"ይሄንን ገለባ፣ መሄጃህ ወዴት ነው?
ብለህ አትጠይቀው፣
የነገው ንፋስ ነው፣
መንገዱን የሚያውቀው"
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ብለህ አትጠይቀው፣
የነገው ንፋስ ነው፣
መንገዱን የሚያውቀው"
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤8👍4👏1
#እንዲህ_ያደርገኛል
እመጣለሁ ብላ የቀጠረችኝ ለት
እንዲህ ያረገኛል
ሰውነቴ ሁሉ ጆሮ ይሆንና
የብናኝ ኮሽታ ገዝፎ ይሰማኛል
ኮቴ እንደመብረቅ
እንደ አንዳች ፍንዳታ
የጆሮዬን ታንቡር ደርሶ ይጠልዘኛል
እመጣለሁ ብላ የቀጠረቺኝ ለት
እንዲህ ያደርገኛል
ጥሞናዬ ረቅቆ መንፈሴን አምጥቆ
የሷን ኮቴ ናፍቆ
የፍቅሬን አካሄድ የሰበር ስካዋን
ከእርምጃዎች ሁሉ ከዳናዎች አውቆ
በናፍቆቷ ደጋን በጉጉት ፍላጻ
ተወርዋሪው ልቤ ተወጥሮ ከረሮ
ጅስሜ እንዳሞራ እንደብርቱ ንስር
ክንፍ አውጥቶ በርሮ
ምድርና ሞላዋን ዓለምን ይቃኛል
ከፍቅሬ በስተቀር
ሁሉም ከንቱ ከንቱ ከንቱ ውእቱ ይለኛል
እመጣለሁ ብላ የቀጠረቺኝ ለት
እንዲህ ያረገኛል
በፍቅሯ ልዕልና በፍቅር ጽናቴ
ከመንደሬ ገዳም ከጎጆ ባዕቴ
ከመላክ .......... ረቅቄ
ከጻድቅ .......... ጸድቄ
.......እጠብቃታለሁ
እመጣለሁ ብላኝ መች ተኝቼ አውቃለሁ
ዓለም ጊዜ ፀሀይ ሁሉም ቀጥ ብለው
የኪዳኔን ታቦት ጽላቴን አክብረው
ይማፀኑልኛል ይማልዱልኛል
«ይህ ምስኪን ጻድቅ ሰው
ከአለም የመነነው
በአቱን የዘጋው
ፀሀይን አስቁሞ ጊዜን የገዘተው
እመጣለሁ ብለሽ እንዳትዘገይ ነው
እንዳትቀሪበት ነው»
ብለው ይሉልኛል
ጨረቃ ከዋክብት ይማልዱልኛል
የፍቅር ብርታቴን ሁሉም ያውቁልኛል
ከአይን ያውጣህ ከአይን ያውጣህ
ከአይን ያውጣህ ይሉኛል
አንዳንዴም ሽው ሲል እንዲህ እሆናለሁ
ከቤቴ ቁጭ ቡዬ በሀሳብ እመጥቃለሁ
እሷን እየጠበቅሁ እፈላሰማለሁ
እላለሁ..............
«ይህ ሁሉ ጥሞና ይሄ ሁሉ ብቃት
ለሌላም ለሌላም ቢሆን ምናለበት
አዬ ጊዜ ደጉ አዬ ወጣትነት»
እላለሁ............
እድሜ ለሷ ፍቅር መንፈሴን ቀጥቅጦ
ልቤን ለሚገዛው
በሌላማ ጊዜ በጥልቅ ለመመለጥ
አይምሮዬን ባዝዘው መች እሺ ይለኛል
መቼ እሺ እላለሁ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አበባዉ መላኩ
እመጣለሁ ብላ የቀጠረችኝ ለት
እንዲህ ያረገኛል
ሰውነቴ ሁሉ ጆሮ ይሆንና
የብናኝ ኮሽታ ገዝፎ ይሰማኛል
ኮቴ እንደመብረቅ
እንደ አንዳች ፍንዳታ
የጆሮዬን ታንቡር ደርሶ ይጠልዘኛል
እመጣለሁ ብላ የቀጠረቺኝ ለት
እንዲህ ያደርገኛል
ጥሞናዬ ረቅቆ መንፈሴን አምጥቆ
የሷን ኮቴ ናፍቆ
የፍቅሬን አካሄድ የሰበር ስካዋን
ከእርምጃዎች ሁሉ ከዳናዎች አውቆ
በናፍቆቷ ደጋን በጉጉት ፍላጻ
ተወርዋሪው ልቤ ተወጥሮ ከረሮ
ጅስሜ እንዳሞራ እንደብርቱ ንስር
ክንፍ አውጥቶ በርሮ
ምድርና ሞላዋን ዓለምን ይቃኛል
ከፍቅሬ በስተቀር
ሁሉም ከንቱ ከንቱ ከንቱ ውእቱ ይለኛል
እመጣለሁ ብላ የቀጠረቺኝ ለት
እንዲህ ያረገኛል
በፍቅሯ ልዕልና በፍቅር ጽናቴ
ከመንደሬ ገዳም ከጎጆ ባዕቴ
ከመላክ .......... ረቅቄ
ከጻድቅ .......... ጸድቄ
.......እጠብቃታለሁ
እመጣለሁ ብላኝ መች ተኝቼ አውቃለሁ
ዓለም ጊዜ ፀሀይ ሁሉም ቀጥ ብለው
የኪዳኔን ታቦት ጽላቴን አክብረው
ይማፀኑልኛል ይማልዱልኛል
«ይህ ምስኪን ጻድቅ ሰው
ከአለም የመነነው
በአቱን የዘጋው
ፀሀይን አስቁሞ ጊዜን የገዘተው
እመጣለሁ ብለሽ እንዳትዘገይ ነው
እንዳትቀሪበት ነው»
ብለው ይሉልኛል
ጨረቃ ከዋክብት ይማልዱልኛል
የፍቅር ብርታቴን ሁሉም ያውቁልኛል
ከአይን ያውጣህ ከአይን ያውጣህ
ከአይን ያውጣህ ይሉኛል
አንዳንዴም ሽው ሲል እንዲህ እሆናለሁ
ከቤቴ ቁጭ ቡዬ በሀሳብ እመጥቃለሁ
እሷን እየጠበቅሁ እፈላሰማለሁ
እላለሁ..............
«ይህ ሁሉ ጥሞና ይሄ ሁሉ ብቃት
ለሌላም ለሌላም ቢሆን ምናለበት
አዬ ጊዜ ደጉ አዬ ወጣትነት»
እላለሁ............
እድሜ ለሷ ፍቅር መንፈሴን ቀጥቅጦ
ልቤን ለሚገዛው
በሌላማ ጊዜ በጥልቅ ለመመለጥ
አይምሮዬን ባዝዘው መች እሺ ይለኛል
መቼ እሺ እላለሁ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አበባዉ መላኩ
❤10
#ብቸኛ_ነበሩ!
በስህተት ተባብሮ ፣ በደቦ ከሚፈርድ፤
የብቻህን ሃሳብ ፣ ዝምታህን ውደድ፤
አለምን ጠቃሚ ፣ ሆነው የተገኙ፤
በመልካም ስራቸው ፣ አንቱ የተሰኙ፤
ብቸኛ ነበሩ ፣ ሁሉም የተዋቸው፤
በደቦ ተባብሮ በግፍ የጣላቸው፤
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
በስህተት ተባብሮ ፣ በደቦ ከሚፈርድ፤
የብቻህን ሃሳብ ፣ ዝምታህን ውደድ፤
አለምን ጠቃሚ ፣ ሆነው የተገኙ፤
በመልካም ስራቸው ፣ አንቱ የተሰኙ፤
ብቸኛ ነበሩ ፣ ሁሉም የተዋቸው፤
በደቦ ተባብሮ በግፍ የጣላቸው፤
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍19❤2
#ምንነት
አብረን በዋልንበት - በሄድንበት ሁሉ
ካንቺ ጋራ ያዩኝ - ያልገባቸው ውሉ
ምኗ ነው እያሉ - ሰው ይጠይቃሉ።
እናምልሽ ውዴ
ምኗ ነው እያሉ - ለሚጠራጠሩ
ስለኔ ምንነት - አውቀው እንዲኖሩ
ከቻልሽ አስረጃቸው - ገልፀሽ በአጭሩ።
እሱ ማለት ለኔ - ገና ከጅምሩ
በሰም የታጠረ - ቅኔ ነው ሚስጥሩ።
ቅኔ ማለት ደግሞ - የማይታይ ጌጡ
ተዘርፎ የማያልቅ - ወርቅ አለ በውስጡ
ለሱ ግን
ከሀብቱ የሚልቅ ሌላ በዚች አለም
ደስታ የሚፈጥር ምንም ይሁን ምንም
ከኔ ሳቅ የሚበልጥ አንዳች ነገር የለም።
መሳቅ ማለት ደስታ - ደስታ ማለት ደሞ
በልቡ ማሳ ላይ - የተዘራው ቀድሞ
የመንፈሱ ችግኝ - ስጋ ያበቀለው
የሚቀጥፈው መውደድ - ጊዜ ያበሰለው
ጣፍጦት የሚበላው የነፍሱ ፍሬ ነው።
ፍሬው ባስተሳሰብ - ዳግም የሚዘራ
የዘሩ ቅርንጫፍ - ከዕምነት የተጋራ
ፍቅር ያዳበረው - ወዳጅ የሚያፈራ
ጥሩ ጓደኛነት - በሚያጠላው ጥላ
እኔ ያስጠለለ - የሆነኝ ከለላ
አፍቅሮኝ የሚኖር - የማይመኝ ሌላ
ታማኝ ወዳጄ ነው - የዕምነቴ ኬላ።
ብለሽ አስረጃቸው
ስለኔ ምንነት - ማወቅ ተስኗቸው
ምኗ ነው ለሚሉ - ፍቅር ላልገባቸው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
አብረን በዋልንበት - በሄድንበት ሁሉ
ካንቺ ጋራ ያዩኝ - ያልገባቸው ውሉ
ምኗ ነው እያሉ - ሰው ይጠይቃሉ።
እናምልሽ ውዴ
ምኗ ነው እያሉ - ለሚጠራጠሩ
ስለኔ ምንነት - አውቀው እንዲኖሩ
ከቻልሽ አስረጃቸው - ገልፀሽ በአጭሩ።
እሱ ማለት ለኔ - ገና ከጅምሩ
በሰም የታጠረ - ቅኔ ነው ሚስጥሩ።
ቅኔ ማለት ደግሞ - የማይታይ ጌጡ
ተዘርፎ የማያልቅ - ወርቅ አለ በውስጡ
ለሱ ግን
ከሀብቱ የሚልቅ ሌላ በዚች አለም
ደስታ የሚፈጥር ምንም ይሁን ምንም
ከኔ ሳቅ የሚበልጥ አንዳች ነገር የለም።
መሳቅ ማለት ደስታ - ደስታ ማለት ደሞ
በልቡ ማሳ ላይ - የተዘራው ቀድሞ
የመንፈሱ ችግኝ - ስጋ ያበቀለው
የሚቀጥፈው መውደድ - ጊዜ ያበሰለው
ጣፍጦት የሚበላው የነፍሱ ፍሬ ነው።
ፍሬው ባስተሳሰብ - ዳግም የሚዘራ
የዘሩ ቅርንጫፍ - ከዕምነት የተጋራ
ፍቅር ያዳበረው - ወዳጅ የሚያፈራ
ጥሩ ጓደኛነት - በሚያጠላው ጥላ
እኔ ያስጠለለ - የሆነኝ ከለላ
አፍቅሮኝ የሚኖር - የማይመኝ ሌላ
ታማኝ ወዳጄ ነው - የዕምነቴ ኬላ።
ብለሽ አስረጃቸው
ስለኔ ምንነት - ማወቅ ተስኗቸው
ምኗ ነው ለሚሉ - ፍቅር ላልገባቸው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤8🥰4👏2🔥1
#ከክፋት_ሰውረኝ?!
የእባብ ልብን ይዘው እርግብ ነን ከሚሉ፣
በቀበሮ ተግባር በበግ ስም ከሚምሉ፣
ቃል እየጠቀሱ በክፋት ከራሱ ፣
በተኩላ ስጋ የብግ ለምድ ከለብሱ፣
የአምላክን ስም ጠርተው በቃሉ ከማይኖሩ፣
በእግዚአብሔር ዝማሬ ሰይጣን ከሚያከብሩ፣
እግራቸው ከመቅደስ ልባቸው ከክፋት፣
ቃላቸው የንብ ማር ተግባራቸው እሬት ፣
ከሆነ ሰዎች ዘንድ እግዚአብሔር ነጥለኝ፣
ጻድቅ ባልሆን እንኳን ከክፋት ሰውረኝ?!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
የእባብ ልብን ይዘው እርግብ ነን ከሚሉ፣
በቀበሮ ተግባር በበግ ስም ከሚምሉ፣
ቃል እየጠቀሱ በክፋት ከራሱ ፣
በተኩላ ስጋ የብግ ለምድ ከለብሱ፣
የአምላክን ስም ጠርተው በቃሉ ከማይኖሩ፣
በእግዚአብሔር ዝማሬ ሰይጣን ከሚያከብሩ፣
እግራቸው ከመቅደስ ልባቸው ከክፋት፣
ቃላቸው የንብ ማር ተግባራቸው እሬት ፣
ከሆነ ሰዎች ዘንድ እግዚአብሔር ነጥለኝ፣
ጻድቅ ባልሆን እንኳን ከክፋት ሰውረኝ?!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍5🥰3👏2🔥1
#ሶሊያና
እኔን ከወንበር ላይ
ቀን ያየሁት እንባ
ቀን ያየሁት ደባ
እንቅልፍ አሳጥቶኝ
ወረቀት ላይ ወስዶኝ
እርሷን ካልጋችን ላይ
እንቅልፍ አሽኮርምሟት
ቀን ያየችው ሁሉ በቅዠት አልፎላት ……
እኔ ከቃላት ጋር ጦርነት ገጥሜ
በሰው ልጆች ጭንቀት እጅግ ተዳክሜ
በሌሊት ጭንቀቴ የቀን ስቃይ ላበርድ
ከደጋው ሃሳቤ በረሃ ስሰደድ
እንባን በፊደላት …
ፊደልን በቃላት…
ቃላትን በሃሳብ ወረቀት ላይ ልወልድ
ወረቀት ላይ ፅፌ ወረቀቱን ስቀድ …
እንዲህ እየፃፍኩኝ እያሰብኩኝ ሳለሁ
‹‹የኔ ነሽ›› የምላት …‹‹ያንተ ነኝ››
የምትል
ፍቅሬ ሶሊያና ተናገረች መሰል በቅዠቷ
መሃል …
‹‹ተመልከት ወዳጀ እኔም ካልጋየ ላይ
አንተን በመናፈቅ በስሜት ስሰቃይ ››
ቀ…ና ብየ ባያት እውነት አለው ቃሏ
ፍም መስሏል አካሏ
ከሌሊት ልብሶቿ ጡቷ ሾልኮ ወጥቷል
እጇ ተዘርግቶ እግሯ ተከፋፍቷል
እኔን በመጓጓት ደሟ ጠቆጥቶ
ፍቅሯ ተሰውቶ
ስሜቷ ተጎድቶ
አንዳች ነገር አይቶ እንደፈራ ህፃን
ፊቷ ሲሸማቀቅ ፀጉራ ሲበታተን …
ካ,ልጋው ላይ ተፅፎ አየሁት እውነቷን
ፍ...ቅ...ሬ ሶ...ሊ...ያ...ና አወራችኝ መሰል
በቅዠቷ መሃል …
አስተውል ወንድሜ …
ባንተ የቀለም ቅብ በድርሰትህ አለም
የሰወች ጥላ እንጅ አካላቸው የለም !
ባንተ ከንቱ ድርሰት በወረቀትህ ላይ
የሰው እንባ ሳይሆን ያንተው ነው የሚታይ
በሌሊት ትጋትህ በድርሰት በግጥም በቀለም ሸራህ ላይ
እኔ ውበቱ ነኝ በፍቅርህ ስሰቃይ
ይህ ሁሉ ቢሆንም
ይህ ሁሉ ቢሆንም . . . ወዲህ እንዳትመጣ
በሌሊት ትጋትህ ሃዘን ሳይቀጣ
በ,ኔ ያልጋ ድርሰት ቅፅበታቶች አሉ
ከየሰው አለም የሚመሳሰሉ
ባንተ ቀለም ሸራ በድርሰትህ ፅሁፍ
ዘመን ይታየኛል እኔን የሚያሳልፍ
ይህ ሁሉ ቢሆንም …
የሰወችን እንባ አትፃፍ ግዴለም
የፍጥረትን ሃዘን ስለህ አትዘልቅም
እውነት አለው ብለህ ሃዘንን አታልም
(ያለቀሱም ሰዎች ሃቀኞች አይደሉም )
ይልቅ የኔን ስሜት ያንተንም እንባዎች
ሁለቱን አሳየኝ
በድርሰት
በግጥም
በቀለም ሸራህ ላይ እኔን ብቻ ሳለኝ !
እኔን ብቻ ፃፈኝ !
‹‹ያልተደሰተች ሴት›› በሚል መፅሃፍህ
ዘ...ላ...ለ...ም አሻግረኝ
ዘ...ላ...ለ...ም ውሰደኝ
ዘ...ላ...ለ...ም አኑረኝ
‹‹የኔ ነሽ›› የምላት …‹‹ያንተ ነኝ››
የምትል
ፍቅሬ ሶሊያና ተናገረች መሰል በቅዠቷ
መሃል …
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ኤፍሬም ስዩም
እኔን ከወንበር ላይ
ቀን ያየሁት እንባ
ቀን ያየሁት ደባ
እንቅልፍ አሳጥቶኝ
ወረቀት ላይ ወስዶኝ
እርሷን ካልጋችን ላይ
እንቅልፍ አሽኮርምሟት
ቀን ያየችው ሁሉ በቅዠት አልፎላት ……
እኔ ከቃላት ጋር ጦርነት ገጥሜ
በሰው ልጆች ጭንቀት እጅግ ተዳክሜ
በሌሊት ጭንቀቴ የቀን ስቃይ ላበርድ
ከደጋው ሃሳቤ በረሃ ስሰደድ
እንባን በፊደላት …
ፊደልን በቃላት…
ቃላትን በሃሳብ ወረቀት ላይ ልወልድ
ወረቀት ላይ ፅፌ ወረቀቱን ስቀድ …
እንዲህ እየፃፍኩኝ እያሰብኩኝ ሳለሁ
‹‹የኔ ነሽ›› የምላት …‹‹ያንተ ነኝ››
የምትል
ፍቅሬ ሶሊያና ተናገረች መሰል በቅዠቷ
መሃል …
‹‹ተመልከት ወዳጀ እኔም ካልጋየ ላይ
አንተን በመናፈቅ በስሜት ስሰቃይ ››
ቀ…ና ብየ ባያት እውነት አለው ቃሏ
ፍም መስሏል አካሏ
ከሌሊት ልብሶቿ ጡቷ ሾልኮ ወጥቷል
እጇ ተዘርግቶ እግሯ ተከፋፍቷል
እኔን በመጓጓት ደሟ ጠቆጥቶ
ፍቅሯ ተሰውቶ
ስሜቷ ተጎድቶ
አንዳች ነገር አይቶ እንደፈራ ህፃን
ፊቷ ሲሸማቀቅ ፀጉራ ሲበታተን …
ካ,ልጋው ላይ ተፅፎ አየሁት እውነቷን
ፍ...ቅ...ሬ ሶ...ሊ...ያ...ና አወራችኝ መሰል
በቅዠቷ መሃል …
አስተውል ወንድሜ …
ባንተ የቀለም ቅብ በድርሰትህ አለም
የሰወች ጥላ እንጅ አካላቸው የለም !
ባንተ ከንቱ ድርሰት በወረቀትህ ላይ
የሰው እንባ ሳይሆን ያንተው ነው የሚታይ
በሌሊት ትጋትህ በድርሰት በግጥም በቀለም ሸራህ ላይ
እኔ ውበቱ ነኝ በፍቅርህ ስሰቃይ
ይህ ሁሉ ቢሆንም
ይህ ሁሉ ቢሆንም . . . ወዲህ እንዳትመጣ
በሌሊት ትጋትህ ሃዘን ሳይቀጣ
በ,ኔ ያልጋ ድርሰት ቅፅበታቶች አሉ
ከየሰው አለም የሚመሳሰሉ
ባንተ ቀለም ሸራ በድርሰትህ ፅሁፍ
ዘመን ይታየኛል እኔን የሚያሳልፍ
ይህ ሁሉ ቢሆንም …
የሰወችን እንባ አትፃፍ ግዴለም
የፍጥረትን ሃዘን ስለህ አትዘልቅም
እውነት አለው ብለህ ሃዘንን አታልም
(ያለቀሱም ሰዎች ሃቀኞች አይደሉም )
ይልቅ የኔን ስሜት ያንተንም እንባዎች
ሁለቱን አሳየኝ
በድርሰት
በግጥም
በቀለም ሸራህ ላይ እኔን ብቻ ሳለኝ !
እኔን ብቻ ፃፈኝ !
‹‹ያልተደሰተች ሴት›› በሚል መፅሃፍህ
ዘ...ላ...ለ...ም አሻግረኝ
ዘ...ላ...ለ...ም ውሰደኝ
ዘ...ላ...ለ...ም አኑረኝ
‹‹የኔ ነሽ›› የምላት …‹‹ያንተ ነኝ››
የምትል
ፍቅሬ ሶሊያና ተናገረች መሰል በቅዠቷ
መሃል …
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ኤፍሬም ስዩም
❤7👍7
#ተሻለህ_አትበሉኝ!
ያሽለኛል ብዬ የጠጣሁት ኮሶ
ይቆርጠኝ ጀመረ ከበሽታው ብሶ
መድሀኒት ይሆነናል ነበረ ምኞቴ
ሃኪሙን አምኜ በእምነት መጠጣቴ
ለካስ ተመረዟል መድሀኒቱ ዛሬ
ለዚህ ነበር ለካስ ብሶብኝ ማደሬ
ተሻለህ አትበሉኝ እያያችሁ ብሶ
መርዝ ሆኖ አሰቃዬኝ ይሄ የዘር ኮሶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ያሽለኛል ብዬ የጠጣሁት ኮሶ
ይቆርጠኝ ጀመረ ከበሽታው ብሶ
መድሀኒት ይሆነናል ነበረ ምኞቴ
ሃኪሙን አምኜ በእምነት መጠጣቴ
ለካስ ተመረዟል መድሀኒቱ ዛሬ
ለዚህ ነበር ለካስ ብሶብኝ ማደሬ
ተሻለህ አትበሉኝ እያያችሁ ብሶ
መርዝ ሆኖ አሰቃዬኝ ይሄ የዘር ኮሶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍9❤4👏3
#እንደገና
እንቁጣጣሽ ነበር መስከረም ሲጠባ
አውቆ የበቀለ ወፍ ዘራሽ አበባ፡፡
ለምለም አረንጓዴ…
ያልተጠበቀ መስክ ከብት የሚግጥበት
የደመና ግላጭ የሚጫወትበት፡፡
ሌላም ብዙ ነበር
ሌላም… ደግሞ ሌላ
አለብኝ ትዝታ!
ዘመዶቼ ሳሙኝ
ጓደኞቼም ጋብዙኝ
ሊስትሮ ጨብጠኝ
ባለጋሪ ንዳ መንገዴን አሳየኝ
ያገሬ ልጅ ቆንጆ ‹‹ቤት ለእንግዳ›› በይኝ
አለብኝ ትዝታ…
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገ/ክርስቶስ ደስታ
እንቁጣጣሽ ነበር መስከረም ሲጠባ
አውቆ የበቀለ ወፍ ዘራሽ አበባ፡፡
ለምለም አረንጓዴ…
ያልተጠበቀ መስክ ከብት የሚግጥበት
የደመና ግላጭ የሚጫወትበት፡፡
ሌላም ብዙ ነበር
ሌላም… ደግሞ ሌላ
አለብኝ ትዝታ!
ዘመዶቼ ሳሙኝ
ጓደኞቼም ጋብዙኝ
ሊስትሮ ጨብጠኝ
ባለጋሪ ንዳ መንገዴን አሳየኝ
ያገሬ ልጅ ቆንጆ ‹‹ቤት ለእንግዳ›› በይኝ
አለብኝ ትዝታ…
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገ/ክርስቶስ ደስታ
❤3
#ውኃ_ማያጠፋው
ውኃ ‚ማያጠፋው ' እሳት ፡ ነው ፡ ፍቅርሽ
ነደድኩኝ "
ቢል ' አልኩኝ "
ተቃጠልኩልሽ ።
ወደድኩሽ "
ወደድኩህ ' በይኝ ፡ እባክሽ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ውኃ ‚ማያጠፋው ' እሳት ፡ ነው ፡ ፍቅርሽ
ነደድኩኝ "
ቢል ' አልኩኝ "
ተቃጠልኩልሽ ።
ወደድኩሽ "
ወደድኩህ ' በይኝ ፡ እባክሽ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
#ዘመም_ይላል_እንጂ
እንደ ጊዜው መክፋት
እንደ ግፉ መስፋት
እንዳገሩ ክስመት
እንዳገሬው ጥመት
እንደሰው ጭካኔ፥እንደ ልቡ ፍሬ
ታምር ነው መትረፍሽ፥ ታምር ነው መኖሬ::
የበጎ ሰው ሀሳብ፥ ሲካድ እለት በእለት
ጉድጓድ ተምሶለት፥ ሰብእና ሲቀበር
በዚህ ዓለም መኖር፥አያስመኝም ነበር ::
ምድሩ ሳር ቅጠሉ፥ በስጋት ተሞልቶ
የማለዳው ሰማይ፥ እንዳንቀልባ ቀልቶ
ታረደ
ነደደ
ከዘብጥያ ወጥቶ
ዘብጥያ ወረደ
የሚል ዜና ብቻ ፥ አየሩን ሲሞላው
ሰው በገዛ ጥላው ፥
በርግጎ ሲሸበር
በዚህ ምድር መኖር፥ አያስመኝም ነበር ፤
አዎ
ለጊዜውም ቢሆን ግፍ ያደነዝዛል
በደል ያስተክዛል
ጊዜም ጠብን ሽሮ፥ ወደ ፊት ይጓዛል
በልብ ሰሌዳ ላይ፤ ቂም ይደበዝዛል
በነገ ያመነ
ልጁን ቀብሮ መጥቶ ፥ ሚስቱን ያስረግዛል ::
ይቅርታና ምህረት
ፍቅርና ህብረት
ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው፥ ቢሆን የሞት ሽረት
ዳገት ይወጣሉ፥ በንጥፍጣፊ አቅም
የመኖር ፍላጎት
ዘመም ይላል እንጂ ፥ተገርስሶ አይወድቅም ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
እንደ ጊዜው መክፋት
እንደ ግፉ መስፋት
እንዳገሩ ክስመት
እንዳገሬው ጥመት
እንደሰው ጭካኔ፥እንደ ልቡ ፍሬ
ታምር ነው መትረፍሽ፥ ታምር ነው መኖሬ::
የበጎ ሰው ሀሳብ፥ ሲካድ እለት በእለት
ጉድጓድ ተምሶለት፥ ሰብእና ሲቀበር
በዚህ ዓለም መኖር፥አያስመኝም ነበር ::
ምድሩ ሳር ቅጠሉ፥ በስጋት ተሞልቶ
የማለዳው ሰማይ፥ እንዳንቀልባ ቀልቶ
ታረደ
ነደደ
ከዘብጥያ ወጥቶ
ዘብጥያ ወረደ
የሚል ዜና ብቻ ፥ አየሩን ሲሞላው
ሰው በገዛ ጥላው ፥
በርግጎ ሲሸበር
በዚህ ምድር መኖር፥ አያስመኝም ነበር ፤
አዎ
ለጊዜውም ቢሆን ግፍ ያደነዝዛል
በደል ያስተክዛል
ጊዜም ጠብን ሽሮ፥ ወደ ፊት ይጓዛል
በልብ ሰሌዳ ላይ፤ ቂም ይደበዝዛል
በነገ ያመነ
ልጁን ቀብሮ መጥቶ ፥ ሚስቱን ያስረግዛል ::
ይቅርታና ምህረት
ፍቅርና ህብረት
ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው፥ ቢሆን የሞት ሽረት
ዳገት ይወጣሉ፥ በንጥፍጣፊ አቅም
የመኖር ፍላጎት
ዘመም ይላል እንጂ ፥ተገርስሶ አይወድቅም ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤6👍3
የታይተው ግል ታሪኮች?
በጣም ግልጽ ሳይሆኑ ፍቅርና ህይወት ተዛማጅ ታሪኮች እያረጉ ኮ በጣም ልዩ የሆነ ይቻላል።
ጣፋጭ ታሪኮች በሌላ ቦታ የማታገኙበት ግል ታሪክ አዲስ በአዲስ ይቀርባል።
ልዩ የማይከሰት ታሪክ ይነቡ – ዘወትር አዲስ ታሪኮች!
#ad InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
በጣም ግልጽ ሳይሆኑ ፍቅርና ህይወት ተዛማጅ ታሪኮች እያረጉ ኮ በጣም ልዩ የሆነ ይቻላል።
ጣፋጭ ታሪኮች በሌላ ቦታ የማታገኙበት ግል ታሪክ አዲስ በአዲስ ይቀርባል።
ልዩ የማይከሰት ታሪክ ይነቡ – ዘወትር አዲስ ታሪኮች!
#ad InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
#የፍቅር_ፍላፃ
ፈረንሣይ እንግሊዝ ጀርመን ጣልያን
ስትጽፍ ስትናገር አይዛት አፏን
ባርኔጣዋ ሠፌድ በፓሪሱ ቄንጥ
የጫማ ተረከዝ ስንዝር የሚበልጥ
ሥልጡን የተማረች የሠለጠነች
ብለው ሲወድሱሽ ሲሻሙሽ ሰዎች
አንዱ በቢዩክ መጥቶ «እንውጣ» ሲልሽ
በሼቭሮሌት አንዱ ሲያንሸረሽርሽ
መዳብ ያለው ብሩን ወርቅ ያለው ዕንቁን
የራስ አክሊል ያለው ሲሰጥሽ ዘውዱን
ማሞገስ የሚያወቅም ሲዘፍን ያንቺን ስም
ወድሻለሁ ያለሽ ሲሸለም ሲሾም
በፍቅርሽ ፍላፃ ተነድፎ እንዱ ደግሞ
ሚስቱን ያገባትን ምሎ ተፈጥሞ
ሲያባርር ሲፈታ ልጆች እያሉት
ትዳሩን ሲያፈርሰው አንቺን ለማግባት
እንዳላየ ዓይቼ ሰምቼ እንዳልሰማ
በፈላስፋ ትዕግሥት ስቀር ሳልሻማ!
በኒያ ሁሉ ልብሽ ቢጨክን ቢጠም
ከንፈርሽ ከሌላ ሰው ከንፈር ባይገጥም!
ፍቅርሽ ተፈትኖ በገንዘብ በእሳቱ
ታወቀ ማለት ነው ጥሩ ወርቅነቱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
💓 ራስዬ አላሳዉሪ።: ዛሬ የተጠበቀውን መፅሐፍ ለመምጣት… ዝም ብሎ ቆመ! ቀጥሎ በሚልጠው ቻናል ተጫኑ | InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
ፈረንሣይ እንግሊዝ ጀርመን ጣልያን
ስትጽፍ ስትናገር አይዛት አፏን
ባርኔጣዋ ሠፌድ በፓሪሱ ቄንጥ
የጫማ ተረከዝ ስንዝር የሚበልጥ
ሥልጡን የተማረች የሠለጠነች
ብለው ሲወድሱሽ ሲሻሙሽ ሰዎች
አንዱ በቢዩክ መጥቶ «እንውጣ» ሲልሽ
በሼቭሮሌት አንዱ ሲያንሸረሽርሽ
መዳብ ያለው ብሩን ወርቅ ያለው ዕንቁን
የራስ አክሊል ያለው ሲሰጥሽ ዘውዱን
ማሞገስ የሚያወቅም ሲዘፍን ያንቺን ስም
ወድሻለሁ ያለሽ ሲሸለም ሲሾም
በፍቅርሽ ፍላፃ ተነድፎ እንዱ ደግሞ
ሚስቱን ያገባትን ምሎ ተፈጥሞ
ሲያባርር ሲፈታ ልጆች እያሉት
ትዳሩን ሲያፈርሰው አንቺን ለማግባት
እንዳላየ ዓይቼ ሰምቼ እንዳልሰማ
በፈላስፋ ትዕግሥት ስቀር ሳልሻማ!
በኒያ ሁሉ ልብሽ ቢጨክን ቢጠም
ከንፈርሽ ከሌላ ሰው ከንፈር ባይገጥም!
ፍቅርሽ ተፈትኖ በገንዘብ በእሳቱ
ታወቀ ማለት ነው ጥሩ ወርቅነቱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
💓 ራስዬ አላሳዉሪ።: ዛሬ የተጠበቀውን መፅሐፍ ለመምጣት… ዝም ብሎ ቆመ! ቀጥሎ በሚልጠው ቻናል ተጫኑ | InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
👍1
አዲስ የ4K ጥራት ፎቶ በፍላጎት ትጠብቃለህ?
በቀላሉ ቦታ እና ለsamrt-profile–wallpaper የምታጠቀም ፎቶዎች, የተመረጡ motivational ገጽታዎችና quotes ይፈልጋሉ?
ኢትዮጵያን የመጀመሪያውን እና ብቸኛ የመሆኑን ቻናል አትተዉ፤ አሁኑኑ join በሉ!
#ad InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
በቀላሉ ቦታ እና ለsamrt-profile–wallpaper የምታጠቀም ፎቶዎች, የተመረጡ motivational ገጽታዎችና quotes ይፈልጋሉ?
ኢትዮጵያን የመጀመሪያውን እና ብቸኛ የመሆኑን ቻናል አትተዉ፤ አሁኑኑ join በሉ!
#ad InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች