#ከዚህም_በላይ_ነሽ
ሳላገኝሽ በፊት…
መውደዴን አብዝቼ…
አንቺን እያሰብኩኝ ቆርቤ ከራሴ
‘’እንዴት ነህ?’’ ለሚሉኝ…
አንገቴን ደፍቼ ዝም ነበር መልሴ
ካገኝሁሽ በኋላ…
ማእረግ እንዳገኘ እግረኛ ወቶአደር
ደረቴን ነፍቼ ቀና ብዬ እያየሁ…
‘’ደህና ነህ?’’ ባይሉ እንኳ
‘’ደህና ነኝ!’’ እላለሁ
ይህ ማለት ምንድን ነው?
ኩራት ደህንነቴ አንች ነሽ ማለት ነው!
ሳላገኝሽ በፊት…
የሰማዩን ቀለም
የውሃውን ጣእም
ያገር ምድሩን ሽታ
ደስ ይበልም አይበል
ይጣፍጥ ወይም ይምረር
መለየት አቅቶኝ ግራ ገብቶኝ ነበር
ካገኘሁሽ በኋላ…
ሰማይ…ሰማያዊ ውሃው ቀለም አልባ
ሀገሬ ምታምር ሽታዋ እንዳ'በባ
መሆኑን አወቅኩኝ ሰላም ከኔ አደረ
ይመስገነው ባንቺ ግራ መግባት ቀረ!
ይህ ማለት ምንድን ነው?
ስሜት ሕዋሳቴ አንቺ ነሽ ማለት ነው!
ሳላገኝሽ በፊት…
የሰኞ ማክሰኞ የመስከረም ጥቅምት
የሴኮንድ መቶኛ የሽራፊ ሰዓት
ልዩነት ሳይገባኝ ቀን በቃል ሳልቆጥር
እንዲሁ እንደዘበት እየኖርኩኝ ነበር
ካገኘሁሽ በኋላ…
ጳጉሜ ተጨምራ…
አስራ ሁለት ወራቶች አንድ ዓመት ሞልተዋል
ሰላሳ ቀናቶች ወር ላይ ተዘርተዋል
ሰኞ ላይ ጀምረው እሁድ የሚያበቁ
ሰባት ቀናት አሉ በስም የታወቁ
ሃያ አራት ሰዓት አንድ ቀን ይባላል
ራሱ ሰዓቱ በስልሳ ተከፍሏል
ስልሳውም በስልሳ ሂደት ይቀጥላል
ይህን ታላቅ እውቀት
ይህን ታላቅ እውነት
ይመስገነውና ይሄው ባንቺ አገኘሁ
ይህ ማለት ምንድን ነው?
ቁጥሩ ብቻ ሳይሆን…
ጊዜዬም በራሱ አንቺ ነሽ ማለት ነው!
ሳላገኝሽ በፊት…
ከየትኛው አህጉር
ከየትኛው ሀገር
ከየትኛው አፈር
ከየትኛውስ ዘር
መምጣት መፈጠሬን አላውቀውም ነበር
ካገኘሁሽ በኋላ…
አህጉሩን ለየሁ
ሀገሬን አገኘሁ
አፈሩን ቀመስኩት
ራሴን አየሁት
ይመስገነውና ዘር የማይለያየኝ
ማንነቴን ያወቅኩ ውብ ኢትዮጲያዊ ነኝ!
ይህ ማለት ምንድን ነው?
እኔን ብቻ ሳይሆን
ሀገሬን ያገኘሁ ባንቺ ነው ማለት ነው!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሰለሞን ሳህለ
ሳላገኝሽ በፊት…
መውደዴን አብዝቼ…
አንቺን እያሰብኩኝ ቆርቤ ከራሴ
‘’እንዴት ነህ?’’ ለሚሉኝ…
አንገቴን ደፍቼ ዝም ነበር መልሴ
ካገኝሁሽ በኋላ…
ማእረግ እንዳገኘ እግረኛ ወቶአደር
ደረቴን ነፍቼ ቀና ብዬ እያየሁ…
‘’ደህና ነህ?’’ ባይሉ እንኳ
‘’ደህና ነኝ!’’ እላለሁ
ይህ ማለት ምንድን ነው?
ኩራት ደህንነቴ አንች ነሽ ማለት ነው!
ሳላገኝሽ በፊት…
የሰማዩን ቀለም
የውሃውን ጣእም
ያገር ምድሩን ሽታ
ደስ ይበልም አይበል
ይጣፍጥ ወይም ይምረር
መለየት አቅቶኝ ግራ ገብቶኝ ነበር
ካገኘሁሽ በኋላ…
ሰማይ…ሰማያዊ ውሃው ቀለም አልባ
ሀገሬ ምታምር ሽታዋ እንዳ'በባ
መሆኑን አወቅኩኝ ሰላም ከኔ አደረ
ይመስገነው ባንቺ ግራ መግባት ቀረ!
ይህ ማለት ምንድን ነው?
ስሜት ሕዋሳቴ አንቺ ነሽ ማለት ነው!
ሳላገኝሽ በፊት…
የሰኞ ማክሰኞ የመስከረም ጥቅምት
የሴኮንድ መቶኛ የሽራፊ ሰዓት
ልዩነት ሳይገባኝ ቀን በቃል ሳልቆጥር
እንዲሁ እንደዘበት እየኖርኩኝ ነበር
ካገኘሁሽ በኋላ…
ጳጉሜ ተጨምራ…
አስራ ሁለት ወራቶች አንድ ዓመት ሞልተዋል
ሰላሳ ቀናቶች ወር ላይ ተዘርተዋል
ሰኞ ላይ ጀምረው እሁድ የሚያበቁ
ሰባት ቀናት አሉ በስም የታወቁ
ሃያ አራት ሰዓት አንድ ቀን ይባላል
ራሱ ሰዓቱ በስልሳ ተከፍሏል
ስልሳውም በስልሳ ሂደት ይቀጥላል
ይህን ታላቅ እውቀት
ይህን ታላቅ እውነት
ይመስገነውና ይሄው ባንቺ አገኘሁ
ይህ ማለት ምንድን ነው?
ቁጥሩ ብቻ ሳይሆን…
ጊዜዬም በራሱ አንቺ ነሽ ማለት ነው!
ሳላገኝሽ በፊት…
ከየትኛው አህጉር
ከየትኛው ሀገር
ከየትኛው አፈር
ከየትኛውስ ዘር
መምጣት መፈጠሬን አላውቀውም ነበር
ካገኘሁሽ በኋላ…
አህጉሩን ለየሁ
ሀገሬን አገኘሁ
አፈሩን ቀመስኩት
ራሴን አየሁት
ይመስገነውና ዘር የማይለያየኝ
ማንነቴን ያወቅኩ ውብ ኢትዮጲያዊ ነኝ!
ይህ ማለት ምንድን ነው?
እኔን ብቻ ሳይሆን
ሀገሬን ያገኘሁ ባንቺ ነው ማለት ነው!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሰለሞን ሳህለ
❤17
#የእድሜ_ፈረስ
ጠዋት የመሰለን የእድሚያችን ነጸብራቅ
ለካስ መሽቶብናል ከአምላክ ሳንታረቅ
ከሰው ተራ ወርደን ከክብር ከፍታ
ስንባዝን በከንቱ ለምድሩ ደስታ
ለብሰን ተከናንበን የበደልን ኩታ
ጠዋት የመሰለን ድንገት ሆኗል ማታ
የእድሜ ፈረስ ፍጥነት እየገሰገሰ
ከንቱ ውበታች ሳይኖር ፈረሰ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ጠዋት የመሰለን የእድሚያችን ነጸብራቅ
ለካስ መሽቶብናል ከአምላክ ሳንታረቅ
ከሰው ተራ ወርደን ከክብር ከፍታ
ስንባዝን በከንቱ ለምድሩ ደስታ
ለብሰን ተከናንበን የበደልን ኩታ
ጠዋት የመሰለን ድንገት ሆኗል ማታ
የእድሜ ፈረስ ፍጥነት እየገሰገሰ
ከንቱ ውበታች ሳይኖር ፈረሰ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤12🔥1
#ህገ_ሰካራም!
‹‹ነገሩ ነው እንጂ ፤ አረቄ አያሰክርም
አሳሪ ከሌለ ፣ ገመድ ሰው አያስርም
ወዳጅ ዘመድ እንጂ….
አፈር ሰው አይቀብርም ፡፡››
ይላል የሰከረ !
አረቄ ቤት ሆኖ ፣
መተዳደሪያውን ፤ ህግ እያዋቀረ፡፡
እንደሰካራም ህግ፤ እንደስካር ወሬ
አረቄ ቤት ሆኜ...
አረቄ እየጠጣሁ፤ በነገር ሰክሬ
ስለ ሰካራም ህግ ፤ ላውራሽማ ፍቅሬ፡፡
እዚህ አረቄ ቤት...
ከተሰበሰበው ፤ የሰካራም አባል
ስሙን የማላውቀው፤ ‹‹ሰካራም›› የሚባል
አንድ የሰከረ ሰው፤ እንደተናገረው
ሀገርሽ ሀገሬ….
‹‹መልሱን ጠጣንበት›› ፣
በሚለው ህግ ነው ፣ የሚተዳደረው፡፡
‹‹ለመብራት›› እያሉን ፤ ገንዘብ እያዋጣን፤
‹‹ለመንገድ›› እያሉን ፤ ገንዘብ እያዋጣን፤
‹‹ለውሀ›› እያሉን ፤ገንዘብ እያዋጣን
ለምን መብራት ጠፋ?
ለምን ውሃ የለም?
እንዴት መንገድ አጣን? ፣ ብሎ ከመጠየቅ፤
ሳይሻል አይቀርም….
መልሱን ጠጣንበት፤ የሚል ህግ ማፅደቅ፡፡
ወንጀለኛው ሁላ….
ዳኛውን ጠብቆ ገንዘብ ካቀበለ
በ ሺህ ምስክር ፊት…
የመሰረትነው ክስ፤ ‹‹ውድቅ›› ከተባለ
ለምን እዴት? የሚል…
የከሳሽ ጥያቄ ፤መልስ ካልተሰጠው፤
በሰካራም አንቀፅ…
መልሱን ጠጣንበት!
የሚለው ህግ ነው ፤የሚረጋገጠው፡፡
እንደ ህገ መንግስት…
ተፈፃሚነቱ፤ ቢሰራም ባይሰራም
መልሱን ጠጣንበት!
ብሎ ያፀደቀው፤ ህግ አለው ሰካራም፡፡
እንደሰካራም ህግ፤ እንደስካር ወሬ
አረቄ ቤት ሆኜ...
አረቄ እየጠጣሁ፤ በነገር ሰክሬ
እኔን አረቄ ቤት፤ምን እንደወሰደኝ
አረቄ መጠጣት ፤ማን እንዳስለመደኝ፤
አትጠይቂኝ ፍቅሬ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በላይ በቀለ ወያ
‹‹ነገሩ ነው እንጂ ፤ አረቄ አያሰክርም
አሳሪ ከሌለ ፣ ገመድ ሰው አያስርም
ወዳጅ ዘመድ እንጂ….
አፈር ሰው አይቀብርም ፡፡››
ይላል የሰከረ !
አረቄ ቤት ሆኖ ፣
መተዳደሪያውን ፤ ህግ እያዋቀረ፡፡
እንደሰካራም ህግ፤ እንደስካር ወሬ
አረቄ ቤት ሆኜ...
አረቄ እየጠጣሁ፤ በነገር ሰክሬ
ስለ ሰካራም ህግ ፤ ላውራሽማ ፍቅሬ፡፡
እዚህ አረቄ ቤት...
ከተሰበሰበው ፤ የሰካራም አባል
ስሙን የማላውቀው፤ ‹‹ሰካራም›› የሚባል
አንድ የሰከረ ሰው፤ እንደተናገረው
ሀገርሽ ሀገሬ….
‹‹መልሱን ጠጣንበት›› ፣
በሚለው ህግ ነው ፣ የሚተዳደረው፡፡
‹‹ለመብራት›› እያሉን ፤ ገንዘብ እያዋጣን፤
‹‹ለመንገድ›› እያሉን ፤ ገንዘብ እያዋጣን፤
‹‹ለውሀ›› እያሉን ፤ገንዘብ እያዋጣን
ለምን መብራት ጠፋ?
ለምን ውሃ የለም?
እንዴት መንገድ አጣን? ፣ ብሎ ከመጠየቅ፤
ሳይሻል አይቀርም….
መልሱን ጠጣንበት፤ የሚል ህግ ማፅደቅ፡፡
ወንጀለኛው ሁላ….
ዳኛውን ጠብቆ ገንዘብ ካቀበለ
በ ሺህ ምስክር ፊት…
የመሰረትነው ክስ፤ ‹‹ውድቅ›› ከተባለ
ለምን እዴት? የሚል…
የከሳሽ ጥያቄ ፤መልስ ካልተሰጠው፤
በሰካራም አንቀፅ…
መልሱን ጠጣንበት!
የሚለው ህግ ነው ፤የሚረጋገጠው፡፡
እንደ ህገ መንግስት…
ተፈፃሚነቱ፤ ቢሰራም ባይሰራም
መልሱን ጠጣንበት!
ብሎ ያፀደቀው፤ ህግ አለው ሰካራም፡፡
እንደሰካራም ህግ፤ እንደስካር ወሬ
አረቄ ቤት ሆኜ...
አረቄ እየጠጣሁ፤ በነገር ሰክሬ
እኔን አረቄ ቤት፤ምን እንደወሰደኝ
አረቄ መጠጣት ፤ማን እንዳስለመደኝ፤
አትጠይቂኝ ፍቅሬ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በላይ በቀለ ወያ
❤8👏3👍1🥴1
"ይሄንን ገለባ፣ መሄጃህ ወዴት ነው?
ብለህ አትጠይቀው፣
የነገው ንፋስ ነው፣
መንገዱን የሚያውቀው"
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ብለህ አትጠይቀው፣
የነገው ንፋስ ነው፣
መንገዱን የሚያውቀው"
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤8👍4👏1
#እንዲህ_ያደርገኛል
እመጣለሁ ብላ የቀጠረችኝ ለት
እንዲህ ያረገኛል
ሰውነቴ ሁሉ ጆሮ ይሆንና
የብናኝ ኮሽታ ገዝፎ ይሰማኛል
ኮቴ እንደመብረቅ
እንደ አንዳች ፍንዳታ
የጆሮዬን ታንቡር ደርሶ ይጠልዘኛል
እመጣለሁ ብላ የቀጠረቺኝ ለት
እንዲህ ያደርገኛል
ጥሞናዬ ረቅቆ መንፈሴን አምጥቆ
የሷን ኮቴ ናፍቆ
የፍቅሬን አካሄድ የሰበር ስካዋን
ከእርምጃዎች ሁሉ ከዳናዎች አውቆ
በናፍቆቷ ደጋን በጉጉት ፍላጻ
ተወርዋሪው ልቤ ተወጥሮ ከረሮ
ጅስሜ እንዳሞራ እንደብርቱ ንስር
ክንፍ አውጥቶ በርሮ
ምድርና ሞላዋን ዓለምን ይቃኛል
ከፍቅሬ በስተቀር
ሁሉም ከንቱ ከንቱ ከንቱ ውእቱ ይለኛል
እመጣለሁ ብላ የቀጠረቺኝ ለት
እንዲህ ያረገኛል
በፍቅሯ ልዕልና በፍቅር ጽናቴ
ከመንደሬ ገዳም ከጎጆ ባዕቴ
ከመላክ .......... ረቅቄ
ከጻድቅ .......... ጸድቄ
.......እጠብቃታለሁ
እመጣለሁ ብላኝ መች ተኝቼ አውቃለሁ
ዓለም ጊዜ ፀሀይ ሁሉም ቀጥ ብለው
የኪዳኔን ታቦት ጽላቴን አክብረው
ይማፀኑልኛል ይማልዱልኛል
«ይህ ምስኪን ጻድቅ ሰው
ከአለም የመነነው
በአቱን የዘጋው
ፀሀይን አስቁሞ ጊዜን የገዘተው
እመጣለሁ ብለሽ እንዳትዘገይ ነው
እንዳትቀሪበት ነው»
ብለው ይሉልኛል
ጨረቃ ከዋክብት ይማልዱልኛል
የፍቅር ብርታቴን ሁሉም ያውቁልኛል
ከአይን ያውጣህ ከአይን ያውጣህ
ከአይን ያውጣህ ይሉኛል
አንዳንዴም ሽው ሲል እንዲህ እሆናለሁ
ከቤቴ ቁጭ ቡዬ በሀሳብ እመጥቃለሁ
እሷን እየጠበቅሁ እፈላሰማለሁ
እላለሁ..............
«ይህ ሁሉ ጥሞና ይሄ ሁሉ ብቃት
ለሌላም ለሌላም ቢሆን ምናለበት
አዬ ጊዜ ደጉ አዬ ወጣትነት»
እላለሁ............
እድሜ ለሷ ፍቅር መንፈሴን ቀጥቅጦ
ልቤን ለሚገዛው
በሌላማ ጊዜ በጥልቅ ለመመለጥ
አይምሮዬን ባዝዘው መች እሺ ይለኛል
መቼ እሺ እላለሁ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አበባዉ መላኩ
እመጣለሁ ብላ የቀጠረችኝ ለት
እንዲህ ያረገኛል
ሰውነቴ ሁሉ ጆሮ ይሆንና
የብናኝ ኮሽታ ገዝፎ ይሰማኛል
ኮቴ እንደመብረቅ
እንደ አንዳች ፍንዳታ
የጆሮዬን ታንቡር ደርሶ ይጠልዘኛል
እመጣለሁ ብላ የቀጠረቺኝ ለት
እንዲህ ያደርገኛል
ጥሞናዬ ረቅቆ መንፈሴን አምጥቆ
የሷን ኮቴ ናፍቆ
የፍቅሬን አካሄድ የሰበር ስካዋን
ከእርምጃዎች ሁሉ ከዳናዎች አውቆ
በናፍቆቷ ደጋን በጉጉት ፍላጻ
ተወርዋሪው ልቤ ተወጥሮ ከረሮ
ጅስሜ እንዳሞራ እንደብርቱ ንስር
ክንፍ አውጥቶ በርሮ
ምድርና ሞላዋን ዓለምን ይቃኛል
ከፍቅሬ በስተቀር
ሁሉም ከንቱ ከንቱ ከንቱ ውእቱ ይለኛል
እመጣለሁ ብላ የቀጠረቺኝ ለት
እንዲህ ያረገኛል
በፍቅሯ ልዕልና በፍቅር ጽናቴ
ከመንደሬ ገዳም ከጎጆ ባዕቴ
ከመላክ .......... ረቅቄ
ከጻድቅ .......... ጸድቄ
.......እጠብቃታለሁ
እመጣለሁ ብላኝ መች ተኝቼ አውቃለሁ
ዓለም ጊዜ ፀሀይ ሁሉም ቀጥ ብለው
የኪዳኔን ታቦት ጽላቴን አክብረው
ይማፀኑልኛል ይማልዱልኛል
«ይህ ምስኪን ጻድቅ ሰው
ከአለም የመነነው
በአቱን የዘጋው
ፀሀይን አስቁሞ ጊዜን የገዘተው
እመጣለሁ ብለሽ እንዳትዘገይ ነው
እንዳትቀሪበት ነው»
ብለው ይሉልኛል
ጨረቃ ከዋክብት ይማልዱልኛል
የፍቅር ብርታቴን ሁሉም ያውቁልኛል
ከአይን ያውጣህ ከአይን ያውጣህ
ከአይን ያውጣህ ይሉኛል
አንዳንዴም ሽው ሲል እንዲህ እሆናለሁ
ከቤቴ ቁጭ ቡዬ በሀሳብ እመጥቃለሁ
እሷን እየጠበቅሁ እፈላሰማለሁ
እላለሁ..............
«ይህ ሁሉ ጥሞና ይሄ ሁሉ ብቃት
ለሌላም ለሌላም ቢሆን ምናለበት
አዬ ጊዜ ደጉ አዬ ወጣትነት»
እላለሁ............
እድሜ ለሷ ፍቅር መንፈሴን ቀጥቅጦ
ልቤን ለሚገዛው
በሌላማ ጊዜ በጥልቅ ለመመለጥ
አይምሮዬን ባዝዘው መች እሺ ይለኛል
መቼ እሺ እላለሁ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አበባዉ መላኩ
❤9
#ብቸኛ_ነበሩ!
በስህተት ተባብሮ ፣ በደቦ ከሚፈርድ፤
የብቻህን ሃሳብ ፣ ዝምታህን ውደድ፤
አለምን ጠቃሚ ፣ ሆነው የተገኙ፤
በመልካም ስራቸው ፣ አንቱ የተሰኙ፤
ብቸኛ ነበሩ ፣ ሁሉም የተዋቸው፤
በደቦ ተባብሮ በግፍ የጣላቸው፤
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
በስህተት ተባብሮ ፣ በደቦ ከሚፈርድ፤
የብቻህን ሃሳብ ፣ ዝምታህን ውደድ፤
አለምን ጠቃሚ ፣ ሆነው የተገኙ፤
በመልካም ስራቸው ፣ አንቱ የተሰኙ፤
ብቸኛ ነበሩ ፣ ሁሉም የተዋቸው፤
በደቦ ተባብሮ በግፍ የጣላቸው፤
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍18❤2
#ምንነት
አብረን በዋልንበት - በሄድንበት ሁሉ
ካንቺ ጋራ ያዩኝ - ያልገባቸው ውሉ
ምኗ ነው እያሉ - ሰው ይጠይቃሉ።
እናምልሽ ውዴ
ምኗ ነው እያሉ - ለሚጠራጠሩ
ስለኔ ምንነት - አውቀው እንዲኖሩ
ከቻልሽ አስረጃቸው - ገልፀሽ በአጭሩ።
እሱ ማለት ለኔ - ገና ከጅምሩ
በሰም የታጠረ - ቅኔ ነው ሚስጥሩ።
ቅኔ ማለት ደግሞ - የማይታይ ጌጡ
ተዘርፎ የማያልቅ - ወርቅ አለ በውስጡ
ለሱ ግን
ከሀብቱ የሚልቅ ሌላ በዚች አለም
ደስታ የሚፈጥር ምንም ይሁን ምንም
ከኔ ሳቅ የሚበልጥ አንዳች ነገር የለም።
መሳቅ ማለት ደስታ - ደስታ ማለት ደሞ
በልቡ ማሳ ላይ - የተዘራው ቀድሞ
የመንፈሱ ችግኝ - ስጋ ያበቀለው
የሚቀጥፈው መውደድ - ጊዜ ያበሰለው
ጣፍጦት የሚበላው የነፍሱ ፍሬ ነው።
ፍሬው ባስተሳሰብ - ዳግም የሚዘራ
የዘሩ ቅርንጫፍ - ከዕምነት የተጋራ
ፍቅር ያዳበረው - ወዳጅ የሚያፈራ
ጥሩ ጓደኛነት - በሚያጠላው ጥላ
እኔ ያስጠለለ - የሆነኝ ከለላ
አፍቅሮኝ የሚኖር - የማይመኝ ሌላ
ታማኝ ወዳጄ ነው - የዕምነቴ ኬላ።
ብለሽ አስረጃቸው
ስለኔ ምንነት - ማወቅ ተስኗቸው
ምኗ ነው ለሚሉ - ፍቅር ላልገባቸው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
አብረን በዋልንበት - በሄድንበት ሁሉ
ካንቺ ጋራ ያዩኝ - ያልገባቸው ውሉ
ምኗ ነው እያሉ - ሰው ይጠይቃሉ።
እናምልሽ ውዴ
ምኗ ነው እያሉ - ለሚጠራጠሩ
ስለኔ ምንነት - አውቀው እንዲኖሩ
ከቻልሽ አስረጃቸው - ገልፀሽ በአጭሩ።
እሱ ማለት ለኔ - ገና ከጅምሩ
በሰም የታጠረ - ቅኔ ነው ሚስጥሩ።
ቅኔ ማለት ደግሞ - የማይታይ ጌጡ
ተዘርፎ የማያልቅ - ወርቅ አለ በውስጡ
ለሱ ግን
ከሀብቱ የሚልቅ ሌላ በዚች አለም
ደስታ የሚፈጥር ምንም ይሁን ምንም
ከኔ ሳቅ የሚበልጥ አንዳች ነገር የለም።
መሳቅ ማለት ደስታ - ደስታ ማለት ደሞ
በልቡ ማሳ ላይ - የተዘራው ቀድሞ
የመንፈሱ ችግኝ - ስጋ ያበቀለው
የሚቀጥፈው መውደድ - ጊዜ ያበሰለው
ጣፍጦት የሚበላው የነፍሱ ፍሬ ነው።
ፍሬው ባስተሳሰብ - ዳግም የሚዘራ
የዘሩ ቅርንጫፍ - ከዕምነት የተጋራ
ፍቅር ያዳበረው - ወዳጅ የሚያፈራ
ጥሩ ጓደኛነት - በሚያጠላው ጥላ
እኔ ያስጠለለ - የሆነኝ ከለላ
አፍቅሮኝ የሚኖር - የማይመኝ ሌላ
ታማኝ ወዳጄ ነው - የዕምነቴ ኬላ።
ብለሽ አስረጃቸው
ስለኔ ምንነት - ማወቅ ተስኗቸው
ምኗ ነው ለሚሉ - ፍቅር ላልገባቸው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤7🥰4👏2🔥1
#ከክፋት_ሰውረኝ?!
የእባብ ልብን ይዘው እርግብ ነን ከሚሉ፣
በቀበሮ ተግባር በበግ ስም ከሚምሉ፣
ቃል እየጠቀሱ በክፋት ከራሱ ፣
በተኩላ ስጋ የብግ ለምድ ከለብሱ፣
የአምላክን ስም ጠርተው በቃሉ ከማይኖሩ፣
በእግዚአብሔር ዝማሬ ሰይጣን ከሚያከብሩ፣
እግራቸው ከመቅደስ ልባቸው ከክፋት፣
ቃላቸው የንብ ማር ተግባራቸው እሬት ፣
ከሆነ ሰዎች ዘንድ እግዚአብሔር ነጥለኝ፣
ጻድቅ ባልሆን እንኳን ከክፋት ሰውረኝ?!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
የእባብ ልብን ይዘው እርግብ ነን ከሚሉ፣
በቀበሮ ተግባር በበግ ስም ከሚምሉ፣
ቃል እየጠቀሱ በክፋት ከራሱ ፣
በተኩላ ስጋ የብግ ለምድ ከለብሱ፣
የአምላክን ስም ጠርተው በቃሉ ከማይኖሩ፣
በእግዚአብሔር ዝማሬ ሰይጣን ከሚያከብሩ፣
እግራቸው ከመቅደስ ልባቸው ከክፋት፣
ቃላቸው የንብ ማር ተግባራቸው እሬት ፣
ከሆነ ሰዎች ዘንድ እግዚአብሔር ነጥለኝ፣
ጻድቅ ባልሆን እንኳን ከክፋት ሰውረኝ?!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍5🥰3👏2🔥1
#ሶሊያና
እኔን ከወንበር ላይ
ቀን ያየሁት እንባ
ቀን ያየሁት ደባ
እንቅልፍ አሳጥቶኝ
ወረቀት ላይ ወስዶኝ
እርሷን ካልጋችን ላይ
እንቅልፍ አሽኮርምሟት
ቀን ያየችው ሁሉ በቅዠት አልፎላት ……
እኔ ከቃላት ጋር ጦርነት ገጥሜ
በሰው ልጆች ጭንቀት እጅግ ተዳክሜ
በሌሊት ጭንቀቴ የቀን ስቃይ ላበርድ
ከደጋው ሃሳቤ በረሃ ስሰደድ
እንባን በፊደላት …
ፊደልን በቃላት…
ቃላትን በሃሳብ ወረቀት ላይ ልወልድ
ወረቀት ላይ ፅፌ ወረቀቱን ስቀድ …
እንዲህ እየፃፍኩኝ እያሰብኩኝ ሳለሁ
‹‹የኔ ነሽ›› የምላት …‹‹ያንተ ነኝ››
የምትል
ፍቅሬ ሶሊያና ተናገረች መሰል በቅዠቷ
መሃል …
‹‹ተመልከት ወዳጀ እኔም ካልጋየ ላይ
አንተን በመናፈቅ በስሜት ስሰቃይ ››
ቀ…ና ብየ ባያት እውነት አለው ቃሏ
ፍም መስሏል አካሏ
ከሌሊት ልብሶቿ ጡቷ ሾልኮ ወጥቷል
እጇ ተዘርግቶ እግሯ ተከፋፍቷል
እኔን በመጓጓት ደሟ ጠቆጥቶ
ፍቅሯ ተሰውቶ
ስሜቷ ተጎድቶ
አንዳች ነገር አይቶ እንደፈራ ህፃን
ፊቷ ሲሸማቀቅ ፀጉራ ሲበታተን …
ካ,ልጋው ላይ ተፅፎ አየሁት እውነቷን
ፍ...ቅ...ሬ ሶ...ሊ...ያ...ና አወራችኝ መሰል
በቅዠቷ መሃል …
አስተውል ወንድሜ …
ባንተ የቀለም ቅብ በድርሰትህ አለም
የሰወች ጥላ እንጅ አካላቸው የለም !
ባንተ ከንቱ ድርሰት በወረቀትህ ላይ
የሰው እንባ ሳይሆን ያንተው ነው የሚታይ
በሌሊት ትጋትህ በድርሰት በግጥም በቀለም ሸራህ ላይ
እኔ ውበቱ ነኝ በፍቅርህ ስሰቃይ
ይህ ሁሉ ቢሆንም
ይህ ሁሉ ቢሆንም . . . ወዲህ እንዳትመጣ
በሌሊት ትጋትህ ሃዘን ሳይቀጣ
በ,ኔ ያልጋ ድርሰት ቅፅበታቶች አሉ
ከየሰው አለም የሚመሳሰሉ
ባንተ ቀለም ሸራ በድርሰትህ ፅሁፍ
ዘመን ይታየኛል እኔን የሚያሳልፍ
ይህ ሁሉ ቢሆንም …
የሰወችን እንባ አትፃፍ ግዴለም
የፍጥረትን ሃዘን ስለህ አትዘልቅም
እውነት አለው ብለህ ሃዘንን አታልም
(ያለቀሱም ሰዎች ሃቀኞች አይደሉም )
ይልቅ የኔን ስሜት ያንተንም እንባዎች
ሁለቱን አሳየኝ
በድርሰት
በግጥም
በቀለም ሸራህ ላይ እኔን ብቻ ሳለኝ !
እኔን ብቻ ፃፈኝ !
‹‹ያልተደሰተች ሴት›› በሚል መፅሃፍህ
ዘ...ላ...ለ...ም አሻግረኝ
ዘ...ላ...ለ...ም ውሰደኝ
ዘ...ላ...ለ...ም አኑረኝ
‹‹የኔ ነሽ›› የምላት …‹‹ያንተ ነኝ››
የምትል
ፍቅሬ ሶሊያና ተናገረች መሰል በቅዠቷ
መሃል …
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ኤፍሬም ስዩም
እኔን ከወንበር ላይ
ቀን ያየሁት እንባ
ቀን ያየሁት ደባ
እንቅልፍ አሳጥቶኝ
ወረቀት ላይ ወስዶኝ
እርሷን ካልጋችን ላይ
እንቅልፍ አሽኮርምሟት
ቀን ያየችው ሁሉ በቅዠት አልፎላት ……
እኔ ከቃላት ጋር ጦርነት ገጥሜ
በሰው ልጆች ጭንቀት እጅግ ተዳክሜ
በሌሊት ጭንቀቴ የቀን ስቃይ ላበርድ
ከደጋው ሃሳቤ በረሃ ስሰደድ
እንባን በፊደላት …
ፊደልን በቃላት…
ቃላትን በሃሳብ ወረቀት ላይ ልወልድ
ወረቀት ላይ ፅፌ ወረቀቱን ስቀድ …
እንዲህ እየፃፍኩኝ እያሰብኩኝ ሳለሁ
‹‹የኔ ነሽ›› የምላት …‹‹ያንተ ነኝ››
የምትል
ፍቅሬ ሶሊያና ተናገረች መሰል በቅዠቷ
መሃል …
‹‹ተመልከት ወዳጀ እኔም ካልጋየ ላይ
አንተን በመናፈቅ በስሜት ስሰቃይ ››
ቀ…ና ብየ ባያት እውነት አለው ቃሏ
ፍም መስሏል አካሏ
ከሌሊት ልብሶቿ ጡቷ ሾልኮ ወጥቷል
እጇ ተዘርግቶ እግሯ ተከፋፍቷል
እኔን በመጓጓት ደሟ ጠቆጥቶ
ፍቅሯ ተሰውቶ
ስሜቷ ተጎድቶ
አንዳች ነገር አይቶ እንደፈራ ህፃን
ፊቷ ሲሸማቀቅ ፀጉራ ሲበታተን …
ካ,ልጋው ላይ ተፅፎ አየሁት እውነቷን
ፍ...ቅ...ሬ ሶ...ሊ...ያ...ና አወራችኝ መሰል
በቅዠቷ መሃል …
አስተውል ወንድሜ …
ባንተ የቀለም ቅብ በድርሰትህ አለም
የሰወች ጥላ እንጅ አካላቸው የለም !
ባንተ ከንቱ ድርሰት በወረቀትህ ላይ
የሰው እንባ ሳይሆን ያንተው ነው የሚታይ
በሌሊት ትጋትህ በድርሰት በግጥም በቀለም ሸራህ ላይ
እኔ ውበቱ ነኝ በፍቅርህ ስሰቃይ
ይህ ሁሉ ቢሆንም
ይህ ሁሉ ቢሆንም . . . ወዲህ እንዳትመጣ
በሌሊት ትጋትህ ሃዘን ሳይቀጣ
በ,ኔ ያልጋ ድርሰት ቅፅበታቶች አሉ
ከየሰው አለም የሚመሳሰሉ
ባንተ ቀለም ሸራ በድርሰትህ ፅሁፍ
ዘመን ይታየኛል እኔን የሚያሳልፍ
ይህ ሁሉ ቢሆንም …
የሰወችን እንባ አትፃፍ ግዴለም
የፍጥረትን ሃዘን ስለህ አትዘልቅም
እውነት አለው ብለህ ሃዘንን አታልም
(ያለቀሱም ሰዎች ሃቀኞች አይደሉም )
ይልቅ የኔን ስሜት ያንተንም እንባዎች
ሁለቱን አሳየኝ
በድርሰት
በግጥም
በቀለም ሸራህ ላይ እኔን ብቻ ሳለኝ !
እኔን ብቻ ፃፈኝ !
‹‹ያልተደሰተች ሴት›› በሚል መፅሃፍህ
ዘ...ላ...ለ...ም አሻግረኝ
ዘ...ላ...ለ...ም ውሰደኝ
ዘ...ላ...ለ...ም አኑረኝ
‹‹የኔ ነሽ›› የምላት …‹‹ያንተ ነኝ››
የምትል
ፍቅሬ ሶሊያና ተናገረች መሰል በቅዠቷ
መሃል …
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ኤፍሬም ስዩም
👍5❤4
#ተሻለህ_አትበሉኝ!
ያሽለኛል ብዬ የጠጣሁት ኮሶ
ይቆርጠኝ ጀመረ ከበሽታው ብሶ
መድሀኒት ይሆነናል ነበረ ምኞቴ
ሃኪሙን አምኜ በእምነት መጠጣቴ
ለካስ ተመረዟል መድሀኒቱ ዛሬ
ለዚህ ነበር ለካስ ብሶብኝ ማደሬ
ተሻለህ አትበሉኝ እያያችሁ ብሶ
መርዝ ሆኖ አሰቃዬኝ ይሄ የዘር ኮሶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ያሽለኛል ብዬ የጠጣሁት ኮሶ
ይቆርጠኝ ጀመረ ከበሽታው ብሶ
መድሀኒት ይሆነናል ነበረ ምኞቴ
ሃኪሙን አምኜ በእምነት መጠጣቴ
ለካስ ተመረዟል መድሀኒቱ ዛሬ
ለዚህ ነበር ለካስ ብሶብኝ ማደሬ
ተሻለህ አትበሉኝ እያያችሁ ብሶ
መርዝ ሆኖ አሰቃዬኝ ይሄ የዘር ኮሶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍8❤3👏3
በአንድ ድምብ ቦታ ላይ የጥሬ ገንዘብ እድሎችን ማግኘት ይፈልጋሉ?
እዚህ የብር ሻሎችን በፍጥነት መሳብ የሚችሉበት የብቸኝነት ዕድል ነው። ከግልጽ መረጃ፣ ራስተማሪ ጨዋታዎችና ጥሬ ገንዘብ ጨረታዎች በየቀኑ በዚህ ቻናል ይገኛሉ።
ዛሬ ብቻ ያሉትን ዕድል አታንስቱ። እንዲያው ለማስተዋወቅ ይጫኑ!
#ad InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
እዚህ የብር ሻሎችን በፍጥነት መሳብ የሚችሉበት የብቸኝነት ዕድል ነው። ከግልጽ መረጃ፣ ራስተማሪ ጨዋታዎችና ጥሬ ገንዘብ ጨረታዎች በየቀኑ በዚህ ቻናል ይገኛሉ።
ዛሬ ብቻ ያሉትን ዕድል አታንስቱ። እንዲያው ለማስተዋወቅ ይጫኑ!
#ad InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
ፈታ ደረቅ ነው። ሰዎች እዚህ የሚነገሩት ቀልዶችን መልሶ ተጫወቱበት አታውቅም! «አንዲት አሳፋሪ ጉዳይ ተነሳ፤ ገና ጠየቀኝ።» ምን አስደንጋጭ ሆኖ ተያይዛለህ? ይገቡ ያውቁ
#ad InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
#ad InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
❤1
ልብስህን ያስቀርበዋል? ወይም ልብስህ በሞት እንደተቀጣ ነው?
በBroken hearts ላይ እንደአንተ የቀጠቀሱ ነፍሶች እዚህ ተሰባበሩ!
አዲሱን መጀመር? ሆኖም ከባለፉት ቤጥሎች አትቀርፉ።
ግባ አንዴ የልብስ ቀለም ከተጠፋበት ቦታ – ከአንደኛው እቻው ወዲያ ልብስህ ይበራል!
#ad InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
በBroken hearts ላይ እንደአንተ የቀጠቀሱ ነፍሶች እዚህ ተሰባበሩ!
አዲሱን መጀመር? ሆኖም ከባለፉት ቤጥሎች አትቀርፉ።
ግባ አንዴ የልብስ ቀለም ከተጠፋበት ቦታ – ከአንደኛው እቻው ወዲያ ልብስህ ይበራል!
#ad InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
#እንደገና
እንቁጣጣሽ ነበር መስከረም ሲጠባ
አውቆ የበቀለ ወፍ ዘራሽ አበባ፡፡
ለምለም አረንጓዴ…
ያልተጠበቀ መስክ ከብት የሚግጥበት
የደመና ግላጭ የሚጫወትበት፡፡
ሌላም ብዙ ነበር
ሌላም… ደግሞ ሌላ
አለብኝ ትዝታ!
ዘመዶቼ ሳሙኝ
ጓደኞቼም ጋብዙኝ
ሊስትሮ ጨብጠኝ
ባለጋሪ ንዳ መንገዴን አሳየኝ
ያገሬ ልጅ ቆንጆ ‹‹ቤት ለእንግዳ›› በይኝ
አለብኝ ትዝታ…
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገ/ክርስቶስ ደስታ
💓 ራስዬ አላሳዉሪ።: የስኬት ተራራን እንዴት መውጣት እንደሚቻል? በስኬት የራስን አብዛኛውን ዘዴ፣ አስተዳደርና እንቅስቃሴ አግኝ፤ የግል ልምድ አግኝ! | InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
እንቁጣጣሽ ነበር መስከረም ሲጠባ
አውቆ የበቀለ ወፍ ዘራሽ አበባ፡፡
ለምለም አረንጓዴ…
ያልተጠበቀ መስክ ከብት የሚግጥበት
የደመና ግላጭ የሚጫወትበት፡፡
ሌላም ብዙ ነበር
ሌላም… ደግሞ ሌላ
አለብኝ ትዝታ!
ዘመዶቼ ሳሙኝ
ጓደኞቼም ጋብዙኝ
ሊስትሮ ጨብጠኝ
ባለጋሪ ንዳ መንገዴን አሳየኝ
ያገሬ ልጅ ቆንጆ ‹‹ቤት ለእንግዳ›› በይኝ
አለብኝ ትዝታ…
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገ/ክርስቶስ ደስታ
💓 ራስዬ አላሳዉሪ።: የስኬት ተራራን እንዴት መውጣት እንደሚቻል? በስኬት የራስን አብዛኛውን ዘዴ፣ አስተዳደርና እንቅስቃሴ አግኝ፤ የግል ልምድ አግኝ! | InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
❤1