#ሳይኖር_አለቀ!
ከአለማነው ይልቅ የአጠፋነው በዝቶ
የቃረምነው እውቀት በዜሮ ተባዝቶ
ቁሳቁስ ተከብሮ ሰውነት ተናቀ
ኖርነው ያልነው ህይወት ሳይኖር አለቀ
የጋራነት ቀርቶ የግል ያልነው በዝቶ
ጥሎ ማለፍ ሆነ እርስ በእርስ ተጋፍቶ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ከአለማነው ይልቅ የአጠፋነው በዝቶ
የቃረምነው እውቀት በዜሮ ተባዝቶ
ቁሳቁስ ተከብሮ ሰውነት ተናቀ
ኖርነው ያልነው ህይወት ሳይኖር አለቀ
የጋራነት ቀርቶ የግል ያልነው በዝቶ
ጥሎ ማለፍ ሆነ እርስ በእርስ ተጋፍቶ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍13❤4🔥1
#እጠብቅሻለሁ
እጠብቅሻለሁ ካለሁበት ቆሜ
ሀሳብና ናፍቆት ፍቅርን ተሸክሜ
እዛው ቦታ አለው እኔን ከተውሽበት
እኔንም ፍቅርሽን ጥለሽ ከሄድሽበት
እጠብቅሻለሁ ደቂቃም ሳላጎል
ምንስ ደህና ባልሆን ሰላሜ ቢታጎል
እዛው አለው ፍቅሬ ያኔ ከቆምንበት
ትተሺኝ መሄድሽን ምንስ ባላምንበት
ቆሜ ስጠብቅሽ ጭራሽ ቀን አልመርጥም እሁድ አልል ሰንበት
እጠብቅሻለሁ ፍቅሬ እዛው ሰፈር
ጥለሽኝ ከሄድሽበት ብለሽ አይንህ ላፈር
እጠብቅሻለሁ ዳግም መምጣትሽን
ምን ልቤ ቢሰጋ፤እንዲያበቃን በማሰብ
ዳግም ለአይነ ስጋ
እዛው አለው ፍቅሬ ያኔ ከቆምንበት
ከፍቅራችን አልፎ ትዳር ካሰብንበት
አዬ ትዳር እቴ እንኳን ትዳር ቀርቶ
ዛሬ አንቺም ሄደሽ ደስታው ተቀይሯል
ወደ ሀዘን ቀረርቶ
እኔ ግን የኔ ውድ ዛሬም ወድሻለሁ
አንቺ ያፈራረስሽው ፍቅሬን አድሻለሁ
ዳግም ካንቺ መሆን መጫወት እሻለሁ
ጊዜ አስተምሮሽ አንቺም እኔን ካሻሽ
ፍቅሬን ይዤ አለሁህኝ ለጥላቻሽ ምላሽ
ፍቅሬ ካንቺ በላይ ጠንቅቄ አውቅሻለሁ
መቅረትሽን ባምንም አንቺ የተውሽውን
ለተረኛ ይዤ እጠብቅሻለሁ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
እጠብቅሻለሁ ካለሁበት ቆሜ
ሀሳብና ናፍቆት ፍቅርን ተሸክሜ
እዛው ቦታ አለው እኔን ከተውሽበት
እኔንም ፍቅርሽን ጥለሽ ከሄድሽበት
እጠብቅሻለሁ ደቂቃም ሳላጎል
ምንስ ደህና ባልሆን ሰላሜ ቢታጎል
እዛው አለው ፍቅሬ ያኔ ከቆምንበት
ትተሺኝ መሄድሽን ምንስ ባላምንበት
ቆሜ ስጠብቅሽ ጭራሽ ቀን አልመርጥም እሁድ አልል ሰንበት
እጠብቅሻለሁ ፍቅሬ እዛው ሰፈር
ጥለሽኝ ከሄድሽበት ብለሽ አይንህ ላፈር
እጠብቅሻለሁ ዳግም መምጣትሽን
ምን ልቤ ቢሰጋ፤እንዲያበቃን በማሰብ
ዳግም ለአይነ ስጋ
እዛው አለው ፍቅሬ ያኔ ከቆምንበት
ከፍቅራችን አልፎ ትዳር ካሰብንበት
አዬ ትዳር እቴ እንኳን ትዳር ቀርቶ
ዛሬ አንቺም ሄደሽ ደስታው ተቀይሯል
ወደ ሀዘን ቀረርቶ
እኔ ግን የኔ ውድ ዛሬም ወድሻለሁ
አንቺ ያፈራረስሽው ፍቅሬን አድሻለሁ
ዳግም ካንቺ መሆን መጫወት እሻለሁ
ጊዜ አስተምሮሽ አንቺም እኔን ካሻሽ
ፍቅሬን ይዤ አለሁህኝ ለጥላቻሽ ምላሽ
ፍቅሬ ካንቺ በላይ ጠንቅቄ አውቅሻለሁ
መቅረትሽን ባምንም አንቺ የተውሽውን
ለተረኛ ይዤ እጠብቅሻለሁ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤6👍6🔥2👏2
#የታል_ፈገግታዬ
ያንን ጣፋጭ ጊዜ፣ምን ዋጠው ደስታየን
የታል ፈገግታየ፣ምን ወሰደው ሳቄን
እንቅልፌስ የት ሄደ፣ቅዠት የሌለበት
አይኖቼ ለ እረፍት፣የተከደኑበት
ከቶ ወዴት ገባ፣የመስኩ ቡረቃ
ስዘል የዋልኩበት፣እያቦካሁ ጭቃ
ዛሬማ ጭንቅ ነው፣ኑሮ በሰቆቃ
መልኬም ይናገራል፣ምቾት እንደሌለኝ
ሀሳቤ ተሰርቆ፣ለተመለከተኝ
ድሮን በመለስኩት፣የልጅነት ወዜን
ድሎት የሞላውን፣ያቺን ነፃነቴን
ጊዜው ተሰደደ፣ሂዷል አሁንማ
በእናት ነበር ኩራት፣ከሷ ወዲህማ
ሳቄም አይበረክት፣ድምፄም አይሰማ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ፋሲል ብስራት
ያንን ጣፋጭ ጊዜ፣ምን ዋጠው ደስታየን
የታል ፈገግታየ፣ምን ወሰደው ሳቄን
እንቅልፌስ የት ሄደ፣ቅዠት የሌለበት
አይኖቼ ለ እረፍት፣የተከደኑበት
ከቶ ወዴት ገባ፣የመስኩ ቡረቃ
ስዘል የዋልኩበት፣እያቦካሁ ጭቃ
ዛሬማ ጭንቅ ነው፣ኑሮ በሰቆቃ
መልኬም ይናገራል፣ምቾት እንደሌለኝ
ሀሳቤ ተሰርቆ፣ለተመለከተኝ
ድሮን በመለስኩት፣የልጅነት ወዜን
ድሎት የሞላውን፣ያቺን ነፃነቴን
ጊዜው ተሰደደ፣ሂዷል አሁንማ
በእናት ነበር ኩራት፣ከሷ ወዲህማ
ሳቄም አይበረክት፣ድምፄም አይሰማ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ፋሲል ብስራት
❤12🔥1
#አበባና_ውበት
የአበባ ውበቱ
ሳቢ ደም ግባቱ
የሚታይ ድምቀቱ
የማር መስሪያነቱ
እሰከሚከስም ነው
ሁሉም የሚከበው
ፍቅረኞች ለፍቅር
አልቃሾች ለቀብር
ንቦች ደግማ ለማር
ለአበባ የሚዘመር
የሚንከባከቡት
አለውህ የሚሉት
ውበቱ እስካለ ነው
ከዚያ ወዳቂ ነው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
የአበባ ውበቱ
ሳቢ ደም ግባቱ
የሚታይ ድምቀቱ
የማር መስሪያነቱ
እሰከሚከስም ነው
ሁሉም የሚከበው
ፍቅረኞች ለፍቅር
አልቃሾች ለቀብር
ንቦች ደግማ ለማር
ለአበባ የሚዘመር
የሚንከባከቡት
አለውህ የሚሉት
ውበቱ እስካለ ነው
ከዚያ ወዳቂ ነው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤11🥰10🔥4👍1😢1
#ከንፈርሽን_ስስመው 💋
ከንፈርሽን ስስመው
የአለም ጨለማ በፍቅራችን በርቶ
በአብርሃም በሳራ መመሠሉ ቀርቶ
ከምድር 'ርቆ በገነት እንዳለ
ፍቅር በ'ኔና አንቺ እየተመሠለ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
አባይ ተገድቦ ሲፈስ ወደ አገሩ
ፅጌረዳ አበቦች በመስመር ሲዘሩ
ባ'በቦቹ መሀል እየተሯሯጥን
ከፅጌረዳው ስር ፍለጋ ስኳትን
ከንፈርሽን ስስመው
ምድርን የሞሏት አበቦቹ ሁሉ
ጣፋጭ ከንፈርሽን መስለው የበቀሉ
ወደ ገነት ደሴት ሲወስደን ባቡሩ
ወፎች ለ'ኔና አንቺ ፍቅር እየዘመሩ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
አለም ለ'ኔና አንቺ ግብር እየከፈለ
ለሁሉ 'ሚበቃ ፍቅር እየታደለ
ሠማይን የሞሉት ከዋክብቱ ሁሉ
ውበትሽን ለማድመቅ የሚንቀለቀሉ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
ውዴ ይሄን ሁሉ አየሁኝ ብልሽም
አይኖቼ ተከድነው አንቺን አላዩሽም::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ከንፈርሽን ስስመው
የአለም ጨለማ በፍቅራችን በርቶ
በአብርሃም በሳራ መመሠሉ ቀርቶ
ከምድር 'ርቆ በገነት እንዳለ
ፍቅር በ'ኔና አንቺ እየተመሠለ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
አባይ ተገድቦ ሲፈስ ወደ አገሩ
ፅጌረዳ አበቦች በመስመር ሲዘሩ
ባ'በቦቹ መሀል እየተሯሯጥን
ከፅጌረዳው ስር ፍለጋ ስኳትን
ከንፈርሽን ስስመው
ምድርን የሞሏት አበቦቹ ሁሉ
ጣፋጭ ከንፈርሽን መስለው የበቀሉ
ወደ ገነት ደሴት ሲወስደን ባቡሩ
ወፎች ለ'ኔና አንቺ ፍቅር እየዘመሩ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
አለም ለ'ኔና አንቺ ግብር እየከፈለ
ለሁሉ 'ሚበቃ ፍቅር እየታደለ
ሠማይን የሞሉት ከዋክብቱ ሁሉ
ውበትሽን ለማድመቅ የሚንቀለቀሉ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
ውዴ ይሄን ሁሉ አየሁኝ ብልሽም
አይኖቼ ተከድነው አንቺን አላዩሽም::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤14👏3🥰2
#የምስኪን_ሆድ_ሲጮኽ
ለመጠራት ለመታደም ከድግሱ
የሰው ዋጋ የሰው ክብሩ ሆኖ ልብሱ
ከደጋሽ በላይ አስተናባሪ ሲያሸረግድ
ለብሰው በመጡት ለመወደድ
አዳፋ ለባሽ የእኔ ቢጤ ሲቁለጨለጭ
በአንድ እጁ ሆዱን በሌላኛው ጸጉሩን ሲነጭ
እግዚአብሔር ሰምቶ የብሶቱን አቤቱታ
አስተናባሪውን ሲያጣድፈው ድንገት ትንታ
ሁሉም ለድግሱ ለሆዱ ለከርሱ አድሮ
መስማት አቅቶት የድሃውን እንጉርጉሮ
በለበሰው ሲኮራ በሚበላው ሲያቅራራ
በጥጋብ እብሪት ግራ ቀኙን ሲንጠራራ!
ለካስ ሰው ይሞታል በድንገት በትንታ
የምስኪን ሆድ ሲጮኽ ወደ ጌታ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ለመጠራት ለመታደም ከድግሱ
የሰው ዋጋ የሰው ክብሩ ሆኖ ልብሱ
ከደጋሽ በላይ አስተናባሪ ሲያሸረግድ
ለብሰው በመጡት ለመወደድ
አዳፋ ለባሽ የእኔ ቢጤ ሲቁለጨለጭ
በአንድ እጁ ሆዱን በሌላኛው ጸጉሩን ሲነጭ
እግዚአብሔር ሰምቶ የብሶቱን አቤቱታ
አስተናባሪውን ሲያጣድፈው ድንገት ትንታ
ሁሉም ለድግሱ ለሆዱ ለከርሱ አድሮ
መስማት አቅቶት የድሃውን እንጉርጉሮ
በለበሰው ሲኮራ በሚበላው ሲያቅራራ
በጥጋብ እብሪት ግራ ቀኙን ሲንጠራራ!
ለካስ ሰው ይሞታል በድንገት በትንታ
የምስኪን ሆድ ሲጮኽ ወደ ጌታ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍6❤5🔥3🥰2👎1
🙏16❤2
#ከመሄድሽ_በፊት
ካንች ቃል ከወጣ ትተሽኝ ለመሄድ
ልብሽ ከወሰነ ከጀመረ መንገድ
ቅሪም አልልሽም
አላስገድድሽም
መንገድሽ ጨርቅ ይሁን ክፉም አይግጠምሽ
ህይወትሽ አይጉደል ኑሮሽ ይስመርልሽ
ከእኔ የተሻለ አዛኝ ሰውን ይስጥሽ
ግን ውዴ ነገ ብትመለሽ.....
አንችን እየጠበኩ ላይሆን ስለሚችል
🚶♀➡️ ከመሄድሽ በፊት....
አርቀሽ አስቢ ተስፋን ፊት አትንሻት
ስሜትን ኮንኚው በእርጋታ ዳኝነት
ለወሬ ጆሮ አትስጭ ምቀኛን አትስሚ
በዛሬ ስሜትን ለነገ አትጨልሚ
በትዕግስት መድሀኒት ኑሮሽን አክሚ
🚶♀➡️ከመሄድሽ በፊት.....
ስላለፈው ኑሮ ስላለፈው ፍቅር
ትዝታን ጠይቂው " ልሂድ? ወይስ ልቅር? "
መልሱን ይነግርሻል
ያኔ ይገባሻል
መቼም ተምረሻል
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ካንች ቃል ከወጣ ትተሽኝ ለመሄድ
ልብሽ ከወሰነ ከጀመረ መንገድ
ቅሪም አልልሽም
አላስገድድሽም
መንገድሽ ጨርቅ ይሁን ክፉም አይግጠምሽ
ህይወትሽ አይጉደል ኑሮሽ ይስመርልሽ
ከእኔ የተሻለ አዛኝ ሰውን ይስጥሽ
ግን ውዴ ነገ ብትመለሽ.....
አንችን እየጠበኩ ላይሆን ስለሚችል
🚶♀➡️ ከመሄድሽ በፊት....
አርቀሽ አስቢ ተስፋን ፊት አትንሻት
ስሜትን ኮንኚው በእርጋታ ዳኝነት
ለወሬ ጆሮ አትስጭ ምቀኛን አትስሚ
በዛሬ ስሜትን ለነገ አትጨልሚ
በትዕግስት መድሀኒት ኑሮሽን አክሚ
🚶♀➡️ከመሄድሽ በፊት.....
ስላለፈው ኑሮ ስላለፈው ፍቅር
ትዝታን ጠይቂው " ልሂድ? ወይስ ልቅር? "
መልሱን ይነግርሻል
ያኔ ይገባሻል
መቼም ተምረሻል
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤25👏6👍2🥰1
የመኖር ፈተና ምንም ቢያንገዳግድ
አታካችም ቢሆን መውጣት እና መውረድ
ነብሴን ልታደጋት ህይወቴን ዘክሬ
ሞቴም ትንሳኤ ነው በህያው መኖሬ
እኔስ ላይቀር ማለፌ
ነበርን አትርፌ
ለመሞት አልኖርም
ለመኖር ነው ሞቴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ መኮንን
አታካችም ቢሆን መውጣት እና መውረድ
ነብሴን ልታደጋት ህይወቴን ዘክሬ
ሞቴም ትንሳኤ ነው በህያው መኖሬ
እኔስ ላይቀር ማለፌ
ነበርን አትርፌ
ለመሞት አልኖርም
ለመኖር ነው ሞቴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ መኮንን
❤17👏2
#ሚስቴ_እና_ሰበቧ!
ለስጋዋ ስትኖር
-- ነፍሷን አሞኝታ
አገኘዃትና
-- ስትሳም ተኝታ
ምነው ምን በደልኩሽ?
-- ብዬ ስጠይቃት
እግሯ ስር ወድቄ
-- በእንባ ስማጸናት
እንደለመደችው
-- ሰበብ አዘጋጅታ
አንተ መስለኸኝ ነው
-- አለችኝ ተነስታ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ለስጋዋ ስትኖር
-- ነፍሷን አሞኝታ
አገኘዃትና
-- ስትሳም ተኝታ
ምነው ምን በደልኩሽ?
-- ብዬ ስጠይቃት
እግሯ ስር ወድቄ
-- በእንባ ስማጸናት
እንደለመደችው
-- ሰበብ አዘጋጅታ
አንተ መስለኸኝ ነው
-- አለችኝ ተነስታ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
😁37👏4❤2🥰1
#ጥላችን_አይደለም
በህይወት ጎዳና ፈጥነን ስንራመድ
ወይም በዝግታ በሀሳብ ስንሄድ
ስንቆም የሚቆመው ሲመሽ የማናየው
ጥላችን አይደለም ለካስ ሞታችን ነው!
የሚከታተለን በእርምጃችን መጠን
ስንፈጥን ስንዘገይ ሁሌ ሚከተለን
ጥላችን አይደለም የምስላችን ቅኔ
ሞታችን ነው ባይ ነኝ እንደገባኝ እኔ
ሲመሽ ተደብቆ ሲነጋ ተገልጦ
ስንተኛ ተኝቶ ስንሮጥ እሮጦ
የያዝነውን ይዞ ስንበላ በልቶ
ሁልግዜም አብሮን ነው ሞታችን አድብቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
በህይወት ጎዳና ፈጥነን ስንራመድ
ወይም በዝግታ በሀሳብ ስንሄድ
ስንቆም የሚቆመው ሲመሽ የማናየው
ጥላችን አይደለም ለካስ ሞታችን ነው!
የሚከታተለን በእርምጃችን መጠን
ስንፈጥን ስንዘገይ ሁሌ ሚከተለን
ጥላችን አይደለም የምስላችን ቅኔ
ሞታችን ነው ባይ ነኝ እንደገባኝ እኔ
ሲመሽ ተደብቆ ሲነጋ ተገልጦ
ስንተኛ ተኝቶ ስንሮጥ እሮጦ
የያዝነውን ይዞ ስንበላ በልቶ
ሁልግዜም አብሮን ነው ሞታችን አድብቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍17❤5🥰1👏1
" #ይስጥሽ"
ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ
ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ
ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ
ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤
ይስጥሽ ከፀጉሬ ከአናቴ ላይ ዘግኖ
ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ
አወይ ፀጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ
ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ
እቴ.....
ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ
ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ
ከዓይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ
እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ።
እቴ....
እጄን ብትፈልጊ እግሬን ብትፈልጊ
አንገቴን ደረቴን
ተሰጥኦ ሀሳቤን
ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ
እግዜር ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ
ያስቀርልኝ ዓይኔን
አንቺን ማየት ብቻ
ያኖረኛል እኔን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ
ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ
ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ
ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤
ይስጥሽ ከፀጉሬ ከአናቴ ላይ ዘግኖ
ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ
አወይ ፀጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ
ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ
እቴ.....
ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ
ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ
ከዓይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ
እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ።
እቴ....
እጄን ብትፈልጊ እግሬን ብትፈልጊ
አንገቴን ደረቴን
ተሰጥኦ ሀሳቤን
ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ
እግዜር ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ
ያስቀርልኝ ዓይኔን
አንቺን ማየት ብቻ
ያኖረኛል እኔን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤18👏7🔥2
#የኔን_ቀን_ገድዬ
የደላኝ መስዬ
ብሶቴን አምቄ
ወደ ውስጤ አልቅሼ
ቀን ብገፋ ስቄ
የኔ ባል ሞኝ ነው
ፍቅር ይሰጠኛል
ስጠላው አያውቅም
ብለሽ አምተሽኛል
በዚህ እኩይ አለም
አምላክ ፊት ቀርቤ
እኔ ለታማሁኝ
ደጁ ተንበርክኬ
የኔን ቀን ገድዬ
ለሷ እጨነቃለሁ
ይቅር በላት እያልኩ
ስፀልይ አድራለሁ
አታውቀውምና
እሷ የኔን ነገር
ከመኖር ያለፈ
እንዴት እንደምኖር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
የደላኝ መስዬ
ብሶቴን አምቄ
ወደ ውስጤ አልቅሼ
ቀን ብገፋ ስቄ
የኔ ባል ሞኝ ነው
ፍቅር ይሰጠኛል
ስጠላው አያውቅም
ብለሽ አምተሽኛል
በዚህ እኩይ አለም
አምላክ ፊት ቀርቤ
እኔ ለታማሁኝ
ደጁ ተንበርክኬ
የኔን ቀን ገድዬ
ለሷ እጨነቃለሁ
ይቅር በላት እያልኩ
ስፀልይ አድራለሁ
አታውቀውምና
እሷ የኔን ነገር
ከመኖር ያለፈ
እንዴት እንደምኖር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤21🥰2🔥1👏1
#ታውቂያለሽ_አይደለ?
ስላንቺ በማሰብ
ዘመኔ ማለፉን
አንቺን በመናፈቅ
እምባየ ማለቁን
አሻግሬ ሳይሽ
እይኔ መደብዘዙን
ኮቴሽን በማድመጥ
ጆሮየ መድከሙን
ታውቂያለሽ አይደለ
ቆሜ ስጠብቅሽ
ቆየኝ ባልሽኝ ስፍራ
በረዶና ዝናብ
በላየ እንዳባራ
እንቅልፍ አልባ
ቀናት በኔ እንደነጎዱ
ጀምበር ከጨረቃ እንደተዋሀዱ
አውቃለሁ አታውቂም አንዳቹንም ነገር
እኔ መውደድ እንጂ አልችልም መናገር፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዘላለም ምህረቱ
ስላንቺ በማሰብ
ዘመኔ ማለፉን
አንቺን በመናፈቅ
እምባየ ማለቁን
አሻግሬ ሳይሽ
እይኔ መደብዘዙን
ኮቴሽን በማድመጥ
ጆሮየ መድከሙን
ታውቂያለሽ አይደለ
ቆሜ ስጠብቅሽ
ቆየኝ ባልሽኝ ስፍራ
በረዶና ዝናብ
በላየ እንዳባራ
እንቅልፍ አልባ
ቀናት በኔ እንደነጎዱ
ጀምበር ከጨረቃ እንደተዋሀዱ
አውቃለሁ አታውቂም አንዳቹንም ነገር
እኔ መውደድ እንጂ አልችልም መናገር፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዘላለም ምህረቱ
❤15👍6🔥5👏2🥰1
#ቃል_ብዬ_ጠራሁሽ
ስላንች ለመፃፍ ብእር እቀርፅና
ቀለሙን አቅልሜ ፈቅፍቄ ብራና
ፊደልና ቃላት እንደልጅ እያማጥኩ
ሀረግ እየመዘዝኩ ምሳሌ እየጠቀስኩ
ቃል ባጣው ልሳኔ ስፅፍ ውዬ አድሬ
ገልጨሽ ሳይበቃኝ ትደርቃለች ብእሬ
ደግሞ ተመልሼ................
ደሜን አንጠፍጥፌ ቀለሙን አቀለምኩ
አጥንቴን ፈቅፍቄ ላንች ብእር ቀረፅኩ
ብእሬን በደሜ ነክሬ ሳወጣው
አንችን እገልፅበት ቅንጣት ቃላት አጣው
ለካንስ ቃልዬ!!!
በፍቅር ነሁልሎ መንፈስ ከደከመ
ናፍቆት አገርጥቶት ልብ ከታመመ
እንኳን ቃል ተዋቅሮ ቅኔ ሊመሰጠር
ደግሞ ስንኝ ሁኖ ግጥም ሊደረደር
ደህና አደርክ ሲባል ለእግዚአብሄር ይመስገን
አንደበት ቃል ያጣል ሲመርቁት ለአሜን
ለዛ ነው ቃልዬ!!!
መግለጫ ቃል ባጣ እልፍ ዘመን ሙሉ
የብራናዬ ገፅ ግራ ገብቶት ውሉ
እየደጋገምኩኝ የፃፍኩት አንድ ቃል
እ
ን
ዲ
ህ
ብቻ ይላል
ሌላ ቃል ተገኝቶ
ወይ ልሳንህ ፈቶ
ህቡእ በሆነ ቃል እስከምትገልፃት
ቃልህ እሷ ነችና ቃሌ ብለህ ጥራት
እናም አንች ቃሌ ነሽ ሀረግና ስንኝ
ካጠገቤ ሁነሽ ሰርክ የምትርቢኝ
እናም የኔ ንግስት
ገፅሽን አድምቄ በልቤ መዝገብ ላይ
ቃሌ ብዬ ፃፍኩሽ ቃል አጣው ቃሌ ላይ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ስላንች ለመፃፍ ብእር እቀርፅና
ቀለሙን አቅልሜ ፈቅፍቄ ብራና
ፊደልና ቃላት እንደልጅ እያማጥኩ
ሀረግ እየመዘዝኩ ምሳሌ እየጠቀስኩ
ቃል ባጣው ልሳኔ ስፅፍ ውዬ አድሬ
ገልጨሽ ሳይበቃኝ ትደርቃለች ብእሬ
ደግሞ ተመልሼ................
ደሜን አንጠፍጥፌ ቀለሙን አቀለምኩ
አጥንቴን ፈቅፍቄ ላንች ብእር ቀረፅኩ
ብእሬን በደሜ ነክሬ ሳወጣው
አንችን እገልፅበት ቅንጣት ቃላት አጣው
ለካንስ ቃልዬ!!!
በፍቅር ነሁልሎ መንፈስ ከደከመ
ናፍቆት አገርጥቶት ልብ ከታመመ
እንኳን ቃል ተዋቅሮ ቅኔ ሊመሰጠር
ደግሞ ስንኝ ሁኖ ግጥም ሊደረደር
ደህና አደርክ ሲባል ለእግዚአብሄር ይመስገን
አንደበት ቃል ያጣል ሲመርቁት ለአሜን
ለዛ ነው ቃልዬ!!!
መግለጫ ቃል ባጣ እልፍ ዘመን ሙሉ
የብራናዬ ገፅ ግራ ገብቶት ውሉ
እየደጋገምኩኝ የፃፍኩት አንድ ቃል
እ
ን
ዲ
ህ
ብቻ ይላል
ሌላ ቃል ተገኝቶ
ወይ ልሳንህ ፈቶ
ህቡእ በሆነ ቃል እስከምትገልፃት
ቃልህ እሷ ነችና ቃሌ ብለህ ጥራት
እናም አንች ቃሌ ነሽ ሀረግና ስንኝ
ካጠገቤ ሁነሽ ሰርክ የምትርቢኝ
እናም የኔ ንግስት
ገፅሽን አድምቄ በልቤ መዝገብ ላይ
ቃሌ ብዬ ፃፍኩሽ ቃል አጣው ቃሌ ላይ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤10👏3👍1🔥1🥰1
#ዘርን_ለማስቆጠር
እንጋባ አትበይኝ ግራ ገብቶኝ ሳለ፤
ተጋቦቶ ለመውለድ ነፃነት የት አለ?
ወልዶ ለመከበረ ጋብቻ ቅዱስ ነው፤
የሚወለደው ልጅ መኖሪያ ከሌለው!
በይ እስኪ ንገሪኝ? አንቺ ግራ ጎኔ፤
በነፃነት አድጎ ሰው በመባል ቅኔ፤
በኢትዮጵያዊነት ካልኮራ ዓይኔ በዐይኔ፤
ለመሳቀቅማ አይበቃም ወይ የእኔ።
ሀገርን ሳልሰራ ሰው መሆን ሳይቀድም፤
ዘርን ለማስቆጠር እኔስ ልጅ አልወልድም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
እንጋባ አትበይኝ ግራ ገብቶኝ ሳለ፤
ተጋቦቶ ለመውለድ ነፃነት የት አለ?
ወልዶ ለመከበረ ጋብቻ ቅዱስ ነው፤
የሚወለደው ልጅ መኖሪያ ከሌለው!
በይ እስኪ ንገሪኝ? አንቺ ግራ ጎኔ፤
በነፃነት አድጎ ሰው በመባል ቅኔ፤
በኢትዮጵያዊነት ካልኮራ ዓይኔ በዐይኔ፤
ለመሳቀቅማ አይበቃም ወይ የእኔ።
ሀገርን ሳልሰራ ሰው መሆን ሳይቀድም፤
ዘርን ለማስቆጠር እኔስ ልጅ አልወልድም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤10👏7👍1
#ፍቅር_አለቀሰ
ፍቅርን ስፈልገው ቀናቶች አለፉ
ፈለግኩት ፈለግኩት ድካም ሆነ ትርፉ
አጋጣሚ ሆኖ ተደብቆ አየሁት
አላምን ስላልኩኝ ምክንያቱን ጠየኩት
"ፍቅር አንተው ነህ ወይ?" ብዬ ብጠይቀው
ምንም መልስ ሳይመልስ እንባ ተናነቀው
ግራ ገባኝና ባግራሞት አየሁት
ቆይ ፍቅር ደስታ ነው ሲባል ሰምቻለሁ
ታድያ ያንተ ለቅሶ ከየት የመጣ ነው?
ፍቅርም መለሰልኝ አይኑን መሬት ተክሎ
መናገር ጀመረ ቃላትን ቀጣጥሎ
"ደስታማ ደስታ ነኝ ላወቀው ሚስጥሬን
ከደስታም በላይ ነኝ ከተረዱኝ እኔን
ያስለቀሰኝ ነገር ሆድ ሆዴን ያስባሰው
በኔ ስም መነገድ መቸ አቆመ ሰው
አፈቀርኩሽ ብሎ ሲዋሻት በኔ ስም
ማሬ ውዴ ብላ ከድታው ስትሄድ እሷም
በኔ ሲጫወቱ የሀሰት ጨዋታ
በኔ ሲባልጉ በኔ ስም ሲምታታ
በውሸት ዓለም ሆነው በኔ ስም ሲጠሩ
እንዴት አላነባ ካልረባ ነገሩ"
ብሎ መለሰልኝ ፍቅር በቀስታ
አንገቱን ቢያስደፉው የሀሰት ጨዋታ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ፍቅርን ስፈልገው ቀናቶች አለፉ
ፈለግኩት ፈለግኩት ድካም ሆነ ትርፉ
አጋጣሚ ሆኖ ተደብቆ አየሁት
አላምን ስላልኩኝ ምክንያቱን ጠየኩት
"ፍቅር አንተው ነህ ወይ?" ብዬ ብጠይቀው
ምንም መልስ ሳይመልስ እንባ ተናነቀው
ግራ ገባኝና ባግራሞት አየሁት
ቆይ ፍቅር ደስታ ነው ሲባል ሰምቻለሁ
ታድያ ያንተ ለቅሶ ከየት የመጣ ነው?
ፍቅርም መለሰልኝ አይኑን መሬት ተክሎ
መናገር ጀመረ ቃላትን ቀጣጥሎ
"ደስታማ ደስታ ነኝ ላወቀው ሚስጥሬን
ከደስታም በላይ ነኝ ከተረዱኝ እኔን
ያስለቀሰኝ ነገር ሆድ ሆዴን ያስባሰው
በኔ ስም መነገድ መቸ አቆመ ሰው
አፈቀርኩሽ ብሎ ሲዋሻት በኔ ስም
ማሬ ውዴ ብላ ከድታው ስትሄድ እሷም
በኔ ሲጫወቱ የሀሰት ጨዋታ
በኔ ሲባልጉ በኔ ስም ሲምታታ
በውሸት ዓለም ሆነው በኔ ስም ሲጠሩ
እንዴት አላነባ ካልረባ ነገሩ"
ብሎ መለሰልኝ ፍቅር በቀስታ
አንገቱን ቢያስደፉው የሀሰት ጨዋታ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤20👏9✍2🔥2🥰1
ጭር አለ ከተማው ጭር አለ መንገዱ
ያ ስምንተኛው ሽህ ተገለጠ ጉዱ
ሰው ሁሉ ተሳቆ ፈርቶት አንዱን አንዱ
እስከዚህ አይሎ ሰው ከሰው ሽሽቱ
ክተት ብሎ ገባ ሁሉም በየቤቱ
ጭር አለ መንገዱ ጭር አለ ከተማው
ክፉ ዘር ሲበዛ ይህን ነው የምንሰማው
እንለያይ ብለን ስንጮህ ስንፎክር
በዘር ተለያይተን አንዱ አንዱን ሲያባርር
ታሪክ እያዛባን ነገር ስንመነዝር
ኮሮና እብዱ መጣ እንደ ከብት የሚያጉር።
እንለያይ ብለን ይሄው ተለያየን
መሸሽ ጀምረናል ሰውን ሰው እያየን።
ሕሊናችን ሞቶ መለያየት ወደን
ሰው ሰውን ሸሸ በባይረስ ተገደን
ያ ስምንተኛው ሽህ ተገለጠ ጉዱ
ጭር አለ ከተማው ጭር አለ መንገዱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ መምህር ግርማ
ያ ስምንተኛው ሽህ ተገለጠ ጉዱ
ሰው ሁሉ ተሳቆ ፈርቶት አንዱን አንዱ
እስከዚህ አይሎ ሰው ከሰው ሽሽቱ
ክተት ብሎ ገባ ሁሉም በየቤቱ
ጭር አለ መንገዱ ጭር አለ ከተማው
ክፉ ዘር ሲበዛ ይህን ነው የምንሰማው
እንለያይ ብለን ስንጮህ ስንፎክር
በዘር ተለያይተን አንዱ አንዱን ሲያባርር
ታሪክ እያዛባን ነገር ስንመነዝር
ኮሮና እብዱ መጣ እንደ ከብት የሚያጉር።
እንለያይ ብለን ይሄው ተለያየን
መሸሽ ጀምረናል ሰውን ሰው እያየን።
ሕሊናችን ሞቶ መለያየት ወደን
ሰው ሰውን ሸሸ በባይረስ ተገደን
ያ ስምንተኛው ሽህ ተገለጠ ጉዱ
ጭር አለ ከተማው ጭር አለ መንገዱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ መምህር ግርማ
👍3❤2🫡2
ነድፋኛለች ብዬ - በውበቷ ምትሃት፣
በይፋ ከስሼ- ፍርድ እንዳላቀርባት
ለካስ እሷ ራሷ - መፅሐፍ ገላጭ ናት
ከፊት እሷን መሳይ - የጠይም ወላላ፣
በድንቡሽ ብርጭቆ - ወይን እየተሞላ፣
እሱን እየጠጡ -
ለሰስ ባለ ዜማ - እየተመሰጡ
ደግሞ በመሃሉ - እየተቃበጡ
ፍቅር ፍቅር ብቻ - እየመሰጠሩ፣
ዓለምን ረስተው - ምናለ ቢኖሩ፣
ጨለምለም ባለ የብርሃን ድባብ ውስጥ፤
እልም ብሎ መጥፋት - ጭልጥ ብሎ ቅልጥ፤
በልቤ ትርታ - በነፍስ ቋንቋዬ፣
እየደባበስኳት - ምነ ባዜምኩላት - አንቺ ሆዬ ብዬ፤
በይፋ ከስሼ- ፍርድ እንዳላቀርባት
ለካስ እሷ ራሷ - መፅሐፍ ገላጭ ናት
ከፊት እሷን መሳይ - የጠይም ወላላ፣
በድንቡሽ ብርጭቆ - ወይን እየተሞላ፣
እሱን እየጠጡ -
ለሰስ ባለ ዜማ - እየተመሰጡ
ደግሞ በመሃሉ - እየተቃበጡ
ፍቅር ፍቅር ብቻ - እየመሰጠሩ፣
ዓለምን ረስተው - ምናለ ቢኖሩ፣
ጨለምለም ባለ የብርሃን ድባብ ውስጥ፤
እልም ብሎ መጥፋት - ጭልጥ ብሎ ቅልጥ፤
በልቤ ትርታ - በነፍስ ቋንቋዬ፣
እየደባበስኳት - ምነ ባዜምኩላት - አንቺ ሆዬ ብዬ፤
❤8👏2🔥1
#ስጠብቅሽ_ልኑር
ቀናቶች ቢረዝሙ ቢቆጠሩ አመታት
ግዜ ቢለያየን ቢያልፉብን ዘመናት
ከልብሽ ብጠፋም ከትዉስታሽ ጓዳ
በስቃይ ታስሬ በናፍቆት ብጎዳ
ህልሜም ባይሳካ የሆዴን ባላገኝ
በደስታየ ዘመን ባይተዋር ቢያረገኝ
ግዴለም ችላለሁ ሁሉን ነገር ችዬ
እጠብቅሻለሁ ልቤን አባብዬ
የሀሳብ በረዶ ይጠለቅ በአናቴ
ይደንዝዝ አካሌ ይድከሙ ጉልበቴ
ትመጪ እንደሁ እያልኩ በተስፋ ልጠብቅ
እልፍ ግዜ ይለፍ ወዜ ሁሉ ይድቀቅ
ምን ያደርግልኛል ካንች ወድያ ኑሮ
ፍቅርሽ ይበቃኛል የስንቅሽ ቋጠሮ
በትዝታሽ ዋሻ እራሴን ደብቄ
በምናቤ ስየ ፍቅርሽን ሰንቄ
እጠብቅሻለሁ በተሰጠኝ እድሜ
ባንች ናፍቆት ፍቅር ካልሞትኩኝ ታምሜ
.....አዎ...
ስጠብቅሽ ልኑር ሳለሁ በህይዎቴ
ፍቅርም ባንች ይብቃኝ ይምከን ፍላጎቴ ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ናቲ ጥላሁን
ቀናቶች ቢረዝሙ ቢቆጠሩ አመታት
ግዜ ቢለያየን ቢያልፉብን ዘመናት
ከልብሽ ብጠፋም ከትዉስታሽ ጓዳ
በስቃይ ታስሬ በናፍቆት ብጎዳ
ህልሜም ባይሳካ የሆዴን ባላገኝ
በደስታየ ዘመን ባይተዋር ቢያረገኝ
ግዴለም ችላለሁ ሁሉን ነገር ችዬ
እጠብቅሻለሁ ልቤን አባብዬ
የሀሳብ በረዶ ይጠለቅ በአናቴ
ይደንዝዝ አካሌ ይድከሙ ጉልበቴ
ትመጪ እንደሁ እያልኩ በተስፋ ልጠብቅ
እልፍ ግዜ ይለፍ ወዜ ሁሉ ይድቀቅ
ምን ያደርግልኛል ካንች ወድያ ኑሮ
ፍቅርሽ ይበቃኛል የስንቅሽ ቋጠሮ
በትዝታሽ ዋሻ እራሴን ደብቄ
በምናቤ ስየ ፍቅርሽን ሰንቄ
እጠብቅሻለሁ በተሰጠኝ እድሜ
ባንች ናፍቆት ፍቅር ካልሞትኩኝ ታምሜ
.....አዎ...
ስጠብቅሽ ልኑር ሳለሁ በህይዎቴ
ፍቅርም ባንች ይብቃኝ ይምከን ፍላጎቴ ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ናቲ ጥላሁን
❤15🥰2
#ስሞት_አታልቅሱ!
ጎርፍ በላዬ ሲሄድ ዝም ካላችሁኝ፤
ምጠጣው አጥቸ ከንፍሬ እንዲህ ደርቆ ካላጠጣችሁኝ፤
ስትበሉ እያየሁ ወስፍቴ እየጮከ ካላበላችሁኝ፤
ምለብሰው አጥቸ እንዲህ ስንቀጠቀጥ፤
ልብስክን በሳጥን ቆልፈህ ካስቀመጥህ፤
ለምን ትጮሀለህ?፤
ለምን ታነባለህ?፤
ለምንስ ደረትክን ትደቁሰዋለህ?፤
"ማን ገደለው?" ቢሉህ እስኪ ማን ትላለህ?፤
እንባ ምን ሊጠቅመኝ እንባ ምን ሊፈይድ?፤
ያለቀሰ ሳይሆን በቁም ሚረዳ ነው ባምላክ የሚወደድ፤
እናልህ ወገኔ...
ደረትክን አትድቃ ሙሾው ገደል ይግባ፤
ገለከኝ አታልቅስ ይቅርብኝ ያዞ እንባ።
ከልብ ካዘናችሁ በነፍሴ ድረሱ፤
እናተ ገላችሁ ስሞት አታልቅሱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ጎርፍ በላዬ ሲሄድ ዝም ካላችሁኝ፤
ምጠጣው አጥቸ ከንፍሬ እንዲህ ደርቆ ካላጠጣችሁኝ፤
ስትበሉ እያየሁ ወስፍቴ እየጮከ ካላበላችሁኝ፤
ምለብሰው አጥቸ እንዲህ ስንቀጠቀጥ፤
ልብስክን በሳጥን ቆልፈህ ካስቀመጥህ፤
ለምን ትጮሀለህ?፤
ለምን ታነባለህ?፤
ለምንስ ደረትክን ትደቁሰዋለህ?፤
"ማን ገደለው?" ቢሉህ እስኪ ማን ትላለህ?፤
እንባ ምን ሊጠቅመኝ እንባ ምን ሊፈይድ?፤
ያለቀሰ ሳይሆን በቁም ሚረዳ ነው ባምላክ የሚወደድ፤
እናልህ ወገኔ...
ደረትክን አትድቃ ሙሾው ገደል ይግባ፤
ገለከኝ አታልቅስ ይቅርብኝ ያዞ እንባ።
ከልብ ካዘናችሁ በነፍሴ ድረሱ፤
እናተ ገላችሁ ስሞት አታልቅሱ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤14🔥1