#ይሄ_ሁሉ_ጣዖት
እናት ያበጀችው ከስጋዋ ከፍላ
ያንን ሁሉ ወጣት ፤ ያንን ጅምር አፍላ
በውነት በፍትህ ስም ፥ እየማሉ ከዱት
እንደ ፋሲካ በግ ፥ወደ ካራው ነዱት::
የቀኑ ቀውስነት፤ የሌለው አምሳያ
ዝናብ እንደፈታው ፥ የገጠር ገበያ
ዘመን ተዘባርቆ፥
አገር በግራጁ ፥ ከቀኝ ኪሱ ሰርቆ
ጉዳችን መች አልቆ!
ትናንት አለም አቀፍ ወዛደራዊነት
ዛሬ በየፈርጁ ፥ዘርማንዘራዊነት
ደሞ ያርማው ብዛት፥ የባንዲራው አይነት
ቢያመልኩት አይራራም፥ እጣን እያጨሱ
ሻማ እየለኮሱ
ይሄ ሁሉ ጣኦት፥ የሰው ደም ነው ምሱ ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
እናት ያበጀችው ከስጋዋ ከፍላ
ያንን ሁሉ ወጣት ፤ ያንን ጅምር አፍላ
በውነት በፍትህ ስም ፥ እየማሉ ከዱት
እንደ ፋሲካ በግ ፥ወደ ካራው ነዱት::
የቀኑ ቀውስነት፤ የሌለው አምሳያ
ዝናብ እንደፈታው ፥ የገጠር ገበያ
ዘመን ተዘባርቆ፥
አገር በግራጁ ፥ ከቀኝ ኪሱ ሰርቆ
ጉዳችን መች አልቆ!
ትናንት አለም አቀፍ ወዛደራዊነት
ዛሬ በየፈርጁ ፥ዘርማንዘራዊነት
ደሞ ያርማው ብዛት፥ የባንዲራው አይነት
ቢያመልኩት አይራራም፥ እጣን እያጨሱ
ሻማ እየለኮሱ
ይሄ ሁሉ ጣኦት፥ የሰው ደም ነው ምሱ ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤10👍5👏5
#ማነው_የተረዳኝ
ማነው የተረዳኝ የገባው ስሜቴ
እኔ በሱ ፍቅር እንቅልፍ ማጣቴ።
ታዲያ እስከ መቼ አፍኜው እኖራለሁ
አንድ ቀን በይፋ ግልፅ አወጣዋለሁ።
እስከዛች ደቂቃ እስከዛች ቀን ድረስ
ይህንን ሚስጥሬን ለማንስ ልተንፍስ።
እሱ ኩራተኛ ፍቅር የማይገባው
የፍቅርን ትርጉም የማይረዳው
መልክና ቁመናው ልብ የሚነዛው
ሳቁና ፈገግታው መንፈሰ የሚያድሰው
ከሁሉ ተግባቢ ያ ቆንጆ ሰው
የኔን ልብ ሰርቆ ወዴት ሰወረው?
እባክህ ተረዳኝ አስብልኝ አንዴ
እኔ ባንተ ፍቅር ተቃርቧል ማበዴ
ሌላ ሴት ጋር ሳይህ እቀናለሁ ባነዴ
ይህን እወቅልኝ እባክህን ውዴ።
አንተ ፈገግ ስትል እኔ የምስቀው
አንተ ስትከፋ እኔ አዝኜ የምውለው
እባክህ ተረዳኝ ስለወደድኩህ ነው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ማነው የተረዳኝ የገባው ስሜቴ
እኔ በሱ ፍቅር እንቅልፍ ማጣቴ።
ታዲያ እስከ መቼ አፍኜው እኖራለሁ
አንድ ቀን በይፋ ግልፅ አወጣዋለሁ።
እስከዛች ደቂቃ እስከዛች ቀን ድረስ
ይህንን ሚስጥሬን ለማንስ ልተንፍስ።
እሱ ኩራተኛ ፍቅር የማይገባው
የፍቅርን ትርጉም የማይረዳው
መልክና ቁመናው ልብ የሚነዛው
ሳቁና ፈገግታው መንፈሰ የሚያድሰው
ከሁሉ ተግባቢ ያ ቆንጆ ሰው
የኔን ልብ ሰርቆ ወዴት ሰወረው?
እባክህ ተረዳኝ አስብልኝ አንዴ
እኔ ባንተ ፍቅር ተቃርቧል ማበዴ
ሌላ ሴት ጋር ሳይህ እቀናለሁ ባነዴ
ይህን እወቅልኝ እባክህን ውዴ።
አንተ ፈገግ ስትል እኔ የምስቀው
አንተ ስትከፋ እኔ አዝኜ የምውለው
እባክህ ተረዳኝ ስለወደድኩህ ነው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤26
ናፍቆት በገደለኝ!!
ልትቀብረኝ በመጣህ፣
እኔም ባገኘዉህ፤
ለቀብር ለሰልስት በማታ በካርታ፣
በመክብብ ጨዋታ፤
በምሽት በወጉ፣
ድንኳን ስጠብቁ፤
ደግሞ ተደጋግሞ ለአርባ ለሰማኒያ፣
ከእኔ እንዳትጠፋ፤
ለተስካር ሙት አመት፣
ለሰባት ለአስራ ሁለት፤
ምነዉ በገደለኝ!
ናፍቆት ሞት ቢሆነኝ፤
ሁሌ ሁሌ ሁሌ እንድታባብለኝ፤
ናፍቆት በገደለኝ!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ረድኤት ተረፈ
ልትቀብረኝ በመጣህ፣
እኔም ባገኘዉህ፤
ለቀብር ለሰልስት በማታ በካርታ፣
በመክብብ ጨዋታ፤
በምሽት በወጉ፣
ድንኳን ስጠብቁ፤
ደግሞ ተደጋግሞ ለአርባ ለሰማኒያ፣
ከእኔ እንዳትጠፋ፤
ለተስካር ሙት አመት፣
ለሰባት ለአስራ ሁለት፤
ምነዉ በገደለኝ!
ናፍቆት ሞት ቢሆነኝ፤
ሁሌ ሁሌ ሁሌ እንድታባብለኝ፤
ናፍቆት በገደለኝ!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ረድኤት ተረፈ
❤22👍4👏1
#እረፉ!
“ዘመመ!” ብላችሁ የሰው ቤት አትግፉ
እሾህ ለማሳመር አበባ አታርግፉ።
እረፍ!
“ቆሜያለሁ!” ለማለት አጥሬን አትደገፍ
ለአመዳም ወዘናህ ቆዳዬን አትግፈፍ።
እረፍ!
በመስመርህ ፍካ በድንበርህ ለምልም
በየአልጋህ እደር በየእንቅልፍህ አልም።
እረፊ!
በኩረጃ ንባብ ትርጉም አትግደፊ
በሰባራ መርፌሽ የሰው ልክ አትስፊ።
ማን አንደጠለፈኝ ማን እንደሰበረኝ
ጠያቂ አጣሁ እንጂ መልስማ ነበረኝ።
ምክንያት ታመመ መፍትሄ ታመመ
ከጥያቄው በፊት መልሱ እየቀደመ።
ሌብነት ገነነ
ግርግር ገነነ
ብልጭልጭ ገነነ
ድንግርግር ገነነ
ኪሳራ ገነነ
ደላሎች ገነኑ፣ ደላሎች ጀገኑ
ባልዋለ ገበያ ዋጋ እየተመኑ!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
“ዘመመ!” ብላችሁ የሰው ቤት አትግፉ
እሾህ ለማሳመር አበባ አታርግፉ።
እረፍ!
“ቆሜያለሁ!” ለማለት አጥሬን አትደገፍ
ለአመዳም ወዘናህ ቆዳዬን አትግፈፍ።
እረፍ!
በመስመርህ ፍካ በድንበርህ ለምልም
በየአልጋህ እደር በየእንቅልፍህ አልም።
እረፊ!
በኩረጃ ንባብ ትርጉም አትግደፊ
በሰባራ መርፌሽ የሰው ልክ አትስፊ።
ማን አንደጠለፈኝ ማን እንደሰበረኝ
ጠያቂ አጣሁ እንጂ መልስማ ነበረኝ።
ምክንያት ታመመ መፍትሄ ታመመ
ከጥያቄው በፊት መልሱ እየቀደመ።
ሌብነት ገነነ
ግርግር ገነነ
ብልጭልጭ ገነነ
ድንግርግር ገነነ
ኪሳራ ገነነ
ደላሎች ገነኑ፣ ደላሎች ጀገኑ
ባልዋለ ገበያ ዋጋ እየተመኑ!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤18👍4🔥3
#አንቺ_የለሽበትም!
መስኮት ቀዶ ገባ፣
ንፋስና ውርጩ፤
ለንጋት አዜሙ፣
ወፎቹ ተንጫጩ፡፡
ተነፋፍቀው የኖሩ፣
ተኳርፈው ያደሩ፤
ለወፎቹ ዜማ፣ ግጥም ያወርዳሉ፤
ለቀዘቀዘ ልብ፣ ሙቀት ይረጫሉ፤
ይተቃቀፋሉ፡፡
አንቺ የለሽበትም፡፡
ከጎረቤት ደጃፍ፣ቡና ይወቀጣል፤
‹‹ቡና ጠጡ›› እያለ፣
እንደመወርወሪያ፣
በመንደሩ መሀል፣ህጻን ልጅ ይሮጣል፡፡
እሱን ተከትለው፤
የመንደሩ ሴቶች፣
ሀሜት አንጠልጥለው፤
ይሽቀዳደማሉ፤
ለነጋው አዲስ ቀን
ንድፍ ያስቀምጣሉ፡፡
አንቺ የለሽበትም፡፡
ደግሞ ቀኑ ጋመ፣ . . . .
አዳሜ ተነሳ፣
ከትናንት ገንፍሎ፣
እንደልሙጥ ሽሮ፣
መግላሊቱን ጥሎ፤
ተስፋ አንጠልጥሎ፤
ሊረግም - ሊመርቅ
ሊጥል ወይ ሊወድቅ፤
ሊያለቅስ ወይም ሊስቅ፤
በናፍቆት - ሊተያይ፤
ተጣልቶ - ሊለያይ፣ . . . .
አሮጌ ትላንቱን፣ ጎጆው እየጣለ፤
አዲስ ቀኑን ሊያትም፣ አደባባይ ዋለ፡፡
አንቺ የለሽበትም፡፡
ደግሞ አመሻሽ ላይ፣ . . . .
ተራራው አናት ላይ፣
ሰአሊው ተፈጥሮ፣
አድማስን ወጥሮ፣
ቀለማት ደርድሮ፤
አንዳንዴ በተስፋ፣
ቢጫ እያበዛ፣ ቀይ እያሳነሰ፤
አንዳንዴ በምሬት፣
ቀዩን እያበዛ፣ ቢጫ እየቀነሰ፤
ተቅላሎት ሲሸምን፣ ፍም እያባዘተ፣
የደከመውን ቀን፣ አባብሎ ሲያስተኛ፣ ውበት እየጋተ፡፡
ደግሞ መለስ ብሎ፣
በልቤ የያዝኩትን፣ ማጣት አስተውሎ፣
በረዥም ቡሩሹ፣ ካድማስ ወዲያ በኩል፣ ጨለማን አጥቅሶ፤
ከሰል ሲያስመስለው፣ ሲሰራ ያዋለውን፣ ሲያፈርሰው መልሶ፤
ለጥበብ ምትሀት፣ ልባቸው የገበረ፤
ሰዎች ተሰብስበው፣ ያደንቁ ነበረ፡፡
አንቺ የለሽበትም፡፡
አንቺ የለሽበትም፡፡
አላገኘሁሽም፡፡
ቢሆንም አውቃለሁ፣ . . .
የለሽም አልልም እፈልግሻለሁ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በድሉ ዋቅጅራ
መስኮት ቀዶ ገባ፣
ንፋስና ውርጩ፤
ለንጋት አዜሙ፣
ወፎቹ ተንጫጩ፡፡
ተነፋፍቀው የኖሩ፣
ተኳርፈው ያደሩ፤
ለወፎቹ ዜማ፣ ግጥም ያወርዳሉ፤
ለቀዘቀዘ ልብ፣ ሙቀት ይረጫሉ፤
ይተቃቀፋሉ፡፡
አንቺ የለሽበትም፡፡
ከጎረቤት ደጃፍ፣ቡና ይወቀጣል፤
‹‹ቡና ጠጡ›› እያለ፣
እንደመወርወሪያ፣
በመንደሩ መሀል፣ህጻን ልጅ ይሮጣል፡፡
እሱን ተከትለው፤
የመንደሩ ሴቶች፣
ሀሜት አንጠልጥለው፤
ይሽቀዳደማሉ፤
ለነጋው አዲስ ቀን
ንድፍ ያስቀምጣሉ፡፡
አንቺ የለሽበትም፡፡
ደግሞ ቀኑ ጋመ፣ . . . .
አዳሜ ተነሳ፣
ከትናንት ገንፍሎ፣
እንደልሙጥ ሽሮ፣
መግላሊቱን ጥሎ፤
ተስፋ አንጠልጥሎ፤
ሊረግም - ሊመርቅ
ሊጥል ወይ ሊወድቅ፤
ሊያለቅስ ወይም ሊስቅ፤
በናፍቆት - ሊተያይ፤
ተጣልቶ - ሊለያይ፣ . . . .
አሮጌ ትላንቱን፣ ጎጆው እየጣለ፤
አዲስ ቀኑን ሊያትም፣ አደባባይ ዋለ፡፡
አንቺ የለሽበትም፡፡
ደግሞ አመሻሽ ላይ፣ . . . .
ተራራው አናት ላይ፣
ሰአሊው ተፈጥሮ፣
አድማስን ወጥሮ፣
ቀለማት ደርድሮ፤
አንዳንዴ በተስፋ፣
ቢጫ እያበዛ፣ ቀይ እያሳነሰ፤
አንዳንዴ በምሬት፣
ቀዩን እያበዛ፣ ቢጫ እየቀነሰ፤
ተቅላሎት ሲሸምን፣ ፍም እያባዘተ፣
የደከመውን ቀን፣ አባብሎ ሲያስተኛ፣ ውበት እየጋተ፡፡
ደግሞ መለስ ብሎ፣
በልቤ የያዝኩትን፣ ማጣት አስተውሎ፣
በረዥም ቡሩሹ፣ ካድማስ ወዲያ በኩል፣ ጨለማን አጥቅሶ፤
ከሰል ሲያስመስለው፣ ሲሰራ ያዋለውን፣ ሲያፈርሰው መልሶ፤
ለጥበብ ምትሀት፣ ልባቸው የገበረ፤
ሰዎች ተሰብስበው፣ ያደንቁ ነበረ፡፡
አንቺ የለሽበትም፡፡
አንቺ የለሽበትም፡፡
አላገኘሁሽም፡፡
ቢሆንም አውቃለሁ፣ . . .
የለሽም አልልም እፈልግሻለሁ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በድሉ ዋቅጅራ
❤14👍1
#ልሂድ_ያልሽ_ለታ
እንዴት ነህ ስትዪኝ ያኔ የመለስኩልሽ
ከሌለሽ የለሁም ብዬ የነገርኩሽ
እንዳትረሺው ብዬ ዛሬም ልድገምልሽ
እውነቴን ነው ፍቅሬ ከሌለሽ የለሁም
አንቺ ስላለሺኝ አሁን ላይ አልሞትኩም
ግን ወዴ ካጣሁሽ በህይወት እያለው
አልቅሰሽ ሳትቀብሪኝ በቁሜ እሞታለው
እስኪ አስቢው ውዴ በቁም ከሞትኩብሽ
አላቅፍሽ፣ አልስምሽ ግጥም አልፅፍልሽ
ባካል አላገኝሽ ወይ አልደውልልሽ
ያለሁበት ጠፍቶኝ ስንከራተትልሽ
እናቴ አልቅሳ በቁሜ አትቀብረኝ
ወይ ድጋሜ አርግዛ እኔኑ አትወልደኝ
ሞትና ቀብሬ ተራርቀውብኝ
እውነት ያበደ ሰው ሆኜ እቀራለውኝ
አንቺ የሄድሽ ጊዜ ገነትንና ሲዖልን እዚው አየዋለው
ገነትን በትዝታ ሲዖልን በእብደት ውስጥ እመለከታለው
ልሂድ ያልሽ ጊዜ ቀኑ ይጨልማል
ጨረቃ ጠዋት ላይ ፀሀይ ማታ ይወጣል
ተፈጥሮ በኔ ላይ ይገለባበጣል
ውዴ ሆይ ልሂድ ያልሽ ለታ
ቀን ላይ እየሞትኩኝ እኖራለው ማታ
አንቺን እያሰብኩኝ ሁሌ በትዝታ
ስለዚህ ፍቅሬ ሞቴ ያማረሽ ጊዜ ምንም እንዳትዪኝ
3 ፊደል ተናግረሽ "ልሂድ" ብቻ በይኝ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
እንዴት ነህ ስትዪኝ ያኔ የመለስኩልሽ
ከሌለሽ የለሁም ብዬ የነገርኩሽ
እንዳትረሺው ብዬ ዛሬም ልድገምልሽ
እውነቴን ነው ፍቅሬ ከሌለሽ የለሁም
አንቺ ስላለሺኝ አሁን ላይ አልሞትኩም
ግን ወዴ ካጣሁሽ በህይወት እያለው
አልቅሰሽ ሳትቀብሪኝ በቁሜ እሞታለው
እስኪ አስቢው ውዴ በቁም ከሞትኩብሽ
አላቅፍሽ፣ አልስምሽ ግጥም አልፅፍልሽ
ባካል አላገኝሽ ወይ አልደውልልሽ
ያለሁበት ጠፍቶኝ ስንከራተትልሽ
እናቴ አልቅሳ በቁሜ አትቀብረኝ
ወይ ድጋሜ አርግዛ እኔኑ አትወልደኝ
ሞትና ቀብሬ ተራርቀውብኝ
እውነት ያበደ ሰው ሆኜ እቀራለውኝ
አንቺ የሄድሽ ጊዜ ገነትንና ሲዖልን እዚው አየዋለው
ገነትን በትዝታ ሲዖልን በእብደት ውስጥ እመለከታለው
ልሂድ ያልሽ ጊዜ ቀኑ ይጨልማል
ጨረቃ ጠዋት ላይ ፀሀይ ማታ ይወጣል
ተፈጥሮ በኔ ላይ ይገለባበጣል
ውዴ ሆይ ልሂድ ያልሽ ለታ
ቀን ላይ እየሞትኩኝ እኖራለው ማታ
አንቺን እያሰብኩኝ ሁሌ በትዝታ
ስለዚህ ፍቅሬ ሞቴ ያማረሽ ጊዜ ምንም እንዳትዪኝ
3 ፊደል ተናግረሽ "ልሂድ" ብቻ በይኝ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤11👍8🔥6❤🔥2🙏1
#እንዳትመጣብኝ !!
እንዲያ እየወደድኳት
እንዲያ እያፈቀርኳት
ልብ እንዳልሰጠኋት
አወይ አለማወቅ ምን አይነቷ ጅል ናት
በጇ ያለውን ወርቅ እንደመዳብ ቆጥራ
የተሰረቀ ነው የሚጣፍጥ ብላ
ልብን ያህል ነገር አሽቀንጥራ ጥላ
ሄዳ ሄዳ ሄዳ
ዘላ ዘላ ዘላ
ካሻት ጋር ተፋቅራ
ካሻት ጋር ተፋታ
የማታ የማታ ሲጨላልምባት
ድንገት ትዝ ስላት
ልትመጣ ነው አሉ
አረ ውዴት ወዴት ! ወዴት ትመጣለች !!
አትሞክሪው በሏት ንገሯት ከሰማች
አመሏን አውቃለው እብድ ትፈራለች
ያ የምታውቂው ልጅ አሁን የለም በሏት
ንገሯት ! ንገሯት
የባጡን የቆጡን ቅብጥርጥር አርጉላት!
አንቺን የሚያይበት አይኖቹን አጥፍቷል!
አንቺን የሰማበት ጆሮዎቹን ደፍኗል
አንቺን ያቀፈበት ክንዶቹን ሰባብሯል
አረ ምኑ ቅጡ እንዳልነበር ሆኗል
ጨርቁን ጥሎ አብዷል ብላችሁ ንገሯት
እንዳትመጣብኝ እንዳትደርስ አድርጓት !!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዳዊት ተ/ማርያም
እንዲያ እየወደድኳት
እንዲያ እያፈቀርኳት
ልብ እንዳልሰጠኋት
አወይ አለማወቅ ምን አይነቷ ጅል ናት
በጇ ያለውን ወርቅ እንደመዳብ ቆጥራ
የተሰረቀ ነው የሚጣፍጥ ብላ
ልብን ያህል ነገር አሽቀንጥራ ጥላ
ሄዳ ሄዳ ሄዳ
ዘላ ዘላ ዘላ
ካሻት ጋር ተፋቅራ
ካሻት ጋር ተፋታ
የማታ የማታ ሲጨላልምባት
ድንገት ትዝ ስላት
ልትመጣ ነው አሉ
አረ ውዴት ወዴት ! ወዴት ትመጣለች !!
አትሞክሪው በሏት ንገሯት ከሰማች
አመሏን አውቃለው እብድ ትፈራለች
ያ የምታውቂው ልጅ አሁን የለም በሏት
ንገሯት ! ንገሯት
የባጡን የቆጡን ቅብጥርጥር አርጉላት!
አንቺን የሚያይበት አይኖቹን አጥፍቷል!
አንቺን የሰማበት ጆሮዎቹን ደፍኗል
አንቺን ያቀፈበት ክንዶቹን ሰባብሯል
አረ ምኑ ቅጡ እንዳልነበር ሆኗል
ጨርቁን ጥሎ አብዷል ብላችሁ ንገሯት
እንዳትመጣብኝ እንዳትደርስ አድርጓት !!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዳዊት ተ/ማርያም
❤21👍4👏3
#አትመለስ
ይኸውልህ ውዴ............
የስከዛሬው ፍቅር የስካሁን መውደዴ፥
እንደሻማ ቢቀልጥ ውሀ ቢሆን ባንዴ፥
ምን ሊበጀኝ እንባ ለምንስ መንደዴ?
ካልተመቸህ ልቤ ከጎረበጠብህ፥
ፍቅሬ ካልጣፈጠህ ሀሞት ከሆነብህ፥
መለየትን ወዶ ከሸፈተ ልብህ፥
አልከለክልህም ግዴታም የለብህ።
እግርህን አስሬ አቲድ አልልክም፥
መልሱልኝ ብዬም አማላጅ አልክም።
እውነቴን ነው ውዴ ሁን እንደ ፈቃድህ፥
ከሰለቸህ ፍቅሬ ተሟጦ መውደድህ፥
ሂድ እሸኝሀለሁ ጨርቅ ይሁን መንገድህ።
...... ግና.....
እንዳለፈው ጊዜ ልክ እንደትላንቱ፥
አስሰህ ስትመጣ ሲበቃህ ዙረቱ፥
ያው እንደለመድኩት እጆቼን ዘርግቼ፥
ምቀበልህ መስሎህ ከ'ቅፌ አስገብቼ፥
አትመለስ ከቶ ዳግም ላታገኘኝ፥
በመሀላ ብዛት በቃል ልትደልለኝ።
ባክህ ተለመነኝ
አትድከም አትምጣ በማምዬ ሞቷ፥
ስለማይመለስ አንዴ ከቆረጠ የሴት ልጅ አንጀቷ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ይኸውልህ ውዴ............
የስከዛሬው ፍቅር የስካሁን መውደዴ፥
እንደሻማ ቢቀልጥ ውሀ ቢሆን ባንዴ፥
ምን ሊበጀኝ እንባ ለምንስ መንደዴ?
ካልተመቸህ ልቤ ከጎረበጠብህ፥
ፍቅሬ ካልጣፈጠህ ሀሞት ከሆነብህ፥
መለየትን ወዶ ከሸፈተ ልብህ፥
አልከለክልህም ግዴታም የለብህ።
እግርህን አስሬ አቲድ አልልክም፥
መልሱልኝ ብዬም አማላጅ አልክም።
እውነቴን ነው ውዴ ሁን እንደ ፈቃድህ፥
ከሰለቸህ ፍቅሬ ተሟጦ መውደድህ፥
ሂድ እሸኝሀለሁ ጨርቅ ይሁን መንገድህ።
...... ግና.....
እንዳለፈው ጊዜ ልክ እንደትላንቱ፥
አስሰህ ስትመጣ ሲበቃህ ዙረቱ፥
ያው እንደለመድኩት እጆቼን ዘርግቼ፥
ምቀበልህ መስሎህ ከ'ቅፌ አስገብቼ፥
አትመለስ ከቶ ዳግም ላታገኘኝ፥
በመሀላ ብዛት በቃል ልትደልለኝ።
ባክህ ተለመነኝ
አትድከም አትምጣ በማምዬ ሞቷ፥
ስለማይመለስ አንዴ ከቆረጠ የሴት ልጅ አንጀቷ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
🥰12❤8👍6
#ጥቂት_ነው_ምኞቴ
እኔ በህይወቴ
ጥቂት ነው ምኞቴ
ከድፍና ከግፍ
የጠዳ
በረንዳ
እዚያ ላይ መቆየት ፥
ከሚደምን ዛፍ ላይ ፥ ቅጠል ሲዘንብ ማየት፤
አኔ በህይወቴ
ጢኖ ነው ምኞቴ
ለከርስ ጤፍ እንጀራ
ለነፍስ ባለንጀራ
ድክመቴን ስናዘዝ ፥ተግቶ ሚያዳምጠኝ
በደሌን መዝኖ ፥ ቀኖና እማይሰጠኝ፤
እኔ በህይወቴ
ጥቂት ነው ምኞቴ
ሊሞላ የቃጣው፥ ደርበብ ያለ ኑሮ
በስዊዝ ቤተ-ንዋይ፥ ሶስት መቶ ሺህ ዩሮ
ደሞ ከተቻለ፥ ቆንጆ ሚስት ወይዘሮ
እግዜርና ሰይጣን ፥ተጋግዘው የሳሏት
ቢቻል ትንሽ ቪላ ፥አስር ክፍሎች ያሏት
ግና ምኞቴ ሆይ ፥ እንዲያው ለመሆኑ
ጥቂት ብሎ ነገር ፥ስንት ነው መጠኑ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍በእውቀቱ ስዩም
እኔ በህይወቴ
ጥቂት ነው ምኞቴ
ከድፍና ከግፍ
የጠዳ
በረንዳ
እዚያ ላይ መቆየት ፥
ከሚደምን ዛፍ ላይ ፥ ቅጠል ሲዘንብ ማየት፤
አኔ በህይወቴ
ጢኖ ነው ምኞቴ
ለከርስ ጤፍ እንጀራ
ለነፍስ ባለንጀራ
ድክመቴን ስናዘዝ ፥ተግቶ ሚያዳምጠኝ
በደሌን መዝኖ ፥ ቀኖና እማይሰጠኝ፤
እኔ በህይወቴ
ጥቂት ነው ምኞቴ
ሊሞላ የቃጣው፥ ደርበብ ያለ ኑሮ
በስዊዝ ቤተ-ንዋይ፥ ሶስት መቶ ሺህ ዩሮ
ደሞ ከተቻለ፥ ቆንጆ ሚስት ወይዘሮ
እግዜርና ሰይጣን ፥ተጋግዘው የሳሏት
ቢቻል ትንሽ ቪላ ፥አስር ክፍሎች ያሏት
ግና ምኞቴ ሆይ ፥ እንዲያው ለመሆኑ
ጥቂት ብሎ ነገር ፥ስንት ነው መጠኑ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍በእውቀቱ ስዩም
❤18👍6👏2
#ማን_ይሆን_ታማኙ
ማን ይሆን ታማኙ ቃሉን የማይበላ፣
ፍፁም ከአንድ በቀር የማያስብ ሌላ?
ማን ይሆን ታማኙ የእውነት አፍቃሪ፣
ሲያምኑት የማይከዳ ቃል ኪዳን አክባሪ?
ኧረ ማነው ከቶ በቃሉ የፀና፣
አስከዳር የሚጓዝ በፍቅር ጎዳና?
ወንዶችም ለሴቷ በግጥም በዜማ፣
ሴቶችም ለወንዱ በግጥም በዜማ፣
እሷም እያማችው እሱም እሷን ሲያማ፣
አይኔ ስንቱን አየ ጆሮየም ስንቱን ሰማ፣
ለሰው አይነገር የዘንድሮውማ።
ከዳችኝ ተወችኝ አፈረሰች ቃሏን፣
ሰባራ ልብ ይዠ ቀረሁኝ ባዶየን፣
እያለ ያማታል ሳይፈትሽ እራሱን፣
በውስጡ አምቆ በደሉን ክፋቱን።
እሷም ልክ እንደሱ በስንኝ ቀምራ፣
የውስጧን መከፋት የልቧን ሰባራ፣
ህይወቴ ጨልማ ሆናለች መራራ፣
እያለች ስታማው አንዱ በአንዱ ሲስቅ፣
ጥፋተኛው ማነው ታድያ እንደት እንወቅ?
ለማንስ እንዘን በማንስ እንሳቅ?
…………እናማ
ሌሎችን ከመውቀስ ከማማረር ይልቅ፣
እኔ ማነኝ ብለን ልባችን እንጠይቅ።
ትዝብት እና ትችት ከእኛው እንጀምር፣
በቅድሚያ እንዘጋጅ ሳንያዝ በፍቅር።
ዘላለም አይጠፋም እሱ ከዚች ምድር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ማን ይሆን ታማኙ ቃሉን የማይበላ፣
ፍፁም ከአንድ በቀር የማያስብ ሌላ?
ማን ይሆን ታማኙ የእውነት አፍቃሪ፣
ሲያምኑት የማይከዳ ቃል ኪዳን አክባሪ?
ኧረ ማነው ከቶ በቃሉ የፀና፣
አስከዳር የሚጓዝ በፍቅር ጎዳና?
ወንዶችም ለሴቷ በግጥም በዜማ፣
ሴቶችም ለወንዱ በግጥም በዜማ፣
እሷም እያማችው እሱም እሷን ሲያማ፣
አይኔ ስንቱን አየ ጆሮየም ስንቱን ሰማ፣
ለሰው አይነገር የዘንድሮውማ።
ከዳችኝ ተወችኝ አፈረሰች ቃሏን፣
ሰባራ ልብ ይዠ ቀረሁኝ ባዶየን፣
እያለ ያማታል ሳይፈትሽ እራሱን፣
በውስጡ አምቆ በደሉን ክፋቱን።
እሷም ልክ እንደሱ በስንኝ ቀምራ፣
የውስጧን መከፋት የልቧን ሰባራ፣
ህይወቴ ጨልማ ሆናለች መራራ፣
እያለች ስታማው አንዱ በአንዱ ሲስቅ፣
ጥፋተኛው ማነው ታድያ እንደት እንወቅ?
ለማንስ እንዘን በማንስ እንሳቅ?
…………እናማ
ሌሎችን ከመውቀስ ከማማረር ይልቅ፣
እኔ ማነኝ ብለን ልባችን እንጠይቅ።
ትዝብት እና ትችት ከእኛው እንጀምር፣
በቅድሚያ እንዘጋጅ ሳንያዝ በፍቅር።
ዘላለም አይጠፋም እሱ ከዚች ምድር።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤20👍3🔥3
#ሳታውቅ_በስህተት
ካፌ ተቀምጣ ጥንዶቹን እያየች
አንተን እያሰበች ደግሞ እየናፈቀች
አንዳንድ ጊዜ ጸጉሯን
እንደገና ሐብሏን በእጇ እየፈተለች
"ምናለ በኖረ ምናለ ባቀፈኝ" ብላ እየተመኘች ባለችበት ቅጽበት በለችበት ሰዓት
አንድ ሠውዬ መጥቶ ወንበሩን ጠየቃት
አንተ እንደሁ የለህም ምናለ ቢቀመጥ?
ይ…ሄ…ው…ተ…ቀ…መ…ጠ
ሐብል የሚያይ መስሎ
መንታ ጡቶቿ ላይ ዐይኑ እንደፈጠጠ
እሱ እንዳንተ አይደለም…
እሳት ነው ምላሱ ወሬ ማያልቅበት
ደቂቃም አልሞላው…
ከንፈሯን ሲያስከፍት ሳቅ ባሕር ሲከታት ሳታውቀው ነው እሷ ሳታውቀው በስህተት ቁጥሯን የሰጠችው በጠየቃት ቅጽበት
ከዛ በሆነ ቀን…
የሆነችው ሁሉ የሰራችው ስህተት
አውቃ ነው አውቃ ነው
አውቃ ነው በድፍረት
ባክህ ይቅር በላት…..
ያንተን የጀርባ እድፍ ሰይጣን ነው ሹክ ያላት
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሰለሞን ሳህለ
ካፌ ተቀምጣ ጥንዶቹን እያየች
አንተን እያሰበች ደግሞ እየናፈቀች
አንዳንድ ጊዜ ጸጉሯን
እንደገና ሐብሏን በእጇ እየፈተለች
"ምናለ በኖረ ምናለ ባቀፈኝ" ብላ እየተመኘች ባለችበት ቅጽበት በለችበት ሰዓት
አንድ ሠውዬ መጥቶ ወንበሩን ጠየቃት
አንተ እንደሁ የለህም ምናለ ቢቀመጥ?
ይ…ሄ…ው…ተ…ቀ…መ…ጠ
ሐብል የሚያይ መስሎ
መንታ ጡቶቿ ላይ ዐይኑ እንደፈጠጠ
እሱ እንዳንተ አይደለም…
እሳት ነው ምላሱ ወሬ ማያልቅበት
ደቂቃም አልሞላው…
ከንፈሯን ሲያስከፍት ሳቅ ባሕር ሲከታት ሳታውቀው ነው እሷ ሳታውቀው በስህተት ቁጥሯን የሰጠችው በጠየቃት ቅጽበት
ከዛ በሆነ ቀን…
የሆነችው ሁሉ የሰራችው ስህተት
አውቃ ነው አውቃ ነው
አውቃ ነው በድፍረት
ባክህ ይቅር በላት…..
ያንተን የጀርባ እድፍ ሰይጣን ነው ሹክ ያላት
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሰለሞን ሳህለ
👍9❤4🥰2😢1
#በዝናብ_ቅጠረኝ
አማልዱኝ ባልልም አስታራቂ ልኬ
ባልማፀንህም ፊትህ ተንበርክኬ
እንባዬ እንዳይታይ ካንተ ተደብቄ
አነባለሁ ዛሬም ዝናቡን ጠብቄ
ልቤ በስቃይ ጣር ብሶቱን ሲያሰማ
ሀዘኔ ተሰምቶህ ልብህ እንዳይደማ
ቀኑ ጨላልሞልኝ ክረምቱ እስኪገባ
መጥተህ አትጠይቀኝ ሆድህም አይባባ
ዝናብ የኔን ብሶት ሃዘኔን ባያጥበው
ሳለቅስ እንዳታይ እንባዬን ይጋርደው
በጉንጨ 'ሚፈሰው ዝናብ እንዲመስልህ
ሁሌ ክረምት ይሁን ጉዳቴ አይታይህ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
አማልዱኝ ባልልም አስታራቂ ልኬ
ባልማፀንህም ፊትህ ተንበርክኬ
እንባዬ እንዳይታይ ካንተ ተደብቄ
አነባለሁ ዛሬም ዝናቡን ጠብቄ
ልቤ በስቃይ ጣር ብሶቱን ሲያሰማ
ሀዘኔ ተሰምቶህ ልብህ እንዳይደማ
ቀኑ ጨላልሞልኝ ክረምቱ እስኪገባ
መጥተህ አትጠይቀኝ ሆድህም አይባባ
ዝናብ የኔን ብሶት ሃዘኔን ባያጥበው
ሳለቅስ እንዳታይ እንባዬን ይጋርደው
በጉንጨ 'ሚፈሰው ዝናብ እንዲመስልህ
ሁሌ ክረምት ይሁን ጉዳቴ አይታይህ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍20❤6👏5👌3
#የተጣለ_ፈረስ
ዘመኑ ያለፈ
ጋማው የረገፈ ፤
የጎድን አጥንቱ ፤ ማበጠርያ መሳይ
ጠዋት ህያው ፍጡር፥ ሌሊት የጅብ ሲሳይ
ከተማው መግቢያ ላይ
አቧራ የሚቅም
የተጣለ ፈረስ አጋጥሞሽ ፤ አያውቅም?
“ካሁን አሁን መጥቶ፤
ይወስደኛል ነድቶ
ከጋጣው አግብቶ ፤ ያበላኛል እብቅ “
እያለ ጌታውን ፥ተግቶ የሚጠብቅ
የዛሬ ተጎታች ፤ የትናንቱ ሰጋር
ተባብሮ የከዳው፤ ጊዜ ከጌታው ጋር
የቸገረው አቅም፥
የተጣለ ፈረስ ፤ አጋጥሞህ አያውቅም?
ደሞስ መች ይጠፋል? ካንቺም ከኔም መንደር
የቀድሞ ወታደር፥
በጨነቀን ጊዜ ፥“በናት ሀገር ጥሪ “
የምናጣድፈው፥
በድል ቀን ከድግስ፥ የማናሳትፈው
ከነጣቂ መዳፍ ፥ አገር የሚያስመልስ
በገዛ አገሩ ላይ፥
መብቱ ከወፍ አንሶ፤ ጎጆ የማይቀልስ፤
ደሞ መች ይጠፋል፤ ከኔም ካንተም ቀየ
መንገድ ላይ ምናልፈው፥ አይተን እንዳለየ
የቀድሞ አስተማሪ
ላብ እያጣቀሰ ፊደል አስቆጣሪ
ቀሪ ሀብት ባይኖረው፤
የቀረውን ዘመን፤ እያሰላ ኗሪ፤
ቪላችንን ሞልተን፥ በሱ ጎጆ ጉድለት
ማሰብ አስተምሮን ፥ የማናስበለት
ቀኖቹን በትኖ፤ ሌሊቶቹን ዘርቶ
ናላውን፥ ጉልበቱን ፥ ውበቱን ሰውቶ
የሚጎተት አገር፥ ከግቡ ለማድረስ
ሺህ መንገድ አቅንቶ፥ ሺህ ገደሎች መውረስ
ሰው ቢሉት ሰው ነው ወይ?
የተጣለ ፈረስ ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ዘመኑ ያለፈ
ጋማው የረገፈ ፤
የጎድን አጥንቱ ፤ ማበጠርያ መሳይ
ጠዋት ህያው ፍጡር፥ ሌሊት የጅብ ሲሳይ
ከተማው መግቢያ ላይ
አቧራ የሚቅም
የተጣለ ፈረስ አጋጥሞሽ ፤ አያውቅም?
“ካሁን አሁን መጥቶ፤
ይወስደኛል ነድቶ
ከጋጣው አግብቶ ፤ ያበላኛል እብቅ “
እያለ ጌታውን ፥ተግቶ የሚጠብቅ
የዛሬ ተጎታች ፤ የትናንቱ ሰጋር
ተባብሮ የከዳው፤ ጊዜ ከጌታው ጋር
የቸገረው አቅም፥
የተጣለ ፈረስ ፤ አጋጥሞህ አያውቅም?
ደሞስ መች ይጠፋል? ካንቺም ከኔም መንደር
የቀድሞ ወታደር፥
በጨነቀን ጊዜ ፥“በናት ሀገር ጥሪ “
የምናጣድፈው፥
በድል ቀን ከድግስ፥ የማናሳትፈው
ከነጣቂ መዳፍ ፥ አገር የሚያስመልስ
በገዛ አገሩ ላይ፥
መብቱ ከወፍ አንሶ፤ ጎጆ የማይቀልስ፤
ደሞ መች ይጠፋል፤ ከኔም ካንተም ቀየ
መንገድ ላይ ምናልፈው፥ አይተን እንዳለየ
የቀድሞ አስተማሪ
ላብ እያጣቀሰ ፊደል አስቆጣሪ
ቀሪ ሀብት ባይኖረው፤
የቀረውን ዘመን፤ እያሰላ ኗሪ፤
ቪላችንን ሞልተን፥ በሱ ጎጆ ጉድለት
ማሰብ አስተምሮን ፥ የማናስበለት
ቀኖቹን በትኖ፤ ሌሊቶቹን ዘርቶ
ናላውን፥ ጉልበቱን ፥ ውበቱን ሰውቶ
የሚጎተት አገር፥ ከግቡ ለማድረስ
ሺህ መንገድ አቅንቶ፥ ሺህ ገደሎች መውረስ
ሰው ቢሉት ሰው ነው ወይ?
የተጣለ ፈረስ ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤10👍4💋1
#ያኔ_ነው_ምሞተው
ውዴ !!!!!!
እንደ ሁሉም ፍጥረት ህመሜ በርትቶ ፤
ነፍሴን ቢወስድብኝ መልዓከ ሞት መጥቶ ፤
ሐውልት ውስጥ ሆኘ በአበባ ብሸለም ፤
ለኔ ቴአትር ነው እሱ ሞት አይደለም ፤
--- ወይ ደግሞ ---
አካሌ ጎስቁሎ እርጅና ተጭኖኝ ፤
ዳዴ እያልኩ ብሔድ መራመድ ተስኖኝ ፤
አለኝ ያልኩት ሁሉ ሂድልኝ እስኪለኝ ፤
ድህነት ቢወርሰኝ ማጣት ሲያቃጥለኝ፤
የሞትኩ ነኝ ብልም ድንገት ተናድጄ ፤
እሱም ሞት አይደለም እመኝኝ ወዳጄ ፤
--- ንገረኝ ካልሽማ !!!!! ---
የመንፈሴ ምግብ መልክሽ ተለዋውጦ ፤
ተስረቅራቂ ድምፅሽ በሳግ ተቆራርጦ ፤
አይንሽ ዕንባ ቋጥሮ ፈገግታሽ ተውጦ ፤
ከፍቶሽ ያዬሁሽ ለት ዓደይ ፊትሽ ከስሎ ፤
...ያኔ ነው ምሞተው ቅስሜ እንክት ብሎ ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ውዴ !!!!!!
እንደ ሁሉም ፍጥረት ህመሜ በርትቶ ፤
ነፍሴን ቢወስድብኝ መልዓከ ሞት መጥቶ ፤
ሐውልት ውስጥ ሆኘ በአበባ ብሸለም ፤
ለኔ ቴአትር ነው እሱ ሞት አይደለም ፤
--- ወይ ደግሞ ---
አካሌ ጎስቁሎ እርጅና ተጭኖኝ ፤
ዳዴ እያልኩ ብሔድ መራመድ ተስኖኝ ፤
አለኝ ያልኩት ሁሉ ሂድልኝ እስኪለኝ ፤
ድህነት ቢወርሰኝ ማጣት ሲያቃጥለኝ፤
የሞትኩ ነኝ ብልም ድንገት ተናድጄ ፤
እሱም ሞት አይደለም እመኝኝ ወዳጄ ፤
--- ንገረኝ ካልሽማ !!!!! ---
የመንፈሴ ምግብ መልክሽ ተለዋውጦ ፤
ተስረቅራቂ ድምፅሽ በሳግ ተቆራርጦ ፤
አይንሽ ዕንባ ቋጥሮ ፈገግታሽ ተውጦ ፤
ከፍቶሽ ያዬሁሽ ለት ዓደይ ፊትሽ ከስሎ ፤
...ያኔ ነው ምሞተው ቅስሜ እንክት ብሎ ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤16👍3🥰3
#ልክ_በዛሬው_ቀን
አበባ ባልሰጥሽ ለራት ባልቀጥርሽም
እኔ ወድሻለሁ…
ባለሽበት ሆነሽ ባለሁበት ሆኜ
አብረን እንደሆንን ራሴን አሳምኜ
እራት እበላለሁ እራትሽን ብይ
ስጦታሽን እንቺ አበባሽን እይ
እኔ ወድሻለሁ…
ያለንበት ቦታ ለስላሳ ሙዚቃ
ሰማሽው አይደለ ላንቺ ይሁን በቃ
እወቃለሁ የኔ ሴት አውቃለሁ የኔ ዓለም
ቀይ መጸሀፍ እንጂ ቀይ ልብስ አትወጂም
ለራት የለበስሽው…
ሰማያዊ ቀሚስ ነጭ እስካርፍ ያለበት
ይሁን ደስ ብሎኛል ደምቀሽ እመሪበት
እኔ ወድሻለሁ…
ዘና በይ ፈገግ በይ
ባለሁበት ሆኜ ባለሽበት ሆነሽ
ብቸኝነት የለም የኔ ሆይ ልንገርሽ
ያሳቤን ስጦታ በይ አሁን ክፈቺው
አየሽው…?
ወደድሽው…?
የልቤ ትንፋሽ ነው በልብሽ ተንፍሺው
እኔ ወድሻለሁ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሰለሞን ሳህሌ
አበባ ባልሰጥሽ ለራት ባልቀጥርሽም
እኔ ወድሻለሁ…
ባለሽበት ሆነሽ ባለሁበት ሆኜ
አብረን እንደሆንን ራሴን አሳምኜ
እራት እበላለሁ እራትሽን ብይ
ስጦታሽን እንቺ አበባሽን እይ
እኔ ወድሻለሁ…
ያለንበት ቦታ ለስላሳ ሙዚቃ
ሰማሽው አይደለ ላንቺ ይሁን በቃ
እወቃለሁ የኔ ሴት አውቃለሁ የኔ ዓለም
ቀይ መጸሀፍ እንጂ ቀይ ልብስ አትወጂም
ለራት የለበስሽው…
ሰማያዊ ቀሚስ ነጭ እስካርፍ ያለበት
ይሁን ደስ ብሎኛል ደምቀሽ እመሪበት
እኔ ወድሻለሁ…
ዘና በይ ፈገግ በይ
ባለሁበት ሆኜ ባለሽበት ሆነሽ
ብቸኝነት የለም የኔ ሆይ ልንገርሽ
ያሳቤን ስጦታ በይ አሁን ክፈቺው
አየሽው…?
ወደድሽው…?
የልቤ ትንፋሽ ነው በልብሽ ተንፍሺው
እኔ ወድሻለሁ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሰለሞን ሳህሌ
❤21👍7🥰4
#ሳሚኝ_እና_ልንቃ
ነግረውሽ እንደሆን…
መጎዳቴን አይተው ህመሜን በዝርዝር
ጤናዬን እንዳጣው ለክፎኝ ያንቺ ፍቅር
የመኖር አኳኋን ውሉ ተዛብቶብኝ
ቀንና ለሊቱ እንደተምታታብኝ
ሰምተሽ እንደሆነ…
አንቺን ካየሁ ወዲህ ሰላም እንደራቀኝ
ፍቅርሽ ውስጤ ገብቶ እንደሚያስጨንቀኝ
ውበትሽ በልቤ ደምቆ እንደተሳለ
የኔ አካል በሀሳብ ካንቺጋ እንደዋለ
ሰምተሽ እንደሆነ…
ብቻ መዋተቴን
እራሴን ማጣቴን
ውሎ አዳር መተከዝ
አለፍ ሲል መፍዘዝ
ለብቻ መፈገግ
ዝም ብሎ መበርገግ
ሆኗልና ግብሬ ሰርክ የማይቀየር
መጥተሽ አንድ በዪኝ ተይ ነገሩ ሳይከር
ባንቺ እንደታመምኩኝ ባንቺው ልዳን በቃ
በውብ ከንፈሮችሽ ሳሚኝና ልንቃ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ነግረውሽ እንደሆን…
መጎዳቴን አይተው ህመሜን በዝርዝር
ጤናዬን እንዳጣው ለክፎኝ ያንቺ ፍቅር
የመኖር አኳኋን ውሉ ተዛብቶብኝ
ቀንና ለሊቱ እንደተምታታብኝ
ሰምተሽ እንደሆነ…
አንቺን ካየሁ ወዲህ ሰላም እንደራቀኝ
ፍቅርሽ ውስጤ ገብቶ እንደሚያስጨንቀኝ
ውበትሽ በልቤ ደምቆ እንደተሳለ
የኔ አካል በሀሳብ ካንቺጋ እንደዋለ
ሰምተሽ እንደሆነ…
ብቻ መዋተቴን
እራሴን ማጣቴን
ውሎ አዳር መተከዝ
አለፍ ሲል መፍዘዝ
ለብቻ መፈገግ
ዝም ብሎ መበርገግ
ሆኗልና ግብሬ ሰርክ የማይቀየር
መጥተሽ አንድ በዪኝ ተይ ነገሩ ሳይከር
ባንቺ እንደታመምኩኝ ባንቺው ልዳን በቃ
በውብ ከንፈሮችሽ ሳሚኝና ልንቃ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤28👏4💯2👍1
#ዋጋዬ_ውድ_ነው!
ክብርህን ለመግዛት ዋጋ የሚያወጡ!
የአንተን ማጣት አይተው በፍጥነት ከመጡ!
እንዲህ ጠይቃቸው?
ምንም ሳትፈራቸው!
ያኔ!! ሳይኖራቸው!ሌሎች ሲገዟቸው!
በሆድ ሲገመቱ ስንት ነው? ዋጋቸው?!
የእኔ ግን ውድ ነው! ዋጋዬ! ተመኑ!
ከሆድ ባሻገር ነው! ጥያቄዬ እመኑ!
ለመኖር ብበላም! ለመብላት አልኖርም!
ሆድ ጎደለ! ብዬ! ክብሬን ግን አልሸጥም!!!
እናም በቃ! ሂዱ! ዋጋዬ ውድ ነው!
የምደራደረው በሰው ልክ ሚዛን ነው!!!
ብለህ ንገራቸው!!!
ድንገት ከገባቸው!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ክብርህን ለመግዛት ዋጋ የሚያወጡ!
የአንተን ማጣት አይተው በፍጥነት ከመጡ!
እንዲህ ጠይቃቸው?
ምንም ሳትፈራቸው!
ያኔ!! ሳይኖራቸው!ሌሎች ሲገዟቸው!
በሆድ ሲገመቱ ስንት ነው? ዋጋቸው?!
የእኔ ግን ውድ ነው! ዋጋዬ! ተመኑ!
ከሆድ ባሻገር ነው! ጥያቄዬ እመኑ!
ለመኖር ብበላም! ለመብላት አልኖርም!
ሆድ ጎደለ! ብዬ! ክብሬን ግን አልሸጥም!!!
እናም በቃ! ሂዱ! ዋጋዬ ውድ ነው!
የምደራደረው በሰው ልክ ሚዛን ነው!!!
ብለህ ንገራቸው!!!
ድንገት ከገባቸው!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
❤26👍8
#አውቆ_እንዳላወቀ
አንተው እያጠፋህ አንተው ስትወቅሰኝ
ይቅርታ ልሀለሁ እውነቱ እየገባኝ
ሲሻህ ስትቆጣ ሲሻህ ስታኮርፈኝ
ለምኛህም ቢሆን እኔ አወራለሁኝ
ነጩንም ጥቁር ነው እያልክ ስትዋሸኝ
ያንንም አልፋለሁ አይቶ እንዳላየሁኝ
ነገን ተስፋ አድርጌ ዛሬን እያጣሁኝ
አንተ ስቀህ ስቱል እኔ እያለቀስኩኝ
መውደዴ እስኪገባህ እንዳልክ እየሆንኩኝ
ዛሬም ያው አለሁኝ ,,,,,,,
ግን እርፍደህ ነቅተህ ትግስቴ ካለቀ
ሌላ ጋር ብታየው ያ ጥርሴ እየሳቀ
አንተም እንድታልፈኝ አውቆ እንዳለወቀ
አንተው እያጠፋህ አንተው ስትወቅሰኝ
ይቅርታ ልሀለሁ እውነቱ እየገባኝ
ሲሻህ ስትቆጣ ሲሻህ ስታኮርፈኝ
ለምኛህም ቢሆን እኔ አወራለሁኝ
ነጩንም ጥቁር ነው እያልክ ስትዋሸኝ
ያንንም አልፋለሁ አይቶ እንዳላየሁኝ
ነገን ተስፋ አድርጌ ዛሬን እያጣሁኝ
አንተ ስቀህ ስቱል እኔ እያለቀስኩኝ
መውደዴ እስኪገባህ እንዳልክ እየሆንኩኝ
ዛሬም ያው አለሁኝ ,,,,,,,
ግን እርፍደህ ነቅተህ ትግስቴ ካለቀ
ሌላ ጋር ብታየው ያ ጥርሴ እየሳቀ
አንተም እንድታልፈኝ አውቆ እንዳለወቀ
❤32👏4
"እመጣለሁ " ብለሽ ፣ ከቀጠርሽኝ ቦታ
እድሜ እንደ "ቅፅበት" ፣ ዘመን እንደ "አፍታ"
ቆሜ ስጠብቅሽ ፣ ሳላገኝሽ ያልፋል
ስትቀሪ ጊዜ...
ዘላለሜ ባክኖ ፣ ናፍቆትሽ ይገዝፋል፡፡"
ምናምን እያለ...
በቃል አሳምሮ ፣ የሚፅፍ ብሶቱን
የደሀ ግጥም ነው ፣ ልንገርሽ እውነቱን ።
.............................................
አናልሽ የኔ ውብ...
ደሀ "ውድ" ያለውን ፣
"ርካሽ ነው" ብሎ ፣ ሀብታም እየገዛው
ለምን ይመስልሻል...
"ውዴ" የሚለው ቃል ፣ ግጥም ላይ የበዛው?
እውነቱን ልንገርሽ...
ደሀ አፍቃሪ ነው ፣
ግጥምን እየፃፈ ፣ "ውዴ"ን ያጠነዛው ።
............................... ..... .......
እናልሽ የኔ ውብ ...
በፍቅርሽ ተቃጥላ ፣ ነፍሴ ብትቀልጥም
ቆሜ ስጠብቅሽ....
እድሜዬ አያልፍም ፣ ዘመኔ አያመልጥም
ባለሽበት ቦታ ...
"ሳልቀጥርሽ ላግኝሽ" ፣ ሚል ነው የኔ ግጥም።
..........................................
ሳልቀጥርሽ ላግኝሽ (ርዕስ)
ደሀ አፍቃሪ ሁሉ...
"በዱር በገደሉ
በፀሃይ በጠሉ
አንቺን በመጠበቅ ፣ተቃጠልን" ሲሉ
"ስፈልግሽ ሳድር ፣ ስፈልግሽ ውዬ
ጎንደር ላይ ሳስፈልግ፣ "ጎጃም" ናት ተብዬ
ጎጃም ላይ ሳስጠይቅ ፣ "ትግራይ" ናት ተብዬ
ትግራይ ላይ ሳስፈልግ ፣ "ወለጋ" ነች ሲሉኝ
ወለጋ ሳስፈልግ ፣ "ሸገር ገባች"ሲሉኝ"
ምናምን እያሉኝ....
ልቤን ከሚያደክመው ፣ በዙረታም ግጥም
"አለች" ባሉት ቦታ....
ሲደርስ ከሄደች፣
"ጠልታኛለች" ብሎ ፣ ለምን ልቡ አይቆርጥም ?!
እናልሽየኔ ውብ ....
ደሀ ነው 'ሚፅፈው ፣እንዲህ አይነት ግጥም ።
............................................
እናልሽ የኔ ውብ....
አንድ የቤት መኪና ፣
ካንድ ቪላ ቤት ጋር ፣ ብሰጥሽ ገዝቼ
ደሀ ቀጥሮ ሲያጣሽ....
እኔ አገኝሻለሁ ፣ሳልቀጥርሽ መጥቼ።
እንጂ አልጠብቅሽም!
"ትመጣለች" እያልኩ እድሜዬን ሸኝቼ፡፡
............................................
እናልሽ የኔ ውብ ....
በፍቅርሽ የምትነድ ፣ ነብሴ ብትቀልጥም
ቆሜ እየጠበኩሽ...
ዘመኔ አያልፍም ፣ እድሜዬ አያመልጥም
መምጣት የማይችል ነው!
"ትመጫለሽ "ብሎ የሚፅፈው ግጥም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በላይ በቀለ ወያ
እድሜ እንደ "ቅፅበት" ፣ ዘመን እንደ "አፍታ"
ቆሜ ስጠብቅሽ ፣ ሳላገኝሽ ያልፋል
ስትቀሪ ጊዜ...
ዘላለሜ ባክኖ ፣ ናፍቆትሽ ይገዝፋል፡፡"
ምናምን እያለ...
በቃል አሳምሮ ፣ የሚፅፍ ብሶቱን
የደሀ ግጥም ነው ፣ ልንገርሽ እውነቱን ።
.............................................
አናልሽ የኔ ውብ...
ደሀ "ውድ" ያለውን ፣
"ርካሽ ነው" ብሎ ፣ ሀብታም እየገዛው
ለምን ይመስልሻል...
"ውዴ" የሚለው ቃል ፣ ግጥም ላይ የበዛው?
እውነቱን ልንገርሽ...
ደሀ አፍቃሪ ነው ፣
ግጥምን እየፃፈ ፣ "ውዴ"ን ያጠነዛው ።
............................... ..... .......
እናልሽ የኔ ውብ ...
በፍቅርሽ ተቃጥላ ፣ ነፍሴ ብትቀልጥም
ቆሜ ስጠብቅሽ....
እድሜዬ አያልፍም ፣ ዘመኔ አያመልጥም
ባለሽበት ቦታ ...
"ሳልቀጥርሽ ላግኝሽ" ፣ ሚል ነው የኔ ግጥም።
..........................................
ሳልቀጥርሽ ላግኝሽ (ርዕስ)
ደሀ አፍቃሪ ሁሉ...
"በዱር በገደሉ
በፀሃይ በጠሉ
አንቺን በመጠበቅ ፣ተቃጠልን" ሲሉ
"ስፈልግሽ ሳድር ፣ ስፈልግሽ ውዬ
ጎንደር ላይ ሳስፈልግ፣ "ጎጃም" ናት ተብዬ
ጎጃም ላይ ሳስጠይቅ ፣ "ትግራይ" ናት ተብዬ
ትግራይ ላይ ሳስፈልግ ፣ "ወለጋ" ነች ሲሉኝ
ወለጋ ሳስፈልግ ፣ "ሸገር ገባች"ሲሉኝ"
ምናምን እያሉኝ....
ልቤን ከሚያደክመው ፣ በዙረታም ግጥም
"አለች" ባሉት ቦታ....
ሲደርስ ከሄደች፣
"ጠልታኛለች" ብሎ ፣ ለምን ልቡ አይቆርጥም ?!
እናልሽየኔ ውብ ....
ደሀ ነው 'ሚፅፈው ፣እንዲህ አይነት ግጥም ።
............................................
እናልሽ የኔ ውብ....
አንድ የቤት መኪና ፣
ካንድ ቪላ ቤት ጋር ፣ ብሰጥሽ ገዝቼ
ደሀ ቀጥሮ ሲያጣሽ....
እኔ አገኝሻለሁ ፣ሳልቀጥርሽ መጥቼ።
እንጂ አልጠብቅሽም!
"ትመጣለች" እያልኩ እድሜዬን ሸኝቼ፡፡
............................................
እናልሽ የኔ ውብ ....
በፍቅርሽ የምትነድ ፣ ነብሴ ብትቀልጥም
ቆሜ እየጠበኩሽ...
ዘመኔ አያልፍም ፣ እድሜዬ አያመልጥም
መምጣት የማይችል ነው!
"ትመጫለሽ "ብሎ የሚፅፈው ግጥም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በላይ በቀለ ወያ
❤23👍4