#በልኬ_ብቀደድ
ገና ያኔ ሳውቅሽ
በቀላል ላሰምጥሽ
እናቴ አሜሪካ
አባቴም ጀማይካ
እኔም ለመዝናናት ልቤ ደስ እንዲለው
በሳምንት በሳምንት ዱባይ እሄዳለው
ብዬ የነገርኩሽ
እሱንን ሰርዢው
ውስጥሽ እንዳትይዢው
ስልክ ስትደውይ
ሄሎ የኔ ፍቅር ጋራጅ ነው ያለሁት
መኪናዬን አሞት ቁሜ 'ያሰራሁት
እና አትመጣም አሁን ብለሽ ስትጠይቂኝ
ባላሰብኩት መንገድ ስታጨናንቂኝ
እ... እመጣልሽ ነበር አላለቀም እንጂ
ትንሽ እንዳላረፍድ በታክሲ አርገሽ ሂጂ
ብዬ የነገርኩሽ
እሱንን ሰርዢው
ውስጥሽ እንዳትይዢው
ደግሞ በሌላ ቀን እስኪ ጋብዘኝ ስትይ
ባክሽ ዛሬ ብታይ የኔ ቀኔ አይደለም
ገንዘብ ስለጨረስኩ ኪሴ ምንም የለም
ባንክ ሄጀ እያለ ለመያዝ ወረፋ
ያጋጣሚ ነገር ኤቲኤሜ ጠፋ
እና በዚ ምክንያት ማታ ላይ አልጠጣም
የብላክ ሌብል ብር የትም አላመጣም
ብዬ የነገርኩሽ
እሱንን ሰርዢው
ውስጥሽ እንዳትይዢው
እውነታው ይሄ ነው
በነገርኩሽ ምኞት ደስ እንኳ ብሰኝም
አይደለም መኪና ኤቲኤም የለኝም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ነጋሲ ግደይ
ገና ያኔ ሳውቅሽ
በቀላል ላሰምጥሽ
እናቴ አሜሪካ
አባቴም ጀማይካ
እኔም ለመዝናናት ልቤ ደስ እንዲለው
በሳምንት በሳምንት ዱባይ እሄዳለው
ብዬ የነገርኩሽ
እሱንን ሰርዢው
ውስጥሽ እንዳትይዢው
ስልክ ስትደውይ
ሄሎ የኔ ፍቅር ጋራጅ ነው ያለሁት
መኪናዬን አሞት ቁሜ 'ያሰራሁት
እና አትመጣም አሁን ብለሽ ስትጠይቂኝ
ባላሰብኩት መንገድ ስታጨናንቂኝ
እ... እመጣልሽ ነበር አላለቀም እንጂ
ትንሽ እንዳላረፍድ በታክሲ አርገሽ ሂጂ
ብዬ የነገርኩሽ
እሱንን ሰርዢው
ውስጥሽ እንዳትይዢው
ደግሞ በሌላ ቀን እስኪ ጋብዘኝ ስትይ
ባክሽ ዛሬ ብታይ የኔ ቀኔ አይደለም
ገንዘብ ስለጨረስኩ ኪሴ ምንም የለም
ባንክ ሄጀ እያለ ለመያዝ ወረፋ
ያጋጣሚ ነገር ኤቲኤሜ ጠፋ
እና በዚ ምክንያት ማታ ላይ አልጠጣም
የብላክ ሌብል ብር የትም አላመጣም
ብዬ የነገርኩሽ
እሱንን ሰርዢው
ውስጥሽ እንዳትይዢው
እውነታው ይሄ ነው
በነገርኩሽ ምኞት ደስ እንኳ ብሰኝም
አይደለም መኪና ኤቲኤም የለኝም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ነጋሲ ግደይ
👏16😁12❤7😱2🤣2⚡1
#ሀገሬ_አበድሪኝ?!
በአበል በስብሰባው ባክኖ ከሚጠፋው፣
በጉቦ ሻይ ቡና ተዘርፎ ከሚያለቀው፣
ሀገሬ አበድሪኝ? ሰርቼ ልክፈልሽ?
ከሚባክን ሀብትሽ ጥቂት ልለምንሽ!?
በጥበብ ህልሜ ላይ ስምሽን ልጠራ፣
ገብቻለሁ እና የቃል ውል አደራ፣
እውን ላደርግበት መክሊቴን ሰብስቤ፣
ከባካኝ ሀብትሽ ላይ ትንሽ ስጭኝ ዱቤ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
በአበል በስብሰባው ባክኖ ከሚጠፋው፣
በጉቦ ሻይ ቡና ተዘርፎ ከሚያለቀው፣
ሀገሬ አበድሪኝ? ሰርቼ ልክፈልሽ?
ከሚባክን ሀብትሽ ጥቂት ልለምንሽ!?
በጥበብ ህልሜ ላይ ስምሽን ልጠራ፣
ገብቻለሁ እና የቃል ውል አደራ፣
እውን ላደርግበት መክሊቴን ሰብስቤ፣
ከባካኝ ሀብትሽ ላይ ትንሽ ስጭኝ ዱቤ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤20🔥5🥰4😁1
#የተከፈተ_በር
የቤታችን በሩ ፤
ከፍተሽው እንደሄድሽ ፤ዛሬም አልተዘጋም
የነበረኝ የለም፤ ለቀማኛ አልሰጋም
እምቢ ካልሽ እምቢ ነው ፤ፅኑ ነው ያንች ቃል
እንደማትመለሽ ፤አእምሮየ ያውቃል
ግን አልፈርድበትም፤ልቤ ቢያመነታ
ምኞት በሞላው ቤት ፤እውቀት የለው ቦታ
ተስፋ አይቆርጥም ደሞ፤
ልቤ ህልሙን ያምናል
ይለኛል ደጋግሞ፤
“ትመለስ ይሆናል
ትመለስ ይሆናል
ትመለስ ይሆናል፤”
እኔም በምላሹ ፤ ልቤን ፊት ሳልሰጠው
እንዲህ እለዋለሁ፤ ተስፋ ላስቆርጠው
“ጠጠር ላይቀቀል፤ አልማዝ ላይከለስ
በደመና ራስጌ፤ ጎጆ ላይቀለስ
እኔም አልሻሻል፤ እሱዋም አትመለስ፤
ሰማይ ሰም ይመስል፤ ቢንጠባጠብ ቀልጦ
የረር ፈልሶ ቢሸሽ፤ ቢከተል እንጦጦ
ባህሮች ቢከስሙ፤ ምድር ብትናወጥ
እሱዋም አትመለስ ፤እኔም አልለወጥ”
በዙርያየ ያለው ፀጋ ብዙ ነበር፤
ግና ክንፍ አብቅሎ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ሲበር
ከኔ ጋር የቀረው
የተቆለፈ ልብ፤ የተከፈተ በር፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
የቤታችን በሩ ፤
ከፍተሽው እንደሄድሽ ፤ዛሬም አልተዘጋም
የነበረኝ የለም፤ ለቀማኛ አልሰጋም
እምቢ ካልሽ እምቢ ነው ፤ፅኑ ነው ያንች ቃል
እንደማትመለሽ ፤አእምሮየ ያውቃል
ግን አልፈርድበትም፤ልቤ ቢያመነታ
ምኞት በሞላው ቤት ፤እውቀት የለው ቦታ
ተስፋ አይቆርጥም ደሞ፤
ልቤ ህልሙን ያምናል
ይለኛል ደጋግሞ፤
“ትመለስ ይሆናል
ትመለስ ይሆናል
ትመለስ ይሆናል፤”
እኔም በምላሹ ፤ ልቤን ፊት ሳልሰጠው
እንዲህ እለዋለሁ፤ ተስፋ ላስቆርጠው
“ጠጠር ላይቀቀል፤ አልማዝ ላይከለስ
በደመና ራስጌ፤ ጎጆ ላይቀለስ
እኔም አልሻሻል፤ እሱዋም አትመለስ፤
ሰማይ ሰም ይመስል፤ ቢንጠባጠብ ቀልጦ
የረር ፈልሶ ቢሸሽ፤ ቢከተል እንጦጦ
ባህሮች ቢከስሙ፤ ምድር ብትናወጥ
እሱዋም አትመለስ ፤እኔም አልለወጥ”
በዙርያየ ያለው ፀጋ ብዙ ነበር፤
ግና ክንፍ አብቅሎ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ሲበር
ከኔ ጋር የቀረው
የተቆለፈ ልብ፤ የተከፈተ በር፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤15🔥3🥰1
#እየሔዱ_መጠበቅ!
‹‹እየሄድክ ጠብቀኝ›› - ስትይኝ ሄጃለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ….
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
እናምልሽ ውዴ…
አክሱምን እንዳየሽ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ጠራቢው እኔ ነኝ!
ያለፍኩት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ሰማይ ጠቀስ ሐውልት - የተፈለፈለ፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
አክሱም ሐውልት ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ጥበብ አለ!!
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
እናምልሽ ውዴ - ላሊበላን አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ፈልፋዩ እኔ ነኝ፤…
ያለፍሁት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ህንፃ ቤተ-መቅደስ ፤ የተፈለፈለ፡፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
በላሊበላ ውስጥ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ፅናት አለ፡፡
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
እናምልሽ ውዴ - ትክል ድንጋይ አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
የኔው መቃብር ነው!
ውድቀቴም እዛው ነው! ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ባባራ ዘመኑ፤
የራሱን መቃብር - ለመትከል የቻለ፤
መኖር የሚመስል - መሞትም ያይደለ፤
በጢያ ድንጋይ ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ውድቀት አለ፡፡
ከውድቀቴ ኋላ - ባይንሽ የምታዪው፤
ታምር የሚመስል - ታሪክ የምትይው፤
ምልክት የሚሆን - መንገድ ስላልተውኩኝ፤
ከመሞቴ በፊት..
ውድቀቴን፤
ሽንፈቴን፤
ከመቃብሬ ላይ - እንዲህ ብዬ ፃፍሁኝ፡፡
ሩጫዬን ጨረስኩ፤
ሰው ነኝ - ተሸነፍኩ!!!
እናምልሽ ውዴ….
‹‹እየሔድህ ጠብቀኝ›› - ያልሽው ቃል ስህተት
ነው፤
ቃሉም ገብቶሽ እንደው…
መራመድ መሄድ ነው፤
መሮጥም መሄድ ነው፤
መብረርም መሄድ ነው፤
አንቺ እንድትደርሺብኝ …
እኔ እየሞትሁ - እጠብቅሻለው!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በላይ በቀለ ወያ
‹‹እየሄድክ ጠብቀኝ›› - ስትይኝ ሄጃለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ….
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
እናምልሽ ውዴ…
አክሱምን እንዳየሽ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ጠራቢው እኔ ነኝ!
ያለፍኩት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ሰማይ ጠቀስ ሐውልት - የተፈለፈለ፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
አክሱም ሐውልት ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ጥበብ አለ!!
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
እናምልሽ ውዴ - ላሊበላን አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ፈልፋዩ እኔ ነኝ፤…
ያለፍሁት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ህንፃ ቤተ-መቅደስ ፤ የተፈለፈለ፡፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
በላሊበላ ውስጥ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ፅናት አለ፡፡
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
እናምልሽ ውዴ - ትክል ድንጋይ አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
የኔው መቃብር ነው!
ውድቀቴም እዛው ነው! ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ባባራ ዘመኑ፤
የራሱን መቃብር - ለመትከል የቻለ፤
መኖር የሚመስል - መሞትም ያይደለ፤
በጢያ ድንጋይ ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ውድቀት አለ፡፡
ከውድቀቴ ኋላ - ባይንሽ የምታዪው፤
ታምር የሚመስል - ታሪክ የምትይው፤
ምልክት የሚሆን - መንገድ ስላልተውኩኝ፤
ከመሞቴ በፊት..
ውድቀቴን፤
ሽንፈቴን፤
ከመቃብሬ ላይ - እንዲህ ብዬ ፃፍሁኝ፡፡
ሩጫዬን ጨረስኩ፤
ሰው ነኝ - ተሸነፍኩ!!!
እናምልሽ ውዴ….
‹‹እየሔድህ ጠብቀኝ›› - ያልሽው ቃል ስህተት
ነው፤
ቃሉም ገብቶሽ እንደው…
መራመድ መሄድ ነው፤
መሮጥም መሄድ ነው፤
መብረርም መሄድ ነው፤
አንቺ እንድትደርሺብኝ …
እኔ እየሞትሁ - እጠብቅሻለው!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በላይ በቀለ ወያ
❤20👏7🥰2💔2
#ጉልቻነት
ተናገሪ በዝቶ
ስሙኝ ባይ በርክቶ!
ትንሹ ትልቁ ፥ ተነስቶ እያዘዘን
በሽንፈታችን ክር፥
ፈታን ያልነው ገዢ ፥ መልሶ ገነዘን።
ንገሩት ያን ገዥ፥
ሀገር ያህል ምጣድ ፥ ያያዘ ጫንቃችን
ተስፋን ያህል ኪዳን ፥ ያሰረ ልባችን
ሲታሰር ሲፈታ ፥ ሲቆላ ሲታመስ
ሰቀቀን ገደለን፥
ምጣድ ከኛ ቀድሞ እንዳይደረመስ።
ትሰሚ እንደሁ ስሚ!
የይነጋል ሕብስት ፥ ቡኮው ኾመጠጠ
ሳትሰሚም
ሳይነጋም ተስፋችን አጠጠ።
ሀገር ምጣድ ሆና ፥
ሳት ላይ ስትጋደም ፥ ስለተስፋ እንጎቻ
አመድ እያቀፈው¡ ፥
ቋያ የሚገርፈው ፥ ህዝብ ነው ጉልቻ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዳግም ህይወት
ተናገሪ በዝቶ
ስሙኝ ባይ በርክቶ!
ትንሹ ትልቁ ፥ ተነስቶ እያዘዘን
በሽንፈታችን ክር፥
ፈታን ያልነው ገዢ ፥ መልሶ ገነዘን።
ንገሩት ያን ገዥ፥
ሀገር ያህል ምጣድ ፥ ያያዘ ጫንቃችን
ተስፋን ያህል ኪዳን ፥ ያሰረ ልባችን
ሲታሰር ሲፈታ ፥ ሲቆላ ሲታመስ
ሰቀቀን ገደለን፥
ምጣድ ከኛ ቀድሞ እንዳይደረመስ።
ትሰሚ እንደሁ ስሚ!
የይነጋል ሕብስት ፥ ቡኮው ኾመጠጠ
ሳትሰሚም
ሳይነጋም ተስፋችን አጠጠ።
ሀገር ምጣድ ሆና ፥
ሳት ላይ ስትጋደም ፥ ስለተስፋ እንጎቻ
አመድ እያቀፈው¡ ፥
ቋያ የሚገርፈው ፥ ህዝብ ነው ጉልቻ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዳግም ህይወት
❤7
#ሀሎ
እድሜ ለ ግራም-ቤል
ሀሎ ብሎ ማውጋት ...ለሰው ላስለመደ ፣
ሰላቢ ፈጠራው
ድምፅ ጭኖ ያልፋል.....እየሸመደደ ።
ካፍ የሚወጣው ቃል ..አንዱም ሳይዛነፍ ፣
ቅላፄ ልሳኑ...ዜማ ምቱ ሳይነጥፍ ፣
መልዕክተ ዲስኩሩም
በመማሰን ደክሞ ..ሆሄ ፣ ቃሉ ሳይረግፍ ፣
እንደ ተቀበለው...ቆጥሮ ያሻግራል ፣
ቀፎ ተለጉሞ
ከባህር ባሻገር ፥ ሰው ሰውን ያወራል ።
በዘመን ዘምኖ ...
አሁን አሁን ደሞ
ራሱ በራሱ ፥ ግራ እስኪጋባ ፣
ከሀሎ ተሻግሮ...
ብዙ መዘውሩ ...ባንድነት ሲገባ ፣
እንደአዳም መሻት...
መተግበሪያው በዝቶ ፥ ክውኑ ሲጋባ ፣
የሰው መወዳጃው....
ሆኖ ቢተለምም ፥ እርምጃው ላጠረ ፣
ሀሎ ብሎ ማሰስ...
ያሳብ ግንብ ፈጥሮ ፥ ስጋን እያጠረ ፣
የሩቅ መነፀሩ ፥
የቤተሰብ ልምዱን ፥
ተካቦ ማውጋቱን እንዳቀነጨረ ፣
አላየም....ፈልሳፊው
አዚም እንደሆነን....የሱ የጅ ቀፎ ፣
በስልክ የተጣደ
ከባእድ ያውካካል ....ከዘመድ ተኳርፎ ።
ሳምንቱን በሙሉ
ሰባቱንም ቀናት...ለሊቱን ጨምሮ ፣
ወሬ ይቃርማል
ስሜተ ህዋሱን ...በመሳ ቀስሮ ።
ለምን....? ብሎ ላለም......
በስመ ስልጠና ፥ ሽንገላ ይበጃል ፣
እንቢኝ ላለውም...
ያረጀ ያፈጀ
ወግ አጥባቂ ይሉት ፥ ሾርኒ ይቀዳጃል ፣
በብቻነቱ ዲን ፥ ብቻውን ይፈጃል ።
..... ይህን ማን ይወዳል ?
ማለፊያ... ነው ... ትልሙ ፣
ማዘኛም ... ነው ... አቅሙ ፣
በክፉ ቀን ሳይቀር ፥ የሰው ልጅ ድኩሙ ፣
ቤቱ ቢዘጋ እንኳ...
ከስልኩ ተተክሎ ...ግዜ አጣ ለደሙ ።
በይነ መረቡ ላይ ፥ ብዙ በመባተል ፣
ያሻውን ጎንጉኖ ፥
ያሻውን በመፍተል ፣
እንዲመቸው አርጎ...
ያሻውን አውርዶ ፥
ያሻውን ይሰቅላል ፣
ሲቀባበል ውሎ ፥ ሲቀባበል ያድራል ።
በዚህ ቀነ ቅኝት....
ኦንላየን ያየውን ፥ ሁሉንም ዘይሮ ፣
አዲስ እያወቀ ፥ አሮጌን አባሮ ፣
ለዋል ፈሰስ ሁሉ...
በሚባክን ግዜ ፥
ብዙ ደባል ይዞ.. ቧልቱ ይጠረቃል ፣
ይህኔ ሺ ለምዶ.. ከየሺው ይርቃል ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አብርሃም ተክሉ
እድሜ ለ ግራም-ቤል
ሀሎ ብሎ ማውጋት ...ለሰው ላስለመደ ፣
ሰላቢ ፈጠራው
ድምፅ ጭኖ ያልፋል.....እየሸመደደ ።
ካፍ የሚወጣው ቃል ..አንዱም ሳይዛነፍ ፣
ቅላፄ ልሳኑ...ዜማ ምቱ ሳይነጥፍ ፣
መልዕክተ ዲስኩሩም
በመማሰን ደክሞ ..ሆሄ ፣ ቃሉ ሳይረግፍ ፣
እንደ ተቀበለው...ቆጥሮ ያሻግራል ፣
ቀፎ ተለጉሞ
ከባህር ባሻገር ፥ ሰው ሰውን ያወራል ።
በዘመን ዘምኖ ...
አሁን አሁን ደሞ
ራሱ በራሱ ፥ ግራ እስኪጋባ ፣
ከሀሎ ተሻግሮ...
ብዙ መዘውሩ ...ባንድነት ሲገባ ፣
እንደአዳም መሻት...
መተግበሪያው በዝቶ ፥ ክውኑ ሲጋባ ፣
የሰው መወዳጃው....
ሆኖ ቢተለምም ፥ እርምጃው ላጠረ ፣
ሀሎ ብሎ ማሰስ...
ያሳብ ግንብ ፈጥሮ ፥ ስጋን እያጠረ ፣
የሩቅ መነፀሩ ፥
የቤተሰብ ልምዱን ፥
ተካቦ ማውጋቱን እንዳቀነጨረ ፣
አላየም....ፈልሳፊው
አዚም እንደሆነን....የሱ የጅ ቀፎ ፣
በስልክ የተጣደ
ከባእድ ያውካካል ....ከዘመድ ተኳርፎ ።
ሳምንቱን በሙሉ
ሰባቱንም ቀናት...ለሊቱን ጨምሮ ፣
ወሬ ይቃርማል
ስሜተ ህዋሱን ...በመሳ ቀስሮ ።
ለምን....? ብሎ ላለም......
በስመ ስልጠና ፥ ሽንገላ ይበጃል ፣
እንቢኝ ላለውም...
ያረጀ ያፈጀ
ወግ አጥባቂ ይሉት ፥ ሾርኒ ይቀዳጃል ፣
በብቻነቱ ዲን ፥ ብቻውን ይፈጃል ።
..... ይህን ማን ይወዳል ?
ማለፊያ... ነው ... ትልሙ ፣
ማዘኛም ... ነው ... አቅሙ ፣
በክፉ ቀን ሳይቀር ፥ የሰው ልጅ ድኩሙ ፣
ቤቱ ቢዘጋ እንኳ...
ከስልኩ ተተክሎ ...ግዜ አጣ ለደሙ ።
በይነ መረቡ ላይ ፥ ብዙ በመባተል ፣
ያሻውን ጎንጉኖ ፥
ያሻውን በመፍተል ፣
እንዲመቸው አርጎ...
ያሻውን አውርዶ ፥
ያሻውን ይሰቅላል ፣
ሲቀባበል ውሎ ፥ ሲቀባበል ያድራል ።
በዚህ ቀነ ቅኝት....
ኦንላየን ያየውን ፥ ሁሉንም ዘይሮ ፣
አዲስ እያወቀ ፥ አሮጌን አባሮ ፣
ለዋል ፈሰስ ሁሉ...
በሚባክን ግዜ ፥
ብዙ ደባል ይዞ.. ቧልቱ ይጠረቃል ፣
ይህኔ ሺ ለምዶ.. ከየሺው ይርቃል ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አብርሃም ተክሉ
❤6🔥1
#ብልኋ_እንቁራሪት
አንዲት እንቁራሪት በኩሬ ውስጥ ያለች
የሚቃጠል መንደር ፥ ከሩቁ እያየች
ትፀልይ ጀመረ ፥ እንደዚህ እያለች
እባክህ ጌታዬ ይህን እሳት አጥፋው
ባለበት እንዲቆም ግዛቱን አታስፋው
ብላ ለፈጣሪ ፥ አዝና ስትናገር
ለካስ ካጠገቧ እባብ ቆሞ ነበር
እሱም በመገረም ፥ በጸሎቷ ነገር
የሽሙጥ እያየ እንዲህ ይላት ጀመር
እንደው ምን ትገርሚ እንደምን ትደንቂ
እሳቱ እንዲጠፋ ፥ ጌታን 'ምጠይቂ
እሱ 'ሚነድ እዛ እሩቅ ነው ካንቺ ዘንድ
በምን ደርሶብሽ ነው ያንቺን ቤት የሚያነድ ?
ደሞም ከውሃ ውስጥ ቁጭ ብለሽ ያለሽው
የማይደርስብሽን ፥ እሳት የምትፈሪው
እያለ በሹፈት ፥ ከልቡ ሳቀባት
ወደታች በንቀት አዘቅዝቆ እያያት
ይህን ጊዜ እቁራሪት እየተገረመች
በእባብ ጅልነት በጣም እያዘነች
እንዲት ትለው ጀመር ቀና ብላ እያየች
አዎ ትክክል ነህ ፥ እሳቱ እሩቅ ነው
እኔም ያለሁበት ዙሪያውን ውሀ ነው
ነገር ግን አስተውል እጅግ አትሳት
ቃጠሎውን ቶሎ ወዲያው ካላቆሙት
ከ'ኔ ዘንድ መ'ተው ነው ውሀ የሚቀዱት
እናም ያላወከው እውነታው ይሄ ነው
ምንም'ኳ እዚህ ብቀመጥ ከውሃው
እዛ እሩቅ ቢሆን መንደሩ 'ሚነደደው
ካልጠፋ በጊዜ ፥ አምላክ ካላቆመው
የ' ኔም ቤት ነውና ተዝቆ የሚያልቀው
ስለዚህ ወዳጄ አያጥቃህ ጅልነት
ቃጠሎው ባይደርስም እኔ ካልሁበት
እዛ ነዶ ነዶ ፥ እጅግ ከባሰበት
ባልዲ ተሸክመው ሲመጡ ለመቅዳት
ይከቱኛል ወስደው ፥ ከሚነደው እሳት
ይህን አውቄ ነው ከሩቁ መፍራቴ
አጥፋው በሚል ፀሎት ምድር መደፋቴ
የአቅሜን ያህል እነሱን መርዳቴ
ብላ ስትናገር ፥ እባብን ገረመው
ማየት ያልቻለውን ገልጣ ስታሳየው
እናም እሩቅ ያለ ከ' እኛ የማይደርስ
የሌላ ነው ያልነው ፥ እሳቱ ሲለኮስ
ስለማይቀር እዚ ፥ መምጣቱ ቀስ በቀስ
ትልቅ እገዛ ነው
የሰው ችግር አይቶ ፥ ለኔ ብሎ ማልቀስ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሚካኤል እንዳለ
አንዲት እንቁራሪት በኩሬ ውስጥ ያለች
የሚቃጠል መንደር ፥ ከሩቁ እያየች
ትፀልይ ጀመረ ፥ እንደዚህ እያለች
እባክህ ጌታዬ ይህን እሳት አጥፋው
ባለበት እንዲቆም ግዛቱን አታስፋው
ብላ ለፈጣሪ ፥ አዝና ስትናገር
ለካስ ካጠገቧ እባብ ቆሞ ነበር
እሱም በመገረም ፥ በጸሎቷ ነገር
የሽሙጥ እያየ እንዲህ ይላት ጀመር
እንደው ምን ትገርሚ እንደምን ትደንቂ
እሳቱ እንዲጠፋ ፥ ጌታን 'ምጠይቂ
እሱ 'ሚነድ እዛ እሩቅ ነው ካንቺ ዘንድ
በምን ደርሶብሽ ነው ያንቺን ቤት የሚያነድ ?
ደሞም ከውሃ ውስጥ ቁጭ ብለሽ ያለሽው
የማይደርስብሽን ፥ እሳት የምትፈሪው
እያለ በሹፈት ፥ ከልቡ ሳቀባት
ወደታች በንቀት አዘቅዝቆ እያያት
ይህን ጊዜ እቁራሪት እየተገረመች
በእባብ ጅልነት በጣም እያዘነች
እንዲት ትለው ጀመር ቀና ብላ እያየች
አዎ ትክክል ነህ ፥ እሳቱ እሩቅ ነው
እኔም ያለሁበት ዙሪያውን ውሀ ነው
ነገር ግን አስተውል እጅግ አትሳት
ቃጠሎውን ቶሎ ወዲያው ካላቆሙት
ከ'ኔ ዘንድ መ'ተው ነው ውሀ የሚቀዱት
እናም ያላወከው እውነታው ይሄ ነው
ምንም'ኳ እዚህ ብቀመጥ ከውሃው
እዛ እሩቅ ቢሆን መንደሩ 'ሚነደደው
ካልጠፋ በጊዜ ፥ አምላክ ካላቆመው
የ' ኔም ቤት ነውና ተዝቆ የሚያልቀው
ስለዚህ ወዳጄ አያጥቃህ ጅልነት
ቃጠሎው ባይደርስም እኔ ካልሁበት
እዛ ነዶ ነዶ ፥ እጅግ ከባሰበት
ባልዲ ተሸክመው ሲመጡ ለመቅዳት
ይከቱኛል ወስደው ፥ ከሚነደው እሳት
ይህን አውቄ ነው ከሩቁ መፍራቴ
አጥፋው በሚል ፀሎት ምድር መደፋቴ
የአቅሜን ያህል እነሱን መርዳቴ
ብላ ስትናገር ፥ እባብን ገረመው
ማየት ያልቻለውን ገልጣ ስታሳየው
እናም እሩቅ ያለ ከ' እኛ የማይደርስ
የሌላ ነው ያልነው ፥ እሳቱ ሲለኮስ
ስለማይቀር እዚ ፥ መምጣቱ ቀስ በቀስ
ትልቅ እገዛ ነው
የሰው ችግር አይቶ ፥ ለኔ ብሎ ማልቀስ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሚካኤል እንዳለ
❤21👏9🥰4
#ውርሰ_ውበት
ሞትሽን አልመኝም
አንቺ ከሞትሽ ግን...
በፈረሶች ፀጉር
ለሚዋቡ ሴቶች
ውርስ ተይላቸው
አብሮሽ አይቀበር
ውበት ይሁናቸው
ብዙ ኩል ቀላቅለው
አሳር ለሚበሉ
ስራ አቅልይላቸው
አይንሽን ይትከሉ
ለቁንጅና ድጋፍ
አፍንጫ ጆሯቸው
ለጌጥ ለሚበሱ
ያንቺን አውርሻቸው
ውብ ጌጥ ነው በራሱ
ሳቃቸው እንዲያምር
ተነቅሰው በመፋቅ
አሳር ለሚበሉት
ጥርስሽን ስጫቸው
ወስደው ያስተክሉት
ሁሉንም አካልሽን
ከአፈር መበስበስ
መቀበር አድኚ
ቆመሽ ብቻ አይደለም
ሞተሽ ውበት ሁኚ
ፀባይሽ ግን ውዴ...
እኔ ያልቻልኩትን
አፈሩ ከቻለው
አደራ አታውርሺ
ፀባይሽ ቢወረስ
ትርፉ መቃጠል ነው
ሞትሽን አልመኝም
አንቺ ከሞትሽ ግን...
ውበትን ለሚሹ
ሴቶች አውርሻቸው
እኔም ያንቺ አፍቃሪ
ውርስሽን ልካፈል
እነሱን ላግባቸው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ልዑል ሀይሌ
ሞትሽን አልመኝም
አንቺ ከሞትሽ ግን...
በፈረሶች ፀጉር
ለሚዋቡ ሴቶች
ውርስ ተይላቸው
አብሮሽ አይቀበር
ውበት ይሁናቸው
ብዙ ኩል ቀላቅለው
አሳር ለሚበሉ
ስራ አቅልይላቸው
አይንሽን ይትከሉ
ለቁንጅና ድጋፍ
አፍንጫ ጆሯቸው
ለጌጥ ለሚበሱ
ያንቺን አውርሻቸው
ውብ ጌጥ ነው በራሱ
ሳቃቸው እንዲያምር
ተነቅሰው በመፋቅ
አሳር ለሚበሉት
ጥርስሽን ስጫቸው
ወስደው ያስተክሉት
ሁሉንም አካልሽን
ከአፈር መበስበስ
መቀበር አድኚ
ቆመሽ ብቻ አይደለም
ሞተሽ ውበት ሁኚ
ፀባይሽ ግን ውዴ...
እኔ ያልቻልኩትን
አፈሩ ከቻለው
አደራ አታውርሺ
ፀባይሽ ቢወረስ
ትርፉ መቃጠል ነው
ሞትሽን አልመኝም
አንቺ ከሞትሽ ግን...
ውበትን ለሚሹ
ሴቶች አውርሻቸው
እኔም ያንቺ አፍቃሪ
ውርስሽን ልካፈል
እነሱን ላግባቸው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ልዑል ሀይሌ
❤18😁5👌1
#መኖር_ላንቺ_እንዴት_ነው?
ሂወትስ እንዴት ናት ንገሪኝ ግድ የለም፥
እንደምንስ ቻልሽው ሞልቶ መኖር በአለም
እንደምን አለፍሽው ችግር ገለመኔ የፈተናን ቀለም፤
እንጃ ብቻ እናቴ ካነሱት ይከብዳል
ኑሮ በባህሪው መፈተን ይወዳል
የወደዱት ጠልቶ ያመኑት ይከዳል
የመጣም ይሄዳል
በዚ ሁሉ መሀል
በታይታ አለም ኖረሽ እኔን ላሳደግሽኝ
ምንም አልፈልግም
እናቴ ክብርሽን መውደድሽን አውርሽኝ
ዘላለም ነው እድሜሽ ሁሌም ለማትረሽኝ
አለሁ ደርሻለው
ከዳዴም አልፌ በእግሮቼ ቆሜያለው
ማገናዘብ ችዬ ማሰብ ጀምሪያለው
ኑሪልኝ ሳላጣሽ እኖርልሻለው
ቀንሽ ሁኖ ሳየው ይህ ዕለት ደመቀ
ቃላትን ለመትፋት ስሜቴም መጠቀ
ፊደላት ደርድሮ ጎርፍ ሁኖ ፈለቀ
እናት ብሎ ሊፅፍ ብዕሬም ነጠቀ
መውደዱን ለመንገር
ከችኮላ ብዛት ስምሽን ተሳሳተ
ልክ እንደ ልማድሽ
ታርሚው ፈልጎ ባይኖቹ ቃተተ
ገፅሽን እያየ ብዙ ተገረመ ብዙ ተመሰጠ
ሀዘንሽን ደስታሽን ሁሉንም እያየ ከጎርፉ ሰመጠ
እንግዲ ምን ቀረው በስሜቱ ጎርፎ ጀልባውን ከረሳ
በእናት ውበት ቀዝፎ ዳግም ካልተነሳ
ስተቱን አርሞ ስምሽን ካላወሳ
ምን አረገ ሊባል ሂወት ለሰጠችው ከሂወቷ ቆርሳ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ሂወትስ እንዴት ናት ንገሪኝ ግድ የለም፥
እንደምንስ ቻልሽው ሞልቶ መኖር በአለም
እንደምን አለፍሽው ችግር ገለመኔ የፈተናን ቀለም፤
እንጃ ብቻ እናቴ ካነሱት ይከብዳል
ኑሮ በባህሪው መፈተን ይወዳል
የወደዱት ጠልቶ ያመኑት ይከዳል
የመጣም ይሄዳል
በዚ ሁሉ መሀል
በታይታ አለም ኖረሽ እኔን ላሳደግሽኝ
ምንም አልፈልግም
እናቴ ክብርሽን መውደድሽን አውርሽኝ
ዘላለም ነው እድሜሽ ሁሌም ለማትረሽኝ
አለሁ ደርሻለው
ከዳዴም አልፌ በእግሮቼ ቆሜያለው
ማገናዘብ ችዬ ማሰብ ጀምሪያለው
ኑሪልኝ ሳላጣሽ እኖርልሻለው
ቀንሽ ሁኖ ሳየው ይህ ዕለት ደመቀ
ቃላትን ለመትፋት ስሜቴም መጠቀ
ፊደላት ደርድሮ ጎርፍ ሁኖ ፈለቀ
እናት ብሎ ሊፅፍ ብዕሬም ነጠቀ
መውደዱን ለመንገር
ከችኮላ ብዛት ስምሽን ተሳሳተ
ልክ እንደ ልማድሽ
ታርሚው ፈልጎ ባይኖቹ ቃተተ
ገፅሽን እያየ ብዙ ተገረመ ብዙ ተመሰጠ
ሀዘንሽን ደስታሽን ሁሉንም እያየ ከጎርፉ ሰመጠ
እንግዲ ምን ቀረው በስሜቱ ጎርፎ ጀልባውን ከረሳ
በእናት ውበት ቀዝፎ ዳግም ካልተነሳ
ስተቱን አርሞ ስምሽን ካላወሳ
ምን አረገ ሊባል ሂወት ለሰጠችው ከሂወቷ ቆርሳ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👏5❤3🥰1
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው ለኢድ አል አድሃ [አረፋ] በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤5👍2
#ተስፋሽን_ፈራሁት
የደጅሽ አበባ፣ እምቡጥ ሲይዝልሽ፤
የአንቀልባሽ ህጻን፣ ጠብቶ ሲያገሳልሽ፤
ደስታሽን አይቼ፤
ተስፋሽን ቃኝቼ፤
................ .....ነገሽን ፈራሁት
እምቡጥ የሚያመክን፣ አመዳይ ትላትል፣ ተምች በሞላበት፤
እምቡጥ የሚቀጥፍ፣ ሰው በሚኖርበት፤
.........በእኔና አንቺ አለም፤
ማንቦጥ መታጨት ነው፣
መውለድ መከተብ ነው፣
.........የዘላለም ሀዘን፣ የዘላለም ህመም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ
የደጅሽ አበባ፣ እምቡጥ ሲይዝልሽ፤
የአንቀልባሽ ህጻን፣ ጠብቶ ሲያገሳልሽ፤
ደስታሽን አይቼ፤
ተስፋሽን ቃኝቼ፤
................ .....ነገሽን ፈራሁት
እምቡጥ የሚያመክን፣ አመዳይ ትላትል፣ ተምች በሞላበት፤
እምቡጥ የሚቀጥፍ፣ ሰው በሚኖርበት፤
.........በእኔና አንቺ አለም፤
ማንቦጥ መታጨት ነው፣
መውለድ መከተብ ነው፣
.........የዘላለም ሀዘን፣ የዘላለም ህመም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ
🔥7❤2
#እድሜዬን_መልሽ!
ጠብቀኝ ባልሽኝ ልክ ቆሜ እየጠበኩሽ፣
ምነው ቃሌን በላሽ ከሌላ ተሞሸርሽ?
እንኳን ሰመረለሽ ማለቴ የውሸት፣
እድሜዬ አሳዘነኝ ላንቺ ያባከንኩት፣
እራሴን አልዋሽም መርቄ ለመዳር፣
ማስመሰል ነው ውዴ አልመርቅሽ ይቅር ፣
አፌ እየመረቀሽ ልቤ ከሚረግምሽ፣
ይቅርብሽ ወዳጄ አልምጣ ከሰርግሽ!
ደስ ይበልህ ለእኔ ስትል አላፈረች፣
የእኔን እድሜ በልታ ከሌላ ከረመች፣
ለፍቅር ዋጋ ክፈል እያለች ጠብቀኝ፣
አርክሳው ተገኘች እርሷው አፈረሰች፣
ክህደቷ ሳይበቃ እምነቴን መናዷ፣
ስርጓን እንድታደም ጠራችኝ በካርዷ፣
ይልቅ እዳ አለብሽ የባከነ ህልሜ፣
በምን ይገመታል የነጠቅሽኝ እድሜ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ጠብቀኝ ባልሽኝ ልክ ቆሜ እየጠበኩሽ፣
ምነው ቃሌን በላሽ ከሌላ ተሞሸርሽ?
እንኳን ሰመረለሽ ማለቴ የውሸት፣
እድሜዬ አሳዘነኝ ላንቺ ያባከንኩት፣
እራሴን አልዋሽም መርቄ ለመዳር፣
ማስመሰል ነው ውዴ አልመርቅሽ ይቅር ፣
አፌ እየመረቀሽ ልቤ ከሚረግምሽ፣
ይቅርብሽ ወዳጄ አልምጣ ከሰርግሽ!
ደስ ይበልህ ለእኔ ስትል አላፈረች፣
የእኔን እድሜ በልታ ከሌላ ከረመች፣
ለፍቅር ዋጋ ክፈል እያለች ጠብቀኝ፣
አርክሳው ተገኘች እርሷው አፈረሰች፣
ክህደቷ ሳይበቃ እምነቴን መናዷ፣
ስርጓን እንድታደም ጠራችኝ በካርዷ፣
ይልቅ እዳ አለብሽ የባከነ ህልሜ፣
በምን ይገመታል የነጠቅሽኝ እድሜ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤12👍5👏1
እ-ን--ለ-ያ--ይ
ፈርዖን ሲያሳድድሽ
ከጭንቅሽ ደርሼ-ከስቃይሽ መንደር፤
በተሰጠኝ በትር
ባሕሩን ከፍዬ-ላሻግርሽ ነበር፤
ግን በትሬን አይተሽ
ገራፊ አደረግሺኝ-በሕዝበ-አዳም መሐል፤
ለመፍረድ ማን ብሎት
ሕዝቡም አንቺን ትቶ-እኔ ላይ ይጮሃል፤
ከጩኸቱም አልፎ
አለንጋ እያነሳ-ሁሉም ሲያሳድደኝ፤
በትሬን ብልከው
ባሕር አልከፍል አለ-ውሃውም ወሰደኝ፤
አወይ ይሄ በትር
ያላንቺ ማይከፍል-ያላንቺ ማይሠራ፤
ከሞት አፋፍ ጥሎኝ
ሊያጣላኝ ደርሷል ከፈጣሪ ጋራ፤
ከፈርዖን የሸሸ
ያ እስራኤል ልብሽ-ዘመን የተሠጠ-ለግብፅ ባርነት፤
ምነው ላዳኝ ከፋ
በትር ለታደለ ለኔ ለሙሴ ዕ'ምነት፤
እንግዲያው በይ ሂጂ
ተመልሰሽ ጊቢ-ከፈርዖን ጉያ ስር፤
በትሬን ልመልስ
ተስማምቶሻልና የግብፃዊው እስር፤
እንግዲያው በይ ሂጂ
ባሕሩም ይንሳፈፍ
ሕልውናው ይሙላ-ከእንግዲ'ም አልከፍለው፤
ፈጣሪንም ሄጄ
ፈርዖኗን ማርላት-በባርነት መኖር-ደልቷታል ልበለው፤
ፍቅር የማያውቀው
ያልታደለ ልብሽ-የግዞት ባርነት ሕይወት የለመደ፤
መሻገር መች ያውቃል
በለበጣ መውደድ-ተንሳ'ፎ እየሄደ፤
እ-ን-ለ-ያ-ይ በቃ!
ሂጂ እኔም ልሂድ
ዳርሽን ያዢልኝ-እኔም ዳር ይዣለሁ፤
ዳግመኛ እንዳትመጪ
በመካከላችን ባሕር አበጃለሁ፤
በትሬም ላንቺ ልብ
ባሕሩን ለመክፈል ዳግም እንዳይነሳ፤
አርቄ እጥላለሁ
እስከ ዘለ-ዓለሜ አንቺን እንድረሳ፤
ፈጣሪም ዳግመኛ
እስራኤል ልብሽን ነፃ አውጣ ከሚለኝ፤
አልታዘዝክም ብሎ
ሺኅ ጊዜ ይጣለኝ ሺኅ ጊዜ ይግደለኝ፤
አ-ል-ፈ-ል-ግ-ም በቃ!
ዕምነት ተሸርሽሮ
ፍቅር ተንጠፍጥፎ-ተደፍቶ ካበቃ፤
ስለማይታፈስ
በሌላ የ'ምነት ቅል በንፁኅ ልብ ዕቃ፤
ተመለሺ ብዬ
በመርዛምነትሽ ዳግመኛ አልቆሽሽም፤
አርደሺኛልና
በምድርም በሠማይ ይቅር አልልሽም፤
ተወኝ ህሊና አሮን
ተወኝ አትመልሰኝ
አይተሃት የለም ወይ
የእግዜር ቃል ስትሽር ልቧ ሲያሳንሰኝ፤
በደነደነ ልብ
ፈርዖን አልሰማ ሲል ባርነቷን ለምዶ፤
ፈጣሪ ሲወዳት
በትር አውርሶናል ከሠማይ አውርዶ፤
ግን ይኸው አይተሃል
ከነፃነት ይልቅ ባርነት ሲጠማት፤
ፈርኦን ምን አጠፋ
የገዛ ፍቃዷ ባሕር ካሠጠማት፤
ተዋት አቦ!
ተዋት!
ተዋት ህሊና አሮን
ይልቅ እንለምነው በትሩን እንዲወስድ ፈጣሪ ኩሉ-ዓለም፤
ከሷ ሚሻው እምነት
ክህደት ሸርሽሮታል ካኖረበት የለም፤
ፈርዖን ሲያሳድድሽ
ከጭንቅሽ ደርሼ-ከስቃይሽ መንደር፤
በተሰጠኝ በትር
ወደፊት ሰንዝሬ-ባሕሩን ከፍዬ-ላሻግርሽ ነበር፤
ግን በትሬን አይተሽ
ገራፊ አደረግሺኝ-በሕዝበ-አዳም መሐል፤
ለመፍረድ ማን ብሎት
ሕዝቡም አንቺን ትቶ-እኔ ላይ ይጮሃል፤
ይጩህ ምናለበት
እኔ የታመምኩትን መች ደርሶ ታሞታል፤
በተዛነፈ ዓለም
ድሮም በቀና ልብ ቅጣት ይበረታል፤
ይጩህ አቦ!
ይጩህ!
ይጩህ ያ ህዝብማ
ጉሮሮ አድሎታል ልቦናው ተሠርቆ፤
ልብሽ ነው ሚገርመኝ
ፈርዖንን ሚማጠን የኔን በትር ንቆ፤
ይስመርልሽ ሂጂ!...
ጊዜሽን ጠብቂ አይደርስም መስሎሻል፤
ሌላ እስራኤል ልብ እንድታሻግሪ
በትር ይሰጥሻል፤
ያም ሌላ እስራኤል ልብ
እንዳንቺ ደንድኖ ፈርኦንን ሲማጠን፤
አስታውሺው ያን ጊዜ
የስብራቴን ልክ የሕመሜን መጠን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ልዑል ኃይሌ
ፈርዖን ሲያሳድድሽ
ከጭንቅሽ ደርሼ-ከስቃይሽ መንደር፤
በተሰጠኝ በትር
ባሕሩን ከፍዬ-ላሻግርሽ ነበር፤
ግን በትሬን አይተሽ
ገራፊ አደረግሺኝ-በሕዝበ-አዳም መሐል፤
ለመፍረድ ማን ብሎት
ሕዝቡም አንቺን ትቶ-እኔ ላይ ይጮሃል፤
ከጩኸቱም አልፎ
አለንጋ እያነሳ-ሁሉም ሲያሳድደኝ፤
በትሬን ብልከው
ባሕር አልከፍል አለ-ውሃውም ወሰደኝ፤
አወይ ይሄ በትር
ያላንቺ ማይከፍል-ያላንቺ ማይሠራ፤
ከሞት አፋፍ ጥሎኝ
ሊያጣላኝ ደርሷል ከፈጣሪ ጋራ፤
ከፈርዖን የሸሸ
ያ እስራኤል ልብሽ-ዘመን የተሠጠ-ለግብፅ ባርነት፤
ምነው ላዳኝ ከፋ
በትር ለታደለ ለኔ ለሙሴ ዕ'ምነት፤
እንግዲያው በይ ሂጂ
ተመልሰሽ ጊቢ-ከፈርዖን ጉያ ስር፤
በትሬን ልመልስ
ተስማምቶሻልና የግብፃዊው እስር፤
እንግዲያው በይ ሂጂ
ባሕሩም ይንሳፈፍ
ሕልውናው ይሙላ-ከእንግዲ'ም አልከፍለው፤
ፈጣሪንም ሄጄ
ፈርዖኗን ማርላት-በባርነት መኖር-ደልቷታል ልበለው፤
ፍቅር የማያውቀው
ያልታደለ ልብሽ-የግዞት ባርነት ሕይወት የለመደ፤
መሻገር መች ያውቃል
በለበጣ መውደድ-ተንሳ'ፎ እየሄደ፤
እ-ን-ለ-ያ-ይ በቃ!
ሂጂ እኔም ልሂድ
ዳርሽን ያዢልኝ-እኔም ዳር ይዣለሁ፤
ዳግመኛ እንዳትመጪ
በመካከላችን ባሕር አበጃለሁ፤
በትሬም ላንቺ ልብ
ባሕሩን ለመክፈል ዳግም እንዳይነሳ፤
አርቄ እጥላለሁ
እስከ ዘለ-ዓለሜ አንቺን እንድረሳ፤
ፈጣሪም ዳግመኛ
እስራኤል ልብሽን ነፃ አውጣ ከሚለኝ፤
አልታዘዝክም ብሎ
ሺኅ ጊዜ ይጣለኝ ሺኅ ጊዜ ይግደለኝ፤
አ-ል-ፈ-ል-ግ-ም በቃ!
ዕምነት ተሸርሽሮ
ፍቅር ተንጠፍጥፎ-ተደፍቶ ካበቃ፤
ስለማይታፈስ
በሌላ የ'ምነት ቅል በንፁኅ ልብ ዕቃ፤
ተመለሺ ብዬ
በመርዛምነትሽ ዳግመኛ አልቆሽሽም፤
አርደሺኛልና
በምድርም በሠማይ ይቅር አልልሽም፤
ተወኝ ህሊና አሮን
ተወኝ አትመልሰኝ
አይተሃት የለም ወይ
የእግዜር ቃል ስትሽር ልቧ ሲያሳንሰኝ፤
በደነደነ ልብ
ፈርዖን አልሰማ ሲል ባርነቷን ለምዶ፤
ፈጣሪ ሲወዳት
በትር አውርሶናል ከሠማይ አውርዶ፤
ግን ይኸው አይተሃል
ከነፃነት ይልቅ ባርነት ሲጠማት፤
ፈርኦን ምን አጠፋ
የገዛ ፍቃዷ ባሕር ካሠጠማት፤
ተዋት አቦ!
ተዋት!
ተዋት ህሊና አሮን
ይልቅ እንለምነው በትሩን እንዲወስድ ፈጣሪ ኩሉ-ዓለም፤
ከሷ ሚሻው እምነት
ክህደት ሸርሽሮታል ካኖረበት የለም፤
ፈርዖን ሲያሳድድሽ
ከጭንቅሽ ደርሼ-ከስቃይሽ መንደር፤
በተሰጠኝ በትር
ወደፊት ሰንዝሬ-ባሕሩን ከፍዬ-ላሻግርሽ ነበር፤
ግን በትሬን አይተሽ
ገራፊ አደረግሺኝ-በሕዝበ-አዳም መሐል፤
ለመፍረድ ማን ብሎት
ሕዝቡም አንቺን ትቶ-እኔ ላይ ይጮሃል፤
ይጩህ ምናለበት
እኔ የታመምኩትን መች ደርሶ ታሞታል፤
በተዛነፈ ዓለም
ድሮም በቀና ልብ ቅጣት ይበረታል፤
ይጩህ አቦ!
ይጩህ!
ይጩህ ያ ህዝብማ
ጉሮሮ አድሎታል ልቦናው ተሠርቆ፤
ልብሽ ነው ሚገርመኝ
ፈርዖንን ሚማጠን የኔን በትር ንቆ፤
ይስመርልሽ ሂጂ!...
ጊዜሽን ጠብቂ አይደርስም መስሎሻል፤
ሌላ እስራኤል ልብ እንድታሻግሪ
በትር ይሰጥሻል፤
ያም ሌላ እስራኤል ልብ
እንዳንቺ ደንድኖ ፈርኦንን ሲማጠን፤
አስታውሺው ያን ጊዜ
የስብራቴን ልክ የሕመሜን መጠን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ልዑል ኃይሌ
❤7👏4🔥2🕊1
#አለሁ_እንደ_ሾላው
በገዛ ጆሮና ፥ በገዛ አይኖችሽ ላይ
ሙሉ ስልጣን ያለሽ
ከቶ እንደምን አለሽ?
አለሁ እንደ ሾላው
እንደ ወፍ መነሻው
እንደ ወፍ መሸሻው
ጸሐይ እየሞቀ ከመተንፈስ በቀር፤ ሌላ እንደማይሻው፤
መኖር ብቻ ሲሆን ፥ የሰው ልጅ እቅዱ
በሲኦል ቢኖርም፥ አይቀርም መልመዱ
እኔም ከመበላት፥ መብላት ይሻል ብየ’
‘ፍሪደም ‘ ቢርቀኝ፥ ፍሪዳየን ጥዬ
ነጻነት ቢርበኝ፥ እየበላሁ እህል
አለሁ ይህን ያህል ፡ ፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
በገዛ ጆሮና ፥ በገዛ አይኖችሽ ላይ
ሙሉ ስልጣን ያለሽ
ከቶ እንደምን አለሽ?
አለሁ እንደ ሾላው
እንደ ወፍ መነሻው
እንደ ወፍ መሸሻው
ጸሐይ እየሞቀ ከመተንፈስ በቀር፤ ሌላ እንደማይሻው፤
መኖር ብቻ ሲሆን ፥ የሰው ልጅ እቅዱ
በሲኦል ቢኖርም፥ አይቀርም መልመዱ
እኔም ከመበላት፥ መብላት ይሻል ብየ’
‘ፍሪደም ‘ ቢርቀኝ፥ ፍሪዳየን ጥዬ
ነጻነት ቢርበኝ፥ እየበላሁ እህል
አለሁ ይህን ያህል ፡ ፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
👍6👏2