#ፍቅር_አለቀሰ
ፍቅርን ስፈልገው ቀናቶች አለፉ
ፈለኩት ፈለኩት ድካም ሆነ ትርፉ
አጋጣሚ ሆኖ ተደብቆ አየሁት
አላምን ስላልኩኝ ምክንያቱን ጠየኩት!
ፍቅር አንተ ነህ ወይ? ብየ ብጠይቀው
ምንም መልስ ሳይመልስ እንባ ተናነቀው
ግራ ገባኝና ባግራሞት አየሁት
ቆይ! ፍቅር ደስታ ነው ሲባል ሰምቻለሁ
ታድያ ያንተ ለቅሶ ከየት የመጣ ነው?
ፍቅርም መለሰልኝ አይኑን መሬት ተክሎ
መናገር ጀመረ ቃላትን ቀጣጥሎ
ደስታማ ደስታ ነኝ ላወቀው ሚስጥሬን
ከደስታም በላይ ነኝ ከተረዱኝ እኔን
ያስለቀሰኝ ነገር ሆድ ሆዴን ያባሰው
በኔ ስም መነገድ መች አቆመ ሰው
አፈቀርኩሺ ብሎ ሲዋሻት በኔ ስም
ማሬ ውዴ ብላ ከድታው ስቴድ እሷም
በኔ ሲጫወቱ የሀሰት ጨዋታ
በኔ ሲባልጉ በኔ ስም ሲምታታ
በውሼት አለም ሆነው በኔ ስም ሲጠሩ
እንደት አላነባ? ካልረባ ነገሩ!
ብሎ መለሰልኝ ፍቅር በቀስታ
አንገቱን ቢያስደፋው የሀሰት ጨዋታ!
በፍቅር አስኪ አሁን መቀለድ ይብቃ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ፍቅርን ስፈልገው ቀናቶች አለፉ
ፈለኩት ፈለኩት ድካም ሆነ ትርፉ
አጋጣሚ ሆኖ ተደብቆ አየሁት
አላምን ስላልኩኝ ምክንያቱን ጠየኩት!
ፍቅር አንተ ነህ ወይ? ብየ ብጠይቀው
ምንም መልስ ሳይመልስ እንባ ተናነቀው
ግራ ገባኝና ባግራሞት አየሁት
ቆይ! ፍቅር ደስታ ነው ሲባል ሰምቻለሁ
ታድያ ያንተ ለቅሶ ከየት የመጣ ነው?
ፍቅርም መለሰልኝ አይኑን መሬት ተክሎ
መናገር ጀመረ ቃላትን ቀጣጥሎ
ደስታማ ደስታ ነኝ ላወቀው ሚስጥሬን
ከደስታም በላይ ነኝ ከተረዱኝ እኔን
ያስለቀሰኝ ነገር ሆድ ሆዴን ያባሰው
በኔ ስም መነገድ መች አቆመ ሰው
አፈቀርኩሺ ብሎ ሲዋሻት በኔ ስም
ማሬ ውዴ ብላ ከድታው ስቴድ እሷም
በኔ ሲጫወቱ የሀሰት ጨዋታ
በኔ ሲባልጉ በኔ ስም ሲምታታ
በውሼት አለም ሆነው በኔ ስም ሲጠሩ
እንደት አላነባ? ካልረባ ነገሩ!
ብሎ መለሰልኝ ፍቅር በቀስታ
አንገቱን ቢያስደፋው የሀሰት ጨዋታ!
በፍቅር አስኪ አሁን መቀለድ ይብቃ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤13👍2
#መልክአ_ሕይወት
ቧልትን ከፈገግታ
ሳቅን ከፌዝ ጋራ
ባንድ ላይ ቀይጠን፥
አቅልመን በጥብጠን
በሐዘን ባሕር ላይ ፥ ብናንቆረቁርም
ባሕሩ ሰፊ ነው፤ መልኩን አይቀይርም::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ቧልትን ከፈገግታ
ሳቅን ከፌዝ ጋራ
ባንድ ላይ ቀይጠን፥
አቅልመን በጥብጠን
በሐዘን ባሕር ላይ ፥ ብናንቆረቁርም
ባሕሩ ሰፊ ነው፤ መልኩን አይቀይርም::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
👍13❤6🔥1
#እንዴት_ይሆን_ፍርድሽ?
ጥቂት ታገሽ ሆዴ መንገዱን አሳብረሽ
ማዶ ማዶ እያየሽ
ብቻ ተስፋ አትቁረጭ ቁጭብለሽ ጠብቂኝ
እንዳትሄጅ ተናደሽ
እርሜን አረፈድኩኝ አንድ መሪ መ'ቶ
መንገድ ተዘጋግቶ
ወደዚ ሂድ ሲሉት ወደዛ ተመለስ
ህዝቤ ተሰላችቶ
ተስፋ ቆርጦ ሳለ
እኔ ግን የኔ ማር ካንቺ ተቃጥሬ
እንዴት እቀራለው ልሂድ ብዬ በግሬ
እየመጣሁኝ ነው ፍቅርሽ ጉልበት ሆኖኝ
ለመድረስ አንቺጋ
አይንሽን ካላየሁ ነብሴም እረፍት የላት
መንፈሴም አትረጋ
አይዞሽ የኔ ቆንጆ አልቀርም አልቀርም
ጥቂት እንደሮጥኩኝ
ቁሙ ባላቹበት ተብለን ብንቆምም
ልቤ እየሮጠች ነው በፍፁም አታርፍም
አቤት ክፉ ጊዜ አይ የቀን ጎዶሎ
ባልጠበቅነው መንገድ ባላሰብነው ውሎ
ደውዬ እንዳልነግርሽ ተዘግቷል ኔትዎርኩ
አልበር እንዳሞራ ለዚህ አልታደልኩ
አወይ የኔ ፍቅር ለጠባቂ ሴኮንድ
ከሰአት በላይ ነው ይህንን አውቃለው
ደቂቃ ዘግይተሽ በቀናት አስልቼም
ተቆጥቼሻለው
ብቻ የኔ አበባ
ምን አሰበ ይሆን ምን ወሰነ ልብሽ ?
ለጠዋት ቀጠሮ ማታም ሳልደርስልሽ
በቃሽ የኔ ነገር ? ጠላሺኝ ወዳጄ
እንዴት ይሆን ፍርድሽ
ለቀረሁ ታግጄ ???
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ጥቂት ታገሽ ሆዴ መንገዱን አሳብረሽ
ማዶ ማዶ እያየሽ
ብቻ ተስፋ አትቁረጭ ቁጭብለሽ ጠብቂኝ
እንዳትሄጅ ተናደሽ
እርሜን አረፈድኩኝ አንድ መሪ መ'ቶ
መንገድ ተዘጋግቶ
ወደዚ ሂድ ሲሉት ወደዛ ተመለስ
ህዝቤ ተሰላችቶ
ተስፋ ቆርጦ ሳለ
እኔ ግን የኔ ማር ካንቺ ተቃጥሬ
እንዴት እቀራለው ልሂድ ብዬ በግሬ
እየመጣሁኝ ነው ፍቅርሽ ጉልበት ሆኖኝ
ለመድረስ አንቺጋ
አይንሽን ካላየሁ ነብሴም እረፍት የላት
መንፈሴም አትረጋ
አይዞሽ የኔ ቆንጆ አልቀርም አልቀርም
ጥቂት እንደሮጥኩኝ
ቁሙ ባላቹበት ተብለን ብንቆምም
ልቤ እየሮጠች ነው በፍፁም አታርፍም
አቤት ክፉ ጊዜ አይ የቀን ጎዶሎ
ባልጠበቅነው መንገድ ባላሰብነው ውሎ
ደውዬ እንዳልነግርሽ ተዘግቷል ኔትዎርኩ
አልበር እንዳሞራ ለዚህ አልታደልኩ
አወይ የኔ ፍቅር ለጠባቂ ሴኮንድ
ከሰአት በላይ ነው ይህንን አውቃለው
ደቂቃ ዘግይተሽ በቀናት አስልቼም
ተቆጥቼሻለው
ብቻ የኔ አበባ
ምን አሰበ ይሆን ምን ወሰነ ልብሽ ?
ለጠዋት ቀጠሮ ማታም ሳልደርስልሽ
በቃሽ የኔ ነገር ? ጠላሺኝ ወዳጄ
እንዴት ይሆን ፍርድሽ
ለቀረሁ ታግጄ ???
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤13😢7👍3
#አንድ_እንባ_ለሁለት_ስሜት
ለሀዘን ለደስታ
የእንባ ቋጠሮ ሲፈታ
ከሁለት አይኖች ለሁለት ስሜት
ለማዘን ወይ ለመደሰት
በሳቅ ታጅቦ ወይም በለቅሶ
በመንታ ጉንጮች ቁልቁል ፈስሶ
ለመለያየት
ለመገናኘት
ብሶት ለመግለጽ ወይ ደስታ
በሁለት ስሜት የሚምታታ
እንባ አንድ ነው ግን ሁለት ስሜት
በሀዘንም በደስታም " ና " ብለው የሚጠሩት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ለሀዘን ለደስታ
የእንባ ቋጠሮ ሲፈታ
ከሁለት አይኖች ለሁለት ስሜት
ለማዘን ወይ ለመደሰት
በሳቅ ታጅቦ ወይም በለቅሶ
በመንታ ጉንጮች ቁልቁል ፈስሶ
ለመለያየት
ለመገናኘት
ብሶት ለመግለጽ ወይ ደስታ
በሁለት ስሜት የሚምታታ
እንባ አንድ ነው ግን ሁለት ስሜት
በሀዘንም በደስታም " ና " ብለው የሚጠሩት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍11❤9
በሔድክበት መንገድ
አይኔን ጣል አድርጌ
በትዝታ መርከብ
በሀሳብ ቀዝፌ
አተን እያሰብኩኝ ጉጬን ተደግፌ
እየጠበኩህ ነው
ትዛለህ ?
ትተኸኝ ስትሔድ
እዳትከተይኝ
ደግመሽ እዳትመጪ በሔድኩበት መንገድ
ብለኸኝ ስትሔድ
ስላስጠነከከኝ እዳልከተልህ
አሳስቶኝ እኳን ዞሬም እዳላይህ
ቃልህን አክብሬ አልተከተልኩህም
ባለህበት ቦታ ፍፁም አልመጣሁም
ነገር ግን እጠብቅሀለሁ
አለሁኝ እዛው ነኝ
እጠብቅሀለሁ ሳልሆን እራስ ወዳድ
ምናልባት ከመጣህ በሔድክበት መንገድ
አይኔን ጣል አድርጌ
በትዝታ መርከብ
በሀሳብ ቀዝፌ
አተን እያሰብኩኝ ጉጬን ተደግፌ
እጠብቅሀለሁ
በትዝታ መርከብ በሀሳብ ቀዝፌ
እየጠበኩህ ነው ጉጬን ተደግፌ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
አይኔን ጣል አድርጌ
በትዝታ መርከብ
በሀሳብ ቀዝፌ
አተን እያሰብኩኝ ጉጬን ተደግፌ
እየጠበኩህ ነው
ትዛለህ ?
ትተኸኝ ስትሔድ
እዳትከተይኝ
ደግመሽ እዳትመጪ በሔድኩበት መንገድ
ብለኸኝ ስትሔድ
ስላስጠነከከኝ እዳልከተልህ
አሳስቶኝ እኳን ዞሬም እዳላይህ
ቃልህን አክብሬ አልተከተልኩህም
ባለህበት ቦታ ፍፁም አልመጣሁም
ነገር ግን እጠብቅሀለሁ
አለሁኝ እዛው ነኝ
እጠብቅሀለሁ ሳልሆን እራስ ወዳድ
ምናልባት ከመጣህ በሔድክበት መንገድ
አይኔን ጣል አድርጌ
በትዝታ መርከብ
በሀሳብ ቀዝፌ
አተን እያሰብኩኝ ጉጬን ተደግፌ
እጠብቅሀለሁ
በትዝታ መርከብ በሀሳብ ቀዝፌ
እየጠበኩህ ነው ጉጬን ተደግፌ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍14❤5
#ሀዘኑ_መች_ጠፋ!!!
ማልቀስ አምሮኝ ነበር እንባ ከየት መጥቶ
ሐዘን በልቤ ውስጥ ተርፎ ተከማችቶ
ከዚህ ሁሉ ሀዘን በዝቶ ከተረፈው
አንዲት ጠብታ እንባ ይቸግረዋል ሰው
እባክህ እንባዬ መንታ ሆነህ ፍሰስ
የታመቀው ውስጤ በጥቂት ይተንፍስ
ሀዘኑ መች ጠፋ ከልባችን ጓዳ
የራቀን ዘንድሮ እንባችን ነው ባዳ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ማልቀስ አምሮኝ ነበር እንባ ከየት መጥቶ
ሐዘን በልቤ ውስጥ ተርፎ ተከማችቶ
ከዚህ ሁሉ ሀዘን በዝቶ ከተረፈው
አንዲት ጠብታ እንባ ይቸግረዋል ሰው
እባክህ እንባዬ መንታ ሆነህ ፍሰስ
የታመቀው ውስጤ በጥቂት ይተንፍስ
ሀዘኑ መች ጠፋ ከልባችን ጓዳ
የራቀን ዘንድሮ እንባችን ነው ባዳ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤19💔10👍1
#ውሻ_ነበር_ያልሽኝ?
ቃል ኪዳን ጠብቄ ለእምነቴ መኖሬን፣
ከራሴ ሰስቼ ላንች መታመኔን፣
ስትመሰክሪልኝ......!
አቻ በሌላቸው በሁለት ቃላቶች፣
ስሜን ከፍ አ'ረግሽው ውሻ ብለሽ ጠርተሽ።
ላንች ውሻ ማለት ስድብ ቢመስልሽም፣
ማክበር እንደሆነ ፈፅሞ አልገባሽም።
አዎ እኔ ውሻ ነኝ........!
ጊዜ አይቼ ምቀርብ ድመት አይደለሁም፣
ለመጣ ለሄደው ጅራቴን አልቆላም።
ቀዘቀዘ ብዬ ቤቴን አልቀይርም፣
ሲሰጡኝ ወድጄ ሲነሱኝ አልጠላም።
አዎ እኔ ውሻ ነኝ...........።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ቃል ኪዳን ጠብቄ ለእምነቴ መኖሬን፣
ከራሴ ሰስቼ ላንች መታመኔን፣
ስትመሰክሪልኝ......!
አቻ በሌላቸው በሁለት ቃላቶች፣
ስሜን ከፍ አ'ረግሽው ውሻ ብለሽ ጠርተሽ።
ላንች ውሻ ማለት ስድብ ቢመስልሽም፣
ማክበር እንደሆነ ፈፅሞ አልገባሽም።
አዎ እኔ ውሻ ነኝ........!
ጊዜ አይቼ ምቀርብ ድመት አይደለሁም፣
ለመጣ ለሄደው ጅራቴን አልቆላም።
ቀዘቀዘ ብዬ ቤቴን አልቀይርም፣
ሲሰጡኝ ወድጄ ሲነሱኝ አልጠላም።
አዎ እኔ ውሻ ነኝ...........።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤11👏9🥰2
#ወዴት_ተሰወሩ?
በሳቃችን ዘመን አብረውን የሳቁ፣
ከእናንተ ውጪ ብለው ትላንት ያደነቁ፣
ሳቃችን ሲጠፋ መከራችን ነግሶ፣
በእህ! እህ! ሲተካ በሀዘን በለቅሶ፣
ወዴት ተሰወሩ? ምንስ ከለላቸው?
የትኛው ተራራ የትኛውስ እርቀት
ገዝፎ ጋረዳቸው ?
በዙሪያችን ከበው በክብር ሸልመው፣
በንግግራችን ፣ በማያስቅ ስቀው!
ለጥቅማቸው ሲሉ ትላንት ያገጠጡ
መካራ ሲገጥመን ወዴት? ፈረጠጡ?!
የሉም፣ አይታዩም! ምን ጉድጓድ ዋጣቸው?!
የትኛውስ እርቀት ከእኛ ሰውራቸው?
የሉም! የሉም! በቃ ዛሬ የሉም!
ሳቃችን ከጠፋ ከቶ አይመለሱም!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
በሳቃችን ዘመን አብረውን የሳቁ፣
ከእናንተ ውጪ ብለው ትላንት ያደነቁ፣
ሳቃችን ሲጠፋ መከራችን ነግሶ፣
በእህ! እህ! ሲተካ በሀዘን በለቅሶ፣
ወዴት ተሰወሩ? ምንስ ከለላቸው?
የትኛው ተራራ የትኛውስ እርቀት
ገዝፎ ጋረዳቸው ?
በዙሪያችን ከበው በክብር ሸልመው፣
በንግግራችን ፣ በማያስቅ ስቀው!
ለጥቅማቸው ሲሉ ትላንት ያገጠጡ
መካራ ሲገጥመን ወዴት? ፈረጠጡ?!
የሉም፣ አይታዩም! ምን ጉድጓድ ዋጣቸው?!
የትኛውስ እርቀት ከእኛ ሰውራቸው?
የሉም! የሉም! በቃ ዛሬ የሉም!
ሳቃችን ከጠፋ ከቶ አይመለሱም!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤10👍9💔4
#ልቤን_መልስልኝ
ልትሄድ ከሆነ ላይቀር መለየቱ
ቢበቃኝ ይሻላል ባንተ መጎዳቱ።
ቀልብህ ካላረፈ እግረኛ ሆነህ
መጓዝህ ካልቀረ ከእኔ መራቅህ
ለምን አስፈለገ ልቤን መስረቅህ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ልትሄድ ከሆነ ላይቀር መለየቱ
ቢበቃኝ ይሻላል ባንተ መጎዳቱ።
ቀልብህ ካላረፈ እግረኛ ሆነህ
መጓዝህ ካልቀረ ከእኔ መራቅህ
ለምን አስፈለገ ልቤን መስረቅህ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
🔥14❤9
#አንተም_እኔም_ተጓዥ
አትግፋኝ ወንድሜ ፣ በከንቱ ጥላቻ፤
ለየትኛው እድሜ ? እንኑር በጡንቻ?
ለኮንትራት ዓለም ፣ ባለቤት ለሌላት፤
ከፍቅር ቀንሰን የምን? መገፋፋት ?
አንተም እኔም ተጓዥ ፣ በተራ ለጣቂ፤
ማን እንደሚቀድም ፣ አምላክ ነው አዋቂ ።
ስትገፋኝ ስገፋህ ፣ አንዱ ላያሸንፍ፤
መጓተት ብቻ ነው ፣ ሌላ የለንም ትርፍ ።
ለፍቅርም አይበቃ ፣ የተሰጠን አድሜ፤
እኔም ነኝ ወንድምህ ፣ አንተም ነህ ወንድሜ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
አትግፋኝ ወንድሜ ፣ በከንቱ ጥላቻ፤
ለየትኛው እድሜ ? እንኑር በጡንቻ?
ለኮንትራት ዓለም ፣ ባለቤት ለሌላት፤
ከፍቅር ቀንሰን የምን? መገፋፋት ?
አንተም እኔም ተጓዥ ፣ በተራ ለጣቂ፤
ማን እንደሚቀድም ፣ አምላክ ነው አዋቂ ።
ስትገፋኝ ስገፋህ ፣ አንዱ ላያሸንፍ፤
መጓተት ብቻ ነው ፣ ሌላ የለንም ትርፍ ።
ለፍቅርም አይበቃ ፣ የተሰጠን አድሜ፤
እኔም ነኝ ወንድምህ ፣ አንተም ነህ ወንድሜ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍14❤8
#ቃና....
ከዉበት እስረኞች...
ጥቁር ፍቅር ይዞኝ
በንስር አይኖቼ...
ፍለጋ ጀመርኩኝ
የጠፋዉን ስሜን...
ልመልስ አልኩና
ማጣጣም ስጀምር..
የህይወቴን ቃና
ለኔ ወጥመድ ሁነዉ...
ዛራና ቻንድራ
ሚስቴ ጋር አጣሉኝ...
ማን ያቅርብ እንጀራ.....
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ከዉበት እስረኞች...
ጥቁር ፍቅር ይዞኝ
በንስር አይኖቼ...
ፍለጋ ጀመርኩኝ
የጠፋዉን ስሜን...
ልመልስ አልኩና
ማጣጣም ስጀምር..
የህይወቴን ቃና
ለኔ ወጥመድ ሁነዉ...
ዛራና ቻንድራ
ሚስቴ ጋር አጣሉኝ...
ማን ያቅርብ እንጀራ.....
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤26😁14👍2😱2🥰1
❤16🥰2
#ቢታነፅ_ቢወቀር!
እኔም አንድ ሰሞን
ልክ እንደ ሰለሞን
"ሁሉም ከንቱ ከንቱ ንፋስን መከተል
ላይጥሉ መታገል: ላይከብሩ መባተል"
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ: እፈላሰፍ ነበር!
ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጓሮ በር በኩል: ሰለሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ንፋስ አሳድጄ እንደ ቆቅ አጠመድሁ
ከፀሀይዋ በታች: ግልገል ፀሀይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ: ብርሀን አበደርሁ
ማቅ የነበረው ጨርቅ: ሸማ ሆኖ ቆየኝ
"ከንቱ የነበረው: "አንቱ" ሆኖ ታየኝ!
ለካስ...
ጠቢብ ቢያስተምረው
መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ: ቢታነፅ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም: ካልወደደ በቀር!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
እኔም አንድ ሰሞን
ልክ እንደ ሰለሞን
"ሁሉም ከንቱ ከንቱ ንፋስን መከተል
ላይጥሉ መታገል: ላይከብሩ መባተል"
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ: እፈላሰፍ ነበር!
ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጓሮ በር በኩል: ሰለሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ንፋስ አሳድጄ እንደ ቆቅ አጠመድሁ
ከፀሀይዋ በታች: ግልገል ፀሀይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ: ብርሀን አበደርሁ
ማቅ የነበረው ጨርቅ: ሸማ ሆኖ ቆየኝ
"ከንቱ የነበረው: "አንቱ" ሆኖ ታየኝ!
ለካስ...
ጠቢብ ቢያስተምረው
መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ: ቢታነፅ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም: ካልወደደ በቀር!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤16🥰6🔥1👏1
#ስጠብቅሽ_ልኑር!
ቀናቶች ቢረዝሙ ቢቆጠሩ አመታት
ግዜ ቢለያየን ቢያልፉብን ዘመናት
ከልብሽ ባልጠፋም ከትዉስታሽ ጓዳ
በስቃይ ታስሬ በናፍቆት ጎዳና
ህልሜም ባይሳካ የሆዴን ባላገኝ
በደስታየ ዘመን ባይተዋር ቢያረገኝ
ግዴለም ችላለሁ ሁሉን ነገር ችዬ
እጠብቅሻለሁ ልቤን አባብየ
የሀሳብ በረዶ ይጥለቅ በአናቴ
ይደንዝዝ አካሌ ይድከሙ ጉልበቴ
አንገናኛለን እያልኩ በተስፋ ልጠብቅ
እልፍ ግዜ ይለፍ ወዜ ሁሉ ይድቀቅ
ምን ያደርግልኛል ካንች ወድያ ንሮ
ፍቅርሽ ይበቃኛል የስንቅሽ ቋጠሮ
በትዝታሽ ዋሻ እራሴን ደብቄ
በምናቤ ስየ ፍቅርሽን ሰንቄ
እጠብቅሻለሁ በተሰጠኝ እድሜ
ባንች ናፍቆት ፍቅር ካልሞትኩኝ ታምሜ
አዎ...ስጠብቅሽ ልኑር ሳለሁ በህይዎቴ
ፍቅርም ባንች ይብቃኝ ይምከን ፍላጎቴ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ቀናቶች ቢረዝሙ ቢቆጠሩ አመታት
ግዜ ቢለያየን ቢያልፉብን ዘመናት
ከልብሽ ባልጠፋም ከትዉስታሽ ጓዳ
በስቃይ ታስሬ በናፍቆት ጎዳና
ህልሜም ባይሳካ የሆዴን ባላገኝ
በደስታየ ዘመን ባይተዋር ቢያረገኝ
ግዴለም ችላለሁ ሁሉን ነገር ችዬ
እጠብቅሻለሁ ልቤን አባብየ
የሀሳብ በረዶ ይጥለቅ በአናቴ
ይደንዝዝ አካሌ ይድከሙ ጉልበቴ
አንገናኛለን እያልኩ በተስፋ ልጠብቅ
እልፍ ግዜ ይለፍ ወዜ ሁሉ ይድቀቅ
ምን ያደርግልኛል ካንች ወድያ ንሮ
ፍቅርሽ ይበቃኛል የስንቅሽ ቋጠሮ
በትዝታሽ ዋሻ እራሴን ደብቄ
በምናቤ ስየ ፍቅርሽን ሰንቄ
እጠብቅሻለሁ በተሰጠኝ እድሜ
ባንች ናፍቆት ፍቅር ካልሞትኩኝ ታምሜ
አዎ...ስጠብቅሽ ልኑር ሳለሁ በህይዎቴ
ፍቅርም ባንች ይብቃኝ ይምከን ፍላጎቴ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤16👍1
#መጪውን_ማን_አውቆ?!
የኖረውን እንጂ ፣ የፊቱን ማን? አውቆ?
እድሜው ላይ፣ ጨመር አብዝቶ ተጨንቆ?
በአለፍነው ካልሆነ ፣ ህይወት የሚለካ፤
የመጪው ባለቤት ፣ እግዚአብሔር ነው ለካ፤
ትላንትን ተሻግሮ ፣ ዛሬን በእጁ ይዞ፤
የእርሱ ባልሆነ ነገ ፣ ያለቅጥ ተክዞ፤
የሚጨናነቀው ፣ ሰው በከንቱ እርቆ ፣
ያለፈውን እንጂ ፤ መጪውን ማን አውቆ?
እንኳንስ ዓመታት ፣ አልፎ ለመገመት ፤
የፈት ለፊት ነገ ፣ የእኛ አይደለም ህይወት ፤
እናም ልቤ አስተውል ፣ በዛሬ ላይ ትጋ፤
ከትላንት ተምረህ ፣ በአምላክ ሀሳብ እርጋ፤
ነገማ ማን አውቆ ፣ መድረሻውን ቆጥሮ፤
ከአምላኩ በስተቀር ፣ ዛሬውን ተሻግሮ ?
እንኳን ዓመታቱን ፣ እሩቅ! ቀድሞ ማየት ፤
በእግዚአብሔር እጅ ነው ፣ የዛሬው ሰአታት!
በከንቱ መጨነቅ ፣ ልባችን ታውሮ ፤
ዛሬያችን ከነፈ ፣ ትላንት ሆኖ በሮ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
የኖረውን እንጂ ፣ የፊቱን ማን? አውቆ?
እድሜው ላይ፣ ጨመር አብዝቶ ተጨንቆ?
በአለፍነው ካልሆነ ፣ ህይወት የሚለካ፤
የመጪው ባለቤት ፣ እግዚአብሔር ነው ለካ፤
ትላንትን ተሻግሮ ፣ ዛሬን በእጁ ይዞ፤
የእርሱ ባልሆነ ነገ ፣ ያለቅጥ ተክዞ፤
የሚጨናነቀው ፣ ሰው በከንቱ እርቆ ፣
ያለፈውን እንጂ ፤ መጪውን ማን አውቆ?
እንኳንስ ዓመታት ፣ አልፎ ለመገመት ፤
የፈት ለፊት ነገ ፣ የእኛ አይደለም ህይወት ፤
እናም ልቤ አስተውል ፣ በዛሬ ላይ ትጋ፤
ከትላንት ተምረህ ፣ በአምላክ ሀሳብ እርጋ፤
ነገማ ማን አውቆ ፣ መድረሻውን ቆጥሮ፤
ከአምላኩ በስተቀር ፣ ዛሬውን ተሻግሮ ?
እንኳን ዓመታቱን ፣ እሩቅ! ቀድሞ ማየት ፤
በእግዚአብሔር እጅ ነው ፣ የዛሬው ሰአታት!
በከንቱ መጨነቅ ፣ ልባችን ታውሮ ፤
ዛሬያችን ከነፈ ፣ ትላንት ሆኖ በሮ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤14👍2
#አድገናል ¡
የዘንድሮ ኑሮ ውሉም አልተያዘኝ፤
እንዴት እንዳደግነ መለኪያው አልገባኝ፤
ብቻ ግን አድገናል፤
በሁለት ዲጅት ወደ ላይ መጥቀናል¡፤
እቤታችን ድረስ ትቦ ተዘርግቷል፤
መብራት ገብቶልናል፤
ሲምም ተሰጦናል፤
ግና ውሀ የለም አንፖሉም አልበራ፤
ባዶ "ሲም" ነው እንጅ "ኔትወርኩም" አልሰራ፤
ብቻ ግን አድገናል፤
በሁለት "ዲጅት" ወደላይ መጥቀናል፤
አፍ ቀላጤ ፈርተን ሳናምነው አምነናል፤
ይህ ነው እድገታችን?፤
በሁለት ዲጅት ላይ ላይ መውጣታችን?፤
እኛም እንጮሀለን፤
እናስተጋባለን፤
ሀሰት እየሰማን አሜን እንላለን፤
እኔን እንደገባኝ....
ወደላይ ወደላይ ወደላይ መለፈፍ፤
ፍሬ ማያፈራው አበባው እስኪረግፍ፤
መና ካምላካችን ወድቆ እስኪዘረገፍ፤
ዝም አለማለት ነው መጮህ ነው ወደላይ፤
መብራቱ፣ ኔትወርኩ ውሃው የሞላላት ኢትዬጵያን እስክናይ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
የዘንድሮ ኑሮ ውሉም አልተያዘኝ፤
እንዴት እንዳደግነ መለኪያው አልገባኝ፤
ብቻ ግን አድገናል፤
በሁለት ዲጅት ወደ ላይ መጥቀናል¡፤
እቤታችን ድረስ ትቦ ተዘርግቷል፤
መብራት ገብቶልናል፤
ሲምም ተሰጦናል፤
ግና ውሀ የለም አንፖሉም አልበራ፤
ባዶ "ሲም" ነው እንጅ "ኔትወርኩም" አልሰራ፤
ብቻ ግን አድገናል፤
በሁለት "ዲጅት" ወደላይ መጥቀናል፤
አፍ ቀላጤ ፈርተን ሳናምነው አምነናል፤
ይህ ነው እድገታችን?፤
በሁለት ዲጅት ላይ ላይ መውጣታችን?፤
እኛም እንጮሀለን፤
እናስተጋባለን፤
ሀሰት እየሰማን አሜን እንላለን፤
እኔን እንደገባኝ....
ወደላይ ወደላይ ወደላይ መለፈፍ፤
ፍሬ ማያፈራው አበባው እስኪረግፍ፤
መና ካምላካችን ወድቆ እስኪዘረገፍ፤
ዝም አለማለት ነው መጮህ ነው ወደላይ፤
መብራቱ፣ ኔትወርኩ ውሃው የሞላላት ኢትዬጵያን እስክናይ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍12❤7
#ተመልሼ_አልመጣም
ከወንጌል ቃል ሁሉ እግዜር ካስተማረው
ነብስያዬን ገዝቶ ቀልቤን የማረከው
ከልቡ የሆነ ይድናል የሚለው !!
ምክንያቱም አለሜ ምክንያቱም ህመሜ
የእውነትን ካልኖርኩ እኔ አልድንም ፆሜ
ፀሎትም አይሰምር አይፈይድም ስግደት
ሰደቃም አያርግ ይስሙላ ካለበት
እናልሽ አለሜ
ከወንጌል ቃል ሁሉ እግዜር ካስተማረው
ነብስያዬን ገዝቶ ቀልቤን የማረከው
ከልቡ የሆነ ይድናል የሚለው!!!
ስለዚህ መሻትሽ ከልብሽ ከሆነ
በፍቅራችን ቅጠል አንቺም ትድኛለሽ የኔም ነብስ ዳነ!!
ግና ነብስያዬን ፍፁም ካልወደድሻት
ውዴ ቀረሽብኝ አንቺም ቀረሽባት!
ደግሞ ካንቺ እርቄ ከሸሸሁኝ በጣም
ውዴ ካለሽበት ተመልሼ አልመጣም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዳዊት ጥዑማይ
ከወንጌል ቃል ሁሉ እግዜር ካስተማረው
ነብስያዬን ገዝቶ ቀልቤን የማረከው
ከልቡ የሆነ ይድናል የሚለው !!
ምክንያቱም አለሜ ምክንያቱም ህመሜ
የእውነትን ካልኖርኩ እኔ አልድንም ፆሜ
ፀሎትም አይሰምር አይፈይድም ስግደት
ሰደቃም አያርግ ይስሙላ ካለበት
እናልሽ አለሜ
ከወንጌል ቃል ሁሉ እግዜር ካስተማረው
ነብስያዬን ገዝቶ ቀልቤን የማረከው
ከልቡ የሆነ ይድናል የሚለው!!!
ስለዚህ መሻትሽ ከልብሽ ከሆነ
በፍቅራችን ቅጠል አንቺም ትድኛለሽ የኔም ነብስ ዳነ!!
ግና ነብስያዬን ፍፁም ካልወደድሻት
ውዴ ቀረሽብኝ አንቺም ቀረሽባት!
ደግሞ ካንቺ እርቄ ከሸሸሁኝ በጣም
ውዴ ካለሽበት ተመልሼ አልመጣም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዳዊት ጥዑማይ
❤6🥰4👍2
ያለቀኔ አፍቅሬሽ፥ ገፍተሽኝ ሄደሻል፣
አቻሽን ፍለጋ፥ ብዙ ተጉዘሻል፤
መቼም አይሰምርልሽ፥ልብ ሰብረሽ ሄደሽ፣
ምንጊዜ ቢረዝም፥ አይቀር መመለስሽ፣
ብዬሽ እንደነበር፥ ቆየሁ ስጠብቅሽ።
ባ'ይኔ ላይ ተስለሽ፥ ዓመታት አልፈዋል፣
በልቤ እንደታተምሽ፥ ልጅነት ኰብልሏል።
ባልተሳካው መሻት፥ በዛለው መንፈስሽ፣
ዓይንሽን ስትገልጪ፥ እርቃን ቀርታ ነፍስሽ፤
ክፍቱን እንደተውሽው፥ ቤቴን አግኝተሻል፣
ስጠብቅሽ ነበር፥ ለ'ኔ ግን ረፍዷል።
መምጫ መንገድሽን ሲያይ፥ ሲባጅ የከረመው፣
በሰለለ ተስፋ፥ ታስሮልሽ የኖረው፤
ማፍቀሩን ሳይቀንስ፥ አንቺን በጠበቀ፣
ናፍቆትሽ ያሳሳው፥ የኔ ገላ አለቀ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
አቻሽን ፍለጋ፥ ብዙ ተጉዘሻል፤
መቼም አይሰምርልሽ፥ልብ ሰብረሽ ሄደሽ፣
ምንጊዜ ቢረዝም፥ አይቀር መመለስሽ፣
ብዬሽ እንደነበር፥ ቆየሁ ስጠብቅሽ።
ባ'ይኔ ላይ ተስለሽ፥ ዓመታት አልፈዋል፣
በልቤ እንደታተምሽ፥ ልጅነት ኰብልሏል።
ባልተሳካው መሻት፥ በዛለው መንፈስሽ፣
ዓይንሽን ስትገልጪ፥ እርቃን ቀርታ ነፍስሽ፤
ክፍቱን እንደተውሽው፥ ቤቴን አግኝተሻል፣
ስጠብቅሽ ነበር፥ ለ'ኔ ግን ረፍዷል።
መምጫ መንገድሽን ሲያይ፥ ሲባጅ የከረመው፣
በሰለለ ተስፋ፥ ታስሮልሽ የኖረው፤
ማፍቀሩን ሳይቀንስ፥ አንቺን በጠበቀ፣
ናፍቆትሽ ያሳሳው፥ የኔ ገላ አለቀ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍9❤1
#መንደር_ላይ_አትከክ!!!
አንተ ብቻ ጽና ፣ በሀገር ውሃ ልክ፤
ወርደህ በዝቅታ፣ መንደር ላይ አትከክ!
በሰውኛ ሚዛን ፣ በእውነት ስሌት ትጋ!
ሀገር ከማይጠቅም ፣ በደቦ አትንጋጋ!
ሰፋ! ብለህ ብረር ! በከፍታ! ሀሳብ ፤
በግፊያው መሀከል ገብተህ አትጣበብ!
በዛሬ ግርግር ፣ ነገን አታበላሽ ፤
በሰውኛ ፈረስ ፣ ሁን ለብቻ ገስጋሽ!
ትውልዱ ሲነቃ ፣ በእውነት ተቀስቅሶ፤
መጠየቅ ሲጀምር ፣ ታሪክን አጣቅሶ፤
ያኔ! አንተ ኮራ በል ፣ ሌላው ሲሸማቀቅ፤
በሀገርህ ምድር ፣ ሰንደቅ ሆነህ ድመቅ!
ከፍ! በል! ለነገ ፣ በአዲስ ህብረ ቅኔ!
ይኸን ነው ዛሬ ላይ ፣ የምመክርህ እኔ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
አንተ ብቻ ጽና ፣ በሀገር ውሃ ልክ፤
ወርደህ በዝቅታ፣ መንደር ላይ አትከክ!
በሰውኛ ሚዛን ፣ በእውነት ስሌት ትጋ!
ሀገር ከማይጠቅም ፣ በደቦ አትንጋጋ!
ሰፋ! ብለህ ብረር ! በከፍታ! ሀሳብ ፤
በግፊያው መሀከል ገብተህ አትጣበብ!
በዛሬ ግርግር ፣ ነገን አታበላሽ ፤
በሰውኛ ፈረስ ፣ ሁን ለብቻ ገስጋሽ!
ትውልዱ ሲነቃ ፣ በእውነት ተቀስቅሶ፤
መጠየቅ ሲጀምር ፣ ታሪክን አጣቅሶ፤
ያኔ! አንተ ኮራ በል ፣ ሌላው ሲሸማቀቅ፤
በሀገርህ ምድር ፣ ሰንደቅ ሆነህ ድመቅ!
ከፍ! በል! ለነገ ፣ በአዲስ ህብረ ቅኔ!
ይኸን ነው ዛሬ ላይ ፣ የምመክርህ እኔ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤12👏2🔥1
#በቃልሽ_ታስሬ
የልቤ ላይ ንግስት አንቺ ውቧ ፍቅሬ
ቀናትን በመቁጠር ወራትን ደምሬ
ከጎንሽ ባልሆንም ከአንቺው ጋር አብሬ
በፍቅርሽ ሰንሰለት በፅናት ታስሬ
አሜን ይሁን ብዬ ቃልሽን አክብሬ
ለልቤ ትርታ ለደም ዝውውሬ
ለመንፈሴ እርካታ ብታመም ዶክተሬ
ደስታን ለማጣጣም ፍቅርሽን ዘምሬ
እስትንፋሴ ነብሴ ሆነሽ ለእኔ ጤና
ለመኖሬ ትርጉም የሂወቴ ቃና
አዛኝ እንደ ሄዋን ሩህሩህ ነሽና
አለም አስር ትሙላ ከቤቴ ግቢና
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
የልቤ ላይ ንግስት አንቺ ውቧ ፍቅሬ
ቀናትን በመቁጠር ወራትን ደምሬ
ከጎንሽ ባልሆንም ከአንቺው ጋር አብሬ
በፍቅርሽ ሰንሰለት በፅናት ታስሬ
አሜን ይሁን ብዬ ቃልሽን አክብሬ
ለልቤ ትርታ ለደም ዝውውሬ
ለመንፈሴ እርካታ ብታመም ዶክተሬ
ደስታን ለማጣጣም ፍቅርሽን ዘምሬ
እስትንፋሴ ነብሴ ሆነሽ ለእኔ ጤና
ለመኖሬ ትርጉም የሂወቴ ቃና
አዛኝ እንደ ሄዋን ሩህሩህ ነሽና
አለም አስር ትሙላ ከቤቴ ግቢና
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤21