#በአንተ
በምወድድህ ፊት
ተመልከተዉ ዳንሴን
እግር አያያዜን
ወገብ አያያዜን
ያይን አወራወሬን
ቃላት አጣጣሌን ...
ተመልከት ዉበቴን
ተመልከተዉ ፊቴን
አስተዉል ሀሳቤን ፣ ጣዕምና ምሬቴን ።
ድካሜን
እረፍቴን
ድልና ሽንፈቴን
ተመልከተዉ ኩሌን
የአይኔን ልቦናዬን
ቅንድቤን ፣ ከንፈሬን ፣ ልቤን ፣ ኩላሊቴን
" ተመልከተኝ እኔን
ገላዉ የረገፈ አበባ መሆኔን "
ተመልከተዉ ሀሬን
ቀሚሴን ጥምጣሜን
ማማሩ
ማማሩ
ማነዉ የሚባሉት ደህነኞች ሲሰክሩ !?
ፍቅር ባፍቃሪዉ ፡ ፊት እንደምን ይሳሳል
የአፍቃሪስ ልብ ሲፈስ በምን ይታፈሳል ።
በምን ይከተታል፣
አፍቃሪ የዘራዉ የቀን ሌቱ ግጥም
ከልብ በቀረ እሳት ማን ይችላል ቢሰጠዉስ አቅም ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
በምወድድህ ፊት
ተመልከተዉ ዳንሴን
እግር አያያዜን
ወገብ አያያዜን
ያይን አወራወሬን
ቃላት አጣጣሌን ...
ተመልከት ዉበቴን
ተመልከተዉ ፊቴን
አስተዉል ሀሳቤን ፣ ጣዕምና ምሬቴን ።
ድካሜን
እረፍቴን
ድልና ሽንፈቴን
ተመልከተዉ ኩሌን
የአይኔን ልቦናዬን
ቅንድቤን ፣ ከንፈሬን ፣ ልቤን ፣ ኩላሊቴን
" ተመልከተኝ እኔን
ገላዉ የረገፈ አበባ መሆኔን "
ተመልከተዉ ሀሬን
ቀሚሴን ጥምጣሜን
ማማሩ
ማማሩ
ማነዉ የሚባሉት ደህነኞች ሲሰክሩ !?
ፍቅር ባፍቃሪዉ ፡ ፊት እንደምን ይሳሳል
የአፍቃሪስ ልብ ሲፈስ በምን ይታፈሳል ።
በምን ይከተታል፣
አፍቃሪ የዘራዉ የቀን ሌቱ ግጥም
ከልብ በቀረ እሳት ማን ይችላል ቢሰጠዉስ አቅም ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤18
መነሻ ስእል
ኣያልቅም ይህ ጉዞ...
ማስመሰል-መተርጎም
በቀለም መዋኘት
በመስመር መዋኘት
ክብርሃን መጋጨት
ለማወቅ ለመፍጠር ባዶ ቦታ መግባት።
መፈለግ....... መፈለግ......
ኣዲስ ነገር መፍጠር
ከማይታየው ጋር ሄዶ መነጋገር።
ህይወትን መጠየቅ
ሃሳብን መጠየቅ
ኣለምን መጠየቅ
መሄድ መሄድ መሄድ....
ከጨረቃ በላይ
ከኮከቦች በላይ
ከሰማዩ በላይ።
መጉዋዝ ወደሌላ - ባዶ ቦታ መግባት
በሃሳብ መደበቅ፥
መፈለግ ማስገኘት።
ኣያልቅም ይህ ጉዞ....
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገብረክርስቶስ ደሰታ
ኣያልቅም ይህ ጉዞ...
ማስመሰል-መተርጎም
በቀለም መዋኘት
በመስመር መዋኘት
ክብርሃን መጋጨት
ለማወቅ ለመፍጠር ባዶ ቦታ መግባት።
መፈለግ....... መፈለግ......
ኣዲስ ነገር መፍጠር
ከማይታየው ጋር ሄዶ መነጋገር።
ህይወትን መጠየቅ
ሃሳብን መጠየቅ
ኣለምን መጠየቅ
መሄድ መሄድ መሄድ....
ከጨረቃ በላይ
ከኮከቦች በላይ
ከሰማዩ በላይ።
መጉዋዝ ወደሌላ - ባዶ ቦታ መግባት
በሃሳብ መደበቅ፥
መፈለግ ማስገኘት።
ኣያልቅም ይህ ጉዞ....
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገብረክርስቶስ ደሰታ
❤12👍1
የስጦታ ፈረስ ባይታይም ጥርሱ
መቼ ሆነ ከቶ መወደድ መርከሱ
ለነገር ነው እንጂ ህሊናችን አብዶ
ምን ይሰራለታል ለመላጣ ሚዶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
መቼ ሆነ ከቶ መወደድ መርከሱ
ለነገር ነው እንጂ ህሊናችን አብዶ
ምን ይሰራለታል ለመላጣ ሚዶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
🔥11🥰6
#ሹም_ሽር
አንቺ እቴ ፔንዱለም
ፌዝና የምርሽ የተደቃቀለ፤
እዚህ ሲሉሽ እዛ
ነፍስሽና ስጋሽ ሁሌ እየዋለለ፤
በውበትሽ ግርማ
አፍቃሪ ከጉያሽ ሲገባ እየዋለ፤
ልቡ እየቀለለ፥
ሰርክ እየማለለ...
በሀሰት ግብርሽ ላይ
ሀቂቃዊ ፍቅሩን ገምዶና ጠቅልሎ፤
ስንቱ አዳም መሰለሽ
በዥዋዥዌሽ ክር የሞተው ተሰቅሎ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አብርሃም ፍቅሬ
አንቺ እቴ ፔንዱለም
ፌዝና የምርሽ የተደቃቀለ፤
እዚህ ሲሉሽ እዛ
ነፍስሽና ስጋሽ ሁሌ እየዋለለ፤
በውበትሽ ግርማ
አፍቃሪ ከጉያሽ ሲገባ እየዋለ፤
ልቡ እየቀለለ፥
ሰርክ እየማለለ...
በሀሰት ግብርሽ ላይ
ሀቂቃዊ ፍቅሩን ገምዶና ጠቅልሎ፤
ስንቱ አዳም መሰለሽ
በዥዋዥዌሽ ክር የሞተው ተሰቅሎ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አብርሃም ፍቅሬ
❤6
#የተሸነፈ_ኩራት!!
በቃኝ!!! ያልሽኝ ዕለት መገፋቴ አሞኝ
እልህ ጉልበት ሆኖኝ
ካንቺ ሌላ ብዬ
ከጣልኩዋቸው መሀል አንዱዋን አሳምኜ
አንቺን እንዳቄልኩሽ እሱዋንም እንዳንቺው ካንቺ ሌላ ብዬ
ቂ…..ቂ….ቂ…..ቂ..
የመጣሌን ህመም የግፊሽን ጉዳት
በእሱዋ እቅፍ ለመርሳት
የሌለኝን መውደድ ያልነካኝን ፍቅር
ሰርክ ስዘረዝር
ስሜቴ ከእምነቴ እየተጣረሰ
እውነቴም ከሐሰቴ እየተካሰሰ፡፡
ይበለኝ!!..
በማስመሰል ብቻ
በመዋሸት ብቻ
ከንፈር ተሳልሜ ትከሻ ታቅፌ
ንጹህ ገላዋ ላይ ሙት ገላ አሳርፌ
ወይኔ..
ልቤ አንቺን እያለኝ
እኔ ኩራት አስሮኝ
በጸጸት ስመግል በቁጭት ስነፍር
እውነቴን ቀበርኩዋት ከሀሰት እግር ስር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
በቃኝ!!! ያልሽኝ ዕለት መገፋቴ አሞኝ
እልህ ጉልበት ሆኖኝ
ካንቺ ሌላ ብዬ
ከጣልኩዋቸው መሀል አንዱዋን አሳምኜ
አንቺን እንዳቄልኩሽ እሱዋንም እንዳንቺው ካንቺ ሌላ ብዬ
ቂ…..ቂ….ቂ…..ቂ..
የመጣሌን ህመም የግፊሽን ጉዳት
በእሱዋ እቅፍ ለመርሳት
የሌለኝን መውደድ ያልነካኝን ፍቅር
ሰርክ ስዘረዝር
ስሜቴ ከእምነቴ እየተጣረሰ
እውነቴም ከሐሰቴ እየተካሰሰ፡፡
ይበለኝ!!..
በማስመሰል ብቻ
በመዋሸት ብቻ
ከንፈር ተሳልሜ ትከሻ ታቅፌ
ንጹህ ገላዋ ላይ ሙት ገላ አሳርፌ
ወይኔ..
ልቤ አንቺን እያለኝ
እኔ ኩራት አስሮኝ
በጸጸት ስመግል በቁጭት ስነፍር
እውነቴን ቀበርኩዋት ከሀሰት እግር ስር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤14🔥1👏1
#ኑረሽ_እይው_በቃ
ጨለማ ነህ ብለሽ እኔን ስትተቺ
ዘለሽ አትጠግቢ፥ስቀሽ አትሰለቺ
ወርሃ ፅጌ ነው ፤አመት ሙሉ ላንቺ
ደሞ በየቀኑ
ፋሲካ ነው ኑሮሽ
ያለም ሰቀቀኑ
ሩቅ ነው ለጆሮሽ
(የፍጥረት ሰቆቃ)
ለጋ ነው ላ'እምሮሽ
ገላሽም ነው ጮርቃ
ሌላም አልልሽም፤ ኖረሽ እይው በቃ ፤
በየጎዳናሽ ላይ ፥አደይ የሚያነጥፍ
በየዛፉ ቅርፊት፥ ስምሽን የሚጥፍ
በዝቶልሽ፥ፈልቶልሽ ፥አንቺን ሚያሽሞነሙን
ቀምሰሺው አታቂም፥ የብቻነት ሸክሙን
አዎ!
መፈቀር ፥ መታጀብ ከኔክታር ይጥማል
ግን ደግሞ ይገጥማል
በተወደሱበት አንደበት መነቀፍ
ውብ ገላ ጠብቆ፣ ርጥብ ነፋስ ማቀፍ፥
አንዳንዴም ይገጥማል
የማይሰምር ምኞት ፥የማይልቅ ጥበቃ
ሌላም አልልሽም፤ ኑረሽ እይው በቃ፤
አንቺ ደስታ ወዳጅ
በለምለም አፀድ ውስጥ፥ ቢራቢሮ አሳዳጅ
ኑሮ ምትታይሽ፤ እንደ ጣኦስ ቀልማ
እንዳትሸወጂ ባዝማሪዎች ዜማ
በሸንጋዮች ቃላት
ህይወትም እንደ ጃርት፥የሾህ ቀሚስ አላት፤
ተድላም ከሃዘን ፣ጋር ያልፋል በፈረቃ
ከሳቅ በስተጀርባ፥ ይሰለፋል ሲቃ
ሌላ ምን ልበልሽ ፥
ኑረሽ እይው በቃ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍በዕውቀቱ ስዩም
ጨለማ ነህ ብለሽ እኔን ስትተቺ
ዘለሽ አትጠግቢ፥ስቀሽ አትሰለቺ
ወርሃ ፅጌ ነው ፤አመት ሙሉ ላንቺ
ደሞ በየቀኑ
ፋሲካ ነው ኑሮሽ
ያለም ሰቀቀኑ
ሩቅ ነው ለጆሮሽ
(የፍጥረት ሰቆቃ)
ለጋ ነው ላ'እምሮሽ
ገላሽም ነው ጮርቃ
ሌላም አልልሽም፤ ኖረሽ እይው በቃ ፤
በየጎዳናሽ ላይ ፥አደይ የሚያነጥፍ
በየዛፉ ቅርፊት፥ ስምሽን የሚጥፍ
በዝቶልሽ፥ፈልቶልሽ ፥አንቺን ሚያሽሞነሙን
ቀምሰሺው አታቂም፥ የብቻነት ሸክሙን
አዎ!
መፈቀር ፥ መታጀብ ከኔክታር ይጥማል
ግን ደግሞ ይገጥማል
በተወደሱበት አንደበት መነቀፍ
ውብ ገላ ጠብቆ፣ ርጥብ ነፋስ ማቀፍ፥
አንዳንዴም ይገጥማል
የማይሰምር ምኞት ፥የማይልቅ ጥበቃ
ሌላም አልልሽም፤ ኑረሽ እይው በቃ፤
አንቺ ደስታ ወዳጅ
በለምለም አፀድ ውስጥ፥ ቢራቢሮ አሳዳጅ
ኑሮ ምትታይሽ፤ እንደ ጣኦስ ቀልማ
እንዳትሸወጂ ባዝማሪዎች ዜማ
በሸንጋዮች ቃላት
ህይወትም እንደ ጃርት፥የሾህ ቀሚስ አላት፤
ተድላም ከሃዘን ፣ጋር ያልፋል በፈረቃ
ከሳቅ በስተጀርባ፥ ይሰለፋል ሲቃ
ሌላ ምን ልበልሽ ፥
ኑረሽ እይው በቃ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍በዕውቀቱ ስዩም
❤13👍8🔥1
#አትገረም
አይክፋህ አትዘን ወንድሜ!
ነግሬህ ነበር እኮ ድሮ አስቀድሜ
አደናቅፎህ ብትወድቅ፥ቧጭሮህ ብትደማ
በማንም አትዘን ማንንም አትማ
መንገድ ሁሉ እንቅፋት በሆነበት አለም
መነሳት ነው እንጂ መውደቅ ብርቅ አይደለም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
አይክፋህ አትዘን ወንድሜ!
ነግሬህ ነበር እኮ ድሮ አስቀድሜ
አደናቅፎህ ብትወድቅ፥ቧጭሮህ ብትደማ
በማንም አትዘን ማንንም አትማ
መንገድ ሁሉ እንቅፋት በሆነበት አለም
መነሳት ነው እንጂ መውደቅ ብርቅ አይደለም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤24👍10👏2
#ባዶ_ቤት_በክረምት
አንች የሌለሽበት
ዝም ጸጥ ብቻ
ጣሪያ መጫወቻ፡፡
አመሻሽ
ኦና ቤት
አንች የሌለሽበት
ፀጥ -ረጭ፣ ብቻ
ወለል መጫወቻ፡፡
ጠረጴዛ፣
ወንበር፣
አንድ አልጋ፣
አንድ በር፣
አንድ እኔ፣
አንድ መስኮት፣
ባዶ ቤ . . . ት በክረምት
አንች የሌለሽበት፣
ፀጥ-ረጭ ብቻ
እም መጫወቻ
ዝም መደሰቻ
ዝም ዝም
ዝም ዝም
ዝም ዝም ለብቻ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ጌትነት እንየው
አንች የሌለሽበት
ዝም ጸጥ ብቻ
ጣሪያ መጫወቻ፡፡
አመሻሽ
ኦና ቤት
አንች የሌለሽበት
ፀጥ -ረጭ፣ ብቻ
ወለል መጫወቻ፡፡
ጠረጴዛ፣
ወንበር፣
አንድ አልጋ፣
አንድ በር፣
አንድ እኔ፣
አንድ መስኮት፣
ባዶ ቤ . . . ት በክረምት
አንች የሌለሽበት፣
ፀጥ-ረጭ ብቻ
እም መጫወቻ
ዝም መደሰቻ
ዝም ዝም
ዝም ዝም
ዝም ዝም ለብቻ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ጌትነት እንየው
❤17👍2
#ጎረቤት_እንደ_እሳት
ሰው ወዳጁን መምረጥ የሚችል ቢሆንም
ጎረቤት መምረጡ ማዳገቱ አይቀርም
ከጎረቤት መኖር ሐቁ ይህ ከሆነ
ጎረቤትን አምኖ እሱም ከታመነ
ጎረቤትን መጉዳት አራስን መጉዳት
መሆኑን ይረዳል ያውቀዋል በእውነት
ሰውን ካጋጠመው የጎረቤት ጥሩ
ለችግሩ እሚደርስ ከዘመድ ከእድሩ
ጎረቤትን በክብር በፍቅር መያዝ
ከመጥቀም በስተቀር የለውም መዘዝ
ይህን የተረዳ ምሥጢሩን ያወቀ
የስጋቱ አግረ ሙቅ ተፈታ ወለቀ
ጎረቤት እንደሳት ሊጠቅምም ሊጎዳ
የሚችል መሆ ኑን ሰው በውል ይረዳ
የጎረቤት ኑሮ ደንቡን ያላወቁ
ጉዳቱ ከጥቅሙ አይባስ ይጠንቀቁ!
ድንገት በአጋጣሚ አሳት እንደሚፋጅ
ለሰው ጎረቤቱ ካልሆነው የሚበጅ
ከነገር ለመራቅ አጥር ይለያቸው
አስታራቂ ዳኛ እንዲሆንላቸው
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ሰው ወዳጁን መምረጥ የሚችል ቢሆንም
ጎረቤት መምረጡ ማዳገቱ አይቀርም
ከጎረቤት መኖር ሐቁ ይህ ከሆነ
ጎረቤትን አምኖ እሱም ከታመነ
ጎረቤትን መጉዳት አራስን መጉዳት
መሆኑን ይረዳል ያውቀዋል በእውነት
ሰውን ካጋጠመው የጎረቤት ጥሩ
ለችግሩ እሚደርስ ከዘመድ ከእድሩ
ጎረቤትን በክብር በፍቅር መያዝ
ከመጥቀም በስተቀር የለውም መዘዝ
ይህን የተረዳ ምሥጢሩን ያወቀ
የስጋቱ አግረ ሙቅ ተፈታ ወለቀ
ጎረቤት እንደሳት ሊጠቅምም ሊጎዳ
የሚችል መሆ ኑን ሰው በውል ይረዳ
የጎረቤት ኑሮ ደንቡን ያላወቁ
ጉዳቱ ከጥቅሙ አይባስ ይጠንቀቁ!
ድንገት በአጋጣሚ አሳት እንደሚፋጅ
ለሰው ጎረቤቱ ካልሆነው የሚበጅ
ከነገር ለመራቅ አጥር ይለያቸው
አስታራቂ ዳኛ እንዲሆንላቸው
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤11🔥1
#ይበቃል
መንገዱም ቆሽሿል ደፍርሷል ባህሩ፡
ወጣቱም ተሰዷል ወጥቷል ከሀገሩ ፡
የተራበች ሀገር መዋደድ የራቃት፡
ዚፕ እንደሌለው ኪስ በዝቷል የሚሰርቃት፡
ወንበር ላይ ተቀምጦ በተናገረው ቃል፡
በማያውቀው ነገር የድሀ ልጅ ያልቃል፡
እርሜን አውጥቻለሁ ሰላም እንደራቀኝ፡
ከወንድሜ ሰርቆ ይለኛል ደብቀኝ፡
በቃኝ ሰልችቶኛል ከንቱ ነች ይቺ ዓለም፡
ላመነችው እንጂ ላመናት አትሆንም፡
ድንገት ምህረት ቢልክ የአምላክ ፍቃድ ቢሆን፡
ያኔ እመለሳለሁ ሰውነት ሰው ሲሆን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሀሽ ማል (ብቸኛው)
መንገዱም ቆሽሿል ደፍርሷል ባህሩ፡
ወጣቱም ተሰዷል ወጥቷል ከሀገሩ ፡
የተራበች ሀገር መዋደድ የራቃት፡
ዚፕ እንደሌለው ኪስ በዝቷል የሚሰርቃት፡
ወንበር ላይ ተቀምጦ በተናገረው ቃል፡
በማያውቀው ነገር የድሀ ልጅ ያልቃል፡
እርሜን አውጥቻለሁ ሰላም እንደራቀኝ፡
ከወንድሜ ሰርቆ ይለኛል ደብቀኝ፡
በቃኝ ሰልችቶኛል ከንቱ ነች ይቺ ዓለም፡
ላመነችው እንጂ ላመናት አትሆንም፡
ድንገት ምህረት ቢልክ የአምላክ ፍቃድ ቢሆን፡
ያኔ እመለሳለሁ ሰውነት ሰው ሲሆን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሀሽ ማል (ብቸኛው)
❤19👏1
#ልጫር_ልሞጫጭረው!
ቃላት አሽሞንሙኖ በፊደላት ደምቆ
በምሁር ቃል ጠቀስ ቢመጥቅ ተራቆ
ቅኔው ቢወሳሰብ አንባቢ ካልፈታው
ጠቢባዊው ሁሉ ለማነው የሚጽፈው ?
ህግጋት ጠብቆ ቀለማትን ቆጥሮ
ምጣኔን መጥኖ ሀረጋትን ቋጥሮ
ምሁሩ ወንድሜ ቅኝት ተከትሎ
እኔን ፊደላዊ ከጥበብ ነጥሎ
እርሱ ባወቀው ልክ መብቴን ከልሎ
ሲከሰኝ ይውላል እንዳትገጥም ብሎ
አንተሙ ለተማሩት ለተመራመሩት
እኔም ለቢጤየ ፊደል ለሚገድፉት
በተሰጠን ድንበር እውቀታዊ ልኬት
አንተም እንዳዋቂ ሳድስን ዝለላት
እኔ ግን ስወዳት ስን እንዴት ልጣላት?
ለስሜ መጠሪያ ሁልጊዜም ከፊት ናት
አንተም ለተማሩት ለተመራመሩት
ስንቴም እጭራለሁ ፊደል ለሚገድፉት
ግን ማወቅ ጥሩ ነው አለማወቅ ክፉ
ሳያውቁ አውቂያለሁ እረዘመ ሰልፉ
አንተ አስተምረኸኝ ለእውቀት እስከበቃ
ልጫር ልሞጫጭረው አትከልክለኝ በቃ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ቃላት አሽሞንሙኖ በፊደላት ደምቆ
በምሁር ቃል ጠቀስ ቢመጥቅ ተራቆ
ቅኔው ቢወሳሰብ አንባቢ ካልፈታው
ጠቢባዊው ሁሉ ለማነው የሚጽፈው ?
ህግጋት ጠብቆ ቀለማትን ቆጥሮ
ምጣኔን መጥኖ ሀረጋትን ቋጥሮ
ምሁሩ ወንድሜ ቅኝት ተከትሎ
እኔን ፊደላዊ ከጥበብ ነጥሎ
እርሱ ባወቀው ልክ መብቴን ከልሎ
ሲከሰኝ ይውላል እንዳትገጥም ብሎ
አንተሙ ለተማሩት ለተመራመሩት
እኔም ለቢጤየ ፊደል ለሚገድፉት
በተሰጠን ድንበር እውቀታዊ ልኬት
አንተም እንዳዋቂ ሳድስን ዝለላት
እኔ ግን ስወዳት ስን እንዴት ልጣላት?
ለስሜ መጠሪያ ሁልጊዜም ከፊት ናት
አንተም ለተማሩት ለተመራመሩት
ስንቴም እጭራለሁ ፊደል ለሚገድፉት
ግን ማወቅ ጥሩ ነው አለማወቅ ክፉ
ሳያውቁ አውቂያለሁ እረዘመ ሰልፉ
አንተ አስተምረኸኝ ለእውቀት እስከበቃ
ልጫር ልሞጫጭረው አትከልክለኝ በቃ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤8👏1
Forwarded from PHOTO STYLE
#Ad
LUCKY HABESHA 🎯
ወረቀት ድሮ ቀረ | ቀጥታ አሸንፎ ብር መውሰድ!
✨ የሚያሸንፉት እርስዎ ሊሆኑ ይችላሉ!
💰 በእያንዳንዱ ጨዋታ አዲስ አሸናፊዎች!
⚡ ፈጣን ክፍያ | 📲 ቀላል ጨዋታ
✅ አሁን ይቀላቀሉ
https://t.me/Lucky_Habesha
🔥 አሁን ይጫወቱ! - እድልዎን ይሞክሩ
#LuckyHabesha #አሸናፊ_ይሁኑ
LUCKY HABESHA 🎯
ወረቀት ድሮ ቀረ | ቀጥታ አሸንፎ ብር መውሰድ!
✨ የሚያሸንፉት እርስዎ ሊሆኑ ይችላሉ!
💰 በእያንዳንዱ ጨዋታ አዲስ አሸናፊዎች!
⚡ ፈጣን ክፍያ | 📲 ቀላል ጨዋታ
✅ አሁን ይቀላቀሉ
https://t.me/Lucky_Habesha
🔥 አሁን ይጫወቱ! - እድልዎን ይሞክሩ
#LuckyHabesha #አሸናፊ_ይሁኑ
Telegram
Lucky_Habesha (ፈጣን ዕጣ)
who is Lucky?
Welcome everyone to Lucky_Habesha 🤞 Lottery!!
በዚህ ግሩፕ የዕጣ ጨዋታ ይኖረናል።
🔸 1️⃣ ዙር በ11 ሰው እናጫውታለን!!
🔹 መደብ 200 ብር
1ኛ ዕጣ----- 1️⃣5️⃣0️⃣0️⃣ ብር
2ኛ ዕጣ ----4️⃣0️⃣0️⃣ ብር
3ኛ ዕጣ ----1️⃣0️⃣0️⃣ ብር
መልካም ዕድል!!
Welcome everyone to Lucky_Habesha 🤞 Lottery!!
በዚህ ግሩፕ የዕጣ ጨዋታ ይኖረናል።
🔸 1️⃣ ዙር በ11 ሰው እናጫውታለን!!
🔹 መደብ 200 ብር
1ኛ ዕጣ----- 1️⃣5️⃣0️⃣0️⃣ ብር
2ኛ ዕጣ ----4️⃣0️⃣0️⃣ ብር
3ኛ ዕጣ ----1️⃣0️⃣0️⃣ ብር
መልካም ዕድል!!
❤1👍1
#ገጣሚና_ግጥም!
ገጣሚ ለጋስ ነው
ከሰማይ እጆች ላይ ጨረቃዋን ነጥቆ
በጠቢብ ምናቡ
በብዕሩ ቀለም ቃላቶች አርቅቆ
የልቡን ለመግለፅ
በሃሳብ ጎዳና ይወርዳል ይወጣል
ከስንኝ ቀምሮ
የጨረቃን ውበት ላንዲት ሴት ይሰጣል፡፡
ገጣሚ የዋህ ነው
ቃላትን ፍለጋ ውቅያኖስን ቀዝፎ
ከምድር አሸዋ
ከማይቆጠረው ስሜቱን አግዝፎ
የውስጡን ሊከትብ
በማይታክት ሀሳብ አድማሳትን ያልፋል
ከልቡ ቁስል ላይ
ደም እያጠቀሰ ላንዲት ሴት ይፅፋል
ገጣሚ ጀግና ነው
በጦርነት አለም መኖሩ ሳይደንቀው
ዘውትር የሚሰማው
የሙታኖች መርዶ ስሜቱን ሳይሰርቀው
የልቡን ትርታ
ብቻ እያዳመጠ ካ'ሳብ ይሟገታል
በምናብ ጦርነት
ስለ ፍቅሯ ታግሎ ላንዲት ሴት ይሞታል፡፡
ገጣሚ ምስኪን ነው
ከብዙሀን መሀል አንዲቷን አብልጦ
ጠቢብ ማንቱን
በማይመጥን ዋጋ ስለ ፍቅሯ ሽጦ
በብቻነት አለም
ሁሉን እየረሳ እርሷን ያስታውሳል
በትዝታ ታስሮ
በብዕር አይኖቹ ላንዲት ሴት ያለቅሳል፡፡
እንዲህ ነው ገጣሚ
ለሄደች ሄዋኑ ቃላት እያማጠ የሚቀበጣጥር
ከዚህ ሁሉ ታግሎ
ስላንዲት ሴት ገድል ስንኝ የሚቋጥር፡፡
ይሄ ነው ገጣሚ
ከጥበቡ ጋራ
አፍቃሪ ልቦናን አብሮ የታደለ
ባልጎደለ ፀጋው
ስላንዲት ሴት ብሎ ክብሩን የገደለ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰ
ገጣሚ ለጋስ ነው
ከሰማይ እጆች ላይ ጨረቃዋን ነጥቆ
በጠቢብ ምናቡ
በብዕሩ ቀለም ቃላቶች አርቅቆ
የልቡን ለመግለፅ
በሃሳብ ጎዳና ይወርዳል ይወጣል
ከስንኝ ቀምሮ
የጨረቃን ውበት ላንዲት ሴት ይሰጣል፡፡
ገጣሚ የዋህ ነው
ቃላትን ፍለጋ ውቅያኖስን ቀዝፎ
ከምድር አሸዋ
ከማይቆጠረው ስሜቱን አግዝፎ
የውስጡን ሊከትብ
በማይታክት ሀሳብ አድማሳትን ያልፋል
ከልቡ ቁስል ላይ
ደም እያጠቀሰ ላንዲት ሴት ይፅፋል
ገጣሚ ጀግና ነው
በጦርነት አለም መኖሩ ሳይደንቀው
ዘውትር የሚሰማው
የሙታኖች መርዶ ስሜቱን ሳይሰርቀው
የልቡን ትርታ
ብቻ እያዳመጠ ካ'ሳብ ይሟገታል
በምናብ ጦርነት
ስለ ፍቅሯ ታግሎ ላንዲት ሴት ይሞታል፡፡
ገጣሚ ምስኪን ነው
ከብዙሀን መሀል አንዲቷን አብልጦ
ጠቢብ ማንቱን
በማይመጥን ዋጋ ስለ ፍቅሯ ሽጦ
በብቻነት አለም
ሁሉን እየረሳ እርሷን ያስታውሳል
በትዝታ ታስሮ
በብዕር አይኖቹ ላንዲት ሴት ያለቅሳል፡፡
እንዲህ ነው ገጣሚ
ለሄደች ሄዋኑ ቃላት እያማጠ የሚቀበጣጥር
ከዚህ ሁሉ ታግሎ
ስላንዲት ሴት ገድል ስንኝ የሚቋጥር፡፡
ይሄ ነው ገጣሚ
ከጥበቡ ጋራ
አፍቃሪ ልቦናን አብሮ የታደለ
ባልጎደለ ፀጋው
ስላንዲት ሴት ብሎ ክብሩን የገደለ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰ
❤13👌5👍1
#ትንሽ_ቦታ
በዚህ ዓመት፣
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሸ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ቦታ መሠደጃ፡፡
ምናለበት፣
ለምናልባት ብንተውለት
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ቦታ እንዋዋል፣በልባችን ደግ እንሁን፡፡
በአንጎላችን መላወሻ፣
ትንሽ ቦታ እንተውለት
‹‹ምናልባት›› የምንልበት!!
ልክ እንደአምና ለዚህ ዓመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሠር ይቅር ማያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ፡፡
ጥግ ድረስ የለም ስራ፣ጥግ ድረስ የለም ፋታ፡፡
በልባችን ደግ በኩል፣ እንፈልግ ባዶ ቦታ፣
የጳጉሜ አይነት ትንሽ ቦታ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ነብዩ መኮንን
በዚህ ዓመት፣
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሸ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ቦታ መሠደጃ፡፡
ምናለበት፣
ለምናልባት ብንተውለት
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ቦታ እንዋዋል፣በልባችን ደግ እንሁን፡፡
በአንጎላችን መላወሻ፣
ትንሽ ቦታ እንተውለት
‹‹ምናልባት›› የምንልበት!!
ልክ እንደአምና ለዚህ ዓመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሠር ይቅር ማያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ፡፡
ጥግ ድረስ የለም ስራ፣ጥግ ድረስ የለም ፋታ፡፡
በልባችን ደግ በኩል፣ እንፈልግ ባዶ ቦታ፣
የጳጉሜ አይነት ትንሽ ቦታ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ነብዩ መኮንን
❤8🔥3👏1
#አንዴ_ብትሰጠኝ
ቀምሼው አላውቅም
እያልኳት አትስጭኝ
ልብሱን ገለጥ አርጋ
መልኩን ብታሳየኝ
እኔው ሰፍ ብዬ
አልኳት ስጭኝ ስጭኝ
እርሷም ሳትሳሳ
አንድ ጊዜ ብትሰጠኝ
ሁሌም ስጭኝ አልኳት
በጣም ነው የጣመኝ
ስሙንም ስትነግረኝ
እንዳይጠፋኝ ብላ
ለካስ የማውቀው ነው
ደስታ ከረሚላ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ቀምሼው አላውቅም
እያልኳት አትስጭኝ
ልብሱን ገለጥ አርጋ
መልኩን ብታሳየኝ
እኔው ሰፍ ብዬ
አልኳት ስጭኝ ስጭኝ
እርሷም ሳትሳሳ
አንድ ጊዜ ብትሰጠኝ
ሁሌም ስጭኝ አልኳት
በጣም ነው የጣመኝ
ስሙንም ስትነግረኝ
እንዳይጠፋኝ ብላ
ለካስ የማውቀው ነው
ደስታ ከረሚላ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
🥰13😁12👍8❤7👏2
#ቢጥፉት_ቢጥፉት
የተላበሱትን
ላይጥሉት አውልቀው
ቢጥፉት፣ቢጥፉት
መቀደዱን ዓይተው
ዲሪቶን ቢደርቱት
ደጋግመው ቢጥፉት
አጋልጦ ይሰጣል
በአዲስ ካልቀየሩት
እንደው ላይከርሙበት
በመጣፌያ ጥፎ
ገበና ላይሸፍን
ሊሰጥ አሳልፎ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ግዛቸው ማሞ
የተላበሱትን
ላይጥሉት አውልቀው
ቢጥፉት፣ቢጥፉት
መቀደዱን ዓይተው
ዲሪቶን ቢደርቱት
ደጋግመው ቢጥፉት
አጋልጦ ይሰጣል
በአዲስ ካልቀየሩት
እንደው ላይከርሙበት
በመጣፌያ ጥፎ
ገበና ላይሸፍን
ሊሰጥ አሳልፎ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ግዛቸው ማሞ
❤8🔥5👏1
#የሰሞኑን_እንጃ
ጋቢዬን ደርቤ
ውስጤን ይበርደኛል
ከእሳቱም ቀርቤ
ያንቀጠቅጠኛል
ሰው መሀልም ሆኜ
ሰው ይናፍቀኛል
ከራሴው ዝምታ
ጩኸት ይሰማኛል
ለወትሮ የወደድኩት
ዛሬ አስጠልቶኛል
የሰሞኑን እንጃ
ፍርሀት ያርደኛል
ልቤ ሁሉን ጠልቶ
አንቺን ብቻ ይለኛል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ጋቢዬን ደርቤ
ውስጤን ይበርደኛል
ከእሳቱም ቀርቤ
ያንቀጠቅጠኛል
ሰው መሀልም ሆኜ
ሰው ይናፍቀኛል
ከራሴው ዝምታ
ጩኸት ይሰማኛል
ለወትሮ የወደድኩት
ዛሬ አስጠልቶኛል
የሰሞኑን እንጃ
ፍርሀት ያርደኛል
ልቤ ሁሉን ጠልቶ
አንቺን ብቻ ይለኛል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤17🥰10👍1
#ቅበጭ_እንደ_ልብሽ
በጫንቃዬ ለዋልሽ ሸክሙ ላልከበደኝ፣
ቅብጠትሽ የመጨ እኔን ከተመቸኝ፣
ምን አርጊ ይሉሻል? ቢሉሽም ተያቸው፣
በእራሴ ትክሻ ምን ቁርጥ አርጓቸው?
ቅበጭ እንደ ልብሽ ደስ ይበልሽ በርቺ፣
ተከፍተሽ ሳይሽ ነው የሚጨንቀኝ ላንቺ፣
ምን ይሉኝ አትበይ ካሉሽም ተያቸው፣
እነርሱን ካልነካሽ ምን ጥልቅ አርጓቸው?
እንኳንስ ጫንቃዬን ልቤንም ወስደሻል፣
ገና እጨምራለሁ ላንቺ እኮ ያንስሻል፣
ብቻ አደራ ውዴ ከሌላ አትቅበጭ፣
በእኔ ሰውነት ላይ ሰክነሽ ተቀመጭ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
በጫንቃዬ ለዋልሽ ሸክሙ ላልከበደኝ፣
ቅብጠትሽ የመጨ እኔን ከተመቸኝ፣
ምን አርጊ ይሉሻል? ቢሉሽም ተያቸው፣
በእራሴ ትክሻ ምን ቁርጥ አርጓቸው?
ቅበጭ እንደ ልብሽ ደስ ይበልሽ በርቺ፣
ተከፍተሽ ሳይሽ ነው የሚጨንቀኝ ላንቺ፣
ምን ይሉኝ አትበይ ካሉሽም ተያቸው፣
እነርሱን ካልነካሽ ምን ጥልቅ አርጓቸው?
እንኳንስ ጫንቃዬን ልቤንም ወስደሻል፣
ገና እጨምራለሁ ላንቺ እኮ ያንስሻል፣
ብቻ አደራ ውዴ ከሌላ አትቅበጭ፣
በእኔ ሰውነት ላይ ሰክነሽ ተቀመጭ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
👏13❤9👍2
#እንደዚም_አለንዴ?
ምን ልበል ስላንቺ ቃላቶቼም ፈሩ፡
አንደበቴም ሞተ ሳይገባ ካፈሩ፡
አይኔም አላይ አለ ግርማሽ አሳውሮት፡
እግሬም አልፀናልኝ ክብርሽ አሸብሮት፡
እጄም ከፍ አለብኝ ድንቅ ውበትሽ ማርኮት፡
እንደዚም አለንዴ ማማር በተፈጥሮ፡
ሰዓሊ ማይስለው ቀለምን አጣምሮ፡
ፀሀፊ ማይገልፀው በብዕር ሞንጭሮ፡
ዘፋኝ የማይዘፍነው ድምፁን አሳምሮ፡
ምሁር ማይደርስበት ዝንት ተመራምሮ፡
ጨረቃን ሰማሗት እሪ ወየው ስትል፡
ፀሀይም በንዴት ፍጥረትን ስታግል፡
ኮከቧም አዝና ወዲያ ስትኮበልል፡
ደመናም ተከፍቶ ዞር ሲል ገለል፡
እንዲ ብስጭት ያሉት ዳሩ ባንቺ ላይ ነው፡
የጨረቃን ድምቀት ለራስሽ አርገሽው፡
የከዋክብትን ውበት በድፍረት ዘርፈሽው፡
የፀሀይን ሙቀት ይዘሽ አፍነሽው፡
የደመናን ግርማ በሀይል ነጥቀሽው፡
አኖረብሽ እንደው ያን ፀዳል ጥበቡን፡
ውበቱን ደፋብሽ ከሱ የሆነውን፡
እኔም ተገርሜ በውበትሽ ውዴ፡
ብዬ ትቼዋለው እንደዚም አለንዴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ምን ልበል ስላንቺ ቃላቶቼም ፈሩ፡
አንደበቴም ሞተ ሳይገባ ካፈሩ፡
አይኔም አላይ አለ ግርማሽ አሳውሮት፡
እግሬም አልፀናልኝ ክብርሽ አሸብሮት፡
እጄም ከፍ አለብኝ ድንቅ ውበትሽ ማርኮት፡
እንደዚም አለንዴ ማማር በተፈጥሮ፡
ሰዓሊ ማይስለው ቀለምን አጣምሮ፡
ፀሀፊ ማይገልፀው በብዕር ሞንጭሮ፡
ዘፋኝ የማይዘፍነው ድምፁን አሳምሮ፡
ምሁር ማይደርስበት ዝንት ተመራምሮ፡
ጨረቃን ሰማሗት እሪ ወየው ስትል፡
ፀሀይም በንዴት ፍጥረትን ስታግል፡
ኮከቧም አዝና ወዲያ ስትኮበልል፡
ደመናም ተከፍቶ ዞር ሲል ገለል፡
እንዲ ብስጭት ያሉት ዳሩ ባንቺ ላይ ነው፡
የጨረቃን ድምቀት ለራስሽ አርገሽው፡
የከዋክብትን ውበት በድፍረት ዘርፈሽው፡
የፀሀይን ሙቀት ይዘሽ አፍነሽው፡
የደመናን ግርማ በሀይል ነጥቀሽው፡
አኖረብሽ እንደው ያን ፀዳል ጥበቡን፡
ውበቱን ደፋብሽ ከሱ የሆነውን፡
እኔም ተገርሜ በውበትሽ ውዴ፡
ብዬ ትቼዋለው እንደዚም አለንዴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍12❤5🔥1🥰1
#በመኖር_አጸድ_ውስጥ
ጊዜ ከሰው መሀል- መርጦ ሲያቀማጥል
ማጣት አለ ደሞ፥
የወለዱትን ልጅ፥ ጉድፍ ላይ የሚያስጥል
በተፈሰከ ቀን፥ ጾምን የሚያስቀጥል::
እድልና ትግል በሚጫወቱበት
በደልዳላው ስፍራ
አለቃና ጭፍራ-
ቃል ሲለዋወጡ፥ ውልና መሀላ
“አብረን እናድጋለን” ቢባል ለይስሙላ
ወንዙን ሳያጎድል ፥ሐይቁ መች ሊሞላ፤
ጸሐይ ብትወጣ
ፍጥረት በጠቅላላው ጸጋዋን ቢቀበል
የደመናም ጠበል፥
ለሁሉ ቢደርስም
አንደኛው አያድግም፥ አንዱን ሳያከስም::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ጊዜ ከሰው መሀል- መርጦ ሲያቀማጥል
ማጣት አለ ደሞ፥
የወለዱትን ልጅ፥ ጉድፍ ላይ የሚያስጥል
በተፈሰከ ቀን፥ ጾምን የሚያስቀጥል::
እድልና ትግል በሚጫወቱበት
በደልዳላው ስፍራ
አለቃና ጭፍራ-
ቃል ሲለዋወጡ፥ ውልና መሀላ
“አብረን እናድጋለን” ቢባል ለይስሙላ
ወንዙን ሳያጎድል ፥ሐይቁ መች ሊሞላ፤
ጸሐይ ብትወጣ
ፍጥረት በጠቅላላው ጸጋዋን ቢቀበል
የደመናም ጠበል፥
ለሁሉ ቢደርስም
አንደኛው አያድግም፥ አንዱን ሳያከስም::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤12🔥3👏2🥰1