🙏
ከ'ሰማዩ ግርማ ከ'ገነት ይበልጣል!!
እንኳን እ'ኔ ቀርቶ…
ሰለሞን ከ'ክብሩ ከንግስናው ወርዷል።
👇👇
እንዲያ ነኝ ስ'ናፍቅ__
ድካም የማይገባኝ ሌ'ት ተ'ቀን የ'ምከንፍ!!
ዘረሰብ ሲያሸልብ እንቅልፍ የ'ማያምረኝ…
ከጨለማው እቅፍ… …።
የ'ማልፈርስ በ'ጩህት
እንደ 'ጎሊያድ ት'ጥቅ እንደያሪ'ኮ ግንብ!!
የ'ወደደኩሽ  ለ'ታ 👈👈
አ'ለት ነው ላንቺ  "ቃል"  ይህ ልቤ ቢ'ጠረብ።
አይፈርስ አይበሰብስ ጀንበር ከጠለቀ
ውስጤ ሙት ባህር ነው ፤
እውነትና መንገድ ፦ ያ'ኔ ያሳየሽኝ፣
ያ'ንቺ ፍቅር ብ'ቻ ነው"።
ድቅድቁን  አልፈራም ጨረቃና ከዋክብት
ቢወጡ  ባይወጡ ፤
ፈልጎ ማግኘት ነው ይ'ህ ልቤ ዳተኛ፣
ሰ'ርክ አንቺን ማ'ማጡ።
ነፍሴ ላይ በቅለሻል
የምሽት   አበባ_ 🌸🌸
የድሜ ልክ ፀሃዬ_፤
በውበትሽ   ፀዳል…
የውስጤን  ጨለማ፣
በፍቅርሽ ገድዬ ።
እሄዳለሁ ሲመሽ  እጓዛለሁ ማታ፣
ተራራው ይናዳል  ጨለማው ይገፋል፦
ያገኘሁሽ ለታ።🙏🙏
እስከዛው ጠ'ብቂኝ!
አንቺ'ን ከ'ኔ ሊያበጅ ከጣለብኝ እንቅልፍ፣
ቃል ለ'ምድር ለ'ሰማይ!!
እስካገኝሽ ድረስ በህልሜ እንኳ'ን አላርፍ ።
👍52🔥1🎄1
ግጥም pinned «https://t.me/Hammer_Bingo»
#ፈርመሐል_በቃ

ብጥልህ ባነሳህ
ብስምህ ብነክስህ
እንደኳስ አጉኘ መልሸ ብቀልብህ
እሹሩሩ እያልኩኝ ስፈልግ ባልልህ
ፈርመሐል በቃ በ80 ገመድ በውል ሽማግሌ
እንደፈለኩ ላድርግህ ነህና የግሌ
ስፈልግ ልፈታህ ስፈልግም ላስርህ
ቅር ባለኝ ጊዜ ንብረት ልካፈልህ
መች ይሆናል ትዳር በዚህ አይነት ሒሳብ
ባሰርኩት ጠፈርኩት የንቧይ  ጫወታ ካብ
በፍቅር አስረሽው ልቡን ካልገዛሽው
በ10 ሽማግሌ በ80 ጣጣ ዘወትር ብጠፍሪው
መች እሱስ እሽ ሊል ልቡ እየሸፈተ
ከውጭ ባየው ዳሌ ዘሎ እየዘመተ
አስሪያለሁ ስትይ ታስረሽ እንዳትቀሪ
ከ80 በላይ ቤት በፍቅር ስሪ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ስንታየሁ ሀብታሙ
👍233
#ወህኒ

ካቻምና በመስቀል ድፎ ባርኬአለሁ።
ዘንድሮ በጩቤ አጥንት ወግቻለሁ።

          ለምን እንዳትሉ፤
           በቃ ሆነ በሉ፤
           የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።

አምና ደግ ነበርኩ ፣ ክፉ ሰው ዘንድሮ
ትናንትና ምሁር ፣ ዛሬ ግን ደንቆሮ ።

            ለምን እንዳትሉ ፤
            በቃ ሆነ በሉ ፤
            የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።

መሆን አምሮኝ ያውቃል፤ ፖለቲከኛ ሰው ፣ ኃያል የጦር መሪ ፤
ተመኝቼም ነበር ለመሆን አዝማሪ ፤
ገጣሚ ለመሆን ስንኝ ቋጥሬአለሁ ፤
ደራሲ ለመሆን ተስዬም አውቃለሁ ፤
ሞዴል አርሶአደርም ለመሆን ፈልጌ ፣
አስጠምጄ ነበር ከ 4 ኪሎ ግርጌ ።
ኢንጂነር ዶክተርም ልሆን ነበር እኮ ፤
እንደዚህ ሆንኩ እንጂ ነገር ሌላ ታኮ ።

            ለምን እንዳትሉ፤
            በቃ ሆነ በሉ ፤
            የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።

አንድ ሰው አንድ ነው ከንግዲህ አትበሉ ፤
            የሰው ልጅ ወህኒ ነው ፤
እልፍ አዕላፍ ሰዎች ታስረው የተጣሉ ፣
መውጫ አጥተው ነው እንጂ፣አንድ ሰው ውስጥ አሉ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
    ✍️ ይስማዕከ ወርቁ
11👍9👏2🔥1🥰1
ለፀሐይ ፍካት ማን ይፈግጋል?
ለሰማይ ንጣት ማን ይደግሳል?
ማን ግድ ብሎት ማን ስሜት ሰጥቶት?
ከምድር አልፎ ሰማዩን አይቶት?¡

ዘልቋል ከውስጥኽ? ገብቶሃል ቅኔው?
ምን ብትነጠፍ ሰማይ ብትሆነው
የያዘው እክል እስካልለቀቀው፧
ከኑሮ አሻግሮ ግትር አንገቱን እስካላዞረው፧
መቼም አያይህ ያልቀናለት ሰው!
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ዓለም
17💘2🔥1🥰1
#ስሞታ_አቀርባለው

በሚያላዝን ቀኔ ገጠመኝ አላውቅም
ለከበደኝ ለአይኔ ሽሙጥ አያምረኝም
ዳገቱን ብቆፍር ጥቅም አገኝ ብዬ
ከዘብጥያ ባድር እንደ ጥሬ እንሻፎ
ባልተማማልኩበት ትቢያ ስር ተጥዬ
ሽቅብ ስመለከት ህማሞቼን ጥዬ

ረግፎ ለታየው ለዚህ ስጋ ለባሽ
ጽዋውን ለቃኘው ለታዛቢው ቢጤ
እንክርዳዱን ቀማሽ…………………..

በደሌን ይቅር በል አስበኝ እያልኩኝ
የልብ ሀዘኔታ ብሶት እያስቃኘው
የክስመቴን ክፋይ ህሊና ቢቀልበው
ክፋት ሲከረፋ እምባ ጣሬን ላየው
ስሞታ አቀርባለው………………።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
     ✍️ ኢያሱ ከበደ
4🔥4🥰3👍1
#ኑ_አብረን_ሞኝ_እንሁን

በሚያስለቅስ እንሳቅ በሚያስቅ እናልቅስ
ኑ አብረን ሞኝ እንሁን በተቃርኖ ድግስ
ሲርበን እንጥገብ ስንጠግብ ይራበን
ሲጠማን እንርካ ስንረካ ይጥማን
በለቅሶ ላይ ዘፈን በሰርግ ላይ ሙሾ
አብረን እንጃጃል በመዘመን እርሾ
እንሰልጥን በጋራ በቂልነት እውቀት
ዘር ዘር ይሻለናል ይቅርብን ሰውነት ።
ከክብር ዝቅ እንበል አንድ ላይ ተባብረን
በሞኝ ስልጣኔ እንጓዝ ቸኩለን!!!
ዓለም ይሳቅብን ስራችን ይቃረን
በደንብ አሳስቆ ውሃው እንዲበላን።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   ስንታየሁ ሀብታሙ
11👍9😁4🥰1