የምስል ጥበብ ስነ-ግጥምን ስታውቃት. . . !
When photography meets poetry...!
@ribkiphoto
#ርብቃሲሳይ #ribkasisay
#ግጥምሲጥም #gitemsitem
When photography meets poetry...!
@ribkiphoto
#ርብቃሲሳይ #ribkasisay
#ግጥምሲጥም #gitemsitem
አስተምረኝ
( ሠይፈ ወርቅ)
አስተምረኝ - ከማዕበል ጋር መደነስ
አሠልጥነኝ - በእሳት ላይ መመላለስ
ስሬን አጥብቅ - እንድታጠፍ ለነፋሳት
ልቤን ግራው - ሲቀጠቀጥ እንዲከፈት
ከዶፍ
ከጎርፍ
ከጣይ፣ ከቁር
ከበረድ ጋር
ከውሽንፍር
ከመብረቅ ጋር እንድጨፍር
ውብ ህይወትን እንድዘምር
አስተምረኝ!
ያለነፋስ - ዋሽንት በድን
ሳይገረፍ - ክራር አይድን
ሳይመታ - ሙት ከበሮ
ለሰከነ - ለነፍስ ጆሮ
በህመም ውስጥ ተቀምሮ
ውብ ዜማ አለ በተፈጥሮ
አስተምረኝ
የማየትን ጥልቀት፣ ርቀት
አሠልጥነኝ
የማድመጥን ስር መሠረት
በሸለቆ
በከፍታ፣ በቁልቀለት
ህመም ሳልሸሽ
ያለህመም ልኑርበት
#አስተምረኝ።
#ምራኝ!
#ማረኝ!
( ሠይፈ ወርቅ )
#አስተምረኝ
#ሰይፉወርቁ #ሰይፈወርቅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
( ሠይፈ ወርቅ)
አስተምረኝ - ከማዕበል ጋር መደነስ
አሠልጥነኝ - በእሳት ላይ መመላለስ
ስሬን አጥብቅ - እንድታጠፍ ለነፋሳት
ልቤን ግራው - ሲቀጠቀጥ እንዲከፈት
ከዶፍ
ከጎርፍ
ከጣይ፣ ከቁር
ከበረድ ጋር
ከውሽንፍር
ከመብረቅ ጋር እንድጨፍር
ውብ ህይወትን እንድዘምር
አስተምረኝ!
ያለነፋስ - ዋሽንት በድን
ሳይገረፍ - ክራር አይድን
ሳይመታ - ሙት ከበሮ
ለሰከነ - ለነፍስ ጆሮ
በህመም ውስጥ ተቀምሮ
ውብ ዜማ አለ በተፈጥሮ
አስተምረኝ
የማየትን ጥልቀት፣ ርቀት
አሠልጥነኝ
የማድመጥን ስር መሠረት
በሸለቆ
በከፍታ፣ በቁልቀለት
ህመም ሳልሸሽ
ያለህመም ልኑርበት
#አስተምረኝ።
#ምራኝ!
#ማረኝ!
( ሠይፈ ወርቅ )
#አስተምረኝ
#ሰይፉወርቁ #ሰይፈወርቅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
ታዳሚዎቹም አቅራቢዎቹም ወደነዋል፣ ጥሞናል፣ ድገሙንም ብለዋል!
የታደማችሁም ያቀረባችሁም ተመስገኑልን! መምጣት ሳትችሉ ብትቀሩም ድጋፋችሁንና ሀሳባችሁን የቸራችሁንም ክበሩ!
ቦታውን ሳታገኙት ቀርታችሁ መምጣት ያልቻላችሁ ደሞ ይቅር በሉን!
ቀጣዩ እንዳያመልጣችሁ ለታህሳስ 10 ቀጠሮ ያዙ ገጾቻችንንም ተከታተሉ
https://t.me/seifetemam
#ኤልያስ_ሽታሁን #ምግባር_ሲራጅ #አንዱ_ጌታቸው #ሌላ_ምስክር #ረቂቅ_አሰገደው
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
ህዳር 12 ከተካሄደው የመጀመሪያው የግጥም ሲጥም ዝግጅት ላይ የተወሰዱ ምስሎች
📷 @AnimaHela
የታደማችሁም ያቀረባችሁም ተመስገኑልን! መምጣት ሳትችሉ ብትቀሩም ድጋፋችሁንና ሀሳባችሁን የቸራችሁንም ክበሩ!
ቦታውን ሳታገኙት ቀርታችሁ መምጣት ያልቻላችሁ ደሞ ይቅር በሉን!
ቀጣዩ እንዳያመልጣችሁ ለታህሳስ 10 ቀጠሮ ያዙ ገጾቻችንንም ተከታተሉ
https://t.me/seifetemam
#ኤልያስ_ሽታሁን #ምግባር_ሲራጅ #አንዱ_ጌታቸው #ሌላ_ምስክር #ረቂቅ_አሰገደው
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
ህዳር 12 ከተካሄደው የመጀመሪያው የግጥም ሲጥም ዝግጅት ላይ የተወሰዱ ምስሎች
📷 @AnimaHela
https://www.youtube.com/watch?v=CZ_sjCXYiQ8
ይህን Amazing Addis የተሰኘ ቤት ብትከታተሉ ግጥሞችን እንዲህ ገጣሚዎቹ እራሳቸው አሳምረው ሲያነቡት ታገኛላችሁ እና እንጠቁማችሁ - ግቡ።
መታሰቢያ እታለማው በአሜዚንግ አዲስ
#መታሰቢያ_እታለማው #አሜዚንግ_አዲስ #ግጥምሲጥም
ይህን Amazing Addis የተሰኘ ቤት ብትከታተሉ ግጥሞችን እንዲህ ገጣሚዎቹ እራሳቸው አሳምረው ሲያነቡት ታገኛላችሁ እና እንጠቁማችሁ - ግቡ።
መታሰቢያ እታለማው በአሜዚንግ አዲስ
#መታሰቢያ_እታለማው #አሜዚንግ_አዲስ #ግጥምሲጥም
YouTube
ገጣሚት መታሰቢያ እታለማው " ተረት ተረት "
የስዊድን መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ የኪነ-ጥበብ እና የባህል ባለሙያዎችን ለመደገፍ እና ለማጠናከር የሚረዳ አዲስ ከ3-5 ዓመት የሚቆይ መርሃ ግብር በማዘጋጀት ላይ ሲሆን ለዚህም ዘለቄታዊነት ያለው እና ለእርስዎ ጠቃሚ የሆነ ፕሮግራም ለማዘጋጀት የእርስዎን ጉልህ አስተያየትና እና ምልከታ እንፈልጋለን ፡፡
ስለሆነም ይህንን የዳሰሳ ጥናት በጥበብ እና ባህል ሙያ ዘርፍ ያለውን ተግዳሮትና ክፍተት ለማሻሻል ለዘርፉ የሚያስፈልገውን ለማሟላት እርሶ መፍትሔ ይሆናል ብለው የሚሰጡንን ሀሳብና አመለካከት እያደነቅን ለትብብርዎ ከልብ እናመሰግናለን!
ጥናት (አማርኛ): shorturl.at/jtyK2
The Swedish government is developing a new 3-5 year-long programme to help support and strengthen art and culture practitioners in Ethiopia and we need your significant feedback and perspective to design a programme that has long-term impact and is relevant for You.
We would therefore very much appreciate if you could fill out this survey and provide your perspective on needs, gaps and possible solutions to improve your condition as an art and culture practitioner.
SURVEY (ENGLISH): shorturl.at/jmpyA
#survey #swidish #creatives #art #culture #ግጥምሲጥም
ስለሆነም ይህንን የዳሰሳ ጥናት በጥበብ እና ባህል ሙያ ዘርፍ ያለውን ተግዳሮትና ክፍተት ለማሻሻል ለዘርፉ የሚያስፈልገውን ለማሟላት እርሶ መፍትሔ ይሆናል ብለው የሚሰጡንን ሀሳብና አመለካከት እያደነቅን ለትብብርዎ ከልብ እናመሰግናለን!
ጥናት (አማርኛ): shorturl.at/jtyK2
The Swedish government is developing a new 3-5 year-long programme to help support and strengthen art and culture practitioners in Ethiopia and we need your significant feedback and perspective to design a programme that has long-term impact and is relevant for You.
We would therefore very much appreciate if you could fill out this survey and provide your perspective on needs, gaps and possible solutions to improve your condition as an art and culture practitioner.
SURVEY (ENGLISH): shorturl.at/jmpyA
#survey #swidish #creatives #art #culture #ግጥምሲጥም
Google Docs
ባህላዊ እና የፈጠራ ኢንደስትሪ በኢትዮጵያ
በ ሲዳ (የሲውዲን ዓለም አቀፍ ልማት ትብብር ኤጀንሲ) በተደረገልን እርዳታ በኪነጥበብና ባህል ዘርፍ ቁልፍ ከሆኑ የሲውዲን ሀገር አቀፍ ኤጀንሲዎች ጋር በመተባበር የሲውዲን ኪነጥበብ እርዳታ ድርጅት ኮሚቴ ከ3-5 አመት የሚቆይና የኢትዮጵያን ኪነጥበብና ባህል የሚረዳ መርሃግብር እያጎለበተ ይገኛል። ይህም በዋናነት የሚተገበረው በኢትዮጵያ የጥበብ ማህበረሰብ የተለያዩ ተሳታፊዎች በማማከር ነው። የእናንተ…
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem pinned «የስዊድን መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ የኪነ-ጥበብ እና የባህል ባለሙያዎችን ለመደገፍ እና ለማጠናከር የሚረዳ አዲስ ከ3-5 ዓመት የሚቆይ መርሃ ግብር በማዘጋጀት ላይ ሲሆን ለዚህም ዘለቄታዊነት ያለው እና ለእርስዎ ጠቃሚ የሆነ ፕሮግራም ለማዘጋጀት የእርስዎን ጉልህ አስተያየትና እና ምልከታ እንፈልጋለን ፡፡ ስለሆነም ይህንን የዳሰሳ ጥናት በጥበብ እና ባህል ሙያ ዘርፍ ያለውን ተግዳሮትና ክፍተት ለማሻሻል…»
እወቂብኝ
ከማላቃቸው መልኮች ላይ ሳቆችሽን ዘግኛለሁ
ለራሴ
በልቤ መንገዶች ላይ በእግሬ ብዙ ተጉዣለሁ
ለነፍሴ
'ምናለውና አይኗ!'
'ትቅራ!'
ብዬም ፍቅር ስቀራ. . .
ብርሃን ተምታቶብኛል
. . .
ብራ ቀኔን ብገብር ምን ይረባታል ማለቴስ
ሰማይ ልቧ ላይ ብበራ ምኗ ነዶ ምኔ ሊጤስ...?
. . .
እኔ ተወርዋሪ ነኝ
ምኔ ጋር እንደጨላለምኩ ምኑ ታወቀኝ ገና
ዥው ብዬ እስከማልፍሽ ይጎበኘኛል ወና
አንቺ ቅጽበት የምትይዢ
ቦግ ብዬ ሳልፍብሽ በብርሃኔ የምትፈዢ
ምኞት 'ምትናዘዢ
ፍቅር የምታፍዢ
እኔ ምኑ ጋር በርቼ ምኔን ጽልመት እንደወጋኝ
ምኑም ምኑም የማይገባኝ
ተወርዋሪ
በሪ
ሰይፍ ነኝ
እወቂብኝ!
እወቂብኝ!
ሰይፈ ተማም
#ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
ከማላቃቸው መልኮች ላይ ሳቆችሽን ዘግኛለሁ
ለራሴ
በልቤ መንገዶች ላይ በእግሬ ብዙ ተጉዣለሁ
ለነፍሴ
'ምናለውና አይኗ!'
'ትቅራ!'
ብዬም ፍቅር ስቀራ. . .
ብርሃን ተምታቶብኛል
. . .
ብራ ቀኔን ብገብር ምን ይረባታል ማለቴስ
ሰማይ ልቧ ላይ ብበራ ምኗ ነዶ ምኔ ሊጤስ...?
. . .
እኔ ተወርዋሪ ነኝ
ምኔ ጋር እንደጨላለምኩ ምኑ ታወቀኝ ገና
ዥው ብዬ እስከማልፍሽ ይጎበኘኛል ወና
አንቺ ቅጽበት የምትይዢ
ቦግ ብዬ ሳልፍብሽ በብርሃኔ የምትፈዢ
ምኞት 'ምትናዘዢ
ፍቅር የምታፍዢ
እኔ ምኑ ጋር በርቼ ምኔን ጽልመት እንደወጋኝ
ምኑም ምኑም የማይገባኝ
ተወርዋሪ
በሪ
ሰይፍ ነኝ
እወቂብኝ!
እወቂብኝ!
ሰይፈ ተማም
#ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
ሰው በሞላው ሃገር
ሰው ባረፈ ቁጥር ትንሽ እሞታለሁ
አገር 'ሚያሰድብ ያገር ሰው እያየሁ
በከሰሩ ቁጥር ትንሽ እረክሳለሁ
በሰከሩ ቁጥር ትንሽ አከስራለሁ
በረከሱ ቁጥር ትንሽ እሰክራለሁ
በከሰሱ ቁጥር ዶሴ አቀብላለሁ
ሰው በሞላው ሃገር
የሰው ያለህ እላለው
ሲመርቁኝ አሜን አልል
ሲነጅሱኝ የምነቅል
ስንቀለቀል የማልነድድ
ሳልለኮስ የምከስል
ሰው በሞላው ሃገር ያውም የረገፈ
አፈር ነካው ዘሬን ጸድቆም ተገዘፈ
ሃሳቤም ተምቧችሮ እልፍ ረፈረፈ
ሆዴም ልብ የባሰው
ልቤም ሆድ የባሰው
ሆኖት እያረፈ
ሰይፈ ተማም
#ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
ሰው ባረፈ ቁጥር ትንሽ እሞታለሁ
አገር 'ሚያሰድብ ያገር ሰው እያየሁ
በከሰሩ ቁጥር ትንሽ እረክሳለሁ
በሰከሩ ቁጥር ትንሽ አከስራለሁ
በረከሱ ቁጥር ትንሽ እሰክራለሁ
በከሰሱ ቁጥር ዶሴ አቀብላለሁ
ሰው በሞላው ሃገር
የሰው ያለህ እላለው
ሲመርቁኝ አሜን አልል
ሲነጅሱኝ የምነቅል
ስንቀለቀል የማልነድድ
ሳልለኮስ የምከስል
ሰው በሞላው ሃገር ያውም የረገፈ
አፈር ነካው ዘሬን ጸድቆም ተገዘፈ
ሃሳቤም ተምቧችሮ እልፍ ረፈረፈ
ሆዴም ልብ የባሰው
ልቤም ሆድ የባሰው
ሆኖት እያረፈ
ሰይፈ ተማም
#ሰይፈተማም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
Forwarded from Roma Publishing and Books - ሮማን ተወልደብርሃን
ሥራችንን በአዲስ መልክ ጀምረናል ሳይሆን አዲሱ ሥራችንን ጀምረናል።
አእምሮ: የበላውን የማይረሳ፣ ባላመጠ መጠን የማይደክም፣ ባመነዠከ ቁጥር የሚሰላ የሚጠነክር ነው፡፡ ሆድማ ላሽ ነው፤ ቅድም የበላውን ምጥን ረስቶ እንቶፈንቶ ሲያቀርቡለት ስልቅጥ ነው፡፡
ለዚህ ውለታ አይረሴ አእምሮ መጽሐፍትን ለራሳችሁ እንዲሁም እንደ ሀብል፣ እንደ ቀለበት አሸብርቆ ለወዳጅ እና ለዘመድ ለመስጠት ስትፈልጉ፣ እኛ አለን።
Book Bouquet/ የመጽሐፍት ጥምር
ለየትኛውም ዝግጅት መጻሕፍትን በስጦታ መስጠት ለምትሹ የመጻሕፍት ጥምር አዘጋጅተን፥ ሊደርስ የምትፈልጉበት ቦታ ላይ ለማድረስ ተዘጋጅተን እየጠበቅናችሁ ነው፡፡
ለእንዲህ አይነት ሰው ምን መጽሐፍ ልስጥ ብትሉም፣ ግዴለም እኛ የሚገባቸውን እና የሚመጥናቸውን ዝርዝር አውጥተን እና ከእናንተ ጋር ተማክረን ለመስጠት ዝግጁ ነን፡፡
**ደራሲያን ወዳጆች ደግሞ ልዩ በደራሲያን የተፈረሙ፣ የተመረጡ መጽሐፍትን አዘጋጅተናል።
-ከአዲስ አበባ፣ በተጨማሪ
--ባህር ዳር እና አማራ ክልል አገልግሎት እንሰጣለን።
--ባህር ማዶም።
እዘዙን እንታዘዛለን
ታዘን ያሉበት ድረስ እናደርሳለን!
በኢንቦክስ ጻፉልን።
በ0993514883 ደውሉልን።
_ _
አእምሮ: የበላውን የማይረሳ፣ ባላመጠ መጠን የማይደክም፣ ባመነዠከ ቁጥር የሚሰላ የሚጠነክር ነው፡፡ ሆድማ ላሽ ነው፤ ቅድም የበላውን ምጥን ረስቶ እንቶፈንቶ ሲያቀርቡለት ስልቅጥ ነው፡፡
ለዚህ ውለታ አይረሴ አእምሮ መጽሐፍትን ለራሳችሁ እንዲሁም እንደ ሀብል፣ እንደ ቀለበት አሸብርቆ ለወዳጅ እና ለዘመድ ለመስጠት ስትፈልጉ፣ እኛ አለን።
Book Bouquet/ የመጽሐፍት ጥምር
ለየትኛውም ዝግጅት መጻሕፍትን በስጦታ መስጠት ለምትሹ የመጻሕፍት ጥምር አዘጋጅተን፥ ሊደርስ የምትፈልጉበት ቦታ ላይ ለማድረስ ተዘጋጅተን እየጠበቅናችሁ ነው፡፡
ለእንዲህ አይነት ሰው ምን መጽሐፍ ልስጥ ብትሉም፣ ግዴለም እኛ የሚገባቸውን እና የሚመጥናቸውን ዝርዝር አውጥተን እና ከእናንተ ጋር ተማክረን ለመስጠት ዝግጁ ነን፡፡
**ደራሲያን ወዳጆች ደግሞ ልዩ በደራሲያን የተፈረሙ፣ የተመረጡ መጽሐፍትን አዘጋጅተናል።
-ከአዲስ አበባ፣ በተጨማሪ
--ባህር ዳር እና አማራ ክልል አገልግሎት እንሰጣለን።
--ባህር ማዶም።
እዘዙን እንታዘዛለን
ታዘን ያሉበት ድረስ እናደርሳለን!
በኢንቦክስ ጻፉልን።
በ0993514883 ደውሉልን።
_ _

