#ሶስቱ_ፍሬ_ቢሶች
የተማረ ሆኖ ዕውቀቱን የማይገልጥ
ባለጠጋ ሆኖ ለደሀ የማይሰጥ
ደሀ ሆኖ መስራት የሚጠላ ልቡ
ሶስቱ ፍሬ ቢሶች ለምንም አይረቡ !
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ከበደ ሚካኤል
የተማረ ሆኖ ዕውቀቱን የማይገልጥ
ባለጠጋ ሆኖ ለደሀ የማይሰጥ
ደሀ ሆኖ መስራት የሚጠላ ልቡ
ሶስቱ ፍሬ ቢሶች ለምንም አይረቡ !
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ከበደ ሚካኤል
👍22❤6💯4
#ያማል!
እና እንደ ነገርኩሽ
የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ
የነብሰጡርን ሞት አይቶ እንደመሳቀቅ
ከተስፋ ጉልላት ተገፍቶ እንደመውደቅ
ታምር በበዛበት በዚች ቧልተኛ አለም
ከዚህ የበለጠ ምንም ህመም የለም
አውቶብሱ ያማል
ሚኒባሱ ያማል
ላዳ ታክሲው ያማል
የማይጎል የሰው ጎርፍ ደራሽ ማዕበሉ
የዕንባ ቅጥልጥሉ
ምንብዬ ልንገርሽ ? ያማል ይሄ ሁሉ
እና እንደ ነገርኩሽ
የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ ካረፈደ
የሚያፈቅሩትን ሰው ቀጥሮ ካረፈደ
ነገር ተበላሸ ህመም ተወለደ
ጨጓራ በገነ
እሳት በዕንፋሎት መልክ በእህታ ተነነ
የሚሆነው ሳይሆን የማይሆነው ሆነ
ሁሉም ተቀይሮ ተተካ በሲቃ
ምንብዬ ልንገርሽ? ይሄም ያማል በቃ
ወጪ ተራማጁ
አስመሳይ ሰጋጁ
ፀሀዩ ዝናቡ
የለምን ምክንያት የለምን ሰበቡ
ተቆራጭ አበባ ሊቆረጥ ማበቡ
ውል የለሽ ደመና ተራራ መክበቡ
እልፍ አዕላፍ ኮከብ ጨረቃን ማጀቡ
ደሞ ለሷ ግጥም እናቷን ጨረቃ
ምንብዬ ልንገርሽ ይህም ያማል በቃ
እና እንደ ነገርኩሽ
ጉንጭ የማትሞላ ኬክ አስር ብር የሸጠ
የካፌ አሳላፊ ወደኔ አፈጠጠ
ዘይት የነካውን መንታ እጁን አጣምሮ
ምን ልታዘዝ ይላል ቁልቁል አቀርቅሮ
ምን ልታዘዝ ይላል…??
እንዴት ቅጥሉ ሰው ቅጥሉን ሰው ያዛል
ማኪያቶ ልዘዝ?
ካፑችኖ ልዘዝ?
ጥቁር ቡና ልዘዝ?
ለምን ሰው አላዝም?
መታዘዝ መናዘዝ እርግማን የሆነው ካፌውን ሊያሳልፍ
እራሱ ግን የሚያልፍ
ቁልቁል አቀርቅሮ
ሞቱን ባንገት ቀብሮ
ምን ልታዘዝ? ይላል
አንድ ማኪያቶ ካንድ እሷ ጋር ልዘዝ?
አንድ ካፑችኖ ካንድ እሷ ጋር ልበል?
ከ
የ`ጭቃ እሾህ ወግቶት
እዥ ያወጣ ቁስል
ትልቁ ነቀዝ ሰው የማንቀዙን ያህል
ብዙ አታስለፍልፊኝ ይሄ ሁሉ ያማል
እና እንደ ነገርኩሽ
ላንቺ የያዝኩት አበባ መጠውለግ አመጣ
ፀሀይ ገባ ወጣ
ዝናብ ቀረ መጣ
ጨረቃም የለችም እናቷን ስላልኳት
ደግሜ ሰድቤ ሺህ አመት እንዳይገርማት
እ. . . .ና. . . .ቷን !
እናቷን ጨረቃ
ተይ አታስለፍልፊኝ ይህም ያማል በቃ
ግን አንቺን ስወድሽ
ይህን ሁሉ ችዬ - ነው ም'ጠብቅሽ
ቢሆንም ግን ያማል !!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሰለሞን ሳህሌ
እና እንደ ነገርኩሽ
የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ
የነብሰጡርን ሞት አይቶ እንደመሳቀቅ
ከተስፋ ጉልላት ተገፍቶ እንደመውደቅ
ታምር በበዛበት በዚች ቧልተኛ አለም
ከዚህ የበለጠ ምንም ህመም የለም
አውቶብሱ ያማል
ሚኒባሱ ያማል
ላዳ ታክሲው ያማል
የማይጎል የሰው ጎርፍ ደራሽ ማዕበሉ
የዕንባ ቅጥልጥሉ
ምንብዬ ልንገርሽ ? ያማል ይሄ ሁሉ
እና እንደ ነገርኩሽ
የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ ካረፈደ
የሚያፈቅሩትን ሰው ቀጥሮ ካረፈደ
ነገር ተበላሸ ህመም ተወለደ
ጨጓራ በገነ
እሳት በዕንፋሎት መልክ በእህታ ተነነ
የሚሆነው ሳይሆን የማይሆነው ሆነ
ሁሉም ተቀይሮ ተተካ በሲቃ
ምንብዬ ልንገርሽ? ይሄም ያማል በቃ
ወጪ ተራማጁ
አስመሳይ ሰጋጁ
ፀሀዩ ዝናቡ
የለምን ምክንያት የለምን ሰበቡ
ተቆራጭ አበባ ሊቆረጥ ማበቡ
ውል የለሽ ደመና ተራራ መክበቡ
እልፍ አዕላፍ ኮከብ ጨረቃን ማጀቡ
ደሞ ለሷ ግጥም እናቷን ጨረቃ
ምንብዬ ልንገርሽ ይህም ያማል በቃ
እና እንደ ነገርኩሽ
ጉንጭ የማትሞላ ኬክ አስር ብር የሸጠ
የካፌ አሳላፊ ወደኔ አፈጠጠ
ዘይት የነካውን መንታ እጁን አጣምሮ
ምን ልታዘዝ ይላል ቁልቁል አቀርቅሮ
ምን ልታዘዝ ይላል…??
እንዴት ቅጥሉ ሰው ቅጥሉን ሰው ያዛል
ማኪያቶ ልዘዝ?
ካፑችኖ ልዘዝ?
ጥቁር ቡና ልዘዝ?
ለምን ሰው አላዝም?
መታዘዝ መናዘዝ እርግማን የሆነው ካፌውን ሊያሳልፍ
እራሱ ግን የሚያልፍ
ቁልቁል አቀርቅሮ
ሞቱን ባንገት ቀብሮ
ምን ልታዘዝ? ይላል
አንድ ማኪያቶ ካንድ እሷ ጋር ልዘዝ?
አንድ ካፑችኖ ካንድ እሷ ጋር ልበል?
ከ
ጥቁር ቡና ጋር እሷን አምጣልበል?
ተይ አታስለፍልፊኝ ይሄ ሁሉ ያማል
የላስቲክ አበባ ያርቲ ቡርቲ ስዕልየ`ጭቃ እሾህ ወግቶት
እዥ ያወጣ ቁስል
ትልቁ ነቀዝ ሰው የማንቀዙን ያህል
ብዙ አታስለፍልፊኝ ይሄ ሁሉ ያማል
እና እንደ ነገርኩሽ
ላንቺ የያዝኩት አበባ መጠውለግ አመጣ
ፀሀይ ገባ ወጣ
ዝናብ ቀረ መጣ
ጨረቃም የለችም እናቷን ስላልኳት
ደግሜ ሰድቤ ሺህ አመት እንዳይገርማት
እ. . . .ና. . . .ቷን !
እናቷን ጨረቃ
ተይ አታስለፍልፊኝ ይህም ያማል በቃ
ግን አንቺን ስወድሽ
ይህን ሁሉ ችዬ - ነው ም'ጠብቅሽ
ቢሆንም ግን ያማል !!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሰለሞን ሳህሌ
🥰12❤8👍4👏2
#እንባዬን_የት_ላርገው
ቀና በል ይሉኛል-- ወዴት ልበል ቀና
ከላይ ተደፍቶብኝ- አገር እንደቁና
ጣራው ባጡ ቀርቦኝ
በር አልባ ግድግዳ- እንደ ዝናር ከቦኝ
በጫጩት ጉልበቴ- እየተወራጨሁ
እንባየን ዘግኘ- ሽቅብ እየረጨሁ
ወደ አማልክት ብጮህ-ጠሎቴን አይሰሙት
በየት በኩል ኖሬ
በየት በኩል ልሙት::
በምን ይገለጻል- የትውልዴ አበሣ
ከመንበርከክ ብዛት- መራመድ የረሣ
ያልፋል ተለጉሞ
ያልፋል ተከርችሞ
የጉልበቱን ኮቴ- ምድር ላይ አትሞ::
ወፈፌ ቀን አልፎ- እብድ ቀን ሲመጣ
ማልቀስ አመጽ ሲሆን- በሸንጎ ሚያስቀጣ
እንባዬን የት ላርገው
ወዴት ልሸሽገው?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ቀና በል ይሉኛል-- ወዴት ልበል ቀና
ከላይ ተደፍቶብኝ- አገር እንደቁና
ጣራው ባጡ ቀርቦኝ
በር አልባ ግድግዳ- እንደ ዝናር ከቦኝ
በጫጩት ጉልበቴ- እየተወራጨሁ
እንባየን ዘግኘ- ሽቅብ እየረጨሁ
ወደ አማልክት ብጮህ-ጠሎቴን አይሰሙት
በየት በኩል ኖሬ
በየት በኩል ልሙት::
በምን ይገለጻል- የትውልዴ አበሣ
ከመንበርከክ ብዛት- መራመድ የረሣ
ያልፋል ተለጉሞ
ያልፋል ተከርችሞ
የጉልበቱን ኮቴ- ምድር ላይ አትሞ::
ወፈፌ ቀን አልፎ- እብድ ቀን ሲመጣ
ማልቀስ አመጽ ሲሆን- በሸንጎ ሚያስቀጣ
እንባዬን የት ላርገው
ወዴት ልሸሽገው?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
❤6👍6🥰2😢2🔥1
#ጸሎቴ_ስለቴ
ጸሎቴ፤
ስለቴ፣ . . .
ለአንድ ጊዜ ብቻ፣ የለሊት ወፍን ክንፍ፤
የጨለመን ዘመን፣ ሰንጥቆ ʽሚያሳልፍ፡፡
እንደየኖህ መርከብ፣ እንደሙሴ በትር፤
ከዘመን ደንቃራ፣
ከገዢ ፉከራ፣
ከመንጋ ገጀራ፣
ፍጡራንን ሁሉ፣ ጠብቆ ʽሚያሻግር፡፡
የሆነ ምትሀት!
የሆነ ብልሀት!
. . . . . . ፈጣሪ ቢያድለኝ!
ጸሎቴ፤
ስለቴ፣ . . .
እንደህጻን ትንፋሽ፣ ሳያነቃ ከእንቅልፍ፤
እንደንጋት ዝናብ፣ ህልም ሳያዛንፍ፤
በዛሬዬ ስፍር - ለነገ እንድበቃ፤
ሽንቁሬን ደፍኜ - ሰው ሆኜ እንድነቃ፤
የሆነ ምትሀት፡፡
የሆነ ብልሀት፡፡
ጸሎቴ፤
ስለቴ፣ . . .
ከታሪክ አለት ላይ፣
በጥላቻ ትርክት፣
በቂም በቀል መሮ የተፈለፈሉ፤
በየእድሩ ደጃፍ፣
በየተራራው ጫፍ፣
. . . . . . . . . . እንዳሸን የፈሉ፤
የጥፋት ርችት፣ አዳፍኔ ሀውልቶች፤
የአብሮነት ፍልፈል፣ አይጠ መጎጦች፤
እንደቅቤ ቀልጠው፣
እመቀመቅ ወርደው፣
በቆሙበት ቦታ፤
ለትውልድ የሚተርፍ፣ ጊዜን የሚረታ፤
የፍትህ፣ የፍቅር፣ የአብሮነት ቁርባን፤
ለልጅ ልጅ የሚቆይ፣ትርጉም ያለው ድርሳን፤
. . . . . . አሻራ እንዲኖረኝ፤
ፈጣሪ ቢያድለን፣
. . . . . . ፈጣሪ ቢያድለኝ!
መቼም መላ የለን፣
. . . . . መቼም መላ የለኝ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በድሉ ዋቅጅራ
ጸሎቴ፤
ስለቴ፣ . . .
ለአንድ ጊዜ ብቻ፣ የለሊት ወፍን ክንፍ፤
የጨለመን ዘመን፣ ሰንጥቆ ʽሚያሳልፍ፡፡
እንደየኖህ መርከብ፣ እንደሙሴ በትር፤
ከዘመን ደንቃራ፣
ከገዢ ፉከራ፣
ከመንጋ ገጀራ፣
ፍጡራንን ሁሉ፣ ጠብቆ ʽሚያሻግር፡፡
የሆነ ምትሀት!
የሆነ ብልሀት!
. . . . . . ፈጣሪ ቢያድለኝ!
ጸሎቴ፤
ስለቴ፣ . . .
እንደህጻን ትንፋሽ፣ ሳያነቃ ከእንቅልፍ፤
እንደንጋት ዝናብ፣ ህልም ሳያዛንፍ፤
በዛሬዬ ስፍር - ለነገ እንድበቃ፤
ሽንቁሬን ደፍኜ - ሰው ሆኜ እንድነቃ፤
የሆነ ምትሀት፡፡
የሆነ ብልሀት፡፡
ጸሎቴ፤
ስለቴ፣ . . .
ከታሪክ አለት ላይ፣
በጥላቻ ትርክት፣
በቂም በቀል መሮ የተፈለፈሉ፤
በየእድሩ ደጃፍ፣
በየተራራው ጫፍ፣
. . . . . . . . . . እንዳሸን የፈሉ፤
የጥፋት ርችት፣ አዳፍኔ ሀውልቶች፤
የአብሮነት ፍልፈል፣ አይጠ መጎጦች፤
እንደቅቤ ቀልጠው፣
እመቀመቅ ወርደው፣
በቆሙበት ቦታ፤
ለትውልድ የሚተርፍ፣ ጊዜን የሚረታ፤
የፍትህ፣ የፍቅር፣ የአብሮነት ቁርባን፤
ለልጅ ልጅ የሚቆይ፣ትርጉም ያለው ድርሳን፤
. . . . . . አሻራ እንዲኖረኝ፤
ፈጣሪ ቢያድለን፣
. . . . . . ፈጣሪ ቢያድለኝ!
መቼም መላ የለን፣
. . . . . መቼም መላ የለኝ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በድሉ ዋቅጅራ
❤2👍2🥰2
#ምስጢር
ሁሉም እንደዘበት፣
ሁሉም በዘልማድ፤
ሁሉም እንዲያው፣ እንዲያው፣
የሚሆን መስሎሃል …
ጉንዳንን ተመልከት፣
የወፍ ቤትን አጥና፣
ንቦችን አስተውል
አንድ የውሻ ጩኸት፣
ሙዚቃ እየሆነ
ዓለምን ያነጋል፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ገብረክርስቶስ ደስታ
ሁሉም እንደዘበት፣
ሁሉም በዘልማድ፤
ሁሉም እንዲያው፣ እንዲያው፣
የሚሆን መስሎሃል …
ጉንዳንን ተመልከት፣
የወፍ ቤትን አጥና፣
ንቦችን አስተውል
አንድ የውሻ ጩኸት፣
ሙዚቃ እየሆነ
ዓለምን ያነጋል፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ገብረክርስቶስ ደስታ
👍5⚡3❤1🔥1
#ይሄን_ቃል_ፍቺልኝ ?
ምን ያደርግልሻል ስለኔ ጥሩነት እየተናገሩ
ጥሎ መኮብለሉ
በማይሆን ሽንገላ በማይዋጥ ቋንቋ
እኔን ማባበሉ
ምናለበት ብትሄጅ ጥፋቴን ተናግረሽ
ለበደልከው በደል ቅጣት ይሁን ብለሽ
ቅስሜም ቢሰባበር ፀፀቱም ቢገለኝ
እራሴን ብኮንን የጄን ስለሰጠኝ
እባክሽ የኔ ሆድ ባክሽ ስለ ፍቅር
ጥሩ ነህ ተብሎ እንዴት ይተዋል ሰው
እኔን አልገባኝም ፍቺው ይሄን ምስጢር
እውነቱን ንገሪኝ ግዴለም አትስጊ
ልስማሽ በጥሞና
ከተዋበ ውሸት የሚያስጠላ እውነት
ይሻለኛልና
ባክሽ በፈጠረሽ! ባክሽ ባርባ'ራቱ
መልስ አምጣ እያለኝ ነው አፍ አውጥቶ ቤቱ
ምን ልመልሰለት ጥላኝ ሄደች ልበል
ስለሆንኩኝ ጥሩ
አምኖስ ይቀበላል ጣራና ግድግዳው
የቤቴ ማገሩ
አያሻኝም እቴ አንቺ አበሽ ብዬ
አብሬ ማበዱ
ምን ይሉታል ይሄን ለወዳጅ ዘመዱ
መኖር አልፈልግም የማይመስል ነገር
እየዘላበዱ
ዳግመኛ አይለምደኝም አላስቸግርሽም
መልሽ ይቺን ብቻ ?
አንቺው ጋር ነው ያለው እንዲህ ያስጨከነሽ
የሚስጥሩ መፍቻ
እኔም ክፉ አልሁን በቀሪው ህይወቴ
ጥሩነቴም አይሁን ምክንያት የሆነኝ
አንቺን ለማጣቴ
ጨካኝ ያረገሽ ሚስጥሩን ፍቺልኝ
በሞቴ በሞቴ
__በሞቴ በሞቴ !!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዳዊት ተ/ማርያም
ምን ያደርግልሻል ስለኔ ጥሩነት እየተናገሩ
ጥሎ መኮብለሉ
በማይሆን ሽንገላ በማይዋጥ ቋንቋ
እኔን ማባበሉ
ምናለበት ብትሄጅ ጥፋቴን ተናግረሽ
ለበደልከው በደል ቅጣት ይሁን ብለሽ
ቅስሜም ቢሰባበር ፀፀቱም ቢገለኝ
እራሴን ብኮንን የጄን ስለሰጠኝ
እባክሽ የኔ ሆድ ባክሽ ስለ ፍቅር
ጥሩ ነህ ተብሎ እንዴት ይተዋል ሰው
እኔን አልገባኝም ፍቺው ይሄን ምስጢር
እውነቱን ንገሪኝ ግዴለም አትስጊ
ልስማሽ በጥሞና
ከተዋበ ውሸት የሚያስጠላ እውነት
ይሻለኛልና
ባክሽ በፈጠረሽ! ባክሽ ባርባ'ራቱ
መልስ አምጣ እያለኝ ነው አፍ አውጥቶ ቤቱ
ምን ልመልሰለት ጥላኝ ሄደች ልበል
ስለሆንኩኝ ጥሩ
አምኖስ ይቀበላል ጣራና ግድግዳው
የቤቴ ማገሩ
አያሻኝም እቴ አንቺ አበሽ ብዬ
አብሬ ማበዱ
ምን ይሉታል ይሄን ለወዳጅ ዘመዱ
መኖር አልፈልግም የማይመስል ነገር
እየዘላበዱ
ዳግመኛ አይለምደኝም አላስቸግርሽም
መልሽ ይቺን ብቻ ?
አንቺው ጋር ነው ያለው እንዲህ ያስጨከነሽ
የሚስጥሩ መፍቻ
እኔም ክፉ አልሁን በቀሪው ህይወቴ
ጥሩነቴም አይሁን ምክንያት የሆነኝ
አንቺን ለማጣቴ
ጨካኝ ያረገሽ ሚስጥሩን ፍቺልኝ
በሞቴ በሞቴ
__በሞቴ በሞቴ !!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ዳዊት ተ/ማርያም
👍6❤3🥰1👏1
#አድዋ
ታሪክ በሰራ ተራራሽ ፣ በኮረብታና ተረተሩ
በሸለቆና በጋራሽ ፣በሰማይና በምድሩ
በአምባላጌ በእንጢቾ ፣ በአባ ዳዕሮ ጉብታ
በእንዳ ኪዳነምሕረት ፣ በኣዲ አቡን ምከታ
በማርያም ሸዊት ሸለቆ ፣ በአዲፍቼና ሰማያታ
በመቀሌው ምሽግ ድርሳን ፣ በእንዳየሱስ ኮረብታ
በአባ ገሪማ ፍልሚያሽ ፣ በዓድዋ እቶን ወላፈን
በሶሎዳ ተራራ ክንድሽ ፣ ግብርሽ ዛሬም ይትረፈን
የሚያሳድደን መከራ ፣ በድልሽ መጀን ይለፈን
ያስተባበርሽው ሕብረት ፣
አንድ ያደረግሽው አንድነት ፣ በጽኑ ክንዱ ይቀፈን
ባንቺ መድኃኒት እንዳን ፣ እናትነትሽ ያትርፈን
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አበባው መላኩ
ታሪክ በሰራ ተራራሽ ፣ በኮረብታና ተረተሩ
በሸለቆና በጋራሽ ፣በሰማይና በምድሩ
በአምባላጌ በእንጢቾ ፣ በአባ ዳዕሮ ጉብታ
በእንዳ ኪዳነምሕረት ፣ በኣዲ አቡን ምከታ
በማርያም ሸዊት ሸለቆ ፣ በአዲፍቼና ሰማያታ
በመቀሌው ምሽግ ድርሳን ፣ በእንዳየሱስ ኮረብታ
በአባ ገሪማ ፍልሚያሽ ፣ በዓድዋ እቶን ወላፈን
በሶሎዳ ተራራ ክንድሽ ፣ ግብርሽ ዛሬም ይትረፈን
የሚያሳድደን መከራ ፣ በድልሽ መጀን ይለፈን
ያስተባበርሽው ሕብረት ፣
አንድ ያደረግሽው አንድነት ፣ በጽኑ ክንዱ ይቀፈን
ባንቺ መድኃኒት እንዳን ፣ እናትነትሽ ያትርፈን
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ አበባው መላኩ
🔥6👍4❤2
#ባክህ_ቶሎ_አትምጣ...
ጥሩ እንዳደረጉ እንደሰሩ ደህና
ብለው ይፀልያሉ ጌታ ሆይ ቶሎ ና፣
እኔ ግን ምስኪኑ ሀጢያተኛ ልጅህ
ይችን ፀሎት ፀለይኩ ወድቄ ከደጀህ፣
አምላኬ...
ካለሁበት ሀጢያት ነብሴን ሳላወጣ
በንስሀ ፀፀት እራሴን ሳልቀጣ
ባክህ ቶሎ አትምጣ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ ዘ-ማርያም
ጥሩ እንዳደረጉ እንደሰሩ ደህና
ብለው ይፀልያሉ ጌታ ሆይ ቶሎ ና፣
እኔ ግን ምስኪኑ ሀጢያተኛ ልጅህ
ይችን ፀሎት ፀለይኩ ወድቄ ከደጀህ፣
አምላኬ...
ካለሁበት ሀጢያት ነብሴን ሳላወጣ
በንስሀ ፀፀት እራሴን ሳልቀጣ
ባክህ ቶሎ አትምጣ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ እዮብ ዘ-ማርያም
👍17❤5😭5👏4😢2
#በመንገዴ
ሁሉም ሲተራመስ……
በመታየት ዘመን ~ ሲሯሯጥ ለታይታ፤
ነብሴ ስትደበቅ……
ካንቺ ብሌን ውጪ ~ መታየቷን ፈርታ፤
ሰ'ው ስጋን ያያል ~ ነብስ ተደብቃ፤
በዚህ ሁሉ መሀል……
ነብሴን ነው 'ምታየው~ነብስሽ አጮልቃ፤
እንዲህ በመንገዴ
የዘነጠ ወጣት ~ መልካም የለበሰ፤
ጎጆ በሌለበት ~ ጎጆ የቀለሰ፤
ወዘናው ያማረ ~ ዓማርጦ የጎረሰ፤
እንዲህ በመንገዴ
ዓይናማ ሚመራ ~ የታወረ መሪ፤
አስራ አራቱ ሀብታም……
መሆኛ መንገዶች~ሚናገር መካሪ፤
እንዲህ በመንገዴ፤
በህዝብ ላቦት ላይ~ሀብቱን የዘረጋ~የሰባ ነጋዴ፤
ሁሉም ኣይኖቼ ላይ~ትምክህቱን ይሰራል፤
ቀኔን ለማጨለም………
ጉድለቴን አግዝፎ ~ ሊያሳየኝ ይጥራል፤
እግዚኦ! ላንቺ መውደድ
ይህን ሁሉ እንዳላይ……
የፍቅርሽ ግድግዳ ~ ሆኖልኛል ተገን፤
ኣቤት! ስትጋርጂኝ…………
ስቄ ነው ማልፋቸው~እግዚሃብሄር ይመስገን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ምስክር ይብራ
ሁሉም ሲተራመስ……
በመታየት ዘመን ~ ሲሯሯጥ ለታይታ፤
ነብሴ ስትደበቅ……
ካንቺ ብሌን ውጪ ~ መታየቷን ፈርታ፤
ሰ'ው ስጋን ያያል ~ ነብስ ተደብቃ፤
በዚህ ሁሉ መሀል……
ነብሴን ነው 'ምታየው~ነብስሽ አጮልቃ፤
እንዲህ በመንገዴ
የዘነጠ ወጣት ~ መልካም የለበሰ፤
ጎጆ በሌለበት ~ ጎጆ የቀለሰ፤
ወዘናው ያማረ ~ ዓማርጦ የጎረሰ፤
እንዲህ በመንገዴ
ዓይናማ ሚመራ ~ የታወረ መሪ፤
አስራ አራቱ ሀብታም……
መሆኛ መንገዶች~ሚናገር መካሪ፤
እንዲህ በመንገዴ፤
በህዝብ ላቦት ላይ~ሀብቱን የዘረጋ~የሰባ ነጋዴ፤
ሁሉም ኣይኖቼ ላይ~ትምክህቱን ይሰራል፤
ቀኔን ለማጨለም………
ጉድለቴን አግዝፎ ~ ሊያሳየኝ ይጥራል፤
እግዚኦ! ላንቺ መውደድ
ይህን ሁሉ እንዳላይ……
የፍቅርሽ ግድግዳ ~ ሆኖልኛል ተገን፤
ኣቤት! ስትጋርጂኝ…………
ስቄ ነው ማልፋቸው~እግዚሃብሄር ይመስገን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ምስክር ይብራ
🔥9👍6❤1
#የፍቅር_ሞረድ
ብእረኛ ባሎችሽ፣ አግብተው የፈቱሽ፣ ፈትተው ያላገቡሽ
ርእስ እየሰጡ፣ አሽቀንጥረው ጣሉሽ
ያገኘሁት ልብሽ፣ ከሰውዳር ተጥሎ
ተፅፎበት ነበር -ነዝናዛ -ጨቅጫቃ-ሻካራ ነሽ ተብሎ
ነዝናዛ-ጨቅጫቃ ሻካራ ነሽ ተብሎ።
ይነዝንዘኝ እቱ፣
ይጨቅጭቀኝ እቱ፣
ሽክረትሽ ጣፋጩ።
መሸረፍ መሳሉን፣ ተዪው ለጨባጩ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በረከት በላይነህ
ብእረኛ ባሎችሽ፣ አግብተው የፈቱሽ፣ ፈትተው ያላገቡሽ
ርእስ እየሰጡ፣ አሽቀንጥረው ጣሉሽ
ያገኘሁት ልብሽ፣ ከሰውዳር ተጥሎ
ተፅፎበት ነበር -ነዝናዛ -ጨቅጫቃ-ሻካራ ነሽ ተብሎ
ነዝናዛ-ጨቅጫቃ ሻካራ ነሽ ተብሎ።
ይነዝንዘኝ እቱ፣
ይጨቅጭቀኝ እቱ፣
ሽክረትሽ ጣፋጩ።
መሸረፍ መሳሉን፣ ተዪው ለጨባጩ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በረከት በላይነህ
👍7❤3
#ይናገራል_ፎቶ
ከኮሞዲኖው ላይ
ከግድግዳውም ላይ
አንቺኑ አንቺኑ ሳይ
ከኔ ዘንድ የቀረ ፥ ፎቶሽን ታቅፌ
ምላሽ ጠብቃለው
ይናገራል ፎቶ ፥ የሚል ግጥም ፅፌ
ይናገራል ፎቶ
ብጠብቃት ቀ.....ና.....ት
ብጠብቃት ሳ...ም...ን...ታ...ት
ብጠብቃት ወ..........ራ............ት
ብጠብቃት አ........መ.......ታ.........ት
እኔን ከማናገር ፥ ዝምታ በልጦባት
ከፎቶው ላይ ቀረች፤
ሳሎን እየዋለች ፥ ሳሎን እያደረች።
ወረቀቱን ቀደድኩ ፥ ግጥሙን ሰርዤው
ፎቶውን መለስኩ ፥ ከአልበሙ ሸጉጬው
እንግዲህ ምን ትሆኚ!
አልፎ አልፎ እየመጣ
እንግዳ ያይሻል ፥ እስረኛ ስትሆኚ።
ሲናፍቅሽ ኮሞዲኖው
ሲናፍቅሽ መደርደሪያው
ሲናፍቅሽ የትላንቱ
ታወሪኝ ይሆናል ፥ ልክ እንደ በፊቱ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሳሙኤል አለሙ
ከኮሞዲኖው ላይ
ከግድግዳውም ላይ
አንቺኑ አንቺኑ ሳይ
ከኔ ዘንድ የቀረ ፥ ፎቶሽን ታቅፌ
ምላሽ ጠብቃለው
ይናገራል ፎቶ ፥ የሚል ግጥም ፅፌ
ይናገራል ፎቶ
ብጠብቃት ቀ.....ና.....ት
ብጠብቃት ሳ...ም...ን...ታ...ት
ብጠብቃት ወ..........ራ............ት
ብጠብቃት አ........መ.......ታ.........ት
እኔን ከማናገር ፥ ዝምታ በልጦባት
ከፎቶው ላይ ቀረች፤
ሳሎን እየዋለች ፥ ሳሎን እያደረች።
ወረቀቱን ቀደድኩ ፥ ግጥሙን ሰርዤው
ፎቶውን መለስኩ ፥ ከአልበሙ ሸጉጬው
እንግዲህ ምን ትሆኚ!
አልፎ አልፎ እየመጣ
እንግዳ ያይሻል ፥ እስረኛ ስትሆኚ።
ሲናፍቅሽ ኮሞዲኖው
ሲናፍቅሽ መደርደሪያው
ሲናፍቅሽ የትላንቱ
ታወሪኝ ይሆናል ፥ ልክ እንደ በፊቱ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ሳሙኤል አለሙ
👍10❤4🔥4
#ጠብቂኝ_አልልም
አንድ ቀን
መጣለው ያልሽው ቃል ልቤ ከተዋህደ፥
ዘመን ጉድፉ አርጎኝ ስንቴ ጥሎኝ ሄደ፥
ስንት ዜ የጣፍኩት መናኛ ኑሮዬ ስንቴ ተቀደደ፥
በእምነት የካብኩት የልቤ የተስፋ ካብ ስንት ዜ ተናደ፥
በቀን መፈራረቅ የፀና ጉልበቴ ስንት ጊዜ ራደ፥
እኮ
ስንቴ?
ስንቴ?
ግዴለም፦
አትደንግጭ የኔ አለም፥
ይህንን ስትሰሚ አትራጅ የኔ ውድ፥
ወትሮም ዘመን ሯጭ ነው ተይው ጥሎኝ ይሂድ፥
ብቻ፦
የመምጣትሽ ወራት ከእድሜዬ ድር ረዝሞ፥
ጠባቂሽ የኔ ልብ እንዳይጎድል ታሞ፥
ናፋቂሽ የኔ አካል እንዳይጫጭ ዘሞ፥
ብዬ የሰጋሁ እለት፦
ከመጠበቅ ይልቅ መፈለግ ሲቀለው አካሌ በተራው፥
ከቤቴ የመጣሽ ለት ከቤትሽ መጥቼ እንዳላጣሽ ፈራው፥
ብቻ ያኔም ቢሆን፦
ልፈልግሽ እንጂ ጠብቂኝ አልልም፥
ልቤ ይህን ያውቃል
የመቅጠርን ያህል መጠበቅ አይቀልም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ቢንያም በሀይሉ
አንድ ቀን
መጣለው ያልሽው ቃል ልቤ ከተዋህደ፥
ዘመን ጉድፉ አርጎኝ ስንቴ ጥሎኝ ሄደ፥
ስንት ዜ የጣፍኩት መናኛ ኑሮዬ ስንቴ ተቀደደ፥
በእምነት የካብኩት የልቤ የተስፋ ካብ ስንት ዜ ተናደ፥
በቀን መፈራረቅ የፀና ጉልበቴ ስንት ጊዜ ራደ፥
እኮ
ስንቴ?
ስንቴ?
ግዴለም፦
አትደንግጭ የኔ አለም፥
ይህንን ስትሰሚ አትራጅ የኔ ውድ፥
ወትሮም ዘመን ሯጭ ነው ተይው ጥሎኝ ይሂድ፥
ብቻ፦
የመምጣትሽ ወራት ከእድሜዬ ድር ረዝሞ፥
ጠባቂሽ የኔ ልብ እንዳይጎድል ታሞ፥
ናፋቂሽ የኔ አካል እንዳይጫጭ ዘሞ፥
ብዬ የሰጋሁ እለት፦
ከመጠበቅ ይልቅ መፈለግ ሲቀለው አካሌ በተራው፥
ከቤቴ የመጣሽ ለት ከቤትሽ መጥቼ እንዳላጣሽ ፈራው፥
ብቻ ያኔም ቢሆን፦
ልፈልግሽ እንጂ ጠብቂኝ አልልም፥
ልቤ ይህን ያውቃል
የመቅጠርን ያህል መጠበቅ አይቀልም።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ቢንያም በሀይሉ
👍5❤2🔥1
#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር
ያሳለፍነዉ ሁሉ
አሁን ትዝታ እንጂ
ዉስጡ ህይወት የለም እያልሽ ላገሩ
ታወሪያለሽ አሉ
(እኔ ግን ልንገርሽ)
የሁለታችን ፍቅር
ምን እንደሚመስል. . .
እንዴት እንደነበር
በሶስት ምስክር
አሁን በቀደም ለት
የሆነ ቦታ ላይ
ድምጻችን ከፍ አርገን የሳቅንበት ቦታ
ፒያሳ አደባባይ
ድንገት
በቀደም ለት
በዛ ቦታ ስሄድ
ከሰባት ወር በፊት
ስቀሽ የነበረዉ
ያንቺ ሳቅ ተሰማኝ
መራመድ አቃተኝ
የሚገርምሽ ነገር
ያለፈ ነዉ ያልሺዉ
ትዝታ ነዉ ያልሽዉ
ፍቅርሽና ሳቅሽ
ከሰባት ወር ኋላ እንደ ወንዝ ፍሳሽ
ይሰማል ልንገርሽ
(ታዲያ ለምንድን ነዉ)
የወንዝ ዉሀ ሳቅሽ
ያለፈ ትዝታ ምናምን ነዉ ብሎ
ማንም ተራ ዘፋኝ የሚሸነግልሽ
(ይልቅ እኔን ስሚኝ)
ወደየትም ሳይሆን
ወዴትም ተመለሽ
የትም ሳትደርሺ
ጊዜን እንዳቆምነዉ
እንኳን ጊዜ ቀርቶ ሰዓት እንዳልሄደ
ደቂቃ እንዳልሄደ
አስረጂ ሊሆንሽ
ምስክር ሊሆንሽ
ከምንም አቅጣጫ. . . የትም ሳትመለሽ
አደባባይ መሀል
ከቡና ጠረን ጋር
እንደወንዝ የሚፈስ
ሳቅሽን ትሰሚያለሽ
ትዝ ይልሽ እንደሆን
ካንቺ መኖሪያ ቤት
(የመጣሁኝ ጊዜ)
የመራራቅ ናፍቆት
አስክሮን ቸኩለን
ሰማያት ለመዝለቅ
ከመሬት ላይ ወድቀን
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ከሴት ወዝሽ ጋራ
የጡትሽ ስር ሽቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ምወደዉን ሸሚዝ
ለመልበስ እርም አልኩኝ
ለብሼዉ እንዳልሄድ
ከበደኝ ጨነቀኝ
ያንቺን ጠረን ማጠብ. . .
ነፍስ የማጥፋት ያህል
ሀጥያት መስሎ ታየኝ
(የሚገርምሽ ነገር)
እስከ ዛሬ ድረስ
በመስኮቱ ዘልቆ. . .በበሬ
የሚወጣዉ የማለዳዉ ነፋስ
በሽቶሽ ጠረን ነዉ መንደሩን የሚብስ
ታስታዉሽ እንደሆን
የሆነ ቅዳሜ
የሆነ ዉብ ሆቴል
ደግሞም አትረሺዉም. . .ፍጻሜ ምሳ ነዉ
ይኼ እንኳን ትዝ ይላል
እና. . .
እኔና አንቺ ብቻ
የተቀመጥንበት ወንበር ጠረጴዛዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ. . .
እዛዉ ቤት ዳግመኛ ተመልሼ ባየዉ
የሚገርምሽ ነገር
ጻፊዉን ባላዉቅም
#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር
የሚል ጽሁፍ ሰቅለዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ
አንድ ለብቻዬ ካንድ አንቺ ናፍቆት ጋር
ነበር ለምትይዉ ለሁለታችን ፍቅር
(ምስክር ሊሆኑን)
ያኔ ሁለታችን የጠጣነዉ ወይን
ከወይንም. . . Two Ocean
እኔ የጨለጥኩት
አንቺ ያጋመስሽዉ
እኛ ያስተረፍነዉ
እስከዛሬ ድረስ
ያተረፍነዉ ማዕድ. . .
ጠርሙስና ጽዋዉ
በክብር ተቀምጧል
ማንም ሳያነሳዉ. . .ያኔ እንደነበረዉ
ታዲያ ምን ማለት ነዉ?
ፒያሳ አደባባይ
የወንዝ ዉሃ ሳቅሽ
ከቡና ጠረን ጋ
ከኔ መኖሪያ ቤት. . .
የምወደዉ ሸሚዝ ላይ
የሽቶ መአዛሽ
ከሴት ላቦትሽ ጋር
ደግሞም
እዚያ ዉብ ሆቴል ስር
ያስተረፍነዉ . . .
ማዕድ ጠርሙስና ጽዋ
አንጀት ከሚበላ
ከቆንጆ ጥቅስ ጋር
‘’#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር::’’
ነበርን እስካሁን
በመሆን እያየሽ
ሳቅሽ ፈሶ ሳያልቅ
ከምወደዉ ሸሚዝ
የሽቶ መዓዛሽ ዉብ ጠረኑ ሳይለቅ
ማዕድ ሳይነሳ ጽዋዉ ሳይታጠብ
ሦሥቱን ምስክሮች በዓይንሽ ፊት እያየሽ
ታዲያ ለምንድን ነዉ?
ያሳለፍነዉ ሁሉ
አሁን_ትዝታ_እንጂ .....
ዉስጡ_ህይወት_የለም
ብለሽ ለመንደሩ
ላገሩ ማዉራትሽ
እዉነት ለምንድን ነዉ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ኤፍሬም ስዩም
ያሳለፍነዉ ሁሉ
አሁን ትዝታ እንጂ
ዉስጡ ህይወት የለም እያልሽ ላገሩ
ታወሪያለሽ አሉ
(እኔ ግን ልንገርሽ)
የሁለታችን ፍቅር
ምን እንደሚመስል. . .
እንዴት እንደነበር
በሶስት ምስክር
አሁን በቀደም ለት
የሆነ ቦታ ላይ
ድምጻችን ከፍ አርገን የሳቅንበት ቦታ
ፒያሳ አደባባይ
ድንገት
በቀደም ለት
በዛ ቦታ ስሄድ
ከሰባት ወር በፊት
ስቀሽ የነበረዉ
ያንቺ ሳቅ ተሰማኝ
መራመድ አቃተኝ
የሚገርምሽ ነገር
ያለፈ ነዉ ያልሺዉ
ትዝታ ነዉ ያልሽዉ
ፍቅርሽና ሳቅሽ
ከሰባት ወር ኋላ እንደ ወንዝ ፍሳሽ
ይሰማል ልንገርሽ
(ታዲያ ለምንድን ነዉ)
የወንዝ ዉሀ ሳቅሽ
ያለፈ ትዝታ ምናምን ነዉ ብሎ
ማንም ተራ ዘፋኝ የሚሸነግልሽ
(ይልቅ እኔን ስሚኝ)
ወደየትም ሳይሆን
ወዴትም ተመለሽ
የትም ሳትደርሺ
ጊዜን እንዳቆምነዉ
እንኳን ጊዜ ቀርቶ ሰዓት እንዳልሄደ
ደቂቃ እንዳልሄደ
አስረጂ ሊሆንሽ
ምስክር ሊሆንሽ
ከምንም አቅጣጫ. . . የትም ሳትመለሽ
አደባባይ መሀል
ከቡና ጠረን ጋር
እንደወንዝ የሚፈስ
ሳቅሽን ትሰሚያለሽ
ትዝ ይልሽ እንደሆን
ካንቺ መኖሪያ ቤት
(የመጣሁኝ ጊዜ)
የመራራቅ ናፍቆት
አስክሮን ቸኩለን
ሰማያት ለመዝለቅ
ከመሬት ላይ ወድቀን
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ከሴት ወዝሽ ጋራ
የጡትሽ ስር ሽቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ምወደዉን ሸሚዝ
ለመልበስ እርም አልኩኝ
ለብሼዉ እንዳልሄድ
ከበደኝ ጨነቀኝ
ያንቺን ጠረን ማጠብ. . .
ነፍስ የማጥፋት ያህል
ሀጥያት መስሎ ታየኝ
(የሚገርምሽ ነገር)
እስከ ዛሬ ድረስ
በመስኮቱ ዘልቆ. . .በበሬ
የሚወጣዉ የማለዳዉ ነፋስ
በሽቶሽ ጠረን ነዉ መንደሩን የሚብስ
ታስታዉሽ እንደሆን
የሆነ ቅዳሜ
የሆነ ዉብ ሆቴል
ደግሞም አትረሺዉም. . .ፍጻሜ ምሳ ነዉ
ይኼ እንኳን ትዝ ይላል
እና. . .
እኔና አንቺ ብቻ
የተቀመጥንበት ወንበር ጠረጴዛዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ. . .
እዛዉ ቤት ዳግመኛ ተመልሼ ባየዉ
የሚገርምሽ ነገር
ጻፊዉን ባላዉቅም
#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር
የሚል ጽሁፍ ሰቅለዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ
አንድ ለብቻዬ ካንድ አንቺ ናፍቆት ጋር
ነበር ለምትይዉ ለሁለታችን ፍቅር
(ምስክር ሊሆኑን)
ያኔ ሁለታችን የጠጣነዉ ወይን
ከወይንም. . . Two Ocean
እኔ የጨለጥኩት
አንቺ ያጋመስሽዉ
እኛ ያስተረፍነዉ
እስከዛሬ ድረስ
ያተረፍነዉ ማዕድ. . .
ጠርሙስና ጽዋዉ
በክብር ተቀምጧል
ማንም ሳያነሳዉ. . .ያኔ እንደነበረዉ
ታዲያ ምን ማለት ነዉ?
ፒያሳ አደባባይ
የወንዝ ዉሃ ሳቅሽ
ከቡና ጠረን ጋ
ከኔ መኖሪያ ቤት. . .
የምወደዉ ሸሚዝ ላይ
የሽቶ መአዛሽ
ከሴት ላቦትሽ ጋር
ደግሞም
እዚያ ዉብ ሆቴል ስር
ያስተረፍነዉ . . .
ማዕድ ጠርሙስና ጽዋ
አንጀት ከሚበላ
ከቆንጆ ጥቅስ ጋር
‘’#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር::’’
ነበርን እስካሁን
በመሆን እያየሽ
ሳቅሽ ፈሶ ሳያልቅ
ከምወደዉ ሸሚዝ
የሽቶ መዓዛሽ ዉብ ጠረኑ ሳይለቅ
ማዕድ ሳይነሳ ጽዋዉ ሳይታጠብ
ሦሥቱን ምስክሮች በዓይንሽ ፊት እያየሽ
ታዲያ ለምንድን ነዉ?
ያሳለፍነዉ ሁሉ
አሁን_ትዝታ_እንጂ .....
ዉስጡ_ህይወት_የለም
ብለሽ ለመንደሩ
ላገሩ ማዉራትሽ
እዉነት ለምንድን ነዉ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ኤፍሬም ስዩም
❤18👍6👏2💔2🔥1
#ሴትነት
ሴትነት በእኔ እምነት
ባጭር ቃል ውሀነት
ወሀ ሁኖ መኖር
ኖሮ ሁሉን ማኖር
ህይወትን ማሳመር
በዚህ በህዋ አለም
ውሀን የሚመስል
ያልተፈታ ረቂቅ
ከሁሉ የሚልቅ
የሁሉ መሰረት
የሚያኖር ደግነት
ሁሉን እንኩ ማለት
ፍቅር ለጋስነት
ማንቃት ማነቃቃት ማብቃት
የለ እንደ እናትነት
የለ እንደ ሴትነት
ውሀነት እናትነት ሴትነት
ሰው የመሆን ትርጉም ሰው የመሆን ልኬት
ለፈጣሪ ታምኖ አደራ መሰጠት
ታጭቶ ለሚስትነት ታጭቶ ለእናትነት
ይች ናት የእኔ ሴት ይች ናት የእኔ እናት
በልቤ በአካሌ በአምሮዬ ሳልኳት
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
መልካም የሴቶች ቀን
ሴትነት በእኔ እምነት
ባጭር ቃል ውሀነት
ወሀ ሁኖ መኖር
ኖሮ ሁሉን ማኖር
ህይወትን ማሳመር
በዚህ በህዋ አለም
ውሀን የሚመስል
ያልተፈታ ረቂቅ
ከሁሉ የሚልቅ
የሁሉ መሰረት
የሚያኖር ደግነት
ሁሉን እንኩ ማለት
ፍቅር ለጋስነት
ማንቃት ማነቃቃት ማብቃት
የለ እንደ እናትነት
የለ እንደ ሴትነት
ውሀነት እናትነት ሴትነት
ሰው የመሆን ትርጉም ሰው የመሆን ልኬት
ለፈጣሪ ታምኖ አደራ መሰጠት
ታጭቶ ለሚስትነት ታጭቶ ለእናትነት
ይች ናት የእኔ ሴት ይች ናት የእኔ እናት
በልቤ በአካሌ በአምሮዬ ሳልኳት
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
መልካም የሴቶች ቀን
❤25👍4❤🔥1👏1
#ለጤዛ_ተዋድቀን
"እድሚያችን ሰባ ነው ቢበዛም ሰማንያ"
ይህም ኑሮ ሆኖ ጠዋት ማታ ፍልሚያ
አንዱ ካንዱ ጥዋ: ጥቃት የቀመሰ
በየደጃፉ ላይ ምሽግ እየማሰ
ጦር እንደ ቄጤማ እየነሰነሰ
መንደሩን ሸንሽኖ ባጋም እሾህ ቅጥር
ወገን እያስለየ ባሰለፈን ቁጥር
ጤናችን ሲሸረፍ
ቀናችን ሲዘረፍ
የት ሸሽተን እንትረፍ
የትገብተን እንረፍ?
በዶፍ ዝናብ አገር ለጤዛ ተዋድቀን
ሰላም እንደራበን ደስታ እንደናፈቀን
ትግላችን ሰልፋችን ያከትማል አንድቀን::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዪም
"እድሚያችን ሰባ ነው ቢበዛም ሰማንያ"
ይህም ኑሮ ሆኖ ጠዋት ማታ ፍልሚያ
አንዱ ካንዱ ጥዋ: ጥቃት የቀመሰ
በየደጃፉ ላይ ምሽግ እየማሰ
ጦር እንደ ቄጤማ እየነሰነሰ
መንደሩን ሸንሽኖ ባጋም እሾህ ቅጥር
ወገን እያስለየ ባሰለፈን ቁጥር
ጤናችን ሲሸረፍ
ቀናችን ሲዘረፍ
የት ሸሽተን እንትረፍ
የትገብተን እንረፍ?
በዶፍ ዝናብ አገር ለጤዛ ተዋድቀን
ሰላም እንደራበን ደስታ እንደናፈቀን
ትግላችን ሰልፋችን ያከትማል አንድቀን::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዪም
👍7🔥6❤3
#የባከነ_ሌሊት!!!!
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ።
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ ወይ ፅድቅ አላፈራሁ።
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው።
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ።
አንዲት ሴት- አዳሪ ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ።
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ።
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ ወይ ፅድቅ አላፈራሁ።
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው።
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ።
አንዲት ሴት- አዳሪ ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ።
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም
👍17👏7❤3🔥3
#መለያየት_ማለት
ይኸው ትላንትና ከትላንትም በስትያ
ያዩሽ ሰዎች ሁላ ከእቅፌ ጉያ
ዛሬን ተራርቀን ብቻዬን ቢያዩኝ
ከድታዋለች ብለው ከንፈር መጠጡልኝ
እባክሽ የኔ አለም!! ፈጥነሽ ንገሪያቸው
ሴትን ማፍቀር እንጂ ማባበል አይችልም ብለሽ አስረጃቸው
ለኔ ና ላንቺ እኮ መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት.....
ያለመተያየት መፋቀርም ማለት
በምናልባት ተስፋ የምትቆም ህይወት
ዘወትር....ዘወትር ምናልባት
ምናልባት እያለች የምትኖር ህይወት
በተስፋዋ መሀል ጥቂት ደስታ አላት
በታስፋችን መሀል መፋቀሩ ካለን
ናፍቆት አካል ገዝቶ እንተያያለን
ብለሽ ንገሪያቸው....
ልቤና ልቦናው ተጣብቀዋል በያችቸው
እንጂ በኛ መሀል መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት....
በሩቅ መሰማማት በድምፅ አልባ ቃላት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ኤፍሬም ስዩም
ይኸው ትላንትና ከትላንትም በስትያ
ያዩሽ ሰዎች ሁላ ከእቅፌ ጉያ
ዛሬን ተራርቀን ብቻዬን ቢያዩኝ
ከድታዋለች ብለው ከንፈር መጠጡልኝ
እባክሽ የኔ አለም!! ፈጥነሽ ንገሪያቸው
ሴትን ማፍቀር እንጂ ማባበል አይችልም ብለሽ አስረጃቸው
ለኔ ና ላንቺ እኮ መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት.....
ያለመተያየት መፋቀርም ማለት
በምናልባት ተስፋ የምትቆም ህይወት
ዘወትር....ዘወትር ምናልባት
ምናልባት እያለች የምትኖር ህይወት
በተስፋዋ መሀል ጥቂት ደስታ አላት
በታስፋችን መሀል መፋቀሩ ካለን
ናፍቆት አካል ገዝቶ እንተያያለን
ብለሽ ንገሪያቸው....
ልቤና ልቦናው ተጣብቀዋል በያችቸው
እንጂ በኛ መሀል መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት....
በሩቅ መሰማማት በድምፅ አልባ ቃላት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ኤፍሬም ስዩም
👍25❤1
#አቅፌ_ልሸኘው
ህልሜን ካመከነ ማገሬን አላልቶ፥
ቃሉን ካፈረሰ አደራውን በልቶ፥
መውደዴን በመውደድ ካልመለሰች ልቡ፥
ፍቅሬን ረግጦ መሄድ ከሆነማ ሀሳቡ፥
ክፉ ሳልናገር መጥፎ ቃል ሳይወጣኝ፥
ፊቴን ሳላጠቁር ማኩረፍም ሳይቃጣኝ፥
ደረቴን ሳልደቃ አመድ ሳልነሰንስ፥
ከመሬት ሳልተኛ ጥቁር ልብስም ሳለብስ፥
አንገቴን አልደፋ ከቶ ለምን ብዬ፥
ቀን ጨለመብኝ አልል አይፈስም እንባዬ።
ጌታ ካልፈቀደ ካልሰጠኝ አጣፍጦ፥
መች በግድ ይሆናል ፍቅርን ተለማምጦ።
ደስታው ደስታዬ ነው ሀዘኑም ሀዘኔ፥
ሀሴት ካደረገ በመራቁ ካይኔ፥
መሄድ ከኔ መሸሽ ከሆነ ሚመኘው፥
ላፍታ አይከፋብኝ
ሁሌ እያፈቀርኩት አቅፌ ልሸኘው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
ህልሜን ካመከነ ማገሬን አላልቶ፥
ቃሉን ካፈረሰ አደራውን በልቶ፥
መውደዴን በመውደድ ካልመለሰች ልቡ፥
ፍቅሬን ረግጦ መሄድ ከሆነማ ሀሳቡ፥
ክፉ ሳልናገር መጥፎ ቃል ሳይወጣኝ፥
ፊቴን ሳላጠቁር ማኩረፍም ሳይቃጣኝ፥
ደረቴን ሳልደቃ አመድ ሳልነሰንስ፥
ከመሬት ሳልተኛ ጥቁር ልብስም ሳለብስ፥
አንገቴን አልደፋ ከቶ ለምን ብዬ፥
ቀን ጨለመብኝ አልል አይፈስም እንባዬ።
ጌታ ካልፈቀደ ካልሰጠኝ አጣፍጦ፥
መች በግድ ይሆናል ፍቅርን ተለማምጦ።
ደስታው ደስታዬ ነው ሀዘኑም ሀዘኔ፥
ሀሴት ካደረገ በመራቁ ካይኔ፥
መሄድ ከኔ መሸሽ ከሆነ ሚመኘው፥
ላፍታ አይከፋብኝ
ሁሌ እያፈቀርኩት አቅፌ ልሸኘው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
👏13❤6😭5👍1
#እስከዚህም_ፍቅርሽ
እስከዚህም ፍቅርሽ:
ከሰንደል ጭስ በላይ:
ደምቆ የማይገዝፈው:
ምንሽን ልፃፈው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ
በጧት የረገፈው:
ከዕድሜ እሬሳ ውጭ
ዋኝታ ምኑን ታውጣው
ነብሴ ከባለፈው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ:
ዘመን ያሳረጠው:
ምኑን አስታውሼ
ሣጌን እየማኩኝ :
እንባዬን ልዋጠው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ
ሲነድፍ ያለሰንኮፍ:
መታሁ ቢልም ለኮፍ:
እንኳንና ሰምበር
ስምሽስ ማን ነበር ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ኑረዲን ኢሳ
እስከዚህም ፍቅርሽ:
ከሰንደል ጭስ በላይ:
ደምቆ የማይገዝፈው:
ምንሽን ልፃፈው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ
በጧት የረገፈው:
ከዕድሜ እሬሳ ውጭ
ዋኝታ ምኑን ታውጣው
ነብሴ ከባለፈው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ:
ዘመን ያሳረጠው:
ምኑን አስታውሼ
ሣጌን እየማኩኝ :
እንባዬን ልዋጠው ?
እስከዚህም ፍቅርሽ
ሲነድፍ ያለሰንኮፍ:
መታሁ ቢልም ለኮፍ:
እንኳንና ሰምበር
ስምሽስ ማን ነበር ?
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ኑረዲን ኢሳ
👍10❤2