#እስከዚህም_ፍቅርሽ
እስከዚህም ፍቅርሽ:
ከሰንደል ጭስ በላይ:
ደምቆ የማይገዝፈው:
ምንሽን ልፃፈው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ
በጧት የረገፈው:
ከዕድሜ እሬሳ ውጭ
ዋኝታ ምኑን ታውጣው
ነብሴ ከባለፈው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ:
ዘመን ያሳረጠው:
ምኑን አስታውሼ
ሣጌን እየማኩኝ :
እንባዬን ልዋጠው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ
ሲነድፍ ያለሰንኮፍ:
መታሁ ቢልም ለኮፍ:
እንኳንና ሰምበር
ስምሽስ ማን ነበር ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ኑረዲን ኢሳ
እስከዚህም ፍቅርሽ:
ከሰንደል ጭስ በላይ:
ደምቆ የማይገዝፈው:
ምንሽን ልፃፈው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ
በጧት የረገፈው:
ከዕድሜ እሬሳ ውጭ
ዋኝታ ምኑን ታውጣው
ነብሴ ከባለፈው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ:
ዘመን ያሳረጠው:
ምኑን አስታውሼ
ሣጌን እየማኩኝ :
እንባዬን ልዋጠው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ
ሲነድፍ ያለሰንኮፍ:
መታሁ ቢልም ለኮፍ:
እንኳንና ሰምበር
ስምሽስ ማን ነበር ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ኑረዲን ኢሳ
👍10❤2
#የፍቅር_ቃጠሎ
ጉንጭሽ ፅጌረዳ ሞቆት የፈነዳ፤
አይንሽ የጠዋት ጨረር
የበራ ማለዳ፡፡
የማትጠገቢ የሥንዴ ራስ ዛላ አገዳ ጥንቅሽ፤
ጠብ አትይ አንጀቴ ባኝክ ብመጥሽ፡፡
ቆንጀ ነሽ አንቺዬ
እሳት ነበልባል ነሽ ንዳድ ባከላቴ፤
ሆነሻል ሙቀቴ፤
ሆነሻል ህይወቴ፡፡
የጋለው ትንፋሽሽ፤
የሞቀው ምላስሽ፤
ማርኮኝ በከንፈርሽ፤
እጄን ሰጥቻለው፤
እስረኛ ሆኛለው፡፡
ያንቀጠቅጠኛል ወባ ቅናት ገብቶ፤
ልቤን አስፈራርቶ፤
ትኩሳት አምጥቶ፡፡
ፍቅርሽ አቃጠለኝ በመልክሽ ልተክዝ፤
እቀፊኝ ልቀዝቅዝ፤
ንከሺኝ ልደንዝዝ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገብረ ክርስቶስ ደስታ
ጉንጭሽ ፅጌረዳ ሞቆት የፈነዳ፤
አይንሽ የጠዋት ጨረር
የበራ ማለዳ፡፡
የማትጠገቢ የሥንዴ ራስ ዛላ አገዳ ጥንቅሽ፤
ጠብ አትይ አንጀቴ ባኝክ ብመጥሽ፡፡
ቆንጀ ነሽ አንቺዬ
እሳት ነበልባል ነሽ ንዳድ ባከላቴ፤
ሆነሻል ሙቀቴ፤
ሆነሻል ህይወቴ፡፡
የጋለው ትንፋሽሽ፤
የሞቀው ምላስሽ፤
ማርኮኝ በከንፈርሽ፤
እጄን ሰጥቻለው፤
እስረኛ ሆኛለው፡፡
ያንቀጠቅጠኛል ወባ ቅናት ገብቶ፤
ልቤን አስፈራርቶ፤
ትኩሳት አምጥቶ፡፡
ፍቅርሽ አቃጠለኝ በመልክሽ ልተክዝ፤
እቀፊኝ ልቀዝቅዝ፤
ንከሺኝ ልደንዝዝ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ገብረ ክርስቶስ ደስታ
👍12🔥2❤1
#ግን_አንድ_ሰው_አለ
እርጅና ሲጫንሽ
እድሜ ተጠራቅሞ ፥እንዳስም ሲያፍንሽ
ሽበት እንዳመዳይ
በጭንቅላትሽ ላይ
በድንገት ሲፈላ
ያይንሽ ከረጢቱ ፥ በንቅልፍሽ ሲሞላ
ምድጃ ዳር ሆነሽ
መጣፍሽን ከፍተሽ
ያለፈውን ዘመን ፥ ከፍተሽ ስታነቢ
የኔን ቃል አስቢ፦
ስንቶች አፈቀሩት ፥ በሐቅ በይስሙላ
የገፅሽን አቦል፥ የውበትሽን አፍላ
ግን አንድ ሰው አለ
ከሌሎች ወንዶች ጋር ፥ ያልተመሳሰለ
በእፁብ ድንቋ ነፍስሽ ፥ ፍቅር የነደደ
የመልክሽ ፀደይ ሲያልፍ
ልክ እንደ መስቀል ወፍ ፤ጥሎሽ ያልነጎደ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በዕውቀቱ ስዩም
እርጅና ሲጫንሽ
እድሜ ተጠራቅሞ ፥እንዳስም ሲያፍንሽ
ሽበት እንዳመዳይ
በጭንቅላትሽ ላይ
በድንገት ሲፈላ
ያይንሽ ከረጢቱ ፥ በንቅልፍሽ ሲሞላ
ምድጃ ዳር ሆነሽ
መጣፍሽን ከፍተሽ
ያለፈውን ዘመን ፥ ከፍተሽ ስታነቢ
የኔን ቃል አስቢ፦
ስንቶች አፈቀሩት ፥ በሐቅ በይስሙላ
የገፅሽን አቦል፥ የውበትሽን አፍላ
ግን አንድ ሰው አለ
ከሌሎች ወንዶች ጋር ፥ ያልተመሳሰለ
በእፁብ ድንቋ ነፍስሽ ፥ ፍቅር የነደደ
የመልክሽ ፀደይ ሲያልፍ
ልክ እንደ መስቀል ወፍ ፤ጥሎሽ ያልነጎደ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በዕውቀቱ ስዩም
👍12👏5❤1
#የዘመን_ፈተና
ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤
የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤
የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡
የሰው ሃሳብ መብላት፤
የሰው ቃል መጠጣት ፤
የሰው ህልም ማየት፤
መቆም የሰው ቁመት፡፡
ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤
የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤
የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡
በሰው አድማስ ማሰስ፤
በሰው ድምፅ መቀደስ፤
በሰው ሽንፈት መፍረስ፤
መሾም በሰው መንገስ፡፡
ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤
የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤
የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡
የሰው ፍርሃት መራድ፤
የሰው ንዴት ማበድ፤
የሰው እዳ መክሰር፤
የሰው ሞት መቀበር፡፡
ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤
የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤
የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡
ታመሃል ሲሉ እህ ዳንክ ሲሉ አሃ፤
ገነት ሲስሉልህ በጠፉ በረሃ፤
አጣህ ሲሉህ እህ አለህ ሲሉ አሃ፤
ሆድክን ሲሞሉልህ በቀቢጸ አመሃ፤
ሄድነ ሲሉህ እህ ቀረን ሲሉ አሃ፤
አለን ሲሉ እህ ሄድነ ሲሉ አሃ፤
ቆምነ ሲሉ እህ ሮጥን ሲሉ አሃ፤
እህ አሃ እህ አሃ እህ እህ አሃ አሃ፤
በመንገድ በርግገህ በመንገድ ቀረሃ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ነብዩ ባዬ
ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤
የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤
የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡
የሰው ሃሳብ መብላት፤
የሰው ቃል መጠጣት ፤
የሰው ህልም ማየት፤
መቆም የሰው ቁመት፡፡
ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤
የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤
የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡
በሰው አድማስ ማሰስ፤
በሰው ድምፅ መቀደስ፤
በሰው ሽንፈት መፍረስ፤
መሾም በሰው መንገስ፡፡
ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤
የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤
የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡
የሰው ፍርሃት መራድ፤
የሰው ንዴት ማበድ፤
የሰው እዳ መክሰር፤
የሰው ሞት መቀበር፡፡
ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤
የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤
የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡
ታመሃል ሲሉ እህ ዳንክ ሲሉ አሃ፤
ገነት ሲስሉልህ በጠፉ በረሃ፤
አጣህ ሲሉህ እህ አለህ ሲሉ አሃ፤
ሆድክን ሲሞሉልህ በቀቢጸ አመሃ፤
ሄድነ ሲሉህ እህ ቀረን ሲሉ አሃ፤
አለን ሲሉ እህ ሄድነ ሲሉ አሃ፤
ቆምነ ሲሉ እህ ሮጥን ሲሉ አሃ፤
እህ አሃ እህ አሃ እህ እህ አሃ አሃ፤
በመንገድ በርግገህ በመንገድ ቀረሃ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ነብዩ ባዬ
👍12❤1👏1
#ትወጂኛለሽ
እኔ እየፈራሁሽ፣ ልቤ እየደፈረሽ
እኔ እየናቅኩሽ ፣ ልቤ እያከበረሽ
እኔ እየጠላሁሽ ፣ ልቤ እያፈቀረሽ
ከራሴ ስጣላ...
እኖራለሁ እንጂ ፣ የልቤን ሀቅ ይዤ
አንድም ቀን አልፎልኝ....
ልቤን እንደልቤ ፣ አላውቅም አዝዤ፡፡
አንቺም ልክ እንደኔ...
ልብሽን እንደልብ ፣ ማዘዝ አትችይም
ልብሽ ይወደኛል ፣ ጠላሁህ ብትይም፡፡
ባትወጂኝም እንኳን...
የመጥላትሽ መጠን ፣ የቱን ያህል ቢያክል
አንቺን አላምንሽም ፣ ልብሽ ነው ትክክል፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
እኔ እየፈራሁሽ፣ ልቤ እየደፈረሽ
እኔ እየናቅኩሽ ፣ ልቤ እያከበረሽ
እኔ እየጠላሁሽ ፣ ልቤ እያፈቀረሽ
ከራሴ ስጣላ...
እኖራለሁ እንጂ ፣ የልቤን ሀቅ ይዤ
አንድም ቀን አልፎልኝ....
ልቤን እንደልቤ ፣ አላውቅም አዝዤ፡፡
አንቺም ልክ እንደኔ...
ልብሽን እንደልብ ፣ ማዘዝ አትችይም
ልብሽ ይወደኛል ፣ ጠላሁህ ብትይም፡፡
ባትወጂኝም እንኳን...
የመጥላትሽ መጠን ፣ የቱን ያህል ቢያክል
አንቺን አላምንሽም ፣ ልብሽ ነው ትክክል፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍25❤4🔥4👏1😍1
#ጨረቃ_ናት_ፍቅሬ
ባልዳብስሽ እንኳ:
ሳላይሽ ከከረምኩ ይለኛል ቅር ቅር
ህይወቴ ይዛባል ይላል ምንቅርቅር
ሰላም ነስተሽኛል:
ልክ እንደ ምትሀት እንደ መስተፋቅር፣
የኔ እንደማትሆኚ እያወኩኝም እንኳን
ስንት ዘመን ሆነኝ:
ልቤ ላይ ከጣልኩኝ የምኞቴን ድንኳን፣
ደግሞ አንዳንድ ግዜ:
ብሶት ይወረኛል ለራሴ አዝናለሁ
መዝጊያዬን ቆልፌ እንሰቀሰቃለሁ፣
ይኸው ዛሬ ከፍቶኝ...
ወደ ውጭ ወጥቼ ከፍቼ የቤቴን በር
ጨረቃን እያየሁ ግጥም ልፅፍ ነበር፣
ግና የሀሳቤን መቼ ከወንኩና
ፈዝዤባት ቀረሁ መፃፌን ተውኩና፣
ይገርማል አንዳንዴ...
ስንት ዘመን ሙሉ:
በፍቅርሽ ሰቀቀን ስንገላታ ኖሬ
በ2 ደቂቃ ተፋሁሽ አንቅሬ
በይ ደህና ሰንብቺ:
ከእንግዲህ በኋላ ጨረቃ ናት ፍቅሬ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ ዘ-ማርያም
ባልዳብስሽ እንኳ:
ሳላይሽ ከከረምኩ ይለኛል ቅር ቅር
ህይወቴ ይዛባል ይላል ምንቅርቅር
ሰላም ነስተሽኛል:
ልክ እንደ ምትሀት እንደ መስተፋቅር፣
የኔ እንደማትሆኚ እያወኩኝም እንኳን
ስንት ዘመን ሆነኝ:
ልቤ ላይ ከጣልኩኝ የምኞቴን ድንኳን፣
ደግሞ አንዳንድ ግዜ:
ብሶት ይወረኛል ለራሴ አዝናለሁ
መዝጊያዬን ቆልፌ እንሰቀሰቃለሁ፣
ይኸው ዛሬ ከፍቶኝ...
ወደ ውጭ ወጥቼ ከፍቼ የቤቴን በር
ጨረቃን እያየሁ ግጥም ልፅፍ ነበር፣
ግና የሀሳቤን መቼ ከወንኩና
ፈዝዤባት ቀረሁ መፃፌን ተውኩና፣
ይገርማል አንዳንዴ...
ስንት ዘመን ሙሉ:
በፍቅርሽ ሰቀቀን ስንገላታ ኖሬ
በ2 ደቂቃ ተፋሁሽ አንቅሬ
በይ ደህና ሰንብቺ:
ከእንግዲህ በኋላ ጨረቃ ናት ፍቅሬ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ ዘ-ማርያም
👍14❤6👏2
#ቢታነፅ_ቢወቀር
እኔም አንድሰሞን
ልክ እንደሶሎሞን
"ሁሉም ከንቱ ከንቱ ነፋስን መከተል"
ላይጥሉ መታገል: ላይከብሩ መባተል
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ
እፈላሰፍ ነበር::
ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጉዋሮ በር በኩል: ሰሎሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ነፋስ አሳድጄ እንደቆቅ አጠመድሁ::
ከፀሓይዋ በታች :ግልገል ፀሃይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ: ብርሃን አበደርሁ
ማቅ የነበረው ጨርቅ: ሸማ ሆኖ ቆየኝ
"ከንቱ "የነበረው "አንቱ "ሆኖ ታየኝ::
ለካስ
ጠቢብ ቢያስተምረው
መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ : ቢታነፅ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም : ካልወደደ በቀር::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በዕውቀቱ ስዩም
እኔም አንድሰሞን
ልክ እንደሶሎሞን
"ሁሉም ከንቱ ከንቱ ነፋስን መከተል"
ላይጥሉ መታገል: ላይከብሩ መባተል
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ
እፈላሰፍ ነበር::
ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጉዋሮ በር በኩል: ሰሎሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ነፋስ አሳድጄ እንደቆቅ አጠመድሁ::
ከፀሓይዋ በታች :ግልገል ፀሃይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ: ብርሃን አበደርሁ
ማቅ የነበረው ጨርቅ: ሸማ ሆኖ ቆየኝ
"ከንቱ "የነበረው "አንቱ "ሆኖ ታየኝ::
ለካስ
ጠቢብ ቢያስተምረው
መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ : ቢታነፅ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም : ካልወደደ በቀር::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በዕውቀቱ ስዩም
👍11❤5👏1
#የፍቅር_ዘመኑ
ወጣቱ .........
አስር – ከሰባቱ
ፀሐይን በጉያህ
ጨረቃን በኪስህ
ዩኒቨርስን ጠቅላዩን
በመዳፍህ ይዘህ
ፍቅርን በቃጠሎ
በትንታግ ታውቃለህ።
ወሬዛው........
ሰላሳ – ካምስቱ
ፀሐይ በቦታዋ
ጠዋት ትወጣና ማታ ትጠልቃለች
ጨረቃም በምሽት
በፀሐይ ዳረጎት በልመና ጨረር
አንሳ ታበራለች።
ፍቅርም እንደልምዱ
ከልቦናህ ያድራል ከተፈጥሮ ግንዱ።
አዛውንቱ .......
ሰባ – ከስምንቱ
ፀሐይ ከቦታዋ
ጥልቁን ትርቃለች
ጨረቃም ተማፅና ጨለማ መግፈፊያ
ብርታቷን ታጣለች።
– በፈንታው –
ትዝታ ክራሩን
ያለፈ ቅኝቱን
ፊትህ ላይ ያከርራል
ዘላለሙን ላይለቅ ፍቅርን ያላዝናል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዮሐንስ ሀብተማሪያም
ወጣቱ .........
አስር – ከሰባቱ
ፀሐይን በጉያህ
ጨረቃን በኪስህ
ዩኒቨርስን ጠቅላዩን
በመዳፍህ ይዘህ
ፍቅርን በቃጠሎ
በትንታግ ታውቃለህ።
ወሬዛው........
ሰላሳ – ካምስቱ
ፀሐይ በቦታዋ
ጠዋት ትወጣና ማታ ትጠልቃለች
ጨረቃም በምሽት
በፀሐይ ዳረጎት በልመና ጨረር
አንሳ ታበራለች።
ፍቅርም እንደልምዱ
ከልቦናህ ያድራል ከተፈጥሮ ግንዱ።
አዛውንቱ .......
ሰባ – ከስምንቱ
ፀሐይ ከቦታዋ
ጥልቁን ትርቃለች
ጨረቃም ተማፅና ጨለማ መግፈፊያ
ብርታቷን ታጣለች።
– በፈንታው –
ትዝታ ክራሩን
ያለፈ ቅኝቱን
ፊትህ ላይ ያከርራል
ዘላለሙን ላይለቅ ፍቅርን ያላዝናል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዮሐንስ ሀብተማሪያም
❤5👍3😁2
#የወንድ_ስንብት
ሊሄድ ያሰበ ሰው — ልቡ የሸፈተ
በ
"ደህና ሁኚ" ብሎ — ዕንባውን ያዘራል
የኀዘኑን ጨሌ — ሙዳይሽ ይሰፍራል
“ቻው” ይላል ዐሥሬ
ያለ ምንም ፍሬ...
ጓዙን ይሸክፋል
ወዲያ ወዲህ ያልፋል...
ይስማል ፍዝ ጉንጭ
ያቅፋል ልዝብ አንገት — እግሩም አይወጣለት
የወንድ ስንብት
“መልሺኝ” መሆኑን — ምነው ብታውቂለት?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሄኖክ በቀለ
ሊሄድ ያሰበ ሰው — ልቡ የሸፈተ
በ
ሌት በጽልመቱ
ምንም ሳይናገር — በር እየከፈተ
እንዳለፈ ክረምት
...እንደ ጠዋት ጤዛ
እንደ ቡና ሐሜት
...እንዲሁ እንደዋዛ
ሄደ ...ሄደ ....ሄደ ...ሄደ ኮበለለ
ይሰጠው ይሆናል — ዕጣው የተሻለ።
እንደኔ ያለው ግን"ደህና ሁኚ" ብሎ — ዕንባውን ያዘራል
የኀዘኑን ጨሌ — ሙዳይሽ ይሰፍራል
“ቻው” ይላል ዐሥሬ
ያለ ምንም ፍሬ...
ጓዙን ይሸክፋል
ወዲያ ወዲህ ያልፋል...
ይስማል ፍዝ ጉንጭ
ያቅፋል ልዝብ አንገት — እግሩም አይወጣለት
የወንድ ስንብት
“መልሺኝ” መሆኑን — ምነው ብታውቂለት?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሄኖክ በቀለ
👍20❤2
"To all my Muslim subscribers, I wish you a very Happy Eid! May this special day be filled with joy, peace, and beautiful moments with your loved ones.”
✨Eid Mubarak!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✨Eid Mubarak!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤6👍4
#ታስፈልጊኛለሽ!
በተለይ በክረምት ፡ ሙቀት ሲያስፈልገኝ
በተለይ በምሽት ፡ የብቻየን ስገኝ !
ብርድና ባዶነት ፡ ተባብረው ሲመጡ
ባንች ተገፍትረው ፡ ፈጥነው እንዲወጡ
ከላየ ቁጭ በይ ፡ ግርማየ ሞገሴ
እቅፍፍፍ ስታደርጊኝ ፡ ትሞቃለች ነፍሴ
ጌጤ ነሽ ለአካሌ ፡ ክብርና ውበቴ
በይ ነይ ልደርብሽ ፡ ከታናሿ ቤቴ
ታ
...ስ
......ፈ
..........ል
..............ጊ
.................ኛ
.....................ለ
.........................ሽ !
ወፍራሟ ጃኬቴ¡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ መላኩ አላምረው
በተለይ በክረምት ፡ ሙቀት ሲያስፈልገኝ
በተለይ በምሽት ፡ የብቻየን ስገኝ !
ብርድና ባዶነት ፡ ተባብረው ሲመጡ
ባንች ተገፍትረው ፡ ፈጥነው እንዲወጡ
ከላየ ቁጭ በይ ፡ ግርማየ ሞገሴ
እቅፍፍፍ ስታደርጊኝ ፡ ትሞቃለች ነፍሴ
ጌጤ ነሽ ለአካሌ ፡ ክብርና ውበቴ
በይ ነይ ልደርብሽ ፡ ከታናሿ ቤቴ
ታ
...ስ
......ፈ
..........ል
..............ጊ
.................ኛ
.....................ለ
.........................ሽ !
ወፍራሟ ጃኬቴ¡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ መላኩ አላምረው
😁24❤10👍6🔥2
#ረስተሽ_ካልሆነ
ነግሬሽ ነበረ ነገሬ በዝቶብሽ ረሳሽው እንጂ
አንቺም ነግረሽኛል ዛሬ ብረሳውም ረስተሽኝ ስትሄጂ
ስላንቺ የፃፍኩት ያሰብኩት በሞላ
የተኮረጀ ነው ካለም የተቀዳ ገና ያልተብላላ
ረስተሸ ካልሆነ አዝማሪ ወዳለሁ
በማሲንቆ ቅኝት ነፍሴን አደምጣለሁ
አናልሽ በቀደም አዝማሪ ቤት ሆኜ
የጠጁን ብርሌ አፌ ላይ ደቅኜ
ከኔ ባርጩማ ጎን አንድ ድንክ ቁጭ ብሏል
መላጣውን ሲያዩት ዲያስፖራ ይመስላል
አዝማሪው ይዘፍናል ለድንኩ ሰውየ
አዲስ ዜማ ፈጥሮ ከባቲ ዋሆየ
‹‹የጎፈሬህ ጫካ መሸፈት ያሰኛል››
‹‹መለሎው ቁመትህ አክሱምን ያስንቃል››
ድንኩ ወዳጃችን በጎፈሬው ፋንታ መላጣው ያበራል
በርጩማ ላይ ቆሞ አዝማሪው ግምባር ላይ መቶ ብር ይመርጋል
ከኔ አለፍ ብለው ኣናረጅም ያሉ ሁለት አሮጊቶች
ይፍለቀለቃሉ ባዝማሪው ቃላቶች
‹‹ጡትሽ ማለት ሎሚ አንገትሽ ብርሌ››
‹‹ስከተልሽ ልኑር አርጊኝና ሎሌ››
ነገርና ብቅል ናላውን ያዞረው
አንዱ ስክር ያለ ላዝማሪው ጠየቀው
‹‹ጡትሽ ማለት ሎሚ ብለህ የገጠምከው››
‹ጡትሽ ሀምሳ ሎሚ ልትል ፈልገህ ነው?››
ሁለቱ አሮጊቶች ሁለት ነገር ሰሩ
ሰካራሙን ጠጪ ከቤት አስባረሩ
አዝማሪው ግምባር ላይ ረብጣ ጋገሩ
ህይወትን ስንፈታው መንታ ትርም አዝሏል
እውነትን መናገር ከደጃፍ ያስጥላል
በውሸት ማሞገስ ሽልማት ያዘንባል
‹‹ አንቺ ማለት ለኔ የምስራቅ ፀሀይ ነሽ ››
‹‹ንጋት እና ምሽት ቀን የምቆጥርብሽ››
ብየ የጻፍኩልሽ ያንድ ቀኑ ግጥም
እርሽው አታስታውሽው ለኔም አልገባኝም
አንቺ ማለት ለኔ በቃ አንቺ ማለት ነሽ
በልቤ ጎዳና ወክ አድርገሽ ያለፍሽ
የሆነ ቀን መጣሽ በሆነ ምሽት ሄድሽ
ስትመጪ ግቢ አልኩሽ ስትሄጂ ረሳሁሽ
መርሳት በሽታየ መርሳት መዳኒቴ
በመርሳት ታምሜ ዳንኩኝ በመርሳቴ
አንድ ሰው ነበረ እንደኔ ሚረሳ
ሲተኛ ይፅፋል እቃዎቹን ሁሉ የት እንዳኖራቸው
‹‹ጫማየ ቴብል ስር ካልሲዎቼ ደግሞ ጫማ ውስጥ ናቸው››
‹‹ሸሚዜ ሻንጣ ውስጥ ሱሪየ ወንበር ላይ››
‹‹ሞባይሌ መሬት እኔ ደሞ አልጋ ላይ ››
በጠዋት ይነሳና ደብተሩን ይገልጣል
ሱሪና ሸሚዙን ሞባይል ሰአቱን ካሉበት ያነሳል
አንድ ነገር ብቻ ከፃፈበት ያጣል
አልጋው ባዶ ሆኗል
እናም እንዳልረሳሽ ልፅፍሽ ስሞክር
አንቺን ከሌላዋ ለይቼ ማሰፍረው አጣሁ ልዩ ነገር
ተመሳሳይ ሀሳብ ባዲስ ገፅ መፃፍ
ደብተር መጨረስ ነው ብእርን ማንጠፍጠፍ
ይህ የፃፍኩት ግጥም ሀሳብና ቋንቋው ለዛና ፍሰቱ እንዳይሆን የሆነው
ላንቺ መታሰቢያ አንቺን እንዲመስል የሳልኩት ስዕል ነው፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዘላለም ምህረቱ
ነግሬሽ ነበረ ነገሬ በዝቶብሽ ረሳሽው እንጂ
አንቺም ነግረሽኛል ዛሬ ብረሳውም ረስተሽኝ ስትሄጂ
ስላንቺ የፃፍኩት ያሰብኩት በሞላ
የተኮረጀ ነው ካለም የተቀዳ ገና ያልተብላላ
ረስተሸ ካልሆነ አዝማሪ ወዳለሁ
በማሲንቆ ቅኝት ነፍሴን አደምጣለሁ
አናልሽ በቀደም አዝማሪ ቤት ሆኜ
የጠጁን ብርሌ አፌ ላይ ደቅኜ
ከኔ ባርጩማ ጎን አንድ ድንክ ቁጭ ብሏል
መላጣውን ሲያዩት ዲያስፖራ ይመስላል
አዝማሪው ይዘፍናል ለድንኩ ሰውየ
አዲስ ዜማ ፈጥሮ ከባቲ ዋሆየ
‹‹የጎፈሬህ ጫካ መሸፈት ያሰኛል››
‹‹መለሎው ቁመትህ አክሱምን ያስንቃል››
ድንኩ ወዳጃችን በጎፈሬው ፋንታ መላጣው ያበራል
በርጩማ ላይ ቆሞ አዝማሪው ግምባር ላይ መቶ ብር ይመርጋል
ከኔ አለፍ ብለው ኣናረጅም ያሉ ሁለት አሮጊቶች
ይፍለቀለቃሉ ባዝማሪው ቃላቶች
‹‹ጡትሽ ማለት ሎሚ አንገትሽ ብርሌ››
‹‹ስከተልሽ ልኑር አርጊኝና ሎሌ››
ነገርና ብቅል ናላውን ያዞረው
አንዱ ስክር ያለ ላዝማሪው ጠየቀው
‹‹ጡትሽ ማለት ሎሚ ብለህ የገጠምከው››
‹ጡትሽ ሀምሳ ሎሚ ልትል ፈልገህ ነው?››
ሁለቱ አሮጊቶች ሁለት ነገር ሰሩ
ሰካራሙን ጠጪ ከቤት አስባረሩ
አዝማሪው ግምባር ላይ ረብጣ ጋገሩ
ህይወትን ስንፈታው መንታ ትርም አዝሏል
እውነትን መናገር ከደጃፍ ያስጥላል
በውሸት ማሞገስ ሽልማት ያዘንባል
‹‹ አንቺ ማለት ለኔ የምስራቅ ፀሀይ ነሽ ››
‹‹ንጋት እና ምሽት ቀን የምቆጥርብሽ››
ብየ የጻፍኩልሽ ያንድ ቀኑ ግጥም
እርሽው አታስታውሽው ለኔም አልገባኝም
አንቺ ማለት ለኔ በቃ አንቺ ማለት ነሽ
በልቤ ጎዳና ወክ አድርገሽ ያለፍሽ
የሆነ ቀን መጣሽ በሆነ ምሽት ሄድሽ
ስትመጪ ግቢ አልኩሽ ስትሄጂ ረሳሁሽ
መርሳት በሽታየ መርሳት መዳኒቴ
በመርሳት ታምሜ ዳንኩኝ በመርሳቴ
አንድ ሰው ነበረ እንደኔ ሚረሳ
ሲተኛ ይፅፋል እቃዎቹን ሁሉ የት እንዳኖራቸው
‹‹ጫማየ ቴብል ስር ካልሲዎቼ ደግሞ ጫማ ውስጥ ናቸው››
‹‹ሸሚዜ ሻንጣ ውስጥ ሱሪየ ወንበር ላይ››
‹‹ሞባይሌ መሬት እኔ ደሞ አልጋ ላይ ››
በጠዋት ይነሳና ደብተሩን ይገልጣል
ሱሪና ሸሚዙን ሞባይል ሰአቱን ካሉበት ያነሳል
አንድ ነገር ብቻ ከፃፈበት ያጣል
አልጋው ባዶ ሆኗል
እናም እንዳልረሳሽ ልፅፍሽ ስሞክር
አንቺን ከሌላዋ ለይቼ ማሰፍረው አጣሁ ልዩ ነገር
ተመሳሳይ ሀሳብ ባዲስ ገፅ መፃፍ
ደብተር መጨረስ ነው ብእርን ማንጠፍጠፍ
ይህ የፃፍኩት ግጥም ሀሳብና ቋንቋው ለዛና ፍሰቱ እንዳይሆን የሆነው
ላንቺ መታሰቢያ አንቺን እንዲመስል የሳልኩት ስዕል ነው፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዘላለም ምህረቱ
👍10👏7❤6
#ሰውና_ምላሱ
አምሮብኝ አጊጬ፥
ቢያዩኝ ተለውጬ፥
ሀብት ንብረት ኖሮኝ ከማጣት አምልጬ፥
..........ቀን ከሌት ብለፋ፥
..........ኑሮዬን ላፋፋ፥
ጥርሴ ሲስቅ ሲያዩኝ ጭንቀቴ ሲጠፋ፥
ሰርቼ በበላሁ ፀዳል ፊቴ ፈክቶ፥
ለፍቼ ባገኘሁ ቤት ማጀቴ ሞልቶ፥
ብኖር ሁለን ችዬ ከሰው ተስማምቼ፥
የግር እሳት ሆነ ይህ ለጠላቶቼ።
"እሷማ ሰላቢ ሌባ ናት ሟርተኛ፥
ሳትሰራ የምታገኝ ጠንቋይ መተተኛ፥
ገንዘብና ንብረት፥
ሰው አቀራት ውበት ፥
ሁሉን ከኛ ሰልባ ክብሯን ሾመችበት።"
.........ስትሉኝ ሰምቼ
..........በጣም ተከፍቼ
ሀብትና ውበቴን ሁሉን ነገር ትቼ፥
ለናንተው አድልቼ ከሰዎች ሸሽቼ፥
ብኖር ሁሉን ጥዬ በሬን ዘጋግቼ፥
በዚህስ መች ተዉኝ
"ጭራሽ ይባስ ብላ ንብረቷን አምክና፥
ገንዘቧን ለሰዎች ለወንዶች በትና፥
ይኸው ባዶ እጆቿን ቀረች በጎዳና፥"
ስትሉኝ ስማሁኝ ወይ የኔ ፈተና።
ቦርጭ አውጥቶ ሆዴ ቢወፍር አካሌ፥
አረገዘች አሉኝ አወየው እድሌ።
እሱንም ሰምቼ
በጣም ተከፍቼ
አካሌን ባከሳ ፍዳዬን በልቼ፥
አስወረደች ሲሉኝ ሰማሁ በጆሮቼ።
አረዲያ እስከመቼ.....
ኤጭ አሁንስ በቃኝ አስጠላኝ መኖሩ፥
ሰለቸኝ እናንተን ማለት እሹሩሩ።
የምላሳችሁ መርዝ ወደማይደርስበት፥
ከሀሜት አምልጬ እፎይይይ የምልበት፥
እናንተም አርፋችሁ እኔም ልረፍበት፥
..........አሁን እኳን ተዉኝ..........
ሞታቹን አልነካሁ ሞቴን ልሙትበት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
አምሮብኝ አጊጬ፥
ቢያዩኝ ተለውጬ፥
ሀብት ንብረት ኖሮኝ ከማጣት አምልጬ፥
..........ቀን ከሌት ብለፋ፥
..........ኑሮዬን ላፋፋ፥
ጥርሴ ሲስቅ ሲያዩኝ ጭንቀቴ ሲጠፋ፥
ሰርቼ በበላሁ ፀዳል ፊቴ ፈክቶ፥
ለፍቼ ባገኘሁ ቤት ማጀቴ ሞልቶ፥
ብኖር ሁለን ችዬ ከሰው ተስማምቼ፥
የግር እሳት ሆነ ይህ ለጠላቶቼ።
"እሷማ ሰላቢ ሌባ ናት ሟርተኛ፥
ሳትሰራ የምታገኝ ጠንቋይ መተተኛ፥
ገንዘብና ንብረት፥
ሰው አቀራት ውበት ፥
ሁሉን ከኛ ሰልባ ክብሯን ሾመችበት።"
.........ስትሉኝ ሰምቼ
..........በጣም ተከፍቼ
ሀብትና ውበቴን ሁሉን ነገር ትቼ፥
ለናንተው አድልቼ ከሰዎች ሸሽቼ፥
ብኖር ሁሉን ጥዬ በሬን ዘጋግቼ፥
በዚህስ መች ተዉኝ
"ጭራሽ ይባስ ብላ ንብረቷን አምክና፥
ገንዘቧን ለሰዎች ለወንዶች በትና፥
ይኸው ባዶ እጆቿን ቀረች በጎዳና፥"
ስትሉኝ ስማሁኝ ወይ የኔ ፈተና።
ቦርጭ አውጥቶ ሆዴ ቢወፍር አካሌ፥
አረገዘች አሉኝ አወየው እድሌ።
እሱንም ሰምቼ
በጣም ተከፍቼ
አካሌን ባከሳ ፍዳዬን በልቼ፥
አስወረደች ሲሉኝ ሰማሁ በጆሮቼ።
አረዲያ እስከመቼ.....
ኤጭ አሁንስ በቃኝ አስጠላኝ መኖሩ፥
ሰለቸኝ እናንተን ማለት እሹሩሩ።
የምላሳችሁ መርዝ ወደማይደርስበት፥
ከሀሜት አምልጬ እፎይይይ የምልበት፥
እናንተም አርፋችሁ እኔም ልረፍበት፥
..........አሁን እኳን ተዉኝ..........
ሞታቹን አልነካሁ ሞቴን ልሙትበት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤10😢4👍3👎1
#ዕድሌ_ነው....
በሚስት ልወሰን እኔ ትዳር ሲያምረኝ
ሳታገባ ምትቆይ አንድም ሴት አትገኝ
እኔ ዲግሪ ስይዝ ዲግሪ ዋጋ ያጣል
ገንዘብ ያለው ሁሉ ዶክትሬት ያመጣል
እኔ መድረክ ስይዝ ይፈታል ጉባኤ፤
እኔ መጾም ሲያምረኝ ይሆናል ትንሣኤ
በቁርባን ለመኖር ንሰሐ ስገባ
አቁራቢው ፖትልኮ ቤተመንግሥት ገባ
እኔ ኳስ ስገዛ ሜዳው ይታረሳል
እኔ ቤት ሲኖረኝ ሰፈሬ ይፈርሳል
ለተሾመ ሁሉ እንዳልኖርሁ ስለፋ
እኔ አለቃ ስሆን የሚታዘዝ ጠፋ
ዕድሌ ነውና...
ከዕለታት አንድ ቀን መንገሤ ባይቀርም
እኔ ንጉስ ስሆን ሀገሪቶ አትኖርም፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
በሚስት ልወሰን እኔ ትዳር ሲያምረኝ
ሳታገባ ምትቆይ አንድም ሴት አትገኝ
እኔ ዲግሪ ስይዝ ዲግሪ ዋጋ ያጣል
ገንዘብ ያለው ሁሉ ዶክትሬት ያመጣል
እኔ መድረክ ስይዝ ይፈታል ጉባኤ፤
እኔ መጾም ሲያምረኝ ይሆናል ትንሣኤ
በቁርባን ለመኖር ንሰሐ ስገባ
አቁራቢው ፖትልኮ ቤተመንግሥት ገባ
እኔ ኳስ ስገዛ ሜዳው ይታረሳል
እኔ ቤት ሲኖረኝ ሰፈሬ ይፈርሳል
ለተሾመ ሁሉ እንዳልኖርሁ ስለፋ
እኔ አለቃ ስሆን የሚታዘዝ ጠፋ
ዕድሌ ነውና...
ከዕለታት አንድ ቀን መንገሤ ባይቀርም
እኔ ንጉስ ስሆን ሀገሪቶ አትኖርም፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍35❤6✍4
#እኔ_አንተን_ከማጣ
...እኔ አንተን ከማጣ....
ደመናው ይቆጣ ያዝንብ ፡ ሚስማር ከላይ
ሲፈልግ ደጎራ ፡ ሲያሻው ጥርብ ድንጋይ
ፀሃይ ብርሃን ታቁም ፡ ስትፈልግ ትበተን
ምድር ዱቄት ትሁን ፡ ሲያሻት ከስላ ትብነን
ጨረቃም ትሠወር ፡ አትውጣ እድሜ ልኳን ።
እኔ አንተን ከማጣ...
ስትፈልግ የሎጥ ሚስት ፡ ጎጃምኛ ትምታ
የፈርኦን ሠራዊት ፡ እስራኤልን ይቅጣ
የኤርትራም ባህር ፡ ይኑር በከፍታ ።
እኔ አንተን ከማጣ...
እፅዋት ይድረቁ ፡ እንስሳት ይለቁ
ፕላኔቶች ሁሉ : ምድር ላይ ይውደቁ ።
እኔ አንተን ከማጣ...
ዳይኖሠር ተነስቶ ፡ በምድር እሣት ይትፋ
ምፃት ነገ ይሁን : አለም ካለም ትጥፋ ።
እኔ አንተን ከማጣ...
ምድረበዳው ያዝንብ : ኤርታሌም ይወርዛ
ኢህአዴግ አስር ሺህ ፡ አመታትን ይግዛ
ሲፈልግ ተሻግሮ ፡ አለማትን ይንዳ ።
እኔ አንተን ከማጣ...
ማወቅ ድብን ይበል : ባፍ ጢሙ ይደፋ
ክፉወች ወፍረው : መልካም አንገት ይድፋ ።
እኔ አንተን ከማጣ....
ፈጣሪ አሲድ ይርጭ : ምድሪቱን ያጉርፋት
ቁጣውን ያበርታ : አይዳኑ ፍጥረታት ።
እኔ አንተን ከማጣ.....
ማንም ምንም ይምጣ ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
...እኔ አንተን ከማጣ....
ደመናው ይቆጣ ያዝንብ ፡ ሚስማር ከላይ
ሲፈልግ ደጎራ ፡ ሲያሻው ጥርብ ድንጋይ
ፀሃይ ብርሃን ታቁም ፡ ስትፈልግ ትበተን
ምድር ዱቄት ትሁን ፡ ሲያሻት ከስላ ትብነን
ጨረቃም ትሠወር ፡ አትውጣ እድሜ ልኳን ።
እኔ አንተን ከማጣ...
ስትፈልግ የሎጥ ሚስት ፡ ጎጃምኛ ትምታ
የፈርኦን ሠራዊት ፡ እስራኤልን ይቅጣ
የኤርትራም ባህር ፡ ይኑር በከፍታ ።
እኔ አንተን ከማጣ...
እፅዋት ይድረቁ ፡ እንስሳት ይለቁ
ፕላኔቶች ሁሉ : ምድር ላይ ይውደቁ ።
እኔ አንተን ከማጣ...
ዳይኖሠር ተነስቶ ፡ በምድር እሣት ይትፋ
ምፃት ነገ ይሁን : አለም ካለም ትጥፋ ።
እኔ አንተን ከማጣ...
ምድረበዳው ያዝንብ : ኤርታሌም ይወርዛ
ኢህአዴግ አስር ሺህ ፡ አመታትን ይግዛ
ሲፈልግ ተሻግሮ ፡ አለማትን ይንዳ ።
እኔ አንተን ከማጣ...
ማወቅ ድብን ይበል : ባፍ ጢሙ ይደፋ
ክፉወች ወፍረው : መልካም አንገት ይድፋ ።
እኔ አንተን ከማጣ....
ፈጣሪ አሲድ ይርጭ : ምድሪቱን ያጉርፋት
ቁጣውን ያበርታ : አይዳኑ ፍጥረታት ።
እኔ አንተን ከማጣ.....
ማንም ምንም ይምጣ ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍15❤9😁4🥰2👏1😢1🙉1
#ሕልሜን_አደራ
ባይመረመሬ ጥበብ ተሽቀርቅሮ
ከወርቃማ ብርሃን፤ ከብርማ ፀዳል
የተሰራ ሸማ፥ ማግኘት ብችል ኖሮ
ከውብ እግሮችሽ ስር፥ እዘረጋው ነበር
ግና ምንም የለኝ፥ ከህልሞቼ በቀር ፡፡
የኔ ውድ እንግዲህ
ሕልሜን እግሮችሽ ስር፥ ከዘረጋሁ ወዲህ፥
ቀስ ብለሽ ርገጪ፥ ዝግ ብለሽ ሂጂ
ህልሜ ላይ ነውና የምትራመጂ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በዕውቀቱ ስዩም
ባይመረመሬ ጥበብ ተሽቀርቅሮ
ከወርቃማ ብርሃን፤ ከብርማ ፀዳል
የተሰራ ሸማ፥ ማግኘት ብችል ኖሮ
ከውብ እግሮችሽ ስር፥ እዘረጋው ነበር
ግና ምንም የለኝ፥ ከህልሞቼ በቀር ፡፡
የኔ ውድ እንግዲህ
ሕልሜን እግሮችሽ ስር፥ ከዘረጋሁ ወዲህ፥
ቀስ ብለሽ ርገጪ፥ ዝግ ብለሽ ሂጂ
ህልሜ ላይ ነውና የምትራመጂ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በዕውቀቱ ስዩም
👍18❤1🥰1
#እጠብቅሻለሁ!!
ሰኞ ለት ቀጥረሺኝ የምን ቀን ነው ብለሽ
ቀረሽ ሳትመጪ
ማክሰኞ ቀጥረሺኝ ታምሚያለሁ ብለሽ ከቤት ሳትወጪ
በረቡዕ ተስማምተን በጊዜ ወጥቼ
ስጠብቅሽ ቆሜ
ደውለሽ ይቅርታ ፆም ነው ለካ ዛሬ በፍስግ ይሻላል ሃሙስ
ወይ ቅዳሜ
ያልሺኝን አመኜ ሃሙስን መርጬ
አንቺን ለማማለል ብወጣም ዘንጬ
ወይ በረሽ አልመጣሽ ወይ ስልክሽ አይሰራ
ምን አገኛት እያልኩ እያሰላሰልኩኝ
ለብቻ ሳወራ
ድንገት ስልኬ ጠራ
"መቼም አታምነኝም ያጎቴ ልጅ ሞቶ
ለቅሶ ቤት ሄጄ ነው
እንዳትቀየመኝ ምንም ይሁን ምንም ነገ ግን ግድ ነው"
ብለሽ አምኛለሁ
ግን ግን ግዴለሽም !
አርብን እንዝለለው ላንቺም ይሻልሻል
በአፍቃሪ እይታ መጠራጠር የለም ሁሉም ይታመናል
ወይ ፆሙን አስታከሽ ወይ በልጁ ቀብር አትመጪም ይሆናል
ስለዚህ ቅዳሜ በተወደደው ቀን
ውጪ ዘንጪና
እኔም ልጠብቅሽ በጊዜ ወጥቼ አይንሽን ለማየት ጓጉቻለሁና
ቅዳሜንስ ለኔ ማነው የፈቀደው
ለመታመን ያህል በትመጪ ተስፋ ከመንገድ ቆሚያለሁ
ይኸው ቀኑም መሸ
የናፈቀው አይኔ ሳያይሽ ሟሸሸ
ካሁን በኋላ ግን እየወጡ መግባት እየገቡ መውጣት ስልችት ስላለኝ
እሁድን እዚያው ነኝ
ሰኞና ማክሰኞ እረቡም አለሁኝ
ሀሙስና አርብን ቅዳሜም አታጪኝ
ጎዳና አጎሳቁሎኝ ገፅታዬ ጠፍቶሽ
አይተሽ ካላለፍሺኝ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዳዊት ተ/ማርያም
ሰኞ ለት ቀጥረሺኝ የምን ቀን ነው ብለሽ
ቀረሽ ሳትመጪ
ማክሰኞ ቀጥረሺኝ ታምሚያለሁ ብለሽ ከቤት ሳትወጪ
በረቡዕ ተስማምተን በጊዜ ወጥቼ
ስጠብቅሽ ቆሜ
ደውለሽ ይቅርታ ፆም ነው ለካ ዛሬ በፍስግ ይሻላል ሃሙስ
ወይ ቅዳሜ
ያልሺኝን አመኜ ሃሙስን መርጬ
አንቺን ለማማለል ብወጣም ዘንጬ
ወይ በረሽ አልመጣሽ ወይ ስልክሽ አይሰራ
ምን አገኛት እያልኩ እያሰላሰልኩኝ
ለብቻ ሳወራ
ድንገት ስልኬ ጠራ
"መቼም አታምነኝም ያጎቴ ልጅ ሞቶ
ለቅሶ ቤት ሄጄ ነው
እንዳትቀየመኝ ምንም ይሁን ምንም ነገ ግን ግድ ነው"
ብለሽ አምኛለሁ
ግን ግን ግዴለሽም !
አርብን እንዝለለው ላንቺም ይሻልሻል
በአፍቃሪ እይታ መጠራጠር የለም ሁሉም ይታመናል
ወይ ፆሙን አስታከሽ ወይ በልጁ ቀብር አትመጪም ይሆናል
ስለዚህ ቅዳሜ በተወደደው ቀን
ውጪ ዘንጪና
እኔም ልጠብቅሽ በጊዜ ወጥቼ አይንሽን ለማየት ጓጉቻለሁና
ቅዳሜንስ ለኔ ማነው የፈቀደው
ለመታመን ያህል በትመጪ ተስፋ ከመንገድ ቆሚያለሁ
ይኸው ቀኑም መሸ
የናፈቀው አይኔ ሳያይሽ ሟሸሸ
ካሁን በኋላ ግን እየወጡ መግባት እየገቡ መውጣት ስልችት ስላለኝ
እሁድን እዚያው ነኝ
ሰኞና ማክሰኞ እረቡም አለሁኝ
ሀሙስና አርብን ቅዳሜም አታጪኝ
ጎዳና አጎሳቁሎኝ ገፅታዬ ጠፍቶሽ
አይተሽ ካላለፍሺኝ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዳዊት ተ/ማርያም
👍24❤14🔥10👏4
#በፀሀይ_ቅጠሪኝ
በዝናብ ስነግርሽ በርትቶብኝ ፍቅሬ
ሳይገባሽ ብታልፊ ዘንግተሽኝ ዛሬ
ብርሀን ሲፈካ ሲፈነጥቅ ጮራ
ጭጋጉ ሲበተን ዝናቡ ሲያባራ
ይሰማሽ ይሆናል እንባዬ ሲያወራ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
በዝናብ ስነግርሽ በርትቶብኝ ፍቅሬ
ሳይገባሽ ብታልፊ ዘንግተሽኝ ዛሬ
ብርሀን ሲፈካ ሲፈነጥቅ ጮራ
ጭጋጉ ሲበተን ዝናቡ ሲያባራ
ይሰማሽ ይሆናል እንባዬ ሲያወራ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👍13❤3👏2🔥1
#ጌታዬ_አቅቶኛል !
ፍቅርና ምህረትህ አልፎብኝ ከልኬ
መሸከም አቃተኝ ከበደኝ አምላኬ!
በየቱ ስራዬ በየቱ ትህትና
ችዬ ልሸከመው ደካማ ነኝና
አንተ ሁሌም ስትምር እኔ ሁሌም በዳይ
ጌታዬ አቅቶኛል ፍቅርህ ከብዶኝ ከላይ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ
ፍቅርና ምህረትህ አልፎብኝ ከልኬ
መሸከም አቃተኝ ከበደኝ አምላኬ!
በየቱ ስራዬ በየቱ ትህትና
ችዬ ልሸከመው ደካማ ነኝና
አንተ ሁሌም ስትምር እኔ ሁሌም በዳይ
ጌታዬ አቅቶኛል ፍቅርህ ከብዶኝ ከላይ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ
❤24👍9🔥2
ያን ጠይሙን ዘመን ...
ያንን ገራም ወራት ...
ያን የጊዜ መቅኔ ያን የዘመን ኣስኳል ፤
በምን ወዜ ላስጊጥ በምን እጄ ልኳል?!
ያ ዘመን ገራሙ ...
ያ ዘመን ህያው ቃል ፤
ነገሩን በሙሉ የቀመሰው ያውቃል።
ብዬ ልተው ይሆን ...
መቼም ይህ ትዝታ ...
የሳሙትን ከንፈር የዳበሱትን ጡት ፤
የተቃኙበትን የነፍስያ ኣውታር ለዛ ስልቱን ሲያጡት ፤
የሚፈጥሩት ዜማ ፣
ከራስ ነፍስ ፈልቆ ለራስ የሚሰማ ፤
የሞት ጠረን ያለው ኑሮ ኑሮ 'ሚሸት ፤
ስሙኝ ስሙኝ የሚል የደናግል ዜማ
ቃሙኝ ቃሙኝ የሚል የማሽላ እሸት ።
( ትዝታ ግን ማለት ... )
ትዝታ ይጥላል ...
ትዝታ ያነሳል ፤
ትዝታ ይቸራል ...
ትዝታ ይነሳል ፤
ትዝታ ሆሄ ነው የተበታተነ የፈራረሰ ቃል ፤
ሲያሻው ያስከብራል በል ሲለው ያስንቃል ፤
ህልም እየነጠቀ ይተናል እንደጉም ፤
ትርጉም ማሳጣት ነው የትዝታ ትርጉም ።
መቼም ይህ ትዝታ ...
የሳሙትን ከንፈር የዳበሱትን ጡት ፤
እንኳን ባ'ይነ ስጋ ኣሻራውን ሲያጡት ፤
የሚደነግጡት ...
የሰቀቀን ሆሳ ።
ከገዛ ቅዠት ጋር በገሃድ የሚያብር ፤
ከንቱ ትላንት ነው ነገን የሚያሸብር ።
እውነት ነው ትዝታ
ከቅዠት ያብራል ፤
እውነት ነው ትዝታ
ነገን ያሸብራል ።
እንደውም ...
እንደውም ...
በዘመን ተብላልቶ የደቀቀ ቅስሙ ፤
እንደውም ትዝታ አሸብር ነው ስሙ ...
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሙሀመድ
ያንን ገራም ወራት ...
ያን የጊዜ መቅኔ ያን የዘመን ኣስኳል ፤
በምን ወዜ ላስጊጥ በምን እጄ ልኳል?!
ያ ዘመን ገራሙ ...
ያ ዘመን ህያው ቃል ፤
ነገሩን በሙሉ የቀመሰው ያውቃል።
ብዬ ልተው ይሆን ...
መቼም ይህ ትዝታ ...
የሳሙትን ከንፈር የዳበሱትን ጡት ፤
የተቃኙበትን የነፍስያ ኣውታር ለዛ ስልቱን ሲያጡት ፤
የሚፈጥሩት ዜማ ፣
ከራስ ነፍስ ፈልቆ ለራስ የሚሰማ ፤
የሞት ጠረን ያለው ኑሮ ኑሮ 'ሚሸት ፤
ስሙኝ ስሙኝ የሚል የደናግል ዜማ
ቃሙኝ ቃሙኝ የሚል የማሽላ እሸት ።
( ትዝታ ግን ማለት ... )
ትዝታ ይጥላል ...
ትዝታ ያነሳል ፤
ትዝታ ይቸራል ...
ትዝታ ይነሳል ፤
ትዝታ ሆሄ ነው የተበታተነ የፈራረሰ ቃል ፤
ሲያሻው ያስከብራል በል ሲለው ያስንቃል ፤
ህልም እየነጠቀ ይተናል እንደጉም ፤
ትርጉም ማሳጣት ነው የትዝታ ትርጉም ።
መቼም ይህ ትዝታ ...
የሳሙትን ከንፈር የዳበሱትን ጡት ፤
እንኳን ባ'ይነ ስጋ ኣሻራውን ሲያጡት ፤
የሚደነግጡት ...
የሰቀቀን ሆሳ ።
ከገዛ ቅዠት ጋር በገሃድ የሚያብር ፤
ከንቱ ትላንት ነው ነገን የሚያሸብር ።
እውነት ነው ትዝታ
ከቅዠት ያብራል ፤
እውነት ነው ትዝታ
ነገን ያሸብራል ።
እንደውም ...
እንደውም ...
በዘመን ተብላልቶ የደቀቀ ቅስሙ ፤
እንደውም ትዝታ አሸብር ነው ስሙ ...
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሙሀመድ
❤6👍2🥰2
''ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤ አሰሮ ለሰይጣን አግአዞ ለአዳም ፤ ሰላም ▸ እምይእዜሰ ፤ ኮነ ▸ ፍስሐ ወሰላም''
''ክርስቶስ በታላቅ በኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ''
ውድ የግጥም ቻናል የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ፥ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ።
በዓሉ የሰላም የፍቅር እና የአንድነት በዓል ይሁንልን አሜን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
''ክርስቶስ በታላቅ በኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ''
ውድ የግጥም ቻናል የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ፥ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ።
በዓሉ የሰላም የፍቅር እና የአንድነት በዓል ይሁንልን አሜን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
❤9👍4🙏2