#የሰው_ልጅ_ገፅ_ነው!
ህይወት እንቆቅልሽ ? ምን አውቅልህ? በይኝ
በለቅሶ ጀምሮ በለቅሶ ሚያበቃ ? እስኪ መልሽልኝ?
ይኼማ ቀላል ነው ሀገርም አልሰጥህ፣
የሰው ልጅ እኮ ነው ይኸው መለስኩልህ!
ሲወለድ አልቅሱ ሲሞት አስለቅሶ፣
መኖሩን ያበቃል አፈር ከላይ ለብሶ!
በእኔ ተፈትኖ ሳቅ ሀዘንን አይቶ፣
ይለቀስለታል በእድሜ ገደብ ሞቶ፣
ምስጢሩ ሲፈታ ቅኔው ሲፈለቅቅ፣
በለቅሶ ተወልዶ አስለቅሶ የሚያልቅ ፣
የሰው ልጅ ገጽ ነው ከአፈር የተገኘ፣
ትቢያነቱን ሳያውቅ በጉራ የናኘ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ህይወት እንቆቅልሽ ? ምን አውቅልህ? በይኝ
በለቅሶ ጀምሮ በለቅሶ ሚያበቃ ? እስኪ መልሽልኝ?
ይኼማ ቀላል ነው ሀገርም አልሰጥህ፣
የሰው ልጅ እኮ ነው ይኸው መለስኩልህ!
ሲወለድ አልቅሱ ሲሞት አስለቅሶ፣
መኖሩን ያበቃል አፈር ከላይ ለብሶ!
በእኔ ተፈትኖ ሳቅ ሀዘንን አይቶ፣
ይለቀስለታል በእድሜ ገደብ ሞቶ፣
ምስጢሩ ሲፈታ ቅኔው ሲፈለቅቅ፣
በለቅሶ ተወልዶ አስለቅሶ የሚያልቅ ፣
የሰው ልጅ ገጽ ነው ከአፈር የተገኘ፣
ትቢያነቱን ሳያውቅ በጉራ የናኘ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍14❤12
#እኔና_ጨረቃ
አመሻሽ ላይ ሆኜ ሳስብሽ ሳስብሽ
በረንዳ ላይ ሆኜ አንቺኑ ስስልሽ
ስላንቺ የሚያወራ ግጥም ስፅፍልሽ
አንባ ከአይኖቼ ዱብ ዱብ እያሉ
አይኔና ጉንጮቼ በእንባ ሲሞሉ
ከሰማይ ላይ ሆና ትታዘበኛለች
አጇን በአፏ አርጋ ታፈጥብኛለች
ደንገጥ አልኩኝና እንባዬን ጠረኩኝ
እሷም ቀስ በቀስ እኔን ቀረበችኝ
ብርሀኗ ልዩ ነው ሁሉን የሚያስረሳ
ፈዝዤ ቀረሁኝ ፎቶ እንደሚነሳ
አኔ ጋር ደረሰች ከዋክብት አጅቧት
መንቀጥቀጥ ጀመርኩኝ እኔም በፍርሀት
ጠጋ አለችና አይዞህ ጨረቃ ነኝ
አትፍራ አትሽሽ ብላ አቀፈችኝ
ኮከብ እንዳጀባት እየነገርችኝ
እንባዬን ጠራርጋ አይኖቼን እያየች
በሹክሹክታ መንፈስ ማውራት ጀመረች
አይዞህ ጠንከር በል ምንም አትሆንም
እውነት ካፈቀርቃት የትም አትሄድም
ለፍቅርክ ምስክር እሆንልካለው
ካለችበት ሄጄ እነግርልሀለው፡፡
ያቺ ውብ ጨረቃ ቀርባ አፅናናችኝ
ለተከፋው ልቤ ደስታን ሰጠችልኝ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
አመሻሽ ላይ ሆኜ ሳስብሽ ሳስብሽ
በረንዳ ላይ ሆኜ አንቺኑ ስስልሽ
ስላንቺ የሚያወራ ግጥም ስፅፍልሽ
አንባ ከአይኖቼ ዱብ ዱብ እያሉ
አይኔና ጉንጮቼ በእንባ ሲሞሉ
ከሰማይ ላይ ሆና ትታዘበኛለች
አጇን በአፏ አርጋ ታፈጥብኛለች
ደንገጥ አልኩኝና እንባዬን ጠረኩኝ
እሷም ቀስ በቀስ እኔን ቀረበችኝ
ብርሀኗ ልዩ ነው ሁሉን የሚያስረሳ
ፈዝዤ ቀረሁኝ ፎቶ እንደሚነሳ
አኔ ጋር ደረሰች ከዋክብት አጅቧት
መንቀጥቀጥ ጀመርኩኝ እኔም በፍርሀት
ጠጋ አለችና አይዞህ ጨረቃ ነኝ
አትፍራ አትሽሽ ብላ አቀፈችኝ
ኮከብ እንዳጀባት እየነገርችኝ
እንባዬን ጠራርጋ አይኖቼን እያየች
በሹክሹክታ መንፈስ ማውራት ጀመረች
አይዞህ ጠንከር በል ምንም አትሆንም
እውነት ካፈቀርቃት የትም አትሄድም
ለፍቅርክ ምስክር እሆንልካለው
ካለችበት ሄጄ እነግርልሀለው፡፡
ያቺ ውብ ጨረቃ ቀርባ አፅናናችኝ
ለተከፋው ልቤ ደስታን ሰጠችልኝ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤23👍6🤣1
#ምን_እየሆንኩ_ልጠብቅሽ?
ቅድ ሰማይ እየሰፋሁ?
እራስ ዳሽንን እየገፋሁ?
ወይስ እየሰራሁ የኖህ መርከብ?
ሳፈላልግ የሰው ኮከብ?
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ..???!
እየዘመርኩ?
እየዘፈንኩ?
እያረመምኩ?
ግራ ገባኝ እኮ
ያለየለት ድል ነው
ያለየለት ምርኮ!
ምን ስሆን ልጠብቅሽ..???!
አባይን ስጠልቀው?
ኤርታሌን ስሞቀው?
ቆዳየን እንደ ጨርቅ ችሎ ቢተኩሰው
ተዋነይ' ጋ ልሃድ ዕፁን እዲምሰው?
ምን ስሆን ልጠብቅሽ...???!
በጌታዬ ግራ? በጌታዬ ቀኙ?
በየት ትመጫለሽ? ወይ አፍቃሪ ሞኙ?
በአብርሃም ቤት አጋር?
ወይስ ባቢሎን ግንብ ጋር?
የት' ጋ ተመጫለሽ..???!
ከዘመን በየትዘመን?
ከንጉስ ማን ንጉስ?
ከባህር የት ባህር?
ከደብር የት ደብር?
ከጫካ የት ጫካ?
ከሰዓት ምን ሰዓት?
ምን እያረኩ ልጠብቅሽ...???!
ከመላእክት ጋር ስገለፍጥ?
የዛፍ ቆዳ ስልጥ!
ግዙፍ ሁኜ ወይ እረቂቅ?
ንፋስ ሆኜ ወይስ ደቂቅ?
ደስታ ሁኜ ወይስ ሀዘን?
ፀሐይ ግርጌ ወይ ጨረቃ?
ግጥም ሁኜ ወይ ሙዚቃ?
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ..???!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ኤልያስ ሽታሁን
ቅድ ሰማይ እየሰፋሁ?
እራስ ዳሽንን እየገፋሁ?
ወይስ እየሰራሁ የኖህ መርከብ?
ሳፈላልግ የሰው ኮከብ?
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ..???!
እየዘመርኩ?
እየዘፈንኩ?
እያረመምኩ?
ግራ ገባኝ እኮ
ያለየለት ድል ነው
ያለየለት ምርኮ!
ምን ስሆን ልጠብቅሽ..???!
አባይን ስጠልቀው?
ኤርታሌን ስሞቀው?
ቆዳየን እንደ ጨርቅ ችሎ ቢተኩሰው
ተዋነይ' ጋ ልሃድ ዕፁን እዲምሰው?
ምን ስሆን ልጠብቅሽ...???!
በጌታዬ ግራ? በጌታዬ ቀኙ?
በየት ትመጫለሽ? ወይ አፍቃሪ ሞኙ?
በአብርሃም ቤት አጋር?
ወይስ ባቢሎን ግንብ ጋር?
የት' ጋ ተመጫለሽ..???!
ከዘመን በየትዘመን?
ከንጉስ ማን ንጉስ?
ከባህር የት ባህር?
ከደብር የት ደብር?
ከጫካ የት ጫካ?
ከሰዓት ምን ሰዓት?
ምን እያረኩ ልጠብቅሽ...???!
ከመላእክት ጋር ስገለፍጥ?
የዛፍ ቆዳ ስልጥ!
ግዙፍ ሁኜ ወይ እረቂቅ?
ንፋስ ሆኜ ወይስ ደቂቅ?
ደስታ ሁኜ ወይስ ሀዘን?
ፀሐይ ግርጌ ወይ ጨረቃ?
ግጥም ሁኜ ወይ ሙዚቃ?
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ..???!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ኤልያስ ሽታሁን
❤31
#ስውር_ኃይል
ውሎ-ገባው መንገድ ፥ ልስልሱ ጎዳና
ቀናት ሲፈጅብኝ ፥ አይቶ ታዘበና ፣
የት ይወለድ እንጃ ፥ ከየትኛው ነገድ
ስንቅ አትያዝ አለኝ፥ አስበህ ለመንገድ።
እውነትም .... እውነትም
......... . ሐሰት የለበትም።
በጊዜ ደረስኹኝ ፥ ዘንድሮ ከአምና
እረሃብና ጥም ፥ ጊዜ አይሰጡምና።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በርናባስ ከበደ
ውሎ-ገባው መንገድ ፥ ልስልሱ ጎዳና
ቀናት ሲፈጅብኝ ፥ አይቶ ታዘበና ፣
የት ይወለድ እንጃ ፥ ከየትኛው ነገድ
ስንቅ አትያዝ አለኝ፥ አስበህ ለመንገድ።
እውነትም .... እውነትም
......... . ሐሰት የለበትም።
በጊዜ ደረስኹኝ ፥ ዘንድሮ ከአምና
እረሃብና ጥም ፥ ጊዜ አይሰጡምና።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በርናባስ ከበደ
👍11❤5
#በምላሴ_ገደፍኩ!!
ለመፆም አስቤ ሁለት ወር ሁዳዴ፣
የከብት ስጋ ትቶ የሰው ለምዶ ሆዴ፣
እንዳልተው ጀምሬ እንዳልበላ ፈራሁ፣
ምላሴን ለጉሜ ሱባኤን ካልገባሁ!
ወተትን ሳልጠጣ ለመክረም አስቤ፣
መፆም ጀመርኩና ጋቢየን ደርቤ፣
በምላሴ ገደፍኩ ቀርቶ ዶሮ ወጡ፣
እንደኔ እንዳትረክሱ ሐሜት አታላምጡ።
የከብት ፁማቸሁ የሰው ስጋ አትብሉ፣
ፍቅርን ስበኩና ሐሜትን ዝለሉ፣
ወተት እየፆሙ የሰው ደም መጠጣት፣
ዶሮ ወጥን ዘሎ የሰው ስጋ መብላት፣
ፍቅር እያፈረሱ ጥላቻን መገንባት፣
ስጋ ባለመብላት እጸድቃለሁ ማለት፣
በርግጥ ፆም ጥሩ ነው ስጋን ያሸንፋል፣
ካልተጠነቀቁ ሐሜት ግን ያረክሳል፣
ጮማውን ለመቁረጥ ልባችን ከፈራ፣
ምነው አንደነግጥ ሐሰት ስናወራ?!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ለመፆም አስቤ ሁለት ወር ሁዳዴ፣
የከብት ስጋ ትቶ የሰው ለምዶ ሆዴ፣
እንዳልተው ጀምሬ እንዳልበላ ፈራሁ፣
ምላሴን ለጉሜ ሱባኤን ካልገባሁ!
ወተትን ሳልጠጣ ለመክረም አስቤ፣
መፆም ጀመርኩና ጋቢየን ደርቤ፣
በምላሴ ገደፍኩ ቀርቶ ዶሮ ወጡ፣
እንደኔ እንዳትረክሱ ሐሜት አታላምጡ።
የከብት ፁማቸሁ የሰው ስጋ አትብሉ፣
ፍቅርን ስበኩና ሐሜትን ዝለሉ፣
ወተት እየፆሙ የሰው ደም መጠጣት፣
ዶሮ ወጥን ዘሎ የሰው ስጋ መብላት፣
ፍቅር እያፈረሱ ጥላቻን መገንባት፣
ስጋ ባለመብላት እጸድቃለሁ ማለት፣
በርግጥ ፆም ጥሩ ነው ስጋን ያሸንፋል፣
ካልተጠነቀቁ ሐሜት ግን ያረክሳል፣
ጮማውን ለመቁረጥ ልባችን ከፈራ፣
ምነው አንደነግጥ ሐሰት ስናወራ?!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤19👍10😢1
ለመላው የቻናላችን እስልምና እምነት ተከታይ ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን ለ 1447ተኛው የ ኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ❤️
🔆 Eid Mubarek ኢድ ሙባረክ 🌙
🔆 Eid Mubarek ኢድ ሙባረክ 🌙
👍11❤3
#የኗሪ_ታዛቢ!
ተይ በሏት ይችን ሰው፥ ምከሯት ትታረም
አጀብ አያሰኝም ፥ጅብ ካህያ መክረም!¡
ታግሼው ነው እንጂ!
እስስት አመልሽን ፥ ስታግለበልቢኝ
ፈርቼሽ አይደለም ፥ እንዳሻሽ ስትገልቢኝ።
ተቻችሎ መክረም!
አንቺ ትብሺ አንተ ፥
በሚል የጋራ ሀሳብ ፥ ፍቅር ካላሰረን
ቤታችን ፈረሰ፥ አውላላ ላይ ቀረን።
እወቂበት በቃ!
ማን የገነባውን ፥ ማን አፍርሶ ያልፋል
በመቻቻል ሲሆን ፥ የኔም ልብ ይሰፋል።
መቼስ ምን ይደረግ!
ጊዜ ላይቀይርሽ !
ታጥቦ ጭቃ አመልሽ ፥ ቀኔን እያስረጀው
(ትኖሪያለሽ እንጂ)
ባኗኗሪነት ነው ፥ እድሜዬን ምፈጀው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ተይ በሏት ይችን ሰው፥ ምከሯት ትታረም
አጀብ አያሰኝም ፥ጅብ ካህያ መክረም!¡
ታግሼው ነው እንጂ!
እስስት አመልሽን ፥ ስታግለበልቢኝ
ፈርቼሽ አይደለም ፥ እንዳሻሽ ስትገልቢኝ።
ተቻችሎ መክረም!
አንቺ ትብሺ አንተ ፥
በሚል የጋራ ሀሳብ ፥ ፍቅር ካላሰረን
ቤታችን ፈረሰ፥ አውላላ ላይ ቀረን።
እወቂበት በቃ!
ማን የገነባውን ፥ ማን አፍርሶ ያልፋል
በመቻቻል ሲሆን ፥ የኔም ልብ ይሰፋል።
መቼስ ምን ይደረግ!
ጊዜ ላይቀይርሽ !
ታጥቦ ጭቃ አመልሽ ፥ ቀኔን እያስረጀው
(ትኖሪያለሽ እንጂ)
ባኗኗሪነት ነው ፥ እድሜዬን ምፈጀው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤17👍6👏3🤯2
#ግማሽ_ቅጠል
አበባ ነኝ እኔ ፥ የአበባ ዛፍ ቅጠል
ማማር ነው ስራዬ ፥ ራስን ሆኖ መብቀል።
አንገቴን አልደፋም ፥ ቢጨፈን ዓይን ሁሉ
የትም እፈካለሁ ፥ በዱር በገደሉ።
እንዲያ ሆኜ ስኖር ...
ከውበታት አንድ ቀን፣ ...
በመስመር ከፈኩት ፥ ከሆኑት ሰልፈኛ
ወጣ ብዬ ቢያየኝ ፥ አንድ አትክልተኛ፣...
የአካሌ ክፋይ ፥ ድንገት ተቀነሰ
ክርክም ለማሳመር ፥ በመቀስ ተላሰ!!
ግማሽ ቅጠል ሆንኩኝ።
የቀረው ግማሼ
እየተንሳፈፈ ... ወደቀ ከአፈር፣
....... እኔን ልንፈራፈር!!!
ቆየና ....
ቀናት አለፉና፣ ...
ያ የኔው እኔነት
ያ የኔው ማንነት፣...
ለምለም የነበረው ፥ ደርቆና በስብሶ
መብል ሆኖ መጣ ፥ ለኔው ተመልሶ።
ተቆርጦ የወደቀው ፥ የአካሌ ቅንጣት
የሞትን መዓዛ ፥ በደም ስሬ አመጣት።
ኦውው!
ለካስ እረባለሁ ፥ ከማማር ባሻገር
ቀስሞ ይወስደኛል ፥ የሌላ አበባ ስር።
እግዚአብሔር ይመስገን!
ሕይወቴን ወደድኩት ፥ አሁን በተለየ
አኗኗር አይከብድም ፥ አሟሟቱን ላዬ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በርናባስ ከበደ
አበባ ነኝ እኔ ፥ የአበባ ዛፍ ቅጠል
ማማር ነው ስራዬ ፥ ራስን ሆኖ መብቀል።
አንገቴን አልደፋም ፥ ቢጨፈን ዓይን ሁሉ
የትም እፈካለሁ ፥ በዱር በገደሉ።
እንዲያ ሆኜ ስኖር ...
ከውበታት አንድ ቀን፣ ...
በመስመር ከፈኩት ፥ ከሆኑት ሰልፈኛ
ወጣ ብዬ ቢያየኝ ፥ አንድ አትክልተኛ፣...
የአካሌ ክፋይ ፥ ድንገት ተቀነሰ
ክርክም ለማሳመር ፥ በመቀስ ተላሰ!!
ግማሽ ቅጠል ሆንኩኝ።
የቀረው ግማሼ
እየተንሳፈፈ ... ወደቀ ከአፈር፣
....... እኔን ልንፈራፈር!!!
ቆየና ....
ቀናት አለፉና፣ ...
ያ የኔው እኔነት
ያ የኔው ማንነት፣...
ለምለም የነበረው ፥ ደርቆና በስብሶ
መብል ሆኖ መጣ ፥ ለኔው ተመልሶ።
ተቆርጦ የወደቀው ፥ የአካሌ ቅንጣት
የሞትን መዓዛ ፥ በደም ስሬ አመጣት።
ኦውው!
ለካስ እረባለሁ ፥ ከማማር ባሻገር
ቀስሞ ይወስደኛል ፥ የሌላ አበባ ስር።
እግዚአብሔር ይመስገን!
ሕይወቴን ወደድኩት ፥ አሁን በተለየ
አኗኗር አይከብድም ፥ አሟሟቱን ላዬ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በርናባስ ከበደ
❤11👍3🔥2
#ውሸት
ውሸት ዳቦ ቢሆን ረሀብ ባልኖረ
ውሸት ልብስ ቢሆን ስንቱ ላይ ባማረ
ውሸት ጥበብ ቢሆን ስንቱ በተካነ
ውሸት ኪነት ቢሆን ስንቱ በዘፈነ
ውሸት እውቀት ቢሆን ስንቱ በተማረ
ውሸት ግን ውሸት ነው ዘበት ሁኖ ቀረ
ግን አንዳንድ ሰዎች ውሸት የሚወዱ
ለውሸት ተገዝተው ለውሸት ያበዱ
በውሸታቸው ልክ ጥርሳቸው ቢወልቅ
የስንቱ ድድ ነበር ፀሐይ የሚሞቅ ?
ውሸታም ነው ብሎ ሰው እንዳይሸሸው
ሰው ነኝ የሚል ሁሉ ውሸትን ይጥላው
ሰው በውሸት ዓለም መንሸርሸሩን ትቶ
ይኑር በሐገሩ በዕውነት ተጨምቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ውሸት ዳቦ ቢሆን ረሀብ ባልኖረ
ውሸት ልብስ ቢሆን ስንቱ ላይ ባማረ
ውሸት ጥበብ ቢሆን ስንቱ በተካነ
ውሸት ኪነት ቢሆን ስንቱ በዘፈነ
ውሸት እውቀት ቢሆን ስንቱ በተማረ
ውሸት ግን ውሸት ነው ዘበት ሁኖ ቀረ
ግን አንዳንድ ሰዎች ውሸት የሚወዱ
ለውሸት ተገዝተው ለውሸት ያበዱ
በውሸታቸው ልክ ጥርሳቸው ቢወልቅ
የስንቱ ድድ ነበር ፀሐይ የሚሞቅ ?
ውሸታም ነው ብሎ ሰው እንዳይሸሸው
ሰው ነኝ የሚል ሁሉ ውሸትን ይጥላው
ሰው በውሸት ዓለም መንሸርሸሩን ትቶ
ይኑር በሐገሩ በዕውነት ተጨምቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤20👏7👍2
#አንቺ_ምን_አለብሽ
ባልጠበቀ ስንኝ በላላ ቋጠሮ
ውበትሽን ለመግለጽ ስጭር እንደ ዶሮ
ቤት መታ ቤት ደፋ እያልኩኝ ለእራሴ
ስደክም ስባክን ስትጨነቅ ነፍሴ
አንቺ ምን አለብሽ ተኝተሽ አልሚ
ክረምቱን በሙቀት ሳይበርድሽ ክረሚ
ብዙ አድናቂ ያለሽ ሲጭር የሚያነጋ
ውበትሽን አወዳሽ የገጣሚ መንጋ
ቃላትን አዋቅሮ ይጭራል ይጽፋል
ውበትሽን ለመግለጽ ስንኝ ይቋጥራል
አንቺ ተኝተሻል አይገድሽ አይሞቅሽ
ይብላኝ ለማይተኛው ቆሞ ለሚያልምሽ
በክረምቱ ቆፈን ብርድ እያነዘረው
ሲያስብሽ አዳሪው እልፍ አላፍ ጫሪ ነው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ባልጠበቀ ስንኝ በላላ ቋጠሮ
ውበትሽን ለመግለጽ ስጭር እንደ ዶሮ
ቤት መታ ቤት ደፋ እያልኩኝ ለእራሴ
ስደክም ስባክን ስትጨነቅ ነፍሴ
አንቺ ምን አለብሽ ተኝተሽ አልሚ
ክረምቱን በሙቀት ሳይበርድሽ ክረሚ
ብዙ አድናቂ ያለሽ ሲጭር የሚያነጋ
ውበትሽን አወዳሽ የገጣሚ መንጋ
ቃላትን አዋቅሮ ይጭራል ይጽፋል
ውበትሽን ለመግለጽ ስንኝ ይቋጥራል
አንቺ ተኝተሻል አይገድሽ አይሞቅሽ
ይብላኝ ለማይተኛው ቆሞ ለሚያልምሽ
በክረምቱ ቆፈን ብርድ እያነዘረው
ሲያስብሽ አዳሪው እልፍ አላፍ ጫሪ ነው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤19👍4👏3
#በሰበብ_አፍቃሪ
ጊዜ እየሄደ ነው ሲነጋና ሲመሽ...
ቀን እየቆጠረ፣
ከኔ የመራቅህ ምስጢር ሳይፈታ...
እንደተቋጠረ፣
እኔው ነኝ ያለሁት ካስቀመጥከኝ ቦታ
እንደተቀመጥኩኝ፣
መተህ ፣ከነገርከኝ ብዬ እየጠበኩኝ፣
ስወጣ ስገባ ከተጣራህ ብዬ ሰላምታ
እያሰብኩኝ፣
ፀጉሬ ከፀጉሬ ተጋምዶ ተሳስሮ፣
ቁጭት ልቤን ሲለኝ አካሌን ሰርስሮ፣
ያየኝ ከንፈር ሲመጥ በአይኔ እንጉርጉሮ፣
አለሁኝ አለሜ ምስጢር እስኪፈታ
ህይወቴ ተቋጥሮ፣
እንደው ታውቀኝ ይሆን ብታየኝ
ምናልባት፣
የመውደድን ደጅ የፍቅርህን እናት፣
ይቅር አታውቀኝም እንኳን ላንተ ቀርቶ፣
ለኔም እንግዳ ነኝ ያልዘራሁት ፈርቶ፣
ባውቀው ምን አለበት ምን እንደበደልኩህ፣
ጥፋቴ ከሆነ እኔው በሸኘሁህ፣
የልቤ ጥያቄ ውስጤን እያመሰው፣
ምን አረክሺው ሲለኝ ምኔን ልመልሰው፣
እንኳን ላንተ ቀርቶ ገራገር ነኝ ለሰው፣
ሂጂ አምጪው ለሚለኝ ለናፈቀህ ቤቴ፣
ጃስሚኔን ለበላው ላስቀረኝ ባጥንቴ፣
ምን ብዬ ልመልስ፣
ምን አንደበት አለኝ የቋጠርከው
ሚስጢር እስኪፈታ ድረስ፣
ምን አድርጌው ይሆን እያልኩኝ ስጠብቅ ልሰማ ከቃልህ፣
ማትመጣውን እንተን በምስጢርህ ሰበብ አለሁኝ ሳፈቅርህ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ጊዜ እየሄደ ነው ሲነጋና ሲመሽ...
ቀን እየቆጠረ፣
ከኔ የመራቅህ ምስጢር ሳይፈታ...
እንደተቋጠረ፣
እኔው ነኝ ያለሁት ካስቀመጥከኝ ቦታ
እንደተቀመጥኩኝ፣
መተህ ፣ከነገርከኝ ብዬ እየጠበኩኝ፣
ስወጣ ስገባ ከተጣራህ ብዬ ሰላምታ
እያሰብኩኝ፣
ፀጉሬ ከፀጉሬ ተጋምዶ ተሳስሮ፣
ቁጭት ልቤን ሲለኝ አካሌን ሰርስሮ፣
ያየኝ ከንፈር ሲመጥ በአይኔ እንጉርጉሮ፣
አለሁኝ አለሜ ምስጢር እስኪፈታ
ህይወቴ ተቋጥሮ፣
እንደው ታውቀኝ ይሆን ብታየኝ
ምናልባት፣
የመውደድን ደጅ የፍቅርህን እናት፣
ይቅር አታውቀኝም እንኳን ላንተ ቀርቶ፣
ለኔም እንግዳ ነኝ ያልዘራሁት ፈርቶ፣
ባውቀው ምን አለበት ምን እንደበደልኩህ፣
ጥፋቴ ከሆነ እኔው በሸኘሁህ፣
የልቤ ጥያቄ ውስጤን እያመሰው፣
ምን አረክሺው ሲለኝ ምኔን ልመልሰው፣
እንኳን ላንተ ቀርቶ ገራገር ነኝ ለሰው፣
ሂጂ አምጪው ለሚለኝ ለናፈቀህ ቤቴ፣
ጃስሚኔን ለበላው ላስቀረኝ ባጥንቴ፣
ምን ብዬ ልመልስ፣
ምን አንደበት አለኝ የቋጠርከው
ሚስጢር እስኪፈታ ድረስ፣
ምን አድርጌው ይሆን እያልኩኝ ስጠብቅ ልሰማ ከቃልህ፣
ማትመጣውን እንተን በምስጢርህ ሰበብ አለሁኝ ሳፈቅርህ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤12👏4💔3😢2
#አደን
አሳዳጄን አመለጥኳት
አመለጠችኝ ያሣደድኳት።
ኗሪ ሆንኩኝ እንደፍየል
በነብርና ቅጠል መሀል።
አቤት አለች ያልጠራኋት
የጠራኋት ድምፅም የላት።
ራቂኝ 'ምላት ጎኔ ወድቃ
ቅረቢኝ ምላት ከኔ ርቃ።
አንዴ ስታደን አንዴም ሳድን
እረፍት አጥቼ ስባክን
የዕድሜዬን ጀምበር ብታዘባት
ልትጠልቅ ምንም አልቀራት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደበበ ሰይፉ
አሳዳጄን አመለጥኳት
አመለጠችኝ ያሣደድኳት።
ኗሪ ሆንኩኝ እንደፍየል
በነብርና ቅጠል መሀል።
አቤት አለች ያልጠራኋት
የጠራኋት ድምፅም የላት።
ራቂኝ 'ምላት ጎኔ ወድቃ
ቅረቢኝ ምላት ከኔ ርቃ።
አንዴ ስታደን አንዴም ሳድን
እረፍት አጥቼ ስባክን
የዕድሜዬን ጀምበር ብታዘባት
ልትጠልቅ ምንም አልቀራት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ደበበ ሰይፉ
❤14👍3👏1
#ድሮ_የኔ_እያለች
ድሮ የኔ እያለች
መርጣ የማትለብስ~ፋሽን ማትከተል
ይሄን ያንን ግዛ~ልሽቀርቀር የማትል
አቅም ስለሌለኝ~በልኩ ምትዘንጥ
በአላት ተውባ~ልቤን የምታቀልጥ
አሁን የሱ ሆና
በየ ቡቲክ ዞራ~ደስ ያላትን ገዝታ
ኮስሞቲክስ ቀያይራ~መርጣ ተቀብታ
እንደልቧ ሆና~ከቤት የምትወጣ
እንደድሮ ችግር~ጭንቅ የሌላት ጣጣ
ድሮ የኔ እያለች
ፍቅሬ ራበኝ ስትል~ሆቴል ማልጋብዛት
ከቤቴ ሰርቼ ~ በፍቅር ማጎርሳት
አንዳንዴ ከሌለ~ሲርበኝ ተርባ
እህል የማትቀምስ~እቤት እስክገባ
አሁን የሱ ሆና
ከአልጋ ላይ ሳትወርድ~አዛ አሰርታ
ወይን ሆቴል ሄዳ~ደስ ያላትን በልታ
በጥጋብ የምትኖር~ረሀብ የማያውቃት
እሱ መጣ ቀረ~የማያስጨንቃት
ድሮ የኔ እያለች
በግራችን ተጉዘን~ሲደክማት ምናርፈው
ጥላስር ቁጭ ብለን~የምናሳልፈው
ማታማታ አቅፌ~ወክ ብዬ ማዞራት
ስንቴ ደጋግሜ~ፍቅሬን የምነግራት
አሁን የሱ ሆና
መኪና ይዛለች~የደከመ ካለ ቆማ ትሸኛለች
በግር ላለመሄድ-ከሁሉ አብልጣ ትጠነቀቃለች
ደሞ የምን ድካም~ከወክ የሚመጣ
ፈልሰስ ትላለች~ገቢና ተቀምጣ
ድሮ የኔ እያለች
ላፍታ እንኳን ከጎኔ~ችዬ ማላርቃት
በስስት እያየው~እቅፍ የማደርጋት
አማረኝ ያለች ቀን~ፍቅርን ሰጥቼ
ከቅዱሱ መዓድ~አብሬያት በልቼ
አሁን የሱ ሆና
በትልቅ አልጋ ላይ~ብቻዋን ተኝታ
ፍቅር ራበኝ የሚል~ያን ልማዷን ትታ
መቅበጥ ሚባል የለም~ከእቅፉ መግባት
ፍቅርም የሚሰሩት~እሱ ያሰኘው እለት
ድሮ የኔ እያለች
ከፍቷት ስታለቅስ~ክንዴን አንተርሼ
አቅፌ እየሳምኩ~እንባዋን አብሼ
ከስሬ ሸጉጬ~ላስቃት ምጥረው
እውነት ይሁን ውሸት~ምቀበጣጥረው
አሁን የሱ ሆና
ሲከፋት ስታዝን~ብቻዋን አልቅሳ
እራሷን አፅናንታ~እንባዋን አብሳ
የትላንቱን ፍቅር~በብር አስረስቷት
ለስጋዋ ደርሶ~ለነብስ አሳጥቷት
ደስታዋዬን በገንዘብ~ካልገዛው ትላለች
እንዴት ትሆን ይሆን~አፈላልጋ ካጣች።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ድሮ የኔ እያለች
መርጣ የማትለብስ~ፋሽን ማትከተል
ይሄን ያንን ግዛ~ልሽቀርቀር የማትል
አቅም ስለሌለኝ~በልኩ ምትዘንጥ
በአላት ተውባ~ልቤን የምታቀልጥ
አሁን የሱ ሆና
በየ ቡቲክ ዞራ~ደስ ያላትን ገዝታ
ኮስሞቲክስ ቀያይራ~መርጣ ተቀብታ
እንደልቧ ሆና~ከቤት የምትወጣ
እንደድሮ ችግር~ጭንቅ የሌላት ጣጣ
ድሮ የኔ እያለች
ፍቅሬ ራበኝ ስትል~ሆቴል ማልጋብዛት
ከቤቴ ሰርቼ ~ በፍቅር ማጎርሳት
አንዳንዴ ከሌለ~ሲርበኝ ተርባ
እህል የማትቀምስ~እቤት እስክገባ
አሁን የሱ ሆና
ከአልጋ ላይ ሳትወርድ~አዛ አሰርታ
ወይን ሆቴል ሄዳ~ደስ ያላትን በልታ
በጥጋብ የምትኖር~ረሀብ የማያውቃት
እሱ መጣ ቀረ~የማያስጨንቃት
ድሮ የኔ እያለች
በግራችን ተጉዘን~ሲደክማት ምናርፈው
ጥላስር ቁጭ ብለን~የምናሳልፈው
ማታማታ አቅፌ~ወክ ብዬ ማዞራት
ስንቴ ደጋግሜ~ፍቅሬን የምነግራት
አሁን የሱ ሆና
መኪና ይዛለች~የደከመ ካለ ቆማ ትሸኛለች
በግር ላለመሄድ-ከሁሉ አብልጣ ትጠነቀቃለች
ደሞ የምን ድካም~ከወክ የሚመጣ
ፈልሰስ ትላለች~ገቢና ተቀምጣ
ድሮ የኔ እያለች
ላፍታ እንኳን ከጎኔ~ችዬ ማላርቃት
በስስት እያየው~እቅፍ የማደርጋት
አማረኝ ያለች ቀን~ፍቅርን ሰጥቼ
ከቅዱሱ መዓድ~አብሬያት በልቼ
አሁን የሱ ሆና
በትልቅ አልጋ ላይ~ብቻዋን ተኝታ
ፍቅር ራበኝ የሚል~ያን ልማዷን ትታ
መቅበጥ ሚባል የለም~ከእቅፉ መግባት
ፍቅርም የሚሰሩት~እሱ ያሰኘው እለት
ድሮ የኔ እያለች
ከፍቷት ስታለቅስ~ክንዴን አንተርሼ
አቅፌ እየሳምኩ~እንባዋን አብሼ
ከስሬ ሸጉጬ~ላስቃት ምጥረው
እውነት ይሁን ውሸት~ምቀበጣጥረው
አሁን የሱ ሆና
ሲከፋት ስታዝን~ብቻዋን አልቅሳ
እራሷን አፅናንታ~እንባዋን አብሳ
የትላንቱን ፍቅር~በብር አስረስቷት
ለስጋዋ ደርሶ~ለነብስ አሳጥቷት
ደስታዋዬን በገንዘብ~ካልገዛው ትላለች
እንዴት ትሆን ይሆን~አፈላልጋ ካጣች።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤15👍8👏2
#ነበረ_ምኞቴ!!
ታንክ ወደ ትራክተር፣
ክላሽም ለቀንበር፣
መትረጊስ ማረሻ፣
ጥይት ተሰብስቦ ይጣል ከቆሻሻ፣
አልቢን ማጭድ ይሁን ከምንሽር ጋራ፣
ሞርተር ይቅለጥና ድልድይን እንስራ፣
ቦንብም መንገድ ይስራ ከድማሚት አብሮ፣
በሞርተር ቀለሐ ይሰራ ከበሮ፣
ነበረ ምኞቴ የዘላለም ህልሜ፣
ማየትን የምሻው ሀገሬ ላይ ቆሜ፣
ግን ሰው ክፉ ነው ታንክ ባይኖረውም፣
ድንጋይን ተጠቅሞ መግደል አያቆምም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ታንክ ወደ ትራክተር፣
ክላሽም ለቀንበር፣
መትረጊስ ማረሻ፣
ጥይት ተሰብስቦ ይጣል ከቆሻሻ፣
አልቢን ማጭድ ይሁን ከምንሽር ጋራ፣
ሞርተር ይቅለጥና ድልድይን እንስራ፣
ቦንብም መንገድ ይስራ ከድማሚት አብሮ፣
በሞርተር ቀለሐ ይሰራ ከበሮ፣
ነበረ ምኞቴ የዘላለም ህልሜ፣
ማየትን የምሻው ሀገሬ ላይ ቆሜ፣
ግን ሰው ክፉ ነው ታንክ ባይኖረውም፣
ድንጋይን ተጠቅሞ መግደል አያቆምም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤24👍6👏3
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።❤
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
መልካም ፋሲካ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
መልካም ፋሲካ
❤10👍1🙏1
#ድሃዉስ_አንተ_ነህ
መቼም ሠዉ ነኝ እና በፍቅርህ ብረታ፤
ከእለት ባንዱ ቀን አመሻሽ ላይ ማታ፤
ፍቅርህ በርትቶብኝ አበባ ታቅፌ ቆሜ ከበራፍህ ፤
እኔ አንተን መዉደዴን ማፍቀሬን ስነግርህ ፤
" ስምሽ ማነው አንቺ የኔ እህት ፤
ታወቂያለሽ አይደለ ደሀ እኮ አያፈቅርም"
ብለህ በማጣቴ ፍቅሬን አኩሠሀል ፤
አንተን በመዉደዴ ስቀህ ተሣልቀሀል፡፡
እርግጥ ነው እዉነት ለመመሥከር ፤
አንተ ባለ መኪና አባትህ ኢንቨስተር፤
እናትህ ነጋዴ ወንድምህ ማናጀር ፤
እህትህ ዝነኛ አለምን የምትዞር ፤
የሀብታችሁ ብዛት ገዝፏል ከተራራ ፤
አጎትህ አክስትህ ናቸዉ ዲያሥፖራ፡፡
ነገር ግን ወዳጄ ቅምጥሉ አበቤት ፤
አንተ እንደምትልኝ የሠዉ ድሃ ማለት፤
ያልሆነ ነጋዴ ያልሠራ ቪላ ቤት ፤
መኪና የሌለው መሪ ያልዘወረ ፤
ድያስፖራ ሆኖ ወንዝ ያልተሻገረ ፤
ድሀ ማለተ ላንተ እንዲያ ከመሠለህ ፤
እኔ አፍቃሪህ ሣልሆን ድሀዉስ አንተ ነህ፡፡
ይልቅስ
ደርሶ መኩራራትህን እርግፍ አርገዉ እና ፤
መወደዴን ተረድተህ ከልቤ ግባ እና ፤
ይልቅስ ላሣይህ ልብህም ይዝናና
ገንዘብ የማይገዛዉ ከገበያ ያልዋለ፤
ከሀብታም ተነጥቆ ለኛ የታደለ ፤
ሺ ፍቅር ሺ ጤና ከድሀ ቤት አለ ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
መቼም ሠዉ ነኝ እና በፍቅርህ ብረታ፤
ከእለት ባንዱ ቀን አመሻሽ ላይ ማታ፤
ፍቅርህ በርትቶብኝ አበባ ታቅፌ ቆሜ ከበራፍህ ፤
እኔ አንተን መዉደዴን ማፍቀሬን ስነግርህ ፤
" ስምሽ ማነው አንቺ የኔ እህት ፤
ታወቂያለሽ አይደለ ደሀ እኮ አያፈቅርም"
ብለህ በማጣቴ ፍቅሬን አኩሠሀል ፤
አንተን በመዉደዴ ስቀህ ተሣልቀሀል፡፡
እርግጥ ነው እዉነት ለመመሥከር ፤
አንተ ባለ መኪና አባትህ ኢንቨስተር፤
እናትህ ነጋዴ ወንድምህ ማናጀር ፤
እህትህ ዝነኛ አለምን የምትዞር ፤
የሀብታችሁ ብዛት ገዝፏል ከተራራ ፤
አጎትህ አክስትህ ናቸዉ ዲያሥፖራ፡፡
ነገር ግን ወዳጄ ቅምጥሉ አበቤት ፤
አንተ እንደምትልኝ የሠዉ ድሃ ማለት፤
ያልሆነ ነጋዴ ያልሠራ ቪላ ቤት ፤
መኪና የሌለው መሪ ያልዘወረ ፤
ድያስፖራ ሆኖ ወንዝ ያልተሻገረ ፤
ድሀ ማለተ ላንተ እንዲያ ከመሠለህ ፤
እኔ አፍቃሪህ ሣልሆን ድሀዉስ አንተ ነህ፡፡
ይልቅስ
ደርሶ መኩራራትህን እርግፍ አርገዉ እና ፤
መወደዴን ተረድተህ ከልቤ ግባ እና ፤
ይልቅስ ላሣይህ ልብህም ይዝናና
ገንዘብ የማይገዛዉ ከገበያ ያልዋለ፤
ከሀብታም ተነጥቆ ለኛ የታደለ ፤
ሺ ፍቅር ሺ ጤና ከድሀ ቤት አለ ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤23👍3🔥3👏3
#ላንቺ_ስል!
ፍቅሬ.............
እውነት እልሻለሁ እምልልሻለሁ
ከምነግርሽ በላይ እኔ እወድሻለሁ
..............ስለ ፍቅር ሲባል
የፈለገ ይምጣ ያልሆንኩት ልባል
ችግር ቢበዛብኝ
ነገር ቢከብድብኝ
ለፍቅርሽ ብገረፍ ክንዴ ቢደማብኝ
ተጎዳሁ አልልም ጎኔ ካለሽልኝ
ሃገር ላገር ስዞር የተንገላታሁት
ስቃይ አልለውም ላንቺ ስል የሆንኩት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ነጋሲ ሃበሽ
ፍቅሬ.............
እውነት እልሻለሁ እምልልሻለሁ
ከምነግርሽ በላይ እኔ እወድሻለሁ
..............ስለ ፍቅር ሲባል
የፈለገ ይምጣ ያልሆንኩት ልባል
ችግር ቢበዛብኝ
ነገር ቢከብድብኝ
ለፍቅርሽ ብገረፍ ክንዴ ቢደማብኝ
ተጎዳሁ አልልም ጎኔ ካለሽልኝ
ሃገር ላገር ስዞር የተንገላታሁት
ስቃይ አልለውም ላንቺ ስል የሆንኩት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ነጋሲ ሃበሽ
👍10❤9🥰5
#የቱ_ጋር_መሰለህ....
መባቻ ጅምርህ
የነፍስህ ድባቴ
ውድቀት እንግልትህ
ያኔ …
ባሽትሪ መያዣ ፣ በሲጋራ ብናኝ
በርጋፊ ቅጠል ፣ ድባቧ የሚቃኝ
በዛች ጠባብ ክፍል
ምጥን መሰብሰቢያ
ዙሪያህን ሰው ሞልቶህ
ቀንህን ማጣፊያ
ለአፕላይ ግብዣ የተዘረጋች ጣት
በሚግተለተል ጢስ ፣ ሰንቃልህ እሳት
እሷን ለመቀበል ስትፈግግ ባ’ክብሮት
የሰበብ አስባብ ጢስ
ቀረ ቤትህን ወርሶት።
የቱ ጋር መሰለህ?
በቀይ መብራት ፍካት
በቅልቅል ሽቶ አዲስ አይነት ክርፋት
በጭላጭ ብርጭቆ ተላኮበት ድራፍት
ከስፒከር ማህፀን ሙዚቃ ተለቆ
ጭፈራ እና ዳንሱ አንድ ላይ ተዛንቆ
የቀይ ሴትን ታፋ ዓይንህ በስስ ሰርቆ
በምራቅህ ድርቀት ጉሮሮህ ተጨንቆ
ጠቅሰህ ስትጠራት
ያቺን የሞት ብልቃጥ
ከባቷ ፈልቅቀህ ዕፅዋን ስትቀምሳት
በገላህ ፍሰሀ መቅደስህን ናድካት ።
የቱ ጋር መሰለህ?
የልጅነት ልምድህ
ከሰንበት ቤት ገዳም
ምልልስ ብርታትህ
በዋዛ ሲቀየር
የያሬዱ ወረብ
በእስክስታ ሲዛወር
ስትዘነጋ ፀሎት
ሳይንስ ከእምነት ልቆት
ኒቼ ቦታ ሲወርስ የየኔታን መንበር
የነፍስህ ቁዘማ መንደርደሪያ ነበር።
ትዝ አለህ?
ዘር መራጭ ስትሆን
የደም ሴል መንጣሪ
ጆሮህ ዳባ ሲለብስ
ለፍጥረት እንግልት
ለህፃናት ጥሪ…
መንገድህ ሲሳለጥ
በ V 8 መኪና
ዝርግ አስፓልት ሲመስልህ
ጉርብጥብጥ ጎዳና ፤
ስቆልኛል ስትል ጥርሱን የነከሰ
እንባው አንሸራሽሮህ ጌታ ዘንድ ደረሰ።
ያን ጊዜ ተከፋህ!
ጥሬ እየቆረጥክ ሆድህ ሲመረመር
እስቲም ሳውና ገብተህ ፊትህ ሲጭበረበር
በድሎትህ መኃል
ገላን የሚያኮስስ የእሾህ ስንጥር ነበር።
ትዝ አለህ?
መኝታህ በምቾት ተሞልቶ በአጀብ
እንቅልፍህ ሲናጠብ?
ትዝ አለህ?
በውድ ቀለም ቤቶች ልጆችህ ሲማሩ
ከግብረገብ ታዛ ተናንሰው ሲቀሩ?
ትዝ አለህ?
የጉያህ መልካም ሴት
የአጥንትህ ፍላጭ
‘አሁን ከምን ጊዜው
ሆነችብኝ ምላጭ? ‘
ብለህ ስትቆዝም … ?
እንዲያ ነው አይዋ…
ግፍ ፅዋው ሲሞላ
በትሩን አይመርጥም።
ትዝ አለህ?
ታወሰህ?
የቱ ጋር መሰለህ?
የተፈታው ውሉ
የጎደልክ ከሙሉ
‘ኧረ ስከን’ ሲሉ
ከዕድሜ የተማሩ
የጋሽ ውቤን ምክር
የእመት ጉሌን ዝክር
ረግጠህ ስትበር…
ስትሻገር ፣ ስጥስ
የምስኪናን ድንበር
የዛሬ ውድቀትህ ፣ በግጥም ሊነገር
ክንፍህ የተመታው ይሄን ጊዜ ነበር።
ትዝ አለህ?
አዎን እሱ ጋር ነው!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሚካኤል አስጨናቂ
መባቻ ጅምርህ
የነፍስህ ድባቴ
ውድቀት እንግልትህ
ያኔ …
ባሽትሪ መያዣ ፣ በሲጋራ ብናኝ
በርጋፊ ቅጠል ፣ ድባቧ የሚቃኝ
በዛች ጠባብ ክፍል
ምጥን መሰብሰቢያ
ዙሪያህን ሰው ሞልቶህ
ቀንህን ማጣፊያ
ለአፕላይ ግብዣ የተዘረጋች ጣት
በሚግተለተል ጢስ ፣ ሰንቃልህ እሳት
እሷን ለመቀበል ስትፈግግ ባ’ክብሮት
የሰበብ አስባብ ጢስ
ቀረ ቤትህን ወርሶት።
የቱ ጋር መሰለህ?
በቀይ መብራት ፍካት
በቅልቅል ሽቶ አዲስ አይነት ክርፋት
በጭላጭ ብርጭቆ ተላኮበት ድራፍት
ከስፒከር ማህፀን ሙዚቃ ተለቆ
ጭፈራ እና ዳንሱ አንድ ላይ ተዛንቆ
የቀይ ሴትን ታፋ ዓይንህ በስስ ሰርቆ
በምራቅህ ድርቀት ጉሮሮህ ተጨንቆ
ጠቅሰህ ስትጠራት
ያቺን የሞት ብልቃጥ
ከባቷ ፈልቅቀህ ዕፅዋን ስትቀምሳት
በገላህ ፍሰሀ መቅደስህን ናድካት ።
የቱ ጋር መሰለህ?
የልጅነት ልምድህ
ከሰንበት ቤት ገዳም
ምልልስ ብርታትህ
በዋዛ ሲቀየር
የያሬዱ ወረብ
በእስክስታ ሲዛወር
ስትዘነጋ ፀሎት
ሳይንስ ከእምነት ልቆት
ኒቼ ቦታ ሲወርስ የየኔታን መንበር
የነፍስህ ቁዘማ መንደርደሪያ ነበር።
ትዝ አለህ?
ዘር መራጭ ስትሆን
የደም ሴል መንጣሪ
ጆሮህ ዳባ ሲለብስ
ለፍጥረት እንግልት
ለህፃናት ጥሪ…
መንገድህ ሲሳለጥ
በ V 8 መኪና
ዝርግ አስፓልት ሲመስልህ
ጉርብጥብጥ ጎዳና ፤
ስቆልኛል ስትል ጥርሱን የነከሰ
እንባው አንሸራሽሮህ ጌታ ዘንድ ደረሰ።
ያን ጊዜ ተከፋህ!
ጥሬ እየቆረጥክ ሆድህ ሲመረመር
እስቲም ሳውና ገብተህ ፊትህ ሲጭበረበር
በድሎትህ መኃል
ገላን የሚያኮስስ የእሾህ ስንጥር ነበር።
ትዝ አለህ?
መኝታህ በምቾት ተሞልቶ በአጀብ
እንቅልፍህ ሲናጠብ?
ትዝ አለህ?
በውድ ቀለም ቤቶች ልጆችህ ሲማሩ
ከግብረገብ ታዛ ተናንሰው ሲቀሩ?
ትዝ አለህ?
የጉያህ መልካም ሴት
የአጥንትህ ፍላጭ
‘አሁን ከምን ጊዜው
ሆነችብኝ ምላጭ? ‘
ብለህ ስትቆዝም … ?
እንዲያ ነው አይዋ…
ግፍ ፅዋው ሲሞላ
በትሩን አይመርጥም።
ትዝ አለህ?
ታወሰህ?
የቱ ጋር መሰለህ?
የተፈታው ውሉ
የጎደልክ ከሙሉ
‘ኧረ ስከን’ ሲሉ
ከዕድሜ የተማሩ
የጋሽ ውቤን ምክር
የእመት ጉሌን ዝክር
ረግጠህ ስትበር…
ስትሻገር ፣ ስጥስ
የምስኪናን ድንበር
የዛሬ ውድቀትህ ፣ በግጥም ሊነገር
ክንፍህ የተመታው ይሄን ጊዜ ነበር።
ትዝ አለህ?
አዎን እሱ ጋር ነው!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሚካኤል አስጨናቂ
❤16
#ደቃቃ_ጎልያዶች
ምን ከንቱ ቢመስል ፥ ነገር ሲጀማምር
ንቀህ አትጣለው ፥ በውል ሳትመረምር።
ድራጎን አይደለም ፥ ዳይኖሰር፣ አንበሳ
ቁጭ ብድግ አርጎ ፥ ያሳየን አበሳ።
ባክቴርያና ቫይረስ ፥ ባይን የማናያቸው
የሰው ልጅ ደመኞች ፥ ጥቃቅኖች ናቸው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በርናባስ ከበደ
ምን ከንቱ ቢመስል ፥ ነገር ሲጀማምር
ንቀህ አትጣለው ፥ በውል ሳትመረምር።
ድራጎን አይደለም ፥ ዳይኖሰር፣ አንበሳ
ቁጭ ብድግ አርጎ ፥ ያሳየን አበሳ።
ባክቴርያና ቫይረስ ፥ ባይን የማናያቸው
የሰው ልጅ ደመኞች ፥ ጥቃቅኖች ናቸው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በርናባስ ከበደ
💯13👏7❤3👍3
#በስካር_አይደለም
በየጎዳናው ላይ የሚንገዳገደው፣
እጅ እያወራጨ ለብቻ የሚያወራው፣
እንዴት አደርክ ሲሉት በቃ ዝም !የሚለው፣
በጨዋታ መሐል በሀሳብ የሚነጉደው፣
ለብቻው በማውራት መኪና የሚስተው፣
ጎዳናውን ሞልቶ የሚርመሰመሰው፣
በስካር አይደለም አቅሉን የነቀለ፣
በኑሮ ነው እንጂ ጉልበቱ የዛለ!
በስካርም መዝገብ ስሙ የሰፈረ፣
የከፋው ምስኪን ነው ሳይኖር ያኗኗረ!
ተፋፍሮ ነው እንጂ ያልከበደው የለም፣
በኑሮ ውድነት ሁሉም ነው ሰካራም፣
ስካር ከየት መጥቶ ? ተርፎ ከሚበላ?!!!
ኑሮ ነው አዙሪት ልቆ የተገኘው ከጠጅ ከጠላ!
የእኔ አይነቱ ምስኪን ለእብደት የቀረበው፣
ሰክሮ ነው አትበሉ ኑሮን ተግቶ ነው!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
በየጎዳናው ላይ የሚንገዳገደው፣
እጅ እያወራጨ ለብቻ የሚያወራው፣
እንዴት አደርክ ሲሉት በቃ ዝም !የሚለው፣
በጨዋታ መሐል በሀሳብ የሚነጉደው፣
ለብቻው በማውራት መኪና የሚስተው፣
ጎዳናውን ሞልቶ የሚርመሰመሰው፣
በስካር አይደለም አቅሉን የነቀለ፣
በኑሮ ነው እንጂ ጉልበቱ የዛለ!
በስካርም መዝገብ ስሙ የሰፈረ፣
የከፋው ምስኪን ነው ሳይኖር ያኗኗረ!
ተፋፍሮ ነው እንጂ ያልከበደው የለም፣
በኑሮ ውድነት ሁሉም ነው ሰካራም፣
ስካር ከየት መጥቶ ? ተርፎ ከሚበላ?!!!
ኑሮ ነው አዙሪት ልቆ የተገኘው ከጠጅ ከጠላ!
የእኔ አይነቱ ምስኪን ለእብደት የቀረበው፣
ሰክሮ ነው አትበሉ ኑሮን ተግቶ ነው!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤17👍3😭1
#ማን_ልበልሽ?
የቁንጅና ውበት፣አሟልቶ የሰጠሽ፤
በጥበብ አስጊጦ፣በፁቭ የተሰራሽ፤
ከራስ ፀጉርሽ፣እስከ እግር ጥፍሮችሽ፤
ጠቢባን በውበት፣የተራቀቁብሽ፤
ደራሲው በድርሰት፣ቃላትን አዋዶ፤
ሰዓሊው በብሩ ፣ቀለማት አዋህዶ፤
ገጣሚው በግጥሙ፣ በቃላት ተጠቦ፤
እንደ ጅረት ውሀ፣እውቀትን አዝንቦ፤
በሙዚቃ ዜማ፣ቢገልፅሽ አስውቦ፤
ሊገልፅሽ ቢሞክር፣በድርሰት ከትቦ፤
ሙሉነት ጎደለው፣አንችነትሽ በልጦ፤
በጥበባት ኮከብ፣በደማቅ ተጊጦ፤
ሞናሊዛየ ነሽ፣ዘመን ተሻጋሪ፤
የዳቬንች አርት፣ሁሌ ምታበሪ፤
እንቁ የእግዜር ስራ፣ምትታይ አብበሽ፤
ሚስጢሬ ሆንሽብኝ፣ስምሽን ማን ልበልሽ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
የቁንጅና ውበት፣አሟልቶ የሰጠሽ፤
በጥበብ አስጊጦ፣በፁቭ የተሰራሽ፤
ከራስ ፀጉርሽ፣እስከ እግር ጥፍሮችሽ፤
ጠቢባን በውበት፣የተራቀቁብሽ፤
ደራሲው በድርሰት፣ቃላትን አዋዶ፤
ሰዓሊው በብሩ ፣ቀለማት አዋህዶ፤
ገጣሚው በግጥሙ፣ በቃላት ተጠቦ፤
እንደ ጅረት ውሀ፣እውቀትን አዝንቦ፤
በሙዚቃ ዜማ፣ቢገልፅሽ አስውቦ፤
ሊገልፅሽ ቢሞክር፣በድርሰት ከትቦ፤
ሙሉነት ጎደለው፣አንችነትሽ በልጦ፤
በጥበባት ኮከብ፣በደማቅ ተጊጦ፤
ሞናሊዛየ ነሽ፣ዘመን ተሻጋሪ፤
የዳቬንች አርት፣ሁሌ ምታበሪ፤
እንቁ የእግዜር ስራ፣ምትታይ አብበሽ፤
ሚስጢሬ ሆንሽብኝ፣ስምሽን ማን ልበልሽ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👏12❤6👍3