ግጥም
4.74K subscribers
23 photos
1 video
10 links
በዚህ ቻናል በጣም ምርጥ እና መንፈስን የሚያድሱ ግጥሞች ፣ ተከታታይ ታሪኮች ፣ የኦንላይን ቢዝነስ ቲፖች ይቀርቡበታል

መርጣችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን

Buy Ads https://telega.io/c/gitm_post

ADMIN 👉 @Big_jor
Download Telegram
#ድሃዉስ_አንተ_ነህ

መቼም ሠዉ ነኝ እና በፍቅርህ ብረታ፤
ከእለት ባንዱ ቀን አመሻሽ ላይ ማታ፤
ፍቅርህ በርትቶብኝ አበባ ታቅፌ ቆሜ ከበራፍህ ፤
እኔ አንተን መዉደዴን ማፍቀሬን ስነግርህ ፤
" ስምሽ ማነው አንቺ የኔ እህት ፤
ታወቂያለሽ አይደለ ደሀ እኮ አያፈቅርም"
ብለህ በማጣቴ ፍቅሬን አኩሠሀል ፤
አንተን በመዉደዴ ስቀህ ተሣልቀሀል፡፡

እርግጥ ነው እዉነት ለመመሥከር ፤
አንተ ባለ መኪና አባትህ ኢንቨስተር፤
እናትህ ነጋዴ ወንድምህ ማናጀር ፤
እህትህ ዝነኛ አለምን የምትዞር ፤

የሀብታችሁ ብዛት ገዝፏል ከተራራ ፤
አጎትህ አክስትህ ናቸዉ ዲያሥፖራ፡፡

ነገር ግን ወዳጄ ቅምጥሉ አበቤት ፤
አንተ እንደምትልኝ የሠዉ ድሃ ማለት፤
ያልሆነ ነጋዴ ያልሠራ ቪላ ቤት ፤
መኪና የሌለው መሪ ያልዘወረ ፤
ድያስፖራ ሆኖ ወንዝ ያልተሻገረ ፤

ድሀ ማለተ ላንተ እንዲያ ከመሠለህ ፤
እኔ አፍቃሪህ ሣልሆን ድሀዉስ አንተ ነህ፡፡

ይልቅስ
ደርሶ መኩራራትህን እርግፍ አርገዉ እና ፤
መወደዴን ተረድተህ ከልቤ ግባ እና ፤
ይልቅስ ላሣይህ ልብህም ይዝናና

ገንዘብ የማይገዛዉ ከገበያ ያልዋለ፤
ከሀብታም ተነጥቆ ለኛ የታደለ ፤
ሺ ፍቅር ሺ ጤና ከድሀ ቤት አለ ፡፡
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
23👍3🔥3👏3
#ላንቺ_ስል!

ፍቅሬ.............
እውነት እልሻለሁ እምልልሻለሁ
ከምነግርሽ በላይ እኔ እወድሻለሁ
..............ስለ ፍቅር ሲባል
የፈለገ ይምጣ ያልሆንኩት ልባል
ችግር ቢበዛብኝ
ነገር ቢከብድብኝ
ለፍቅርሽ ብገረፍ ክንዴ ቢደማብኝ
ተጎዳሁ አልልም ጎኔ ካለሽልኝ
ሃገር ላገር ስዞር የተንገላታሁት
ስቃይ አልለውም ላንቺ ስል የሆንኩት።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
        ነጋሲ ሃበሽ
👍109🥰5
#የቱ_ጋር_መሰለህ....

መባቻ ጅምርህ
የነፍስህ ድባቴ
ውድቀት እንግልትህ
ያኔ …
ባሽትሪ መያዣ ፣ በሲጋራ ብናኝ
በርጋፊ ቅጠል ፣ ድባቧ የሚቃኝ
በዛች ጠባብ ክፍል
ምጥን መሰብሰቢያ
ዙሪያህን ሰው ሞልቶህ
ቀንህን ማጣፊያ
ለአፕላይ ግብዣ የተዘረጋች ጣት
በሚግተለተል ጢስ ፣ ሰንቃልህ እሳት
እሷን ለመቀበል ስትፈግግ ባ’ክብሮት
የሰበብ አስባብ ጢስ
ቀረ ቤትህን ወርሶት።

የቱ ጋር መሰለህ?

በቀይ መብራት ፍካት
በቅልቅል ሽቶ አዲስ አይነት ክርፋት
በጭላጭ ብርጭቆ ተላኮበት ድራፍት
ከስፒከር ማህፀን ሙዚቃ ተለቆ
ጭፈራ እና ዳንሱ አንድ ላይ ተዛንቆ
የቀይ ሴትን ታፋ ዓይንህ በስስ ሰርቆ
በምራቅህ ድርቀት ጉሮሮህ ተጨንቆ
ጠቅሰህ ስትጠራት
ያቺን የሞት ብልቃጥ
ከባቷ ፈልቅቀህ ዕፅዋን ስትቀምሳት
በገላህ ፍሰሀ መቅደስህን ናድካት ።

የቱ ጋር መሰለህ?

የልጅነት ልምድህ
ከሰንበት ቤት ገዳም
ምልልስ ብርታትህ
በዋዛ ሲቀየር
የያሬዱ ወረብ
በእስክስታ ሲዛወር
ስትዘነጋ ፀሎት
ሳይንስ ከእምነት ልቆት
ኒቼ ቦታ ሲወርስ የየኔታን መንበር
የነፍስህ ቁዘማ መንደርደሪያ ነበር።

ትዝ አለህ?

ዘር መራጭ ስትሆን
የደም ሴል መንጣሪ
ጆሮህ ዳባ ሲለብስ
ለፍጥረት እንግልት
ለህፃናት ጥሪ…
መንገድህ ሲሳለጥ
በ V 8 መኪና
ዝርግ አስፓልት ሲመስልህ
ጉርብጥብጥ ጎዳና ፤
ስቆልኛል ስትል ጥርሱን የነከሰ
እንባው አንሸራሽሮህ ጌታ ዘንድ ደረሰ።

ያን ጊዜ ተከፋህ!

ጥሬ እየቆረጥክ ሆድህ ሲመረመር
እስቲም ሳውና ገብተህ ፊትህ ሲጭበረበር
በድሎትህ መኃል
ገላን የሚያኮስስ የእሾህ ስንጥር ነበር።

ትዝ አለህ?

መኝታህ በምቾት ተሞልቶ በአጀብ
እንቅልፍህ ሲናጠብ?

ትዝ አለህ?

በውድ ቀለም ቤቶች ልጆችህ ሲማሩ
ከግብረገብ ታዛ ተናንሰው ሲቀሩ?

ትዝ አለህ?

የጉያህ መልካም ሴት
የአጥንትህ ፍላጭ
‘አሁን ከምን ጊዜው
ሆነችብኝ ምላጭ? ‘
ብለህ ስትቆዝም … ?

እንዲያ ነው አይዋ…
ግፍ ፅዋው ሲሞላ
በትሩን አይመርጥም።

ትዝ አለህ?
ታወሰህ?
የቱ ጋር መሰለህ?
የተፈታው ውሉ
የጎደልክ ከሙሉ
‘ኧረ ስከን’ ሲሉ
ከዕድሜ የተማሩ
የጋሽ ውቤን ምክር
የእመት ጉሌን ዝክር
ረግጠህ ስትበር…
ስትሻገር ፣ ስጥስ
የምስኪናን ድንበር
የዛሬ ውድቀትህ ፣ በግጥም ሊነገር
ክንፍህ የተመታው ይሄን ጊዜ ነበር።
ትዝ አለህ?

አዎን እሱ ጋር ነው!
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
  ሚካኤል አስጨናቂ
16
#ደቃቃ_ጎልያዶች

ምን ከንቱ ቢመስል ፥ ነገር ሲጀማምር
ንቀህ አትጣለው ፥ በውል ሳትመረምር።
ድራጎን አይደለም ፥ ዳይኖሰር፣ አንበሳ
ቁጭ ብድግ አርጎ ፥ ያሳየን አበሳ።
ባክቴርያና ቫይረስ ፥ ባይን የማናያቸው
የሰው ልጅ ደመኞች ፥ ጥቃቅኖች ናቸው።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
   በርናባስ ከበደ
💯13👏73👍3
#በስካር_አይደለም

በየጎዳናው ላይ የሚንገዳገደው፣
እጅ እያወራጨ ለብቻ የሚያወራው፣
እንዴት አደርክ ሲሉት በቃ ዝም !የሚለው፣
በጨዋታ መሐል በሀሳብ የሚነጉደው፣
ለብቻው በማውራት መኪና የሚስተው፣
ጎዳናውን ሞልቶ የሚርመሰመሰው፣
በስካር አይደለም አቅሉን የነቀለ፣
በኑሮ ነው እንጂ ጉልበቱ የዛለ!
በስካርም መዝገብ ስሙ የሰፈረ፣
የከፋው ምስኪን ነው ሳይኖር ያኗኗረ!
ተፋፍሮ ነው እንጂ ያልከበደው የለም፣
በኑሮ ውድነት ሁሉም ነው ሰካራም፣
ስካር ከየት መጥቶ ? ተርፎ ከሚበላ?!!!
ኑሮ ነው አዙሪት ልቆ የተገኘው ከጠጅ ከጠላ!
የእኔ አይነቱ ምስኪን ለእብደት የቀረበው፣
ሰክሮ ነው አትበሉ ኑሮን ተግቶ ነው!!!
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
     ስንታየሁ ሀብታሙ
17👍3😭1
#ማን_ልበልሽ?

የቁንጅና ውበት፣አሟልቶ የሰጠሽ፤
በጥበብ አስጊጦ፣በፁቭ የተሰራሽ፤
ከራስ ፀጉርሽ፣እስከ እግር ጥፍሮችሽ፤
ጠቢባን በውበት፣የተራቀቁብሽ፤
ደራሲው በድርሰት፣ቃላትን አዋዶ፤
ሰዓሊው በብሩ ፣ቀለማት አዋህዶ፤
ገጣሚው በግጥሙ፣ በቃላት ተጠቦ፤
እንደ ጅረት ውሀ፣እውቀትን አዝንቦ፤
በሙዚቃ ዜማ፣ቢገልፅሽ አስውቦ፤
ሊገልፅሽ ቢሞክር፣በድርሰት ከትቦ፤
ሙሉነት ጎደለው፣አንችነትሽ በልጦ፤
በጥበባት ኮከብ፣በደማቅ ተጊጦ፤
ሞናሊዛየ ነሽ፣ዘመን ተሻጋሪ፤
የዳቬንች አርት፣ሁሌ ምታበሪ፤
እንቁ የእግዜር ስራ፣ምትታይ አብበሽ፤
ሚስጢሬ ሆንሽብኝ፣ስምሽን ማን ልበልሽ?
       @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢʰᵃʳᵉ
👏126👍3
#ስሞታ_አቀርባለው

በሚያላዝን ቀኔ ገጠመኝ አላውቅም
ለከበደኝ ለአይኔ ሽሙጥ አያምረኝም
ዳገቱን ብቆፍር ጥቅም አገኝ ብዬ
ከዘብጥያ ባድር እንደ ጥሬ እንሻፎ
ባልተማማልኩበት ትቢያ ስር ተጥዬ
ሽቅብ ስመለከት ህማሞቼን ጥዬ

ረግፎ ለታየው ለዚህ ስጋ ለባሽ
ጽዋውን ለቃኘው ለታዛቢው ቢጤ
እንክርዳዱን ቀማሽ…………………..

በደሌን ይቅር በል አስበኝ እያልኩኝ
የልብ ሀዘኔታ ብሶት እያስቃኘው
የክስመቴን ክፋይ ህሊና ቢቀልበው
ክፋት ሲከረፋ እምባ ጣሬን ላየው
ስሞታ አቀርባለው………………።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢʰᵃʳᵉ
       ✍️ ኢያሱ ከበደ
7👍2🔥2
#ኦና_ብዕር…!!
ህያበይ……💗
ስሜት ያጣ
አልቦ ታሬክ
ትርጉም የለሽ  ኦና ስንኝ
ቃል ሰድሬ
እንድቋጥር
ቀልቤን ገዝቶ ያሸፈተኝ

ፍች የራቀው
ትርጉም ያጣ የገረጣ
የተምታታ
ዝብርቅ ያለ ቅጡን ያጣ

ሰዋሰዉ የነተበ
ሽንቁርቁሩ
……በቃል መርፌ የተሰፋ
ሚስጥር ቅኔው
ትርጉም ፍቺው
………ህብረ ቃሉ የከረፋ

ለዛ የራቀው
ግራ የገባው ስንኩል ዜማ
ጣር ያዘለ
የህመም ቅኝት እንዳሰማ

ኩሩ ልቤን
ከመጀነን ከኩራቱ
ከከፍታው ከዘይኒቱ

ቁልቁል ስቦ
እመቀመቅ ወስዶ የጣለ
በአንቀልባው
እልፍ መውደድ ፍቅር ያዘለ

ጀምበር መሳይ
ጠይም ነፍሱ በበጎነት የተኳለ
አንድ አንቺ እንጂ
አንቺን መሰል ወዴት አለ?

ኧረ እንደውም …
ልክ እንደዚህ
ኦና ብዕር አልቦ ግጥም
ቃል ደርድሬ እንድገጥም
ፈጥኖ ደርሶ
ምስኪን ልቤን ቀድሞ ያነቃ
ከመውደድሽ የገዘፈ
ከየት ሊገኝ ብርቱ አለቃ?

ልክ እንደዚህ…
በአፍታ ስለቴ በውልብታ
ዝብርቅ ያለ የተምታታ
ቅኔ እንድቀኝ
ቶሎ ንቃ  ተነስ ያለ
ፍቅርሽ እንጂ
ሌላ ቀስቃሽ ወዴት አለ?
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢʰᵃʳᵉ
  ዳግም ሄራን
13
#ሀሁ

ፊደል ላስቆጥርሽ እጅሽን ደግፌ በምቾት ታቅፌ
ፊደል ላስቆጥርሽ ባንቺነትሽ ፍቅር በመውደድ ፈዝዤ ደንዝዤ
አቡጊዳ ልበል መቁጠሪያውን ይዤ
አይንሽን እያየው በፍቅርሽ ፈዝዤ
ባንቺነትሽ ግርማ እኔነቴን ትቼ
ፊደል ላስቆጥርሽ መቁጠሪያውን ይዤ
ከሀ ይጀምራል የሁሉም መነሻ
ምነው አንቺን ለኔ ባረገሽ መሸሻ
የመጀመሪያዬ የእስትንፋሴ ዋሻ
ባደረገሽ አንቺን ለኔ መነሻም መድረሻ
ያኔ የኔታ የፊደሉ ጌታ
ፊደል ሲያስቆጥሩን ቁጭ አርገው በተርታ
እንሰማቸው ነበር በዝምታ ቃታ
የድምጣቸው ቃና የፊደሉ ሞገስ
ማህሌት ሚመስል ቅዳሴ ሚሰለስ
ጥዑም ነው ዜማቸው እጅግ የሚማርክ
ለቅዳሴ ቤቱ ይፈለጋል በሰርክ
ማህሌት ሲሰማ ሰአታቱ ሲቀርብ
ይሰማን ነበረ ድምጣቸው ከርቀት
የሚገርመኝ ነገር በሀ አስመስዬ ያንቺን ስም መጥራቴ
በሁ አስመስዬ ስልሽ ነው ህይወቴ
ምን ተሰማሽ ታድያ ንገሪኝ በሞቴ
ልቤም ከጅሎሻል አንድ በይኝ እቴ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢʰᵃʳᵉ
14👏4🥰2
#ልብን_እየሰጡ!

ከቆሻሻ ጉድጓድ ዝንብ እያባረሩ፣
ማርን ይናፍቃል የጉድ ነው ሀገሩ፣
ልብ ለሌለው ሰው ልብን እየሰጡ፣
ፍቅር የለም ማለት ገላ እያጋለጡ፣
ጉልቻ ቢለወጥ ወጥን ላያሳምር፣
ከሺ ቢጋደሙ መች ይሆናል ፍቅር፣
ይቆሽሻል እንጅ ቤተ መቅደስ ገላ፣
እግር ስለ ዞረ መች የልብ ሊሞላ!!!
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
     ስንታየሁ ሀብታሙ
🔥13👏64❤‍🔥3👍2
#የፈጣሪ_ቅኔ

" አፈር ነበርክና ትሆናለህ አፈር "
እንዲል ቃለ-እግዚአብሔር
ጭቃ ቤት ውስጥ ሆኜ የማስበው ሁሉ
ከስንት ሰው አካል እንደተሰራ ነው
ግድግዳው በሙሉ፡፡

እግዜር ግን ሲገርም!!!

የተጠናወተው የሙስና አባዜ -
የሰው ባለ-ጊዜ
በእሳትና ሴራ
ፎቅ ቤቱን ሊሰራ
የድሆች ቤት ሲያፈርስ፣
ገበያ ሲያተራምስ፣
አንዳንዴም ሲያቃጥል
በሳት- እያጋየው፤
የነገው 'ራሱን በአሽሙር አሳየው፡፡
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢʰᵃʳᵉ
አማኑኤል አለሙ
16👍51
#ቢታሰር_ቀለበት

ጣትሽ ላይ ያሰርኩት ቀለበቱ ላልቶ
ጠፋብሽ ወይ ውዴ ቃልኪዳን ዘንግቶ
ለነገሩ ይጥፋ ድሮም አልጠበቀም
ልብ ካልታሰረ በጣት ፍቅር የለም
እሰርልኝ አልሽኝ አሰርኩ ተበድሬ
ጥለሽው ተመለሽ አበቃ ትዳሬ
ልብሽን ሸሽገሽ ጣትሽን ዘርግተሽ
በደለኝ አልሽ አሉ ቃልኪዳን አፍርሰሽ
እንዳይሆን እንዳይሆን በጥድፊያ ነገሩ
ልብ ሳይግባባ ጣት በጣት ማሰሩ
ከንቱ ድካም ብቻ ፍቅር አይመሰርት
አልማዝ ወርቅ መርጦ ቢታሰር ቀለበት።
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
     ስንታየሁ ሀብታሙ
14👍5🥰2
#አልወድሽም_እንጂ!

አልወድሽም እንጂ እኔ ከወደድኩሽ
ያዩሽም አይኖሩ ይቅርና የነኩሽ
አልወድሽም እንጂ ከወደድኩሽማ
አደባባይ ቆሜ ከመሃል ከተማ
በጂጉ በሚልቅ ከወፎቹ ዜማ
አዜምልሽ ነበር ህዝብ ሁሉ እንዲሰማ
ያው እንደነገርኩሽ
አልወድሽም እንጂ እኔ ከወደድኩሽ
ፅሀይ ትቆማለች ጨርቃም አትወጣም
ነፋሱም ፅጥ ይላል ብርዱም አይበረታም
ወንዞችም አይፈሱም ቆመው ይሰማሉ
የፍቅራቸው ነገር ዕፁብ ነው ዕያሉ
ከፍቅራችን በላይ እጅግ የሚገርመው
እኛ ስንጎዳ ህዝቡን ነው የሚያመው
አልወድሽም እንጂ
አልወድሽም እንጂ
እኔ ከወደድኩሽ
ያው እንደነገርኩሽ
አመት አንድ ቀን ነው በፊትሽ በፊቴ
ምድርም አንድ እርምጃ ላንቺ ና ኔ ኮቴ
እኔማ ስወድሽ
ሰማይ ትጠባለች በፍቅራችን ደስታ
እኛ ከፈለግን ቀን ይሆናል ማታ
እምልልሻለሁ "አልወድሽም እንጂ ከወደድኩሽ ብዬ"
ደስ አሰኝሻለሁ ሰጎንን ቀድሜ አንበሳን ታግዬ
እኔ ከወደድኩሽ
እየተራመድን ነፋስ እንቀድማለን
እየተናገርን ዓለት እንሰብራለን
ከደመና መሃል ደመና እንፈጥራለን
አትጠራጠሪ
አልወድሽም እንጂ የወደድኩሽ ዕለት
ብረት እና ሳት ነን አንቺ ና ኔ ማለት
እሳት ና ብረት ግጥም እና ዜማ
ንጉስ እና ንግስት እግር እና ጫማ
አንድ መሆን ታውቂያለሽ አንድ መልክ አንድ ቀለም
እኔ አንችን ስወድሽ የሚመስለን የለም
ግን....
እኔ ከማልኩልሽ በሚበልጥ መሃላ
ከምድራዊው ፍቅር ባይደለ በሌላ
የሚወዱሽ አሉ
እኔ ከወደድኩሽ ታዲያ እነዚህ ሰዎች ምንድን ይሆናሉ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
🔥10👏75
#እማ...

ምድር ሲሰለችሽ መሄድ ስትፈልጊ በቅቶሽ ስትጠሪ
ሰባቱንም ሰማይ ላውርድልሽና አንዱን መርጠሽ ኑሪ
አትጠራጠሪ ከእነርሱ በአንዱ ነዉ ሚኖረው ፈጣሪ  
ለአፍታ ዞር ብለሽ አንቺን ካጣውማ ድንገት ብትቀሪ
ይነጣጠላሉ ነፍስና ሥጋዬ ሆነዉ ለቀባሪ

እማ...

ለኔ እኮ ጠረንሽ የአንገትሽ ሥር ሽታ ከናርዶስ ይልቃል
በእስትንፋስሽ ብቻ ውስጤ በሐሴት ሞልቶ ዝንታለም ይኖራል
ላልነቃ ልተኛ እራሴን አሻሽተሽ ሽጉጥ አርጊኝና ከደረትሽ ወለል
ከዚህ አለም ክፋት ከዚህ አለም ተንኮል ከእምነትሽ ልጠለል
ጣቶችሽ በላዬ ሲንሸራሸሩማ ምድርን ለቅቄ ደርሼ ከራማ
የደስታ ጥግ ሥር ከምንጩ ጠጥቼ መንፈሴን አድሼ በሰማይ ከተማ
በእሳት ሠረገላ በዳመና መንገድ በመላዕክት ዜማ
ታጅቤ መጣለሁ እራሴን ሳስታውስ አንቺ ስትናፍቂኝ
ከጎኔ እያለሽ ከእቅፍሽ ውስጥ ሆኜ ያጣውሽ ሲመስለኝ

እማ...

ስጪኝ መቀነትሽን ወገብሽን ዞሮ ሀዘንና ደስታን የሚካፈልሽን
የደረሰብሽን በሆድሽ ያለውን ችለሽ የኖርሽውን
እሱ ይነግረኛል ያንቺን ጥንካሬ ለእኔ የሆንሽውን
ስንት ጊዜ ታመሽ ስንት ጊዜ እንደ ዳንኩ በፀሎት በምልጃሽ
ስንት ጊዜ ርቦሽ ስንት ጊዜ  ጠምቶሽ እኔን እያስቀደምሽ
እራስሽን ክደሽ በዚያ ፅኑ ፍቅርሽ ልጄን ልጄን እያልሽ

እናም እናትዬ

ምድር ሲሰለችሽ መሄድ ስትፈልጊ በቅቶሽ ስትጠሪ
ሰባቱንም ሰማይ ላውርድልሽና አንዱን መርጠሽ ኑሪ።
አትጠራጠሪ ከእነርሱ በአንዱ ነዉ ሚኖረው ፈጣሪ
ለአፍታ ዞር ብለሽ አንቺን ካጣውማ ድንገት ብትቀሪ
ይነጣጠላሉ ነፍስና ሥጋዬ ሆነዉ ለቀባሪ
አይበለውና
እንደው አይበለውና አምላክ መጥቶ ደጅሽ
ወይ መለዓኩን ልኮ የሞት ፅዋ አስይዞ ከእኔ ሊነጥልሽ ተረኛ ነሽ ቢልሽ
በእማ ቀልድ አላውቅም ከገዛ ዙፋኑ እኔው ተሰይሜ
እፋረደዋለው ከእግዜር ችሎት ቆሜ እስከቻለ አቅሜ
ሺ ሟች ሞልቶ በሀገር መንገደኛ ገስጋሽ እሷን ያየኽብኝ
ምን ኖሮኝ ልኖር ነዉ እሷኑ ሰጥተኸኝ መልሰህ ብትነጥቀኝ
እናም ልለምንህ ባለህ ሀይል ሁሉ አትጠቀምብኝ
እንዲህ ጠይቃለው ስለ እናትህ ስትል እናቴን ተውልኝ፡፡
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
    አማኑኤል ብርሃኑ

ሺህ ዓመት ኑሪልኝ እናቴ
መልካም የእናቶች ቀን ❤️
17😢5👍2
#በልኬ_ብቀደድ

ገና ያኔ ሳውቅሽ
በቀላል ላሰምጥሽ
እናቴ አሜሪካ
አባቴም ጀማይካ
እኔም ለመዝናናት ልቤ ደስ እንዲለው
በሳምንት በሳምንት ዱባይ እሄዳለው
ብዬ የነገርኩሽ
እሱንን ሰርዢው
ውስጥሽ እንዳትይዢው

ስልክ ስትደውይ
ሄሎ የኔ ፍቅር ጋራጅ ነው ያለሁት
መኪናዬን አሞት ቁሜ 'ያሰራሁት
እና አትመጣም አሁን ብለሽ ስትጠይቂኝ
ባላሰብኩት መንገድ ስታጨናንቂኝ
እ... እመጣልሽ ነበር አላለቀም እንጂ
ትንሽ እንዳላረፍድ በታክሲ አርገሽ ሂጂ
ብዬ የነገርኩሽ
እሱንን ሰርዢው
ውስጥሽ እንዳትይዢው

ደግሞ በሌላ ቀን እስኪ ጋብዘኝ ስትይ
ባክሽ ዛሬ ብታይ የኔ ቀኔ አይደለም
ገንዘብ ስለጨረስኩ ኪሴ ምንም የለም
ባንክ ሄጀ እያለ ለመያዝ ወረፋ
ያጋጣሚ ነገር ኤቲኤሜ ጠፋ
እና በዚ ምክንያት ማታ ላይ አልጠጣም
የብላክ ሌብል ብር የትም አላመጣም
ብዬ የነገርኩሽ
እሱንን ሰርዢው
ውስጥሽ እንዳትይዢው

እውነታው ይሄ ነው
በነገርኩሽ ምኞት ደስ እንኳ ብሰኝም
አይደለም መኪና ኤቲኤም የለኝም።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ነጋሲ ግደይ
👏16😁127😱2🤣21
#ሀገሬ_አበድሪኝ?!

በአበል በስብሰባው ባክኖ ከሚጠፋው፣
በጉቦ ሻይ ቡና ተዘርፎ ከሚያለቀው፣
ሀገሬ አበድሪኝ? ሰርቼ ልክፈልሽ?
ከሚባክን ሀብትሽ ጥቂት ልለምንሽ!?
በጥበብ ህልሜ ላይ ስምሽን ልጠራ፣
ገብቻለሁ እና የቃል ውል አደራ፣
እውን ላደርግበት መክሊቴን ሰብስቤ፣
ከባካኝ ሀብትሽ ላይ ትንሽ ስጭኝ ዱቤ!
         @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
     ስንታየሁ ሀብታሙ
20🔥5🥰4😁1
#የተከፈተ_በር

የቤታችን በሩ ፤
ከፍተሽው እንደሄድሽ ፤ዛሬም አልተዘጋም
የነበረኝ የለም፤ ለቀማኛ አልሰጋም
እምቢ ካልሽ እምቢ ነው ፤ፅኑ ነው ያንች ቃል
እንደማትመለሽ ፤አእምሮየ ያውቃል
ግን አልፈርድበትም፤ልቤ ቢያመነታ
ምኞት በሞላው ቤት ፤እውቀት የለው ቦታ
ተስፋ አይቆርጥም ደሞ፤
ልቤ ህልሙን ያምናል
ይለኛል ደጋግሞ፤
“ትመለስ ይሆናል
ትመለስ ይሆናል
ትመለስ ይሆናል፤”
እኔም በምላሹ ፤ ልቤን ፊት ሳልሰጠው
እንዲህ እለዋለሁ፤ ተስፋ ላስቆርጠው
“ጠጠር ላይቀቀል፤ አልማዝ ላይከለስ
በደመና ራስጌ፤ ጎጆ ላይቀለስ
እኔም አልሻሻል፤ እሱዋም አትመለስ፤
ሰማይ ሰም ይመስል፤ ቢንጠባጠብ ቀልጦ
የረር ፈልሶ ቢሸሽ፤ ቢከተል እንጦጦ
ባህሮች ቢከስሙ፤ ምድር ብትናወጥ
እሱዋም አትመለስ ፤እኔም አልለወጥ”
በዙርያየ ያለው ፀጋ ብዙ ነበር፤
ግና ክንፍ አብቅሎ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ሲበር
ከኔ ጋር የቀረው
የተቆለፈ ልብ፤ የተከፈተ በር፡፡
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
በእውቀቱ ስዩም
15🔥3🥰1
#እየሔዱ_መጠበቅ!

‹‹እየሄድክ ጠብቀኝ›› - ስትይኝ ሄጃለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ….
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡

እናምልሽ ውዴ…
አክሱምን እንዳየሽ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ጠራቢው እኔ ነኝ!
ያለፍኩት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ሰማይ ጠቀስ ሐውልት - የተፈለፈለ፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
አክሱም ሐውልት ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ጥበብ አለ!!
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡

እናምልሽ ውዴ - ላሊበላን አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ፈልፋዩ እኔ ነኝ፤…
ያለፍሁት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ህንፃ ቤተ-መቅደስ ፤ የተፈለፈለ፡፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
በላሊበላ ውስጥ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ፅናት አለ፡፡
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡

እናምልሽ ውዴ - ትክል ድንጋይ አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
የኔው መቃብር ነው!
ውድቀቴም እዛው ነው! ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ባባራ ዘመኑ፤
የራሱን መቃብር - ለመትከል የቻለ፤
መኖር የሚመስል - መሞትም ያይደለ፤
በጢያ ድንጋይ ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ውድቀት አለ፡፡
ከውድቀቴ ኋላ - ባይንሽ የምታዪው፤
ታምር የሚመስል - ታሪክ የምትይው፤
ምልክት የሚሆን - መንገድ ስላልተውኩኝ፤
ከመሞቴ በፊት..
ውድቀቴን፤
ሽንፈቴን፤
ከመቃብሬ ላይ - እንዲህ ብዬ ፃፍሁኝ፡፡
ሩጫዬን ጨረስኩ፤
ሰው ነኝ - ተሸነፍኩ!!!
እናምልሽ ውዴ….
‹‹እየሔድህ ጠብቀኝ›› - ያልሽው ቃል ስህተት
ነው፤
ቃሉም ገብቶሽ እንደው…
መራመድ መሄድ ነው፤
መሮጥም መሄድ ነው፤
መብረርም መሄድ ነው፤
አንቺ እንድትደርሺብኝ …
እኔ እየሞትሁ - እጠብቅሻለው!!!
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
    በላይ በቀለ ወያ
20👏7🥰2💔2
#ጉልቻነት

ተናገሪ በዝቶ
ስሙኝ ባይ በርክቶ!
ትንሹ ትልቁ ፥ ተነስቶ እያዘዘን
በሽንፈታችን ክር፥
ፈታን ያልነው ገዢ ፥ መልሶ ገነዘን።
ንገሩት ያን ገዥ፥
ሀገር ያህል ምጣድ ፥ ያያዘ ጫንቃችን
ተስፋን ያህል ኪዳን ፥ ያሰረ ልባችን
ሲታሰር ሲፈታ ፥ ሲቆላ ሲታመስ
ሰቀቀን ገደለን፥
ምጣድ ከኛ ቀድሞ እንዳይደረመስ።
ትሰሚ እንደሁ ስሚ!
የይነጋል ሕብስት ፥ ቡኮው ኾመጠጠ
ሳትሰሚም
ሳይነጋም ተስፋችን አጠጠ።
ሀገር ምጣድ ሆና ፥
ሳት ላይ ስትጋደም ፥ ስለተስፋ እንጎቻ
አመድ እያቀፈው¡ ፥
ቋያ የሚገርፈው ፥ ህዝብ ነው ጉልቻ።
        @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ዳግም ህይወት
7
#ሀሎ

እድሜ ለ ግራም-ቤል
ሀሎ ብሎ ማውጋት ...ለሰው ላስለመደ ፣
ሰላቢ ፈጠራው
ድምፅ ጭኖ ያልፋል.....እየሸመደደ ።

ካፍ የሚወጣው ቃል ..አንዱም ሳይዛነፍ ፣
ቅላፄ ልሳኑ...ዜማ ምቱ ሳይነጥፍ ፣
መልዕክተ ዲስኩሩም
በመማሰን ደክሞ ..ሆሄ ፣ ቃሉ ሳይረግፍ ፣
እንደ ተቀበለው...ቆጥሮ ያሻግራል ፣
ቀፎ ተለጉሞ
ከባህር ባሻገር ፥ ሰው ሰውን ያወራል ።

በዘመን ዘምኖ ...
አሁን አሁን ደሞ
ራሱ በራሱ ፥ ግራ እስኪጋባ ፣
ከሀሎ ተሻግሮ...
ብዙ መዘውሩ ...ባንድነት ሲገባ ፣
እንደአዳም መሻት...
መተግበሪያው በዝቶ ፥ ክውኑ ሲጋባ ፣
የሰው መወዳጃው....
ሆኖ ቢተለምም ፥ እርምጃው ላጠረ ፣
ሀሎ ብሎ ማሰስ...
ያሳብ ግንብ ፈጥሮ ፥ ስጋን እያጠረ ፣
የሩቅ መነፀሩ ፥
የቤተሰብ ልምዱን ፥
ተካቦ ማውጋቱን እንዳቀነጨረ ፣
አላየም....ፈልሳፊው
አዚም እንደሆነን....የሱ የጅ ቀፎ ፣
በስልክ የተጣደ
ከባእድ ያውካካል ....ከዘመድ ተኳርፎ ።
ሳምንቱን በሙሉ
ሰባቱንም ቀናት...ለሊቱን ጨምሮ ፣
ወሬ ይቃርማል
ስሜተ ህዋሱን ...በመሳ ቀስሮ ።

ለምን....? ብሎ ላለም......
በስመ ስልጠና  ፥ ሽንገላ ይበጃል ፣
እንቢኝ ላለውም...
ያረጀ ያፈጀ
ወግ አጥባቂ ይሉት ፥ ሾርኒ ይቀዳጃል ፣
በብቻነቱ ዲን ፥ ብቻውን ይፈጃል ።

..... ይህን ማን ይወዳል ?

ማለፊያ... ነው ...  ትልሙ ፣
ማዘኛም ...  ነው ... አቅሙ ፣
በክፉ ቀን ሳይቀር ፥ የሰው ልጅ ድኩሙ ፣
ቤቱ ቢዘጋ እንኳ...
ከስልኩ ተተክሎ ...ግዜ አጣ ለደሙ ።

በይነ መረቡ ላይ ፥ ብዙ በመባተል ፣
ያሻውን ጎንጉኖ ፥
ያሻውን በመፍተል ፣
              እንዲመቸው አርጎ...
ያሻውን አውርዶ ፥
ያሻውን ይሰቅላል ፣
ሲቀባበል ውሎ ፥ ሲቀባበል ያድራል ።
በዚህ ቀነ ቅኝት....
ኦንላየን ያየውን ፥ ሁሉንም ዘይሮ ፣
አዲስ እያወቀ ፥ አሮጌን አባሮ ፣
ለዋል ፈሰስ ሁሉ...
በሚባክን ግዜ ፥
ብዙ ደባል ይዞ.. ቧልቱ ይጠረቃል ፣
ይህኔ ሺ ለምዶ.. ከየሺው ይርቃል ።
       @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
አብርሃም ተክሉ
6🔥1
#ብልኋ_እንቁራሪት

አንዲት እንቁራሪት በኩሬ ውስጥ ያለች
የሚቃጠል መንደር ፥ ከሩቁ እያየች
ትፀልይ ጀመረ ፥ እንደዚህ እያለች

እባክህ ጌታዬ ይህን እሳት አጥፋው
ባለበት እንዲቆም ግዛቱን አታስፋው
ብላ ለፈጣሪ ፥ አዝና ስትናገር
ለካስ ካጠገቧ እባብ ቆሞ ነበር
እሱም በመገረም ፥ በጸሎቷ ነገር
የሽሙጥ እያየ እንዲህ ይላት ጀመር

እንደው ምን ትገርሚ እንደምን ትደንቂ
እሳቱ እንዲጠፋ ፥ ጌታን 'ምጠይቂ
እሱ 'ሚነድ እዛ እሩቅ ነው ካንቺ ዘንድ
በምን ደርሶብሽ ነው ያንቺን ቤት የሚያነድ ?
ደሞም ከውሃ ውስጥ ቁጭ ብለሽ ያለሽው
የማይደርስብሽን ፥ እሳት የምትፈሪው
እያለ በሹፈት ፥ ከልቡ ሳቀባት
ወደታች በንቀት አዘቅዝቆ እያያት

ይህን ጊዜ እቁራሪት እየተገረመች
በእባብ ጅልነት በጣም እያዘነች
እንዲት ትለው ጀመር ቀና ብላ እያየች
አዎ ትክክል ነህ ፥ እሳቱ እሩቅ ነው
እኔም ያለሁበት ዙሪያውን ውሀ ነው
ነገር ግን አስተውል እጅግ አትሳት
ቃጠሎውን ቶሎ ወዲያው ካላቆሙት
ከ'ኔ ዘንድ መ'ተው ነው ውሀ የሚቀዱት

እናም ያላወከው እውነታው ይሄ ነው
ምንም'ኳ እዚህ ብቀመጥ ከውሃው
እዛ እሩቅ ቢሆን መንደሩ 'ሚነደደው
ካልጠፋ በጊዜ ፥ አምላክ ካላቆመው
የ' ኔም ቤት ነውና ተዝቆ የሚያልቀው

ስለዚህ ወዳጄ አያጥቃህ ጅልነት
ቃጠሎው ባይደርስም እኔ ካልሁበት
እዛ ነዶ ነዶ ፥ እጅግ ከባሰበት
ባልዲ ተሸክመው ሲመጡ ለመቅዳት
ይከቱኛል ወስደው ፥ ከሚነደው እሳት

ይህን አውቄ ነው ከሩቁ መፍራቴ
አጥፋው በሚል ፀሎት ምድር መደፋቴ
የአቅሜን ያህል እነሱን መርዳቴ
ብላ ስትናገር ፥ እባብን ገረመው
ማየት ያልቻለውን ገልጣ ስታሳየው

እናም እሩቅ ያለ ከ' እኛ የማይደርስ
የሌላ ነው ያልነው ፥ እሳቱ ሲለኮስ
ስለማይቀር እዚ ፥ መምጣቱ ቀስ በቀስ
ትልቅ እገዛ ነው
የሰው ችግር አይቶ ፥ ለኔ ብሎ ማልቀስ።
       @gitm_post
    ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ
ሚካኤል እንዳለ
21👏9🥰4