''ኧረ እሰየው ተመስገን ተመስገን አዲስ ፀሐይ ወጣ
ሞት የለህም ከእንግዲህ ችግር ምናምንቴ በል ከቤቴ ውጣ
ከእንግዲህ አትችለኝም ጠንካራ ነኝ እኔ
ሰንቄያለሁና ከብረት የላቀ የብርሃን ወኔ
እስከመቼ ነፍሴ ከእውነት ቤት እርቃ
ዘልቀህ ላታዛልቅ ካንተ ጋር ተጣብቃ
ከሚወፍር በኃጥያት እንጀራ ገላዬ
መርጫለሁ መክሳት በንጹህ ህሊናዬ
ልታለማምደኝ እርኩሰት
ተጠቅመህ በቴሌቭዢን መስኮት
ባህል ሐይማኖቴን እንድረሳ
ሞክረሃል ተሞልተህ ብዙ ተስፋ
እርግጥ እልፍ አእላፎች ይዘሃል
እንደምትገዛም እቺን ምድር ተጽፏል
ግን እብሪትህ በጣም አየለና
እቺን ቁድስ አገር አዓይኑ አየና
ባምናው ቤቴ ላይ ነግሰህ ስታሸኝ ኖረሃል ያ ክንድህ በርትቶ
‘ምታለብሰኝ ያለም ካባ የሚያልፍ የሚነጥፍ የተንኮል ድሪቶ
ከእንግዲህ ግን ይብቃ ጠንካራ ነኝ እኔ
ሰንቄያለሁና ከብረት የላቀ የብርሃን ወኔ
. . . ''
በቃ በቃ - አማን ኪያሞ / Aman Kiyamo
#አማን_ኪያሞ #Aman_Kiyamo #ግጥምሲጥም #gitemsitem #ግጥማዊቅዳሜ #poeticsaturdays
ሞት የለህም ከእንግዲህ ችግር ምናምንቴ በል ከቤቴ ውጣ
ከእንግዲህ አትችለኝም ጠንካራ ነኝ እኔ
ሰንቄያለሁና ከብረት የላቀ የብርሃን ወኔ
እስከመቼ ነፍሴ ከእውነት ቤት እርቃ
ዘልቀህ ላታዛልቅ ካንተ ጋር ተጣብቃ
ከሚወፍር በኃጥያት እንጀራ ገላዬ
መርጫለሁ መክሳት በንጹህ ህሊናዬ
ልታለማምደኝ እርኩሰት
ተጠቅመህ በቴሌቭዢን መስኮት
ባህል ሐይማኖቴን እንድረሳ
ሞክረሃል ተሞልተህ ብዙ ተስፋ
እርግጥ እልፍ አእላፎች ይዘሃል
እንደምትገዛም እቺን ምድር ተጽፏል
ግን እብሪትህ በጣም አየለና
እቺን ቁድስ አገር አዓይኑ አየና
ባምናው ቤቴ ላይ ነግሰህ ስታሸኝ ኖረሃል ያ ክንድህ በርትቶ
‘ምታለብሰኝ ያለም ካባ የሚያልፍ የሚነጥፍ የተንኮል ድሪቶ
ከእንግዲህ ግን ይብቃ ጠንካራ ነኝ እኔ
ሰንቄያለሁና ከብረት የላቀ የብርሃን ወኔ
. . . ''
በቃ በቃ - አማን ኪያሞ / Aman Kiyamo
#አማን_ኪያሞ #Aman_Kiyamo #ግጥምሲጥም #gitemsitem #ግጥማዊቅዳሜ #poeticsaturdays