#አለሁ_እንደ_ሾላው
በገዛ ጆሮና ፥ በገዛ አይኖችሽ ላይ
ሙሉ ስልጣን ያለሽ
ከቶ እንደምን አለሽ?
አለሁ እንደ ሾላው
እንደ ወፍ መነሻው
እንደ ወፍ መሸሻው
ጸሐይ እየሞቀ ከመተንፈስ በቀር፤ ሌላ እንደማይሻው፤
መኖር ብቻ ሲሆን ፥ የሰው ልጅ እቅዱ
በሲኦል ቢኖርም፥ አይቀርም መልመዱ
እኔም ከመበላት፥ መብላት ይሻል ብየ’
‘ፍሪደም ‘ ቢርቀኝ፥ ፍሪዳየን ጥዬ
ነጻነት ቢርበኝ፥ እየበላሁ እህል
አለሁ ይህን ያህል ፡ ፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
በገዛ ጆሮና ፥ በገዛ አይኖችሽ ላይ
ሙሉ ስልጣን ያለሽ
ከቶ እንደምን አለሽ?
አለሁ እንደ ሾላው
እንደ ወፍ መነሻው
እንደ ወፍ መሸሻው
ጸሐይ እየሞቀ ከመተንፈስ በቀር፤ ሌላ እንደማይሻው፤
መኖር ብቻ ሲሆን ፥ የሰው ልጅ እቅዱ
በሲኦል ቢኖርም፥ አይቀርም መልመዱ
እኔም ከመበላት፥ መብላት ይሻል ብየ’
‘ፍሪደም ‘ ቢርቀኝ፥ ፍሪዳየን ጥዬ
ነጻነት ቢርበኝ፥ እየበላሁ እህል
አለሁ ይህን ያህል ፡ ፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
👍9❤6👏3
#እራሴንስ_እንዴት_ልመን?
ላስታውስሽ አስብና
ከሩቅ ላይሽ በትዝታ
ብዙ አይደለም ላንዲት አፍታ
ለቅፅበት እንደትንታ ፣እንደነጎድጓድ ብልጭታ
አይመጣልኝም ሁነትሽ
ጠፍቷል ምስልሽ ከአዕምሮየ
የቱ ዝናብ አጥቦት ይሆን
ጠረንሽን ከገላየ
ድምፅሽን ከልቦናየ?
ስንት ዘመን አብረን ስቀን
ከድሚያችን ላይ ስንት ዓመታት
ተሰጣጥተን ተሰራርቀን
ያረፈብን የፍቅር ወበቅ
ገሞራው ጫካ የሚያደርቅ
ያሳለፍነው ብዙ ክረምት
እሳት ቆፈኑን የማይገፈው
እንዴት ነው ያ ሁሉ ህይዎት
በቀን ክንድ የሚራገፈው?
"ነበረች ግን?"እያልኩ ነው
ነበርሽ ግን ፈጥሬሽ ነው?
እንዳ'ቧራ እንደብናኝ
እፍ ሲሉት በቃ የለም?
ቅዤት ይሆን አልነበርንም
እኔና አንች በዚች አለም?
ፍቅራችን ደንቆት ከተማው
"ጉድ እኒህ ልጆች" አላለም?
እቅፌ ውስጥ እንዴት ሟሟሽ?
ቆይ ሞቃት ነበርሽ ቀዝቃዛ
ሸካራ ነበርሽስ ለስላሳ ?
እንዴት ቅንጣት ነገር ልጣ
በጣት እንኳን የሚነሳ
እንደ ህልም እንደዋዛ?!
መቸ ነበር የመጣሽው
መቸስ ነው መምጣት የተውሽው?
ከየት ነበር የምትመጭው
እንደፀሀይ የምትወጭው?
እንዳልነበር እንዳልሆነ
ምን ምድጃ ላይ ብጣድ ነው
ስምሽ ሳይቀር ከነፍሴ ውስጥ
ብን ብሎ የተነነ ?
ቀን ብቻ ነው ያረሳሳን
ወይስ ትላንት ሙተን
ሌላ ሰው ሆነን ተነሳን?
ምን አወራን ምን አቀድን
የቱን ክበን የቱን ናድን?
ስንቱን አድባር ተሳልመን
በየወንዙ ተማምለን
ለምልክት ከረሳሁሽ
ራሴንስ እንዴት ልመን?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አሌክስ አብርሃም
ላስታውስሽ አስብና
ከሩቅ ላይሽ በትዝታ
ብዙ አይደለም ላንዲት አፍታ
ለቅፅበት እንደትንታ ፣እንደነጎድጓድ ብልጭታ
አይመጣልኝም ሁነትሽ
ጠፍቷል ምስልሽ ከአዕምሮየ
የቱ ዝናብ አጥቦት ይሆን
ጠረንሽን ከገላየ
ድምፅሽን ከልቦናየ?
ስንት ዘመን አብረን ስቀን
ከድሚያችን ላይ ስንት ዓመታት
ተሰጣጥተን ተሰራርቀን
ያረፈብን የፍቅር ወበቅ
ገሞራው ጫካ የሚያደርቅ
ያሳለፍነው ብዙ ክረምት
እሳት ቆፈኑን የማይገፈው
እንዴት ነው ያ ሁሉ ህይዎት
በቀን ክንድ የሚራገፈው?
"ነበረች ግን?"እያልኩ ነው
ነበርሽ ግን ፈጥሬሽ ነው?
እንዳ'ቧራ እንደብናኝ
እፍ ሲሉት በቃ የለም?
ቅዤት ይሆን አልነበርንም
እኔና አንች በዚች አለም?
ፍቅራችን ደንቆት ከተማው
"ጉድ እኒህ ልጆች" አላለም?
እቅፌ ውስጥ እንዴት ሟሟሽ?
ቆይ ሞቃት ነበርሽ ቀዝቃዛ
ሸካራ ነበርሽስ ለስላሳ ?
እንዴት ቅንጣት ነገር ልጣ
በጣት እንኳን የሚነሳ
እንደ ህልም እንደዋዛ?!
መቸ ነበር የመጣሽው
መቸስ ነው መምጣት የተውሽው?
ከየት ነበር የምትመጭው
እንደፀሀይ የምትወጭው?
እንዳልነበር እንዳልሆነ
ምን ምድጃ ላይ ብጣድ ነው
ስምሽ ሳይቀር ከነፍሴ ውስጥ
ብን ብሎ የተነነ ?
ቀን ብቻ ነው ያረሳሳን
ወይስ ትላንት ሙተን
ሌላ ሰው ሆነን ተነሳን?
ምን አወራን ምን አቀድን
የቱን ክበን የቱን ናድን?
ስንቱን አድባር ተሳልመን
በየወንዙ ተማምለን
ለምልክት ከረሳሁሽ
ራሴንስ እንዴት ልመን?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አሌክስ አብርሃም
❤8👍4😇1
#በሉ_መልሱልኝ!!?
ግራ የገባውን ቀኙ የጠፋበት
ለተዘጋጀ ሰው እራሱን ለማጥፋት
አድኑት ቢሏችሁ በተስፋ መልሱት
ምንስ ብትሉት ነው የሚድን ከመሞት?
የችግሩን ሰንኮፍ ነቅሎ የሚጥል ቃል
ምረጡ ቢይሏችሁ ችግሩን ለማቅለል
ምንድን ነው መልሳችሁ? ክፋትን የሚጥል
ሟችን አጠንክሮ ሞትን የሚገድል!
እራሱን ሊያጠፋ ለተሰናዳ ሰው
የህይወት አዙሪት ግራ ቀኝ ለጠፋው
የትኛው ምክር ነው ተስፋ የሚሰጠው
ሰርስሮ ችግሩን ነቅሎ የሚጥለው
በሉ መልሱልኝ ልጠይቅ መካሪ
ለሆነበት ምስኪን ማውለቅ ባንገት ሱሪ
የትኛው ቃል ሰብሮ ሞቱን ያሸንፋል?
ከስር መሰረቱ ስቃዩን ያክማል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ግራ የገባውን ቀኙ የጠፋበት
ለተዘጋጀ ሰው እራሱን ለማጥፋት
አድኑት ቢሏችሁ በተስፋ መልሱት
ምንስ ብትሉት ነው የሚድን ከመሞት?
የችግሩን ሰንኮፍ ነቅሎ የሚጥል ቃል
ምረጡ ቢይሏችሁ ችግሩን ለማቅለል
ምንድን ነው መልሳችሁ? ክፋትን የሚጥል
ሟችን አጠንክሮ ሞትን የሚገድል!
እራሱን ሊያጠፋ ለተሰናዳ ሰው
የህይወት አዙሪት ግራ ቀኝ ለጠፋው
የትኛው ምክር ነው ተስፋ የሚሰጠው
ሰርስሮ ችግሩን ነቅሎ የሚጥለው
በሉ መልሱልኝ ልጠይቅ መካሪ
ለሆነበት ምስኪን ማውለቅ ባንገት ሱሪ
የትኛው ቃል ሰብሮ ሞቱን ያሸንፋል?
ከስር መሰረቱ ስቃዩን ያክማል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤16💔4
#ደረትና_እውነት
የልጅነት ነገር ፤ ቴሜቴ ጨዋታ፤
ደረቴን ስትደቂ ፤ ደረትሽን ስመታ
የነገርሽኝ ነገር ፤
ትላንት ስትከጂኝ ፤ትዝ ብሎኝ ነበር፤
እቴ ሜቴ የሎሚ ሽታ፤
ያ ሰውዬ ምን አለሽ ማታ?
ብዬ ስጠይቅሽ ፤ በለጋ አንደበቴ
ምንም
ምንም
ምንም አላለም ፤
ብለሽ የመለስሽው ፤ ከሆድሽ አይደለም
ደግሞም አውቅሻለሁ ፤ ቅጥፈት ስታስቢ
እንዳንች ቀጣፊ የለም
ንገሪኝ በሞቴ ፤
ሳይቦዝዝ ቅላቴ፤
እቴ ሜቴ እያልኩሽ ፤ በተባ አንደበቴ
ያ ሰውዬ ምን አለሽ ማታ? ብዬ 'ምጠይቅሽ፤
እውነት አምሮኝ እንጂ ፤ ቀንቼ እንዳይመስልሽ
አየሽ...
በውሸት ሀገር ላይ ፤ እውነት የሚናገር
ውሸታም ይባላል ፤ በሀቀኞች ሰፈር
ውሸት ተደጋግሞ ፤ ከእውነት ሚስተካከል፤
ከእውነት 'ሚሳከር ፤
ረስተሽ ይሆን እንጂ ፤ የኛ ሀገር ነበር
እውነቱን ከውሸት ፤
ውሸቱን ከእውነት ፤ ስላደባለቅነው
ያንቺን የውሸት እውነት ፤
እንዴት አምንሻለው?
በውሸታም ሀገር እውነት ተናጋሪ
ውሸታም ይባላል
በውሸቶች ሀገር መሲህ ይሰቀላል
እቴ ሜቴ የሎሚ ሽታ፤
ያ ሰውዬ ምን አለሽ ማታ?
ምንም ምንም አላለኝ፤
ትዳርሽን ፈቶ ልውሰድሽ አለኝ
በጨዋታ መሀል ፤ ቅር አለኝ መሠለኝ
የልጅነት ነገር ፤ ቴሜቴ ጨዋታ
ደረቴን ስትደቂ ፤ ደረትሽን ስመታ
የነገርሽኝ ነገር ፤
እድሜ ተቀይሮ ፤ ጥለሽኝ ስትሄጂ ፤
ትዝ ብሎኝ ነበር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በረከት ታደሰ
የልጅነት ነገር ፤ ቴሜቴ ጨዋታ፤
ደረቴን ስትደቂ ፤ ደረትሽን ስመታ
የነገርሽኝ ነገር ፤
ትላንት ስትከጂኝ ፤ትዝ ብሎኝ ነበር፤
እቴ ሜቴ የሎሚ ሽታ፤
ያ ሰውዬ ምን አለሽ ማታ?
ብዬ ስጠይቅሽ ፤ በለጋ አንደበቴ
ምንም
ምንም
ምንም አላለም ፤
ብለሽ የመለስሽው ፤ ከሆድሽ አይደለም
ደግሞም አውቅሻለሁ ፤ ቅጥፈት ስታስቢ
እንዳንች ቀጣፊ የለም
ንገሪኝ በሞቴ ፤
ሳይቦዝዝ ቅላቴ፤
እቴ ሜቴ እያልኩሽ ፤ በተባ አንደበቴ
ያ ሰውዬ ምን አለሽ ማታ? ብዬ 'ምጠይቅሽ፤
እውነት አምሮኝ እንጂ ፤ ቀንቼ እንዳይመስልሽ
አየሽ...
በውሸት ሀገር ላይ ፤ እውነት የሚናገር
ውሸታም ይባላል ፤ በሀቀኞች ሰፈር
ውሸት ተደጋግሞ ፤ ከእውነት ሚስተካከል፤
ከእውነት 'ሚሳከር ፤
ረስተሽ ይሆን እንጂ ፤ የኛ ሀገር ነበር
እውነቱን ከውሸት ፤
ውሸቱን ከእውነት ፤ ስላደባለቅነው
ያንቺን የውሸት እውነት ፤
እንዴት አምንሻለው?
በውሸታም ሀገር እውነት ተናጋሪ
ውሸታም ይባላል
በውሸቶች ሀገር መሲህ ይሰቀላል
እቴ ሜቴ የሎሚ ሽታ፤
ያ ሰውዬ ምን አለሽ ማታ?
ምንም ምንም አላለኝ፤
ትዳርሽን ፈቶ ልውሰድሽ አለኝ
በጨዋታ መሀል ፤ ቅር አለኝ መሠለኝ
የልጅነት ነገር ፤ ቴሜቴ ጨዋታ
ደረቴን ስትደቂ ፤ ደረትሽን ስመታ
የነገርሽኝ ነገር ፤
እድሜ ተቀይሮ ፤ ጥለሽኝ ስትሄጂ ፤
ትዝ ብሎኝ ነበር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በረከት ታደሰ
🔥10❤9
#ይነጋል
ታድለሻል ቢሉም፣
የ13 ወር ፀሀይ፣ የ13 ወር ፀጋ
ብርሀንሽ ተሰርቆ፣
ሲጨላልም እንጂ፣ መች አየን ሲነጋ?
ተፈጥሮ ቸር ሆና፣
ሰማይዋ ባይነጥፍ፣ ምድሯ ቢለመልም፣
ከልጆቿ ልብ ውስጥ፣
ፍቅር ሲጎድል ነው፣ ሀገር የምትጨልም!፣
"አረ ነግቷል" ቢሉ የታለ የነጋው?
አዕላፋት ተቧድነው፣ በየጎጥ በመንጋው፣
ሰው ከነገ ይልቅ፣ ዛሬን እያሰጋው የታለ የነጋው?
ታሪኩን እንዳይፅፍ፣ ትውልድ እጁ ታስሮ፣
በትላንቱ ሾተል ዛሬው ተሸንቁሮ፣
ባልኖረው ተካሶ፣ ባልሰራው ተዋቅሶ፣
ለፀብ መዶለቻ፣ ያ'ያቱን ስም ጠቅሶ፣
ላለፈው ሲናከስ ለመጪው ሳይተጋ፣
በምን ስሌት ይሆን፣
ትዉልዷ ጨልሞ ሀገር የምትነጋ?
የህሊና መስታወት በጥበብ ሲፀዳ፣
ማስተዋል እንዳ'አደይ ፈክቶ ሲፈነዳ፣
መገፋፋት ሲቀር ፣መደጋገፍ ነግሶ
አንዱ ማገር ሲሆን፣ ሌላኛው ምሰሶ፣
የአብሮነትን ሸማ ትዉልዱ ሲሸምን፣
ያኔ ነው ሀገሬ መንጋቷን የማምን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በረከት በላይነህ
ታድለሻል ቢሉም፣
የ13 ወር ፀሀይ፣ የ13 ወር ፀጋ
ብርሀንሽ ተሰርቆ፣
ሲጨላልም እንጂ፣ መች አየን ሲነጋ?
ተፈጥሮ ቸር ሆና፣
ሰማይዋ ባይነጥፍ፣ ምድሯ ቢለመልም፣
ከልጆቿ ልብ ውስጥ፣
ፍቅር ሲጎድል ነው፣ ሀገር የምትጨልም!፣
"አረ ነግቷል" ቢሉ የታለ የነጋው?
አዕላፋት ተቧድነው፣ በየጎጥ በመንጋው፣
ሰው ከነገ ይልቅ፣ ዛሬን እያሰጋው የታለ የነጋው?
ታሪኩን እንዳይፅፍ፣ ትውልድ እጁ ታስሮ፣
በትላንቱ ሾተል ዛሬው ተሸንቁሮ፣
ባልኖረው ተካሶ፣ ባልሰራው ተዋቅሶ፣
ለፀብ መዶለቻ፣ ያ'ያቱን ስም ጠቅሶ፣
ላለፈው ሲናከስ ለመጪው ሳይተጋ፣
በምን ስሌት ይሆን፣
ትዉልዷ ጨልሞ ሀገር የምትነጋ?
የህሊና መስታወት በጥበብ ሲፀዳ፣
ማስተዋል እንዳ'አደይ ፈክቶ ሲፈነዳ፣
መገፋፋት ሲቀር ፣መደጋገፍ ነግሶ
አንዱ ማገር ሲሆን፣ ሌላኛው ምሰሶ፣
የአብሮነትን ሸማ ትዉልዱ ሲሸምን፣
ያኔ ነው ሀገሬ መንጋቷን የማምን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በረከት በላይነህ
❤19🥰3
"ጾም" የመጣ ግዜ
ልባችን ተሰብሮ ሆነን በትካዜ፤
እህል ሳንቀምስ
ማር ጣፋጭ ሳንልስ፤ ተግተን እንጾማለን
ቁርስ ምሳ ዘለን መክሰስ እንወዳለን፡፡
ፀሎታችን ሰምሮ ይደርስ ዘንድ እርሱ
ቁርስ ምሳ ዘለን ይቅርብን መክሰሱ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ ዘ ማሪያም
ልባችን ተሰብሮ ሆነን በትካዜ፤
እህል ሳንቀምስ
ማር ጣፋጭ ሳንልስ፤ ተግተን እንጾማለን
ቁርስ ምሳ ዘለን መክሰስ እንወዳለን፡፡
ፀሎታችን ሰምሮ ይደርስ ዘንድ እርሱ
ቁርስ ምሳ ዘለን ይቅርብን መክሰሱ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ ዘ ማሪያም
❤12
#እንዲህ_ይመስለኛል
ከእለታት አንድ ቀን ስም እየተሰጠ
ለፍጥረታት ሁሉ እየተመረጠ
አንድ ሰው መጥቶ መድረክ ላይ ቆመና
”አባት” ነህ ተባለ ምግባሩም ታየና
ከዛም ባለተራ አንዲት ሴት ብቅ አለች
”እህት” ነሽ ተብላ እሷም ተሰየመች
ደግሞ አንዱ ሲመጣ እሱም ደርሶት እጣ
”ወንድም” ነህ ብለውት ከመድረኩ ወጣ
”አክስት፣አጐት፣አያት” ሁሉም ጥሪ አገኙ
እንደ ምግባራቸው በስሞች ተቀኙ፤
በስተ መጨረሻ አንዲት ሴት ብቅ አለች
በመልካምነቷ ከኋላ የቀረች ፣
ስም አውጭውም ያኔ በጣም ተጨነቀ
ስሟን ምን እንደሚል ፍፁም አላወቀ፣
”ተናገር! ተናገር!” ብለው አጣደፉት
አንድ ስም ስለሷ መናገር አቅቶት
ጭንቀት ሲበዛበት አንዲት ቃል አምልጣ
”እ…” ሲል ተሰማች ከፀጥታው በልጣ፤
ስም ሳይገኝላት ይህ በእንዲህ እያለ
ስም ማውጫው ዳቦ አልቆ ትሪው ተሰቀለ፣
ከዛም ”ማን ናት?” ሲባል ያች መልካሟ ሴት
'' ’እ’ ናት ” ብለው አሉ ስም ሳይገኝላት
ስም አውጭውም ሰምቶ ዝም ስላላቸው
መስሏቸው ቀጠሉ የተቀበላቸው
እንጂማ ቢሞከር ምግባሯን ለመስፈር
ስንት ስም ተጠርቶ ምን ይበቃት ነበር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሰብለወንጌል ወርቁ
ከእለታት አንድ ቀን ስም እየተሰጠ
ለፍጥረታት ሁሉ እየተመረጠ
አንድ ሰው መጥቶ መድረክ ላይ ቆመና
”አባት” ነህ ተባለ ምግባሩም ታየና
ከዛም ባለተራ አንዲት ሴት ብቅ አለች
”እህት” ነሽ ተብላ እሷም ተሰየመች
ደግሞ አንዱ ሲመጣ እሱም ደርሶት እጣ
”ወንድም” ነህ ብለውት ከመድረኩ ወጣ
”አክስት፣አጐት፣አያት” ሁሉም ጥሪ አገኙ
እንደ ምግባራቸው በስሞች ተቀኙ፤
በስተ መጨረሻ አንዲት ሴት ብቅ አለች
በመልካምነቷ ከኋላ የቀረች ፣
ስም አውጭውም ያኔ በጣም ተጨነቀ
ስሟን ምን እንደሚል ፍፁም አላወቀ፣
”ተናገር! ተናገር!” ብለው አጣደፉት
አንድ ስም ስለሷ መናገር አቅቶት
ጭንቀት ሲበዛበት አንዲት ቃል አምልጣ
”እ…” ሲል ተሰማች ከፀጥታው በልጣ፤
ስም ሳይገኝላት ይህ በእንዲህ እያለ
ስም ማውጫው ዳቦ አልቆ ትሪው ተሰቀለ፣
ከዛም ”ማን ናት?” ሲባል ያች መልካሟ ሴት
'' ’እ’ ናት ” ብለው አሉ ስም ሳይገኝላት
ስም አውጭውም ሰምቶ ዝም ስላላቸው
መስሏቸው ቀጠሉ የተቀበላቸው
እንጂማ ቢሞከር ምግባሯን ለመስፈር
ስንት ስም ተጠርቶ ምን ይበቃት ነበር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሰብለወንጌል ወርቁ
❤19👍2🥰2
#ጠመንጃ_ወይ_ብዕር?
ሀሳብ ጉልበት ኖሮት ጠመንጃን ካልረታ
ብዕር እውቀት ወልዶ ትጥቅን ካላስፈታ
ምኑ ነው መሰልጠን? የቱ ነው ጀግንነት?
ሚዛኑ ልኬቱ የሰው ሰው ማንነት!!!
መነጋገር ሸሽቶ እውነትን ደብቆ
አንዱ ያንዱን ስራ አጣጥሎ ንቆ
መድረሻው ወዴት ነው? የስኬቱ ምስጢር?
ሀገርን ካልመራ እውቀትና ብዕር!!!
የቱ ነው መሰልጠን? የቱ ነው መደንቆር?
ጠመንጃ ወይ ብዕር? ሀገር የሚያሻግር?
ሀሳብ እየሸሹ ጉልበት መለካካት
ሀቁን እንጋፈጥ ይኼ ነው ቂልነት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ሀሳብ ጉልበት ኖሮት ጠመንጃን ካልረታ
ብዕር እውቀት ወልዶ ትጥቅን ካላስፈታ
ምኑ ነው መሰልጠን? የቱ ነው ጀግንነት?
ሚዛኑ ልኬቱ የሰው ሰው ማንነት!!!
መነጋገር ሸሽቶ እውነትን ደብቆ
አንዱ ያንዱን ስራ አጣጥሎ ንቆ
መድረሻው ወዴት ነው? የስኬቱ ምስጢር?
ሀገርን ካልመራ እውቀትና ብዕር!!!
የቱ ነው መሰልጠን? የቱ ነው መደንቆር?
ጠመንጃ ወይ ብዕር? ሀገር የሚያሻግር?
ሀሳብ እየሸሹ ጉልበት መለካካት
ሀቁን እንጋፈጥ ይኼ ነው ቂልነት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤5👍3🔥3
#አትፅናኝ
ሞትን አንመልሰዉ፣ እናውቃለን አይሸሽ
ስንት ጥፍራም ኀዘን አይተናል መሰለሽ!
ስንት ጥፍራም ኀዘን፣ እንደማቀይር አምነን
ስንት ጥፍራም ኀዘን፣ እንደማይቀር አምነሽ፤
ዳሩ ታውቂዋለሽ።
አቀጣጡ ክፋት፤
አመጣጡ ም‘ፃት፤
ግን ከሄደው ሁሉ፣ ከተመላለሰዉ
ምን ይባላል ይኼ፣ ባንቺ የደረሰዉ?!
ምን ይባላል ይኼ? አንቺስ ምን ልትባይ?
እኩይ ነዉ እታለም፣ ሽንገላ እንደ ሥራይ።
በእድፋም ጥፍሩ፣ ቧጦሽ ጥፍራም ኀዘን
መፅናናት መመኘት፣ ምንድነዉ መማፀን?
ምንድን ነዉ ዕንባ አባሽ?
ምንድን ነዉ ማገገም?
ዕንባሽን ማድረቂያ፣ አልሰጥሽም ማ‘ረም።
እሪ በይ!
ቢል በይ!
ኩርምት በይ–ዋኔ!
ላንቺ መፅናናትን፣ አልመኝም እኔ።
ወይኔ በይ!
ወዮ በይ!
ተይ አልልም ጭራሽ፤
አለመፅናናት ነዉ፣ አንቺን የሚያፅናናሽ!
የሚገርም አይነት ጽሑፍ፣ ለዛውም የግጥም ጽሑፍ ማንበብ እንዲህ ከፍ ያደርጋል ለካ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ መዘክር ግርማ
ሞትን አንመልሰዉ፣ እናውቃለን አይሸሽ
ስንት ጥፍራም ኀዘን አይተናል መሰለሽ!
ስንት ጥፍራም ኀዘን፣ እንደማቀይር አምነን
ስንት ጥፍራም ኀዘን፣ እንደማይቀር አምነሽ፤
ዳሩ ታውቂዋለሽ።
አቀጣጡ ክፋት፤
አመጣጡ ም‘ፃት፤
ግን ከሄደው ሁሉ፣ ከተመላለሰዉ
ምን ይባላል ይኼ፣ ባንቺ የደረሰዉ?!
ምን ይባላል ይኼ? አንቺስ ምን ልትባይ?
እኩይ ነዉ እታለም፣ ሽንገላ እንደ ሥራይ።
በእድፋም ጥፍሩ፣ ቧጦሽ ጥፍራም ኀዘን
መፅናናት መመኘት፣ ምንድነዉ መማፀን?
ምንድን ነዉ ዕንባ አባሽ?
ምንድን ነዉ ማገገም?
ዕንባሽን ማድረቂያ፣ አልሰጥሽም ማ‘ረም።
እሪ በይ!
ቢል በይ!
ኩርምት በይ–ዋኔ!
ላንቺ መፅናናትን፣ አልመኝም እኔ።
ወይኔ በይ!
ወዮ በይ!
ተይ አልልም ጭራሽ፤
አለመፅናናት ነዉ፣ አንቺን የሚያፅናናሽ!
የሚገርም አይነት ጽሑፍ፣ ለዛውም የግጥም ጽሑፍ ማንበብ እንዲህ ከፍ ያደርጋል ለካ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ መዘክር ግርማ
👏6🔥2❤1
#ታገስ_ተስፋ_አትቁረጥ
እኩል ተሰልፎ ከብርቱካን ማሳ
እንቧይ ከደረሰው እጣውን ሲያነሳ
ፈተናው ነውና የህይወት ጎዳና
ሌላ እጣ መሞከር መፋቅ እንደገና
እንቧይ በማግኘቱ ህይወትን ከመርገም
ነገን እያሰበ ተግቶ መደጋገም
ዛሬ በሞከረው ነገን ከማጨለም
ሌላ ሰልፍ ፈልጎ እድልን ማለምለም
ለወርቅ ተሰልፎ መዳብ የወሰደ
ተስፋውን ሰንቆ እየተራመደ
በትጋት ጎዳና ዘወትር የሚተጋ
አይቀርም ይወስዳል አለው የወርቅ ዋጋ
ግዜው ሊያስተምረው መዳብ እየሰጠ
የትግስቱን ውጤት በእንቁ እየለወጠ
የጥረቱን ፍሬ ያጭዳል አዝመራውን
ዛሬን በመታገስ ከሰራ ነገውን!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
እኩል ተሰልፎ ከብርቱካን ማሳ
እንቧይ ከደረሰው እጣውን ሲያነሳ
ፈተናው ነውና የህይወት ጎዳና
ሌላ እጣ መሞከር መፋቅ እንደገና
እንቧይ በማግኘቱ ህይወትን ከመርገም
ነገን እያሰበ ተግቶ መደጋገም
ዛሬ በሞከረው ነገን ከማጨለም
ሌላ ሰልፍ ፈልጎ እድልን ማለምለም
ለወርቅ ተሰልፎ መዳብ የወሰደ
ተስፋውን ሰንቆ እየተራመደ
በትጋት ጎዳና ዘወትር የሚተጋ
አይቀርም ይወስዳል አለው የወርቅ ዋጋ
ግዜው ሊያስተምረው መዳብ እየሰጠ
የትግስቱን ውጤት በእንቁ እየለወጠ
የጥረቱን ፍሬ ያጭዳል አዝመራውን
ዛሬን በመታገስ ከሰራ ነገውን!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤9🔥1
"ከጎራው ዘልቄ ፣ እስኪ ልነጋገር
ያለሰው ቢወዱት ምን ያደርጋል አገር
ሕንጻ መች ሆነና ፣ የድንጋይ ክምር
የእኔ ውብ ከተማ
መንገድ መች ሆነና ፣ የድንጋይ አጥር
የእኔ ውብ ከተማ ፣ የእኔ ውብ አገር
የሰው ልጅ ልብ ነው
የሌለው ዳርቻ ፣ የሌለው ድንበር
ሕንጻው ምን ቢረዝም ፣ ምን ቢጸዳ ቤቱ
መንገዱ ቢሰፋ ፣ ቢንጣለል አስፋልቱ
ሰው ሰው ካልሸተተ ፣ ምንድን ነው ውበቱ ?"
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በዓሉ ግርማ
ያለሰው ቢወዱት ምን ያደርጋል አገር
ሕንጻ መች ሆነና ፣ የድንጋይ ክምር
የእኔ ውብ ከተማ
መንገድ መች ሆነና ፣ የድንጋይ አጥር
የእኔ ውብ ከተማ ፣ የእኔ ውብ አገር
የሰው ልጅ ልብ ነው
የሌለው ዳርቻ ፣ የሌለው ድንበር
ሕንጻው ምን ቢረዝም ፣ ምን ቢጸዳ ቤቱ
መንገዱ ቢሰፋ ፣ ቢንጣለል አስፋልቱ
ሰው ሰው ካልሸተተ ፣ ምንድን ነው ውበቱ ?"
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በዓሉ ግርማ
❤5👏2