#የሰሞኑን_እንጃ
ጋቢዬን ደርቤ
ውስጤን ይበርደኛል
ከእሳቱም ቀርቤ
ያንቀጠቅጠኛል
ሰው መሀልም ሆኜ
ሰው ይናፍቀኛል
ከራሴው ዝምታ
ጩኸት ይሰማኛል
ለወትሮ የወደድኩት
ዛሬ አስጠልቶኛል
የሰሞኑን እንጃ
ፍርሀት ያርደኛል
ልቤ ሁሉን ጠልቶ
አንቺን ብቻ ይለኛል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ጋቢዬን ደርቤ
ውስጤን ይበርደኛል
ከእሳቱም ቀርቤ
ያንቀጠቅጠኛል
ሰው መሀልም ሆኜ
ሰው ይናፍቀኛል
ከራሴው ዝምታ
ጩኸት ይሰማኛል
ለወትሮ የወደድኩት
ዛሬ አስጠልቶኛል
የሰሞኑን እንጃ
ፍርሀት ያርደኛል
ልቤ ሁሉን ጠልቶ
አንቺን ብቻ ይለኛል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤17🥰10👍1
#ቅበጭ_እንደ_ልብሽ
በጫንቃዬ ለዋልሽ ሸክሙ ላልከበደኝ፣
ቅብጠትሽ የመጨ እኔን ከተመቸኝ፣
ምን አርጊ ይሉሻል? ቢሉሽም ተያቸው፣
በእራሴ ትክሻ ምን ቁርጥ አርጓቸው?
ቅበጭ እንደ ልብሽ ደስ ይበልሽ በርቺ፣
ተከፍተሽ ሳይሽ ነው የሚጨንቀኝ ላንቺ፣
ምን ይሉኝ አትበይ ካሉሽም ተያቸው፣
እነርሱን ካልነካሽ ምን ጥልቅ አርጓቸው?
እንኳንስ ጫንቃዬን ልቤንም ወስደሻል፣
ገና እጨምራለሁ ላንቺ እኮ ያንስሻል፣
ብቻ አደራ ውዴ ከሌላ አትቅበጭ፣
በእኔ ሰውነት ላይ ሰክነሽ ተቀመጭ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
በጫንቃዬ ለዋልሽ ሸክሙ ላልከበደኝ፣
ቅብጠትሽ የመጨ እኔን ከተመቸኝ፣
ምን አርጊ ይሉሻል? ቢሉሽም ተያቸው፣
በእራሴ ትክሻ ምን ቁርጥ አርጓቸው?
ቅበጭ እንደ ልብሽ ደስ ይበልሽ በርቺ፣
ተከፍተሽ ሳይሽ ነው የሚጨንቀኝ ላንቺ፣
ምን ይሉኝ አትበይ ካሉሽም ተያቸው፣
እነርሱን ካልነካሽ ምን ጥልቅ አርጓቸው?
እንኳንስ ጫንቃዬን ልቤንም ወስደሻል፣
ገና እጨምራለሁ ላንቺ እኮ ያንስሻል፣
ብቻ አደራ ውዴ ከሌላ አትቅበጭ፣
በእኔ ሰውነት ላይ ሰክነሽ ተቀመጭ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👏13❤9👍2
#እንደዚም_አለንዴ?
ምን ልበል ስላንቺ ቃላቶቼም ፈሩ፡
አንደበቴም ሞተ ሳይገባ ካፈሩ፡
አይኔም አላይ አለ ግርማሽ አሳውሮት፡
እግሬም አልፀናልኝ ክብርሽ አሸብሮት፡
እጄም ከፍ አለብኝ ድንቅ ውበትሽ ማርኮት፡
እንደዚም አለንዴ ማማር በተፈጥሮ፡
ሰዓሊ ማይስለው ቀለምን አጣምሮ፡
ፀሀፊ ማይገልፀው በብዕር ሞንጭሮ፡
ዘፋኝ የማይዘፍነው ድምፁን አሳምሮ፡
ምሁር ማይደርስበት ዝንት ተመራምሮ፡
ጨረቃን ሰማሗት እሪ ወየው ስትል፡
ፀሀይም በንዴት ፍጥረትን ስታግል፡
ኮከቧም አዝና ወዲያ ስትኮበልል፡
ደመናም ተከፍቶ ዞር ሲል ገለል፡
እንዲ ብስጭት ያሉት ዳሩ ባንቺ ላይ ነው፡
የጨረቃን ድምቀት ለራስሽ አርገሽው፡
የከዋክብትን ውበት በድፍረት ዘርፈሽው፡
የፀሀይን ሙቀት ይዘሽ አፍነሽው፡
የደመናን ግርማ በሀይል ነጥቀሽው፡
አኖረብሽ እንደው ያን ፀዳል ጥበቡን፡
ውበቱን ደፋብሽ ከሱ የሆነውን፡
እኔም ተገርሜ በውበትሽ ውዴ፡
ብዬ ትቼዋለው እንደዚም አለንዴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ምን ልበል ስላንቺ ቃላቶቼም ፈሩ፡
አንደበቴም ሞተ ሳይገባ ካፈሩ፡
አይኔም አላይ አለ ግርማሽ አሳውሮት፡
እግሬም አልፀናልኝ ክብርሽ አሸብሮት፡
እጄም ከፍ አለብኝ ድንቅ ውበትሽ ማርኮት፡
እንደዚም አለንዴ ማማር በተፈጥሮ፡
ሰዓሊ ማይስለው ቀለምን አጣምሮ፡
ፀሀፊ ማይገልፀው በብዕር ሞንጭሮ፡
ዘፋኝ የማይዘፍነው ድምፁን አሳምሮ፡
ምሁር ማይደርስበት ዝንት ተመራምሮ፡
ጨረቃን ሰማሗት እሪ ወየው ስትል፡
ፀሀይም በንዴት ፍጥረትን ስታግል፡
ኮከቧም አዝና ወዲያ ስትኮበልል፡
ደመናም ተከፍቶ ዞር ሲል ገለል፡
እንዲ ብስጭት ያሉት ዳሩ ባንቺ ላይ ነው፡
የጨረቃን ድምቀት ለራስሽ አርገሽው፡
የከዋክብትን ውበት በድፍረት ዘርፈሽው፡
የፀሀይን ሙቀት ይዘሽ አፍነሽው፡
የደመናን ግርማ በሀይል ነጥቀሽው፡
አኖረብሽ እንደው ያን ፀዳል ጥበቡን፡
ውበቱን ደፋብሽ ከሱ የሆነውን፡
እኔም ተገርሜ በውበትሽ ውዴ፡
ብዬ ትቼዋለው እንደዚም አለንዴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍12❤5🔥1🥰1
#በመኖር_አጸድ_ውስጥ
ጊዜ ከሰው መሀል- መርጦ ሲያቀማጥል
ማጣት አለ ደሞ፥
የወለዱትን ልጅ፥ ጉድፍ ላይ የሚያስጥል
በተፈሰከ ቀን፥ ጾምን የሚያስቀጥል::
እድልና ትግል በሚጫወቱበት
በደልዳላው ስፍራ
አለቃና ጭፍራ-
ቃል ሲለዋወጡ፥ ውልና መሀላ
“አብረን እናድጋለን” ቢባል ለይስሙላ
ወንዙን ሳያጎድል ፥ሐይቁ መች ሊሞላ፤
ጸሐይ ብትወጣ
ፍጥረት በጠቅላላው ጸጋዋን ቢቀበል
የደመናም ጠበል፥
ለሁሉ ቢደርስም
አንደኛው አያድግም፥ አንዱን ሳያከስም::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ጊዜ ከሰው መሀል- መርጦ ሲያቀማጥል
ማጣት አለ ደሞ፥
የወለዱትን ልጅ፥ ጉድፍ ላይ የሚያስጥል
በተፈሰከ ቀን፥ ጾምን የሚያስቀጥል::
እድልና ትግል በሚጫወቱበት
በደልዳላው ስፍራ
አለቃና ጭፍራ-
ቃል ሲለዋወጡ፥ ውልና መሀላ
“አብረን እናድጋለን” ቢባል ለይስሙላ
ወንዙን ሳያጎድል ፥ሐይቁ መች ሊሞላ፤
ጸሐይ ብትወጣ
ፍጥረት በጠቅላላው ጸጋዋን ቢቀበል
የደመናም ጠበል፥
ለሁሉ ቢደርስም
አንደኛው አያድግም፥ አንዱን ሳያከስም::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤12🔥3👏2🥰1
ንገሪኝ ካልክማ •••••••
ትተኸው የሄድከው ያ የዋሁ ልቤ
በመቆየትህ ልክ መቅረትህን አምኖ
ያንተን ትውስታዎች በሌላ ሸፍኖ
ከትዝታህ ባህር ከናፍቆትህ ሞገድ
ከብቸኝነት ጥግ ከረጂሙ መንገድ
ሊወጣ አሰበና ከሌላው ሊላመድ
መግባባት ጀምሮ መተዋወቅ ጣረ
አንዱ አልሆንህ ሲለው ሌላ እየሞከረ
ብዙ በጋ ክረምት በመሀል በረረ
ግና ምን ዋጋ አለው •••
የየዋህ ልቤ ልክ ባንተ ተመጥኖ
ላንዱ እየጠበበ ላንዱ ሰፊ ሁኖ
ካብሮነት ተቃርኖ•••
ዛሬም ለብቻው ነው ከፍቅር እርቆ
መርሳት ያልቻለውን ትዝታህን አንቆ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ትተኸው የሄድከው ያ የዋሁ ልቤ
በመቆየትህ ልክ መቅረትህን አምኖ
ያንተን ትውስታዎች በሌላ ሸፍኖ
ከትዝታህ ባህር ከናፍቆትህ ሞገድ
ከብቸኝነት ጥግ ከረጂሙ መንገድ
ሊወጣ አሰበና ከሌላው ሊላመድ
መግባባት ጀምሮ መተዋወቅ ጣረ
አንዱ አልሆንህ ሲለው ሌላ እየሞከረ
ብዙ በጋ ክረምት በመሀል በረረ
ግና ምን ዋጋ አለው •••
የየዋህ ልቤ ልክ ባንተ ተመጥኖ
ላንዱ እየጠበበ ላንዱ ሰፊ ሁኖ
ካብሮነት ተቃርኖ•••
ዛሬም ለብቻው ነው ከፍቅር እርቆ
መርሳት ያልቻለውን ትዝታህን አንቆ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤20👏6👍2💔2🔥1
#ለከርሞ_ልጠብቅ!
ክሴን የሚሰማ አድማጭ ዳኛ ጠፍቶ
ይግባኝ በል ይሉኛል የቀደመው ቀርቶ
ቀድሞ ፍትህ ጎድሎ ሚዛኑ በገንዘብ
ሰሚ ጆሮ የለም ይግባኝ ቢደራረብ
ችሎት ቢለዋወጥ ፍትህ ካልነገሰ
አውነት እንደጥንቱ በገንዘብ ካነሰ
እንዳምና ታቻምናው ድሐ ካለቀሰ
ጥጋበኛ በዝቶ ወንበር ከረከሰ
አቤት ቢባል ያው ነው የጅብ ቆዳ ክራር
እንብላው ነው ዜማው የት ሊገባው ፍቅር
እባብ እያራቡ የእርግም ጫጩት የለም
ይግባኝ በል አትበሉኝ በቃ ችየው ልክረም
አምና ከፈረደው የዘንድሮው ብሶ
ሲረክስ እያየሁ እውነት ዛሬም አንሶ
ስንት ዶሴ ቀርቷል አቧራውን ለብሶ
ላይረታ በከንቱ ድሐ ሀብታም ከሶ
ገና ከጅምሩ ፍርድ ሚዛን ከሳተ
ዋናው ጉዳይ ቀሎ እየተጓተተ
በይግባኝ አልረታም ልተወው ዘንድሮ
ለከርሞ ልጠብቅ ድሐ ሰሚ ጆሮ!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ክሴን የሚሰማ አድማጭ ዳኛ ጠፍቶ
ይግባኝ በል ይሉኛል የቀደመው ቀርቶ
ቀድሞ ፍትህ ጎድሎ ሚዛኑ በገንዘብ
ሰሚ ጆሮ የለም ይግባኝ ቢደራረብ
ችሎት ቢለዋወጥ ፍትህ ካልነገሰ
አውነት እንደጥንቱ በገንዘብ ካነሰ
እንዳምና ታቻምናው ድሐ ካለቀሰ
ጥጋበኛ በዝቶ ወንበር ከረከሰ
አቤት ቢባል ያው ነው የጅብ ቆዳ ክራር
እንብላው ነው ዜማው የት ሊገባው ፍቅር
እባብ እያራቡ የእርግም ጫጩት የለም
ይግባኝ በል አትበሉኝ በቃ ችየው ልክረም
አምና ከፈረደው የዘንድሮው ብሶ
ሲረክስ እያየሁ እውነት ዛሬም አንሶ
ስንት ዶሴ ቀርቷል አቧራውን ለብሶ
ላይረታ በከንቱ ድሐ ሀብታም ከሶ
ገና ከጅምሩ ፍርድ ሚዛን ከሳተ
ዋናው ጉዳይ ቀሎ እየተጓተተ
በይግባኝ አልረታም ልተወው ዘንድሮ
ለከርሞ ልጠብቅ ድሐ ሰሚ ጆሮ!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤10👍4🔥2
#ሳይኖር_አለቀ!
ከአለማነው ይልቅ የአጠፋነው በዝቶ
የቃረምነው እውቀት በዜሮ ተባዝቶ
ቁሳቁስ ተከብሮ ሰውነት ተናቀ
ኖርነው ያልነው ህይወት ሳይኖር አለቀ
የጋራነት ቀርቶ የግል ያልነው በዝቶ
ጥሎ ማለፍ ሆነ እርስ በእርስ ተጋፍቶ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ከአለማነው ይልቅ የአጠፋነው በዝቶ
የቃረምነው እውቀት በዜሮ ተባዝቶ
ቁሳቁስ ተከብሮ ሰውነት ተናቀ
ኖርነው ያልነው ህይወት ሳይኖር አለቀ
የጋራነት ቀርቶ የግል ያልነው በዝቶ
ጥሎ ማለፍ ሆነ እርስ በእርስ ተጋፍቶ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍13❤4🔥1
#እጠብቅሻለሁ
እጠብቅሻለሁ ካለሁበት ቆሜ
ሀሳብና ናፍቆት ፍቅርን ተሸክሜ
እዛው ቦታ አለው እኔን ከተውሽበት
እኔንም ፍቅርሽን ጥለሽ ከሄድሽበት
እጠብቅሻለሁ ደቂቃም ሳላጎል
ምንስ ደህና ባልሆን ሰላሜ ቢታጎል
እዛው አለው ፍቅሬ ያኔ ከቆምንበት
ትተሺኝ መሄድሽን ምንስ ባላምንበት
ቆሜ ስጠብቅሽ ጭራሽ ቀን አልመርጥም እሁድ አልል ሰንበት
እጠብቅሻለሁ ፍቅሬ እዛው ሰፈር
ጥለሽኝ ከሄድሽበት ብለሽ አይንህ ላፈር
እጠብቅሻለሁ ዳግም መምጣትሽን
ምን ልቤ ቢሰጋ፤እንዲያበቃን በማሰብ
ዳግም ለአይነ ስጋ
እዛው አለው ፍቅሬ ያኔ ከቆምንበት
ከፍቅራችን አልፎ ትዳር ካሰብንበት
አዬ ትዳር እቴ እንኳን ትዳር ቀርቶ
ዛሬ አንቺም ሄደሽ ደስታው ተቀይሯል
ወደ ሀዘን ቀረርቶ
እኔ ግን የኔ ውድ ዛሬም ወድሻለሁ
አንቺ ያፈራረስሽው ፍቅሬን አድሻለሁ
ዳግም ካንቺ መሆን መጫወት እሻለሁ
ጊዜ አስተምሮሽ አንቺም እኔን ካሻሽ
ፍቅሬን ይዤ አለሁህኝ ለጥላቻሽ ምላሽ
ፍቅሬ ካንቺ በላይ ጠንቅቄ አውቅሻለሁ
መቅረትሽን ባምንም አንቺ የተውሽውን
ለተረኛ ይዤ እጠብቅሻለሁ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
እጠብቅሻለሁ ካለሁበት ቆሜ
ሀሳብና ናፍቆት ፍቅርን ተሸክሜ
እዛው ቦታ አለው እኔን ከተውሽበት
እኔንም ፍቅርሽን ጥለሽ ከሄድሽበት
እጠብቅሻለሁ ደቂቃም ሳላጎል
ምንስ ደህና ባልሆን ሰላሜ ቢታጎል
እዛው አለው ፍቅሬ ያኔ ከቆምንበት
ትተሺኝ መሄድሽን ምንስ ባላምንበት
ቆሜ ስጠብቅሽ ጭራሽ ቀን አልመርጥም እሁድ አልል ሰንበት
እጠብቅሻለሁ ፍቅሬ እዛው ሰፈር
ጥለሽኝ ከሄድሽበት ብለሽ አይንህ ላፈር
እጠብቅሻለሁ ዳግም መምጣትሽን
ምን ልቤ ቢሰጋ፤እንዲያበቃን በማሰብ
ዳግም ለአይነ ስጋ
እዛው አለው ፍቅሬ ያኔ ከቆምንበት
ከፍቅራችን አልፎ ትዳር ካሰብንበት
አዬ ትዳር እቴ እንኳን ትዳር ቀርቶ
ዛሬ አንቺም ሄደሽ ደስታው ተቀይሯል
ወደ ሀዘን ቀረርቶ
እኔ ግን የኔ ውድ ዛሬም ወድሻለሁ
አንቺ ያፈራረስሽው ፍቅሬን አድሻለሁ
ዳግም ካንቺ መሆን መጫወት እሻለሁ
ጊዜ አስተምሮሽ አንቺም እኔን ካሻሽ
ፍቅሬን ይዤ አለሁህኝ ለጥላቻሽ ምላሽ
ፍቅሬ ካንቺ በላይ ጠንቅቄ አውቅሻለሁ
መቅረትሽን ባምንም አንቺ የተውሽውን
ለተረኛ ይዤ እጠብቅሻለሁ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤6👍6🔥2👏2
#የታል_ፈገግታዬ
ያንን ጣፋጭ ጊዜ፣ምን ዋጠው ደስታየን
የታል ፈገግታየ፣ምን ወሰደው ሳቄን
እንቅልፌስ የት ሄደ፣ቅዠት የሌለበት
አይኖቼ ለ እረፍት፣የተከደኑበት
ከቶ ወዴት ገባ፣የመስኩ ቡረቃ
ስዘል የዋልኩበት፣እያቦካሁ ጭቃ
ዛሬማ ጭንቅ ነው፣ኑሮ በሰቆቃ
መልኬም ይናገራል፣ምቾት እንደሌለኝ
ሀሳቤ ተሰርቆ፣ለተመለከተኝ
ድሮን በመለስኩት፣የልጅነት ወዜን
ድሎት የሞላውን፣ያቺን ነፃነቴን
ጊዜው ተሰደደ፣ሂዷል አሁንማ
በእናት ነበር ኩራት፣ከሷ ወዲህማ
ሳቄም አይበረክት፣ድምፄም አይሰማ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ፋሲል ብስራት
ያንን ጣፋጭ ጊዜ፣ምን ዋጠው ደስታየን
የታል ፈገግታየ፣ምን ወሰደው ሳቄን
እንቅልፌስ የት ሄደ፣ቅዠት የሌለበት
አይኖቼ ለ እረፍት፣የተከደኑበት
ከቶ ወዴት ገባ፣የመስኩ ቡረቃ
ስዘል የዋልኩበት፣እያቦካሁ ጭቃ
ዛሬማ ጭንቅ ነው፣ኑሮ በሰቆቃ
መልኬም ይናገራል፣ምቾት እንደሌለኝ
ሀሳቤ ተሰርቆ፣ለተመለከተኝ
ድሮን በመለስኩት፣የልጅነት ወዜን
ድሎት የሞላውን፣ያቺን ነፃነቴን
ጊዜው ተሰደደ፣ሂዷል አሁንማ
በእናት ነበር ኩራት፣ከሷ ወዲህማ
ሳቄም አይበረክት፣ድምፄም አይሰማ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ፋሲል ብስራት
❤12🔥1
#አበባና_ውበት
የአበባ ውበቱ
ሳቢ ደም ግባቱ
የሚታይ ድምቀቱ
የማር መስሪያነቱ
እሰከሚከስም ነው
ሁሉም የሚከበው
ፍቅረኞች ለፍቅር
አልቃሾች ለቀብር
ንቦች ደግማ ለማር
ለአበባ የሚዘመር
የሚንከባከቡት
አለውህ የሚሉት
ውበቱ እስካለ ነው
ከዚያ ወዳቂ ነው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
የአበባ ውበቱ
ሳቢ ደም ግባቱ
የሚታይ ድምቀቱ
የማር መስሪያነቱ
እሰከሚከስም ነው
ሁሉም የሚከበው
ፍቅረኞች ለፍቅር
አልቃሾች ለቀብር
ንቦች ደግማ ለማር
ለአበባ የሚዘመር
የሚንከባከቡት
አለውህ የሚሉት
ውበቱ እስካለ ነው
ከዚያ ወዳቂ ነው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤11🥰10🔥4👍1😢1
#ከንፈርሽን_ስስመው 💋
ከንፈርሽን ስስመው
የአለም ጨለማ በፍቅራችን በርቶ
በአብርሃም በሳራ መመሠሉ ቀርቶ
ከምድር 'ርቆ በገነት እንዳለ
ፍቅር በ'ኔና አንቺ እየተመሠለ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
አባይ ተገድቦ ሲፈስ ወደ አገሩ
ፅጌረዳ አበቦች በመስመር ሲዘሩ
ባ'በቦቹ መሀል እየተሯሯጥን
ከፅጌረዳው ስር ፍለጋ ስኳትን
ከንፈርሽን ስስመው
ምድርን የሞሏት አበቦቹ ሁሉ
ጣፋጭ ከንፈርሽን መስለው የበቀሉ
ወደ ገነት ደሴት ሲወስደን ባቡሩ
ወፎች ለ'ኔና አንቺ ፍቅር እየዘመሩ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
አለም ለ'ኔና አንቺ ግብር እየከፈለ
ለሁሉ 'ሚበቃ ፍቅር እየታደለ
ሠማይን የሞሉት ከዋክብቱ ሁሉ
ውበትሽን ለማድመቅ የሚንቀለቀሉ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
ውዴ ይሄን ሁሉ አየሁኝ ብልሽም
አይኖቼ ተከድነው አንቺን አላዩሽም::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ከንፈርሽን ስስመው
የአለም ጨለማ በፍቅራችን በርቶ
በአብርሃም በሳራ መመሠሉ ቀርቶ
ከምድር 'ርቆ በገነት እንዳለ
ፍቅር በ'ኔና አንቺ እየተመሠለ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
አባይ ተገድቦ ሲፈስ ወደ አገሩ
ፅጌረዳ አበቦች በመስመር ሲዘሩ
ባ'በቦቹ መሀል እየተሯሯጥን
ከፅጌረዳው ስር ፍለጋ ስኳትን
ከንፈርሽን ስስመው
ምድርን የሞሏት አበቦቹ ሁሉ
ጣፋጭ ከንፈርሽን መስለው የበቀሉ
ወደ ገነት ደሴት ሲወስደን ባቡሩ
ወፎች ለ'ኔና አንቺ ፍቅር እየዘመሩ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
አለም ለ'ኔና አንቺ ግብር እየከፈለ
ለሁሉ 'ሚበቃ ፍቅር እየታደለ
ሠማይን የሞሉት ከዋክብቱ ሁሉ
ውበትሽን ለማድመቅ የሚንቀለቀሉ
...መስሎ ይታየኛል...
ከንፈርሽን ስስመው
ውዴ ይሄን ሁሉ አየሁኝ ብልሽም
አይኖቼ ተከድነው አንቺን አላዩሽም::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤14👏3🥰2
#የምስኪን_ሆድ_ሲጮኽ
ለመጠራት ለመታደም ከድግሱ
የሰው ዋጋ የሰው ክብሩ ሆኖ ልብሱ
ከደጋሽ በላይ አስተናባሪ ሲያሸረግድ
ለብሰው በመጡት ለመወደድ
አዳፋ ለባሽ የእኔ ቢጤ ሲቁለጨለጭ
በአንድ እጁ ሆዱን በሌላኛው ጸጉሩን ሲነጭ
እግዚአብሔር ሰምቶ የብሶቱን አቤቱታ
አስተናባሪውን ሲያጣድፈው ድንገት ትንታ
ሁሉም ለድግሱ ለሆዱ ለከርሱ አድሮ
መስማት አቅቶት የድሃውን እንጉርጉሮ
በለበሰው ሲኮራ በሚበላው ሲያቅራራ
በጥጋብ እብሪት ግራ ቀኙን ሲንጠራራ!
ለካስ ሰው ይሞታል በድንገት በትንታ
የምስኪን ሆድ ሲጮኽ ወደ ጌታ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ለመጠራት ለመታደም ከድግሱ
የሰው ዋጋ የሰው ክብሩ ሆኖ ልብሱ
ከደጋሽ በላይ አስተናባሪ ሲያሸረግድ
ለብሰው በመጡት ለመወደድ
አዳፋ ለባሽ የእኔ ቢጤ ሲቁለጨለጭ
በአንድ እጁ ሆዱን በሌላኛው ጸጉሩን ሲነጭ
እግዚአብሔር ሰምቶ የብሶቱን አቤቱታ
አስተናባሪውን ሲያጣድፈው ድንገት ትንታ
ሁሉም ለድግሱ ለሆዱ ለከርሱ አድሮ
መስማት አቅቶት የድሃውን እንጉርጉሮ
በለበሰው ሲኮራ በሚበላው ሲያቅራራ
በጥጋብ እብሪት ግራ ቀኙን ሲንጠራራ!
ለካስ ሰው ይሞታል በድንገት በትንታ
የምስኪን ሆድ ሲጮኽ ወደ ጌታ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍6❤5🔥3🥰2👎1
🙏16❤2
#ከመሄድሽ_በፊት
ካንች ቃል ከወጣ ትተሽኝ ለመሄድ
ልብሽ ከወሰነ ከጀመረ መንገድ
ቅሪም አልልሽም
አላስገድድሽም
መንገድሽ ጨርቅ ይሁን ክፉም አይግጠምሽ
ህይወትሽ አይጉደል ኑሮሽ ይስመርልሽ
ከእኔ የተሻለ አዛኝ ሰውን ይስጥሽ
ግን ውዴ ነገ ብትመለሽ.....
አንችን እየጠበኩ ላይሆን ስለሚችል
🚶♀➡️ ከመሄድሽ በፊት....
አርቀሽ አስቢ ተስፋን ፊት አትንሻት
ስሜትን ኮንኚው በእርጋታ ዳኝነት
ለወሬ ጆሮ አትስጭ ምቀኛን አትስሚ
በዛሬ ስሜትን ለነገ አትጨልሚ
በትዕግስት መድሀኒት ኑሮሽን አክሚ
🚶♀➡️ከመሄድሽ በፊት.....
ስላለፈው ኑሮ ስላለፈው ፍቅር
ትዝታን ጠይቂው " ልሂድ? ወይስ ልቅር? "
መልሱን ይነግርሻል
ያኔ ይገባሻል
መቼም ተምረሻል
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ካንች ቃል ከወጣ ትተሽኝ ለመሄድ
ልብሽ ከወሰነ ከጀመረ መንገድ
ቅሪም አልልሽም
አላስገድድሽም
መንገድሽ ጨርቅ ይሁን ክፉም አይግጠምሽ
ህይወትሽ አይጉደል ኑሮሽ ይስመርልሽ
ከእኔ የተሻለ አዛኝ ሰውን ይስጥሽ
ግን ውዴ ነገ ብትመለሽ.....
አንችን እየጠበኩ ላይሆን ስለሚችል
🚶♀➡️ ከመሄድሽ በፊት....
አርቀሽ አስቢ ተስፋን ፊት አትንሻት
ስሜትን ኮንኚው በእርጋታ ዳኝነት
ለወሬ ጆሮ አትስጭ ምቀኛን አትስሚ
በዛሬ ስሜትን ለነገ አትጨልሚ
በትዕግስት መድሀኒት ኑሮሽን አክሚ
🚶♀➡️ከመሄድሽ በፊት.....
ስላለፈው ኑሮ ስላለፈው ፍቅር
ትዝታን ጠይቂው " ልሂድ? ወይስ ልቅር? "
መልሱን ይነግርሻል
ያኔ ይገባሻል
መቼም ተምረሻል
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤25👏6👍2🥰1
የመኖር ፈተና ምንም ቢያንገዳግድ
አታካችም ቢሆን መውጣት እና መውረድ
ነብሴን ልታደጋት ህይወቴን ዘክሬ
ሞቴም ትንሳኤ ነው በህያው መኖሬ
እኔስ ላይቀር ማለፌ
ነበርን አትርፌ
ለመሞት አልኖርም
ለመኖር ነው ሞቴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ መኮንን
አታካችም ቢሆን መውጣት እና መውረድ
ነብሴን ልታደጋት ህይወቴን ዘክሬ
ሞቴም ትንሳኤ ነው በህያው መኖሬ
እኔስ ላይቀር ማለፌ
ነበርን አትርፌ
ለመሞት አልኖርም
ለመኖር ነው ሞቴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ መኮንን
❤17👏2
#ሚስቴ_እና_ሰበቧ!
ለስጋዋ ስትኖር
-- ነፍሷን አሞኝታ
አገኘዃትና
-- ስትሳም ተኝታ
ምነው ምን በደልኩሽ?
-- ብዬ ስጠይቃት
እግሯ ስር ወድቄ
-- በእንባ ስማጸናት
እንደለመደችው
-- ሰበብ አዘጋጅታ
አንተ መስለኸኝ ነው
-- አለችኝ ተነስታ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ለስጋዋ ስትኖር
-- ነፍሷን አሞኝታ
አገኘዃትና
-- ስትሳም ተኝታ
ምነው ምን በደልኩሽ?
-- ብዬ ስጠይቃት
እግሯ ስር ወድቄ
-- በእንባ ስማጸናት
እንደለመደችው
-- ሰበብ አዘጋጅታ
አንተ መስለኸኝ ነው
-- አለችኝ ተነስታ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
😁37👏4❤2🥰1
#ጥላችን_አይደለም
በህይወት ጎዳና ፈጥነን ስንራመድ
ወይም በዝግታ በሀሳብ ስንሄድ
ስንቆም የሚቆመው ሲመሽ የማናየው
ጥላችን አይደለም ለካስ ሞታችን ነው!
የሚከታተለን በእርምጃችን መጠን
ስንፈጥን ስንዘገይ ሁሌ ሚከተለን
ጥላችን አይደለም የምስላችን ቅኔ
ሞታችን ነው ባይ ነኝ እንደገባኝ እኔ
ሲመሽ ተደብቆ ሲነጋ ተገልጦ
ስንተኛ ተኝቶ ስንሮጥ እሮጦ
የያዝነውን ይዞ ስንበላ በልቶ
ሁልግዜም አብሮን ነው ሞታችን አድብቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
በህይወት ጎዳና ፈጥነን ስንራመድ
ወይም በዝግታ በሀሳብ ስንሄድ
ስንቆም የሚቆመው ሲመሽ የማናየው
ጥላችን አይደለም ለካስ ሞታችን ነው!
የሚከታተለን በእርምጃችን መጠን
ስንፈጥን ስንዘገይ ሁሌ ሚከተለን
ጥላችን አይደለም የምስላችን ቅኔ
ሞታችን ነው ባይ ነኝ እንደገባኝ እኔ
ሲመሽ ተደብቆ ሲነጋ ተገልጦ
ስንተኛ ተኝቶ ስንሮጥ እሮጦ
የያዝነውን ይዞ ስንበላ በልቶ
ሁልግዜም አብሮን ነው ሞታችን አድብቶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👍17❤5🥰1👏1
" #ይስጥሽ"
ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ
ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ
ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ
ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤
ይስጥሽ ከፀጉሬ ከአናቴ ላይ ዘግኖ
ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ
አወይ ፀጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ
ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ
እቴ.....
ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ
ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ
ከዓይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ
እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ።
እቴ....
እጄን ብትፈልጊ እግሬን ብትፈልጊ
አንገቴን ደረቴን
ተሰጥኦ ሀሳቤን
ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ
እግዜር ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ
ያስቀርልኝ ዓይኔን
አንቺን ማየት ብቻ
ያኖረኛል እኔን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ
ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ
ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ
ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤
ይስጥሽ ከፀጉሬ ከአናቴ ላይ ዘግኖ
ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ
አወይ ፀጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ
ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ
እቴ.....
ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ
ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ
ከዓይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ
እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ።
እቴ....
እጄን ብትፈልጊ እግሬን ብትፈልጊ
አንገቴን ደረቴን
ተሰጥኦ ሀሳቤን
ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ
እግዜር ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ
ያስቀርልኝ ዓይኔን
አንቺን ማየት ብቻ
ያኖረኛል እኔን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤18👏7🔥2
#የኔን_ቀን_ገድዬ
የደላኝ መስዬ
ብሶቴን አምቄ
ወደ ውስጤ አልቅሼ
ቀን ብገፋ ስቄ
የኔ ባል ሞኝ ነው
ፍቅር ይሰጠኛል
ስጠላው አያውቅም
ብለሽ አምተሽኛል
በዚህ እኩይ አለም
አምላክ ፊት ቀርቤ
እኔ ለታማሁኝ
ደጁ ተንበርክኬ
የኔን ቀን ገድዬ
ለሷ እጨነቃለሁ
ይቅር በላት እያልኩ
ስፀልይ አድራለሁ
አታውቀውምና
እሷ የኔን ነገር
ከመኖር ያለፈ
እንዴት እንደምኖር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
የደላኝ መስዬ
ብሶቴን አምቄ
ወደ ውስጤ አልቅሼ
ቀን ብገፋ ስቄ
የኔ ባል ሞኝ ነው
ፍቅር ይሰጠኛል
ስጠላው አያውቅም
ብለሽ አምተሽኛል
በዚህ እኩይ አለም
አምላክ ፊት ቀርቤ
እኔ ለታማሁኝ
ደጁ ተንበርክኬ
የኔን ቀን ገድዬ
ለሷ እጨነቃለሁ
ይቅር በላት እያልኩ
ስፀልይ አድራለሁ
አታውቀውምና
እሷ የኔን ነገር
ከመኖር ያለፈ
እንዴት እንደምኖር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤21🥰2🔥1👏1
#ታውቂያለሽ_አይደለ?
ስላንቺ በማሰብ
ዘመኔ ማለፉን
አንቺን በመናፈቅ
እምባየ ማለቁን
አሻግሬ ሳይሽ
እይኔ መደብዘዙን
ኮቴሽን በማድመጥ
ጆሮየ መድከሙን
ታውቂያለሽ አይደለ
ቆሜ ስጠብቅሽ
ቆየኝ ባልሽኝ ስፍራ
በረዶና ዝናብ
በላየ እንዳባራ
እንቅልፍ አልባ
ቀናት በኔ እንደነጎዱ
ጀምበር ከጨረቃ እንደተዋሀዱ
አውቃለሁ አታውቂም አንዳቹንም ነገር
እኔ መውደድ እንጂ አልችልም መናገር፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዘላለም ምህረቱ
ስላንቺ በማሰብ
ዘመኔ ማለፉን
አንቺን በመናፈቅ
እምባየ ማለቁን
አሻግሬ ሳይሽ
እይኔ መደብዘዙን
ኮቴሽን በማድመጥ
ጆሮየ መድከሙን
ታውቂያለሽ አይደለ
ቆሜ ስጠብቅሽ
ቆየኝ ባልሽኝ ስፍራ
በረዶና ዝናብ
በላየ እንዳባራ
እንቅልፍ አልባ
ቀናት በኔ እንደነጎዱ
ጀምበር ከጨረቃ እንደተዋሀዱ
አውቃለሁ አታውቂም አንዳቹንም ነገር
እኔ መውደድ እንጂ አልችልም መናገር፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዘላለም ምህረቱ
❤15👍6🔥5👏2🥰1
#ቃል_ብዬ_ጠራሁሽ
ስላንች ለመፃፍ ብእር እቀርፅና
ቀለሙን አቅልሜ ፈቅፍቄ ብራና
ፊደልና ቃላት እንደልጅ እያማጥኩ
ሀረግ እየመዘዝኩ ምሳሌ እየጠቀስኩ
ቃል ባጣው ልሳኔ ስፅፍ ውዬ አድሬ
ገልጨሽ ሳይበቃኝ ትደርቃለች ብእሬ
ደግሞ ተመልሼ................
ደሜን አንጠፍጥፌ ቀለሙን አቀለምኩ
አጥንቴን ፈቅፍቄ ላንች ብእር ቀረፅኩ
ብእሬን በደሜ ነክሬ ሳወጣው
አንችን እገልፅበት ቅንጣት ቃላት አጣው
ለካንስ ቃልዬ!!!
በፍቅር ነሁልሎ መንፈስ ከደከመ
ናፍቆት አገርጥቶት ልብ ከታመመ
እንኳን ቃል ተዋቅሮ ቅኔ ሊመሰጠር
ደግሞ ስንኝ ሁኖ ግጥም ሊደረደር
ደህና አደርክ ሲባል ለእግዚአብሄር ይመስገን
አንደበት ቃል ያጣል ሲመርቁት ለአሜን
ለዛ ነው ቃልዬ!!!
መግለጫ ቃል ባጣ እልፍ ዘመን ሙሉ
የብራናዬ ገፅ ግራ ገብቶት ውሉ
እየደጋገምኩኝ የፃፍኩት አንድ ቃል
እ
ን
ዲ
ህ
ብቻ ይላል
ሌላ ቃል ተገኝቶ
ወይ ልሳንህ ፈቶ
ህቡእ በሆነ ቃል እስከምትገልፃት
ቃልህ እሷ ነችና ቃሌ ብለህ ጥራት
እናም አንች ቃሌ ነሽ ሀረግና ስንኝ
ካጠገቤ ሁነሽ ሰርክ የምትርቢኝ
እናም የኔ ንግስት
ገፅሽን አድምቄ በልቤ መዝገብ ላይ
ቃሌ ብዬ ፃፍኩሽ ቃል አጣው ቃሌ ላይ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ስላንች ለመፃፍ ብእር እቀርፅና
ቀለሙን አቅልሜ ፈቅፍቄ ብራና
ፊደልና ቃላት እንደልጅ እያማጥኩ
ሀረግ እየመዘዝኩ ምሳሌ እየጠቀስኩ
ቃል ባጣው ልሳኔ ስፅፍ ውዬ አድሬ
ገልጨሽ ሳይበቃኝ ትደርቃለች ብእሬ
ደግሞ ተመልሼ................
ደሜን አንጠፍጥፌ ቀለሙን አቀለምኩ
አጥንቴን ፈቅፍቄ ላንች ብእር ቀረፅኩ
ብእሬን በደሜ ነክሬ ሳወጣው
አንችን እገልፅበት ቅንጣት ቃላት አጣው
ለካንስ ቃልዬ!!!
በፍቅር ነሁልሎ መንፈስ ከደከመ
ናፍቆት አገርጥቶት ልብ ከታመመ
እንኳን ቃል ተዋቅሮ ቅኔ ሊመሰጠር
ደግሞ ስንኝ ሁኖ ግጥም ሊደረደር
ደህና አደርክ ሲባል ለእግዚአብሄር ይመስገን
አንደበት ቃል ያጣል ሲመርቁት ለአሜን
ለዛ ነው ቃልዬ!!!
መግለጫ ቃል ባጣ እልፍ ዘመን ሙሉ
የብራናዬ ገፅ ግራ ገብቶት ውሉ
እየደጋገምኩኝ የፃፍኩት አንድ ቃል
እ
ን
ዲ
ህ
ብቻ ይላል
ሌላ ቃል ተገኝቶ
ወይ ልሳንህ ፈቶ
ህቡእ በሆነ ቃል እስከምትገልፃት
ቃልህ እሷ ነችና ቃሌ ብለህ ጥራት
እናም አንች ቃሌ ነሽ ሀረግና ስንኝ
ካጠገቤ ሁነሽ ሰርክ የምትርቢኝ
እናም የኔ ንግስት
ገፅሽን አድምቄ በልቤ መዝገብ ላይ
ቃሌ ብዬ ፃፍኩሽ ቃል አጣው ቃሌ ላይ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤10👏3👍1🔥1🥰1