አለ? ምልክት?
ላለመኖር ማስረገጫ
መኖርን በአንጻር ማስጌጫ?
ይገኛል ትርጉም?
ነፋስ ከሚወዘውዘው
ዐይኔ ከሚያየው ጀርባ
የለም እያልኩሽ ስላለው?
በማለም ሽንቁር ሾልኬ
ግልገል ሞቴን ተመርኩዤ
ከሐሳብ ቁልል መሐል
አለመኖርን መዝዤ
ስመላለስበት ባነጋ
(ሳውቅ)
ማመኔን ሳይደገፍ
መካድ ብቻውን እንዳይረጋ..
ጎሕ ቀደደ
እውኔ ብርሃን ሲያርፍበት
ሕልሜ ጥላ አረቀቀ
የካድሁትን ሆኜ ተነሳሁ
ያመንሁት ከእጄ ወደቀ
(እንዲህ እናምናለን
ስለማሰብ ሐሳብ ሆነን
ስለመፍጠር ተፈጥረን
ሕልሞቻችን እንዲያልሙ
መገፋት ደግፏቸው
ተቃርኖዎች እንደቆሙ...
እንዲህ እናምናለን
ስናምን እንክዳለን..
በማየት በማወቅ ብርታት ስልሽ
ከዚህ መለስ ህይወት የለም
የቱ ህይወት? ከየት ወዲያ?
ብለሽ ብትጠይቂ
መጥራት ህይወት አልፈጠረም?
በተቃርኖ እርቅ ጠራን
እንዲህ ክደን ማመን ዘራን!)
ግልገል ሞቴን ተንተርሼ
ነፍስ ስለመዝራት አስባለሁ
(ነጋ! ነቃሁ ብዬሽ ነበረ?)
ይሄን እየነገርኩሽ መምሸቱን ረስቻለሁ
(ስለማወቅ ስንታመም
መርሳት ደስታ አልሆነም?)
(ቃል ብርሃን ሆኖ ሕዋው ልብ ላይ ፈስሶኣል። እታች፥ ምድር እንደሕያው ዐይኖቼን በብልጭታው ተክዬ
እንዲህ ነን አይደለ?
ወደ'የሉም' ስንጠራ
ሰማይ ዜማ ልንሰራ
ግጥም ሆነን ልናበራ?
ባይ'ረዱን
የማይታይ ይቅር
የምንታይን ካዱን)
ጎሕ ቀደደ ዳግመኛ
በሄድሁበት ዞሬ መጣሁ
መኖሬ ላይ ሕይወት አጣሁ
አየሽ?
መንገድ መድረስን ሲረታው?
(ሕልሜና ዕውኔ መሐል የነበረች ስስ መጋረጃ ተገፈፈች። ነፋሱ የገፋት ቅጠል ተንሳፋ ፊቴ ላይ አረፈች... ሕይወት መገለጥ ሆነ!
ምን ነበረ የለም ያልኩሽ...?
እንዲህ እናምናለን
በማመን እንክዳለን!
በማየት በማወቅ ብርታት ስልሽ
ከዚህ መለስ ህይወት የለም
የቱ ህይወት? ከየት ወዲያ?
ብለሽ ብትጠይቂ
መጥራት ህይወት አልፈጠረም?
በተቃርኖ እርቅ ጠራን
እንዲህ ክደን ነፍስ ዘራን!)
በጀርባዬ ተንበልብዬ
ዐይኖቼን ሕዋው ልብ ላይ ተክዬ
እንደሌለሁ
እንደሌለሽ ይሄንን እውነት ስረሳ
(ብልጭ ያልነው እኛ አይደለን?)
ግጥሞች ሆነን ስንነሳ?
(እንረሳለን
እንጂ..
ካየነው ጀርባ አለን!)
ለ Migbar Siraj
#ማርቆስ_ዘመንበረ_ልዑል #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
ላለመኖር ማስረገጫ
መኖርን በአንጻር ማስጌጫ?
ይገኛል ትርጉም?
ነፋስ ከሚወዘውዘው
ዐይኔ ከሚያየው ጀርባ
የለም እያልኩሽ ስላለው?
በማለም ሽንቁር ሾልኬ
ግልገል ሞቴን ተመርኩዤ
ከሐሳብ ቁልል መሐል
አለመኖርን መዝዤ
ስመላለስበት ባነጋ
(ሳውቅ)
ማመኔን ሳይደገፍ
መካድ ብቻውን እንዳይረጋ..
ጎሕ ቀደደ
እውኔ ብርሃን ሲያርፍበት
ሕልሜ ጥላ አረቀቀ
የካድሁትን ሆኜ ተነሳሁ
ያመንሁት ከእጄ ወደቀ
(እንዲህ እናምናለን
ስለማሰብ ሐሳብ ሆነን
ስለመፍጠር ተፈጥረን
ሕልሞቻችን እንዲያልሙ
መገፋት ደግፏቸው
ተቃርኖዎች እንደቆሙ...
እንዲህ እናምናለን
ስናምን እንክዳለን..
በማየት በማወቅ ብርታት ስልሽ
ከዚህ መለስ ህይወት የለም
የቱ ህይወት? ከየት ወዲያ?
ብለሽ ብትጠይቂ
መጥራት ህይወት አልፈጠረም?
በተቃርኖ እርቅ ጠራን
እንዲህ ክደን ማመን ዘራን!)
ግልገል ሞቴን ተንተርሼ
ነፍስ ስለመዝራት አስባለሁ
(ነጋ! ነቃሁ ብዬሽ ነበረ?)
ይሄን እየነገርኩሽ መምሸቱን ረስቻለሁ
(ስለማወቅ ስንታመም
መርሳት ደስታ አልሆነም?)
(ቃል ብርሃን ሆኖ ሕዋው ልብ ላይ ፈስሶኣል። እታች፥ ምድር እንደሕያው ዐይኖቼን በብልጭታው ተክዬ
እንዲህ ነን አይደለ?
ወደ'የሉም' ስንጠራ
ሰማይ ዜማ ልንሰራ
ግጥም ሆነን ልናበራ?
ባይ'ረዱን
የማይታይ ይቅር
የምንታይን ካዱን)
ጎሕ ቀደደ ዳግመኛ
በሄድሁበት ዞሬ መጣሁ
መኖሬ ላይ ሕይወት አጣሁ
አየሽ?
መንገድ መድረስን ሲረታው?
(ሕልሜና ዕውኔ መሐል የነበረች ስስ መጋረጃ ተገፈፈች። ነፋሱ የገፋት ቅጠል ተንሳፋ ፊቴ ላይ አረፈች... ሕይወት መገለጥ ሆነ!
ምን ነበረ የለም ያልኩሽ...?
እንዲህ እናምናለን
በማመን እንክዳለን!
በማየት በማወቅ ብርታት ስልሽ
ከዚህ መለስ ህይወት የለም
የቱ ህይወት? ከየት ወዲያ?
ብለሽ ብትጠይቂ
መጥራት ህይወት አልፈጠረም?
በተቃርኖ እርቅ ጠራን
እንዲህ ክደን ነፍስ ዘራን!)
በጀርባዬ ተንበልብዬ
ዐይኖቼን ሕዋው ልብ ላይ ተክዬ
እንደሌለሁ
እንደሌለሽ ይሄንን እውነት ስረሳ
(ብልጭ ያልነው እኛ አይደለን?)
ግጥሞች ሆነን ስንነሳ?
(እንረሳለን
እንጂ..
ካየነው ጀርባ አለን!)
ለ Migbar Siraj
#ማርቆስ_ዘመንበረ_ልዑል #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
Meet our musician who possesses various creative sides.
Checkout her works here 👉🏾https://www.youtube.com/watch?v=gznrO3wHb4o&list=RDgznrO3wHb4o&start_radio=1&t=0
#rekik_asegidew #ረቂቅ_አሰግደው #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
Checkout her works here 👉🏾https://www.youtube.com/watch?v=gznrO3wHb4o&list=RDgznrO3wHb4o&start_radio=1&t=0
#rekik_asegidew #ረቂቅ_አሰግደው #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
Here is your event calendar from @linkupaddis for the next two weeks.
Thank you @linkupaddis for the usual support and for including our event in your calendar!
Checkout their TV channel here 👇🏽 http://www.linkupaddis.com/linkup-tv
Thank you @linkupaddis for the usual support and for including our event in your calendar!
Checkout their TV channel here 👇🏽 http://www.linkupaddis.com/linkup-tv
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኤሊያስ ሽታሁን በግጥም ሲጥም!
Forwarded from የኤልያስ ሽታሁን ግጥሞች እና እይታዎች via @like
Elias Shitahun:
(ከሚወጣው መድብል ቅምሻ
:
:
ካቲካላ የለም ፤ ከዛሬ ጀምሮ!
ለምን?
መለኪያው ተሰብሮ።
(ብለሽ
ደሞ መሸጥ ቀጠልሽ)
ጥያቄ!
መለኪያው ነው እንጂ የተሰባበረው፣
ካቲካላሽማ… በርሜሉን ሙሉ ነው።
ይሄንን ስትሰሚ
እንዳትገረሚ።
መኮመሪያ ቤትሽ ፣ መስፈሪያ የጣለ
ባገኘው ይ፟ለካል ፤ ያገኘውን ኹሉ ፣ ልኬት ነው እያለ፡፡
እረ ያንቺስ እውነት ፣ ልኩን ያሳጣሽው፣
በምን ለክተሽ ነው?
አንድ አረቄ እያሉ ፣ በርሜል የጨረሽው።
መለኪያሽን ዐየሽ ፣ ንቀሽው ተሰብሮ፤
በዋጋ ያጣላል ፤ ልክ የሌለው ኑሮ።
ለዋጋሽ መለኪያ፤
ለስካር መለኪያ፤
ለማወቅ መለኪያ፤
ለመኖር መለኪያ ፣ ጠፍቶሽ እንዳሰምጪ፤
አረቄሽን ዘግተሽ ፣ መለኪያሽን አውጪ፤
ተይ በልክ ቅጂ!
ቀጥ ብሎ እየገቡ ፣ ሲወጡ በዳዴ፣
በምን ሰጠሻቸው ፣ ሰከሩልሽ ባንዴ።
የአረቄሽ ሞገስ…
ሰው እየመሰለው ፣ ዐይኑ ደም ሲቀላ፣
ገ፟ዳም ናት ይልሻል ፤ ሰው ቤትሽ ሲሞላ።
ገድሽ መለኪያሽ ነው! የተሰበረልሽ፤
አትሰሰትም ብሎ ፣ ሰው የሚያመጣልሽ።
ሀገሬው ሀገርሽ ፣ ስስት ከመለካት ተደበላልቆበት፣
የሚለካን ኹሉ ፣ ስስታም የሚል ስም ፣ ወስዶ ለጠፈበት።
ተይ በልክ ቅጂ!
ማይለካ አረቄ ፣ እያደልሽው በገፍ፣
ሀገር ሰከረልሽ ፤ በምኑ ይደገፍ።
ተይ በልክ ቅጂ!
ጤነኛውስ ይኹን ፤ እብድ አታስብጂ፤
ተይ በልክ ቅጂ!
-------//////-------
ኤልያስ ሽታሁን
(ከሚወጣው መድብል ቅምሻ
:
:
ካቲካላ የለም ፤ ከዛሬ ጀምሮ!
ለምን?
መለኪያው ተሰብሮ።
(ብለሽ
ደሞ መሸጥ ቀጠልሽ)
ጥያቄ!
መለኪያው ነው እንጂ የተሰባበረው፣
ካቲካላሽማ… በርሜሉን ሙሉ ነው።
ይሄንን ስትሰሚ
እንዳትገረሚ።
መኮመሪያ ቤትሽ ፣ መስፈሪያ የጣለ
ባገኘው ይ፟ለካል ፤ ያገኘውን ኹሉ ፣ ልኬት ነው እያለ፡፡
እረ ያንቺስ እውነት ፣ ልኩን ያሳጣሽው፣
በምን ለክተሽ ነው?
አንድ አረቄ እያሉ ፣ በርሜል የጨረሽው።
መለኪያሽን ዐየሽ ፣ ንቀሽው ተሰብሮ፤
በዋጋ ያጣላል ፤ ልክ የሌለው ኑሮ።
ለዋጋሽ መለኪያ፤
ለስካር መለኪያ፤
ለማወቅ መለኪያ፤
ለመኖር መለኪያ ፣ ጠፍቶሽ እንዳሰምጪ፤
አረቄሽን ዘግተሽ ፣ መለኪያሽን አውጪ፤
ተይ በልክ ቅጂ!
ቀጥ ብሎ እየገቡ ፣ ሲወጡ በዳዴ፣
በምን ሰጠሻቸው ፣ ሰከሩልሽ ባንዴ።
የአረቄሽ ሞገስ…
ሰው እየመሰለው ፣ ዐይኑ ደም ሲቀላ፣
ገ፟ዳም ናት ይልሻል ፤ ሰው ቤትሽ ሲሞላ።
ገድሽ መለኪያሽ ነው! የተሰበረልሽ፤
አትሰሰትም ብሎ ፣ ሰው የሚያመጣልሽ።
ሀገሬው ሀገርሽ ፣ ስስት ከመለካት ተደበላልቆበት፣
የሚለካን ኹሉ ፣ ስስታም የሚል ስም ፣ ወስዶ ለጠፈበት።
ተይ በልክ ቅጂ!
ማይለካ አረቄ ፣ እያደልሽው በገፍ፣
ሀገር ሰከረልሽ ፤ በምኑ ይደገፍ።
ተይ በልክ ቅጂ!
ጤነኛውስ ይኹን ፤ እብድ አታስብጂ፤
ተይ በልክ ቅጂ!
-------//////-------
ኤልያስ ሽታሁን
የምስል ጥበብ ስነ-ግጥምን ስታውቃት. . . !
When photography meets poetry...!
@ribkiphoto
#ርብቃሲሳይ #ribkasisay
#ግጥምሲጥም #gitemsitem
When photography meets poetry...!
@ribkiphoto
#ርብቃሲሳይ #ribkasisay
#ግጥምሲጥም #gitemsitem
አስተምረኝ
( ሠይፈ ወርቅ)
አስተምረኝ - ከማዕበል ጋር መደነስ
አሠልጥነኝ - በእሳት ላይ መመላለስ
ስሬን አጥብቅ - እንድታጠፍ ለነፋሳት
ልቤን ግራው - ሲቀጠቀጥ እንዲከፈት
ከዶፍ
ከጎርፍ
ከጣይ፣ ከቁር
ከበረድ ጋር
ከውሽንፍር
ከመብረቅ ጋር እንድጨፍር
ውብ ህይወትን እንድዘምር
አስተምረኝ!
ያለነፋስ - ዋሽንት በድን
ሳይገረፍ - ክራር አይድን
ሳይመታ - ሙት ከበሮ
ለሰከነ - ለነፍስ ጆሮ
በህመም ውስጥ ተቀምሮ
ውብ ዜማ አለ በተፈጥሮ
አስተምረኝ
የማየትን ጥልቀት፣ ርቀት
አሠልጥነኝ
የማድመጥን ስር መሠረት
በሸለቆ
በከፍታ፣ በቁልቀለት
ህመም ሳልሸሽ
ያለህመም ልኑርበት
#አስተምረኝ።
#ምራኝ!
#ማረኝ!
( ሠይፈ ወርቅ )
#አስተምረኝ
#ሰይፉወርቁ #ሰይፈወርቅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
( ሠይፈ ወርቅ)
አስተምረኝ - ከማዕበል ጋር መደነስ
አሠልጥነኝ - በእሳት ላይ መመላለስ
ስሬን አጥብቅ - እንድታጠፍ ለነፋሳት
ልቤን ግራው - ሲቀጠቀጥ እንዲከፈት
ከዶፍ
ከጎርፍ
ከጣይ፣ ከቁር
ከበረድ ጋር
ከውሽንፍር
ከመብረቅ ጋር እንድጨፍር
ውብ ህይወትን እንድዘምር
አስተምረኝ!
ያለነፋስ - ዋሽንት በድን
ሳይገረፍ - ክራር አይድን
ሳይመታ - ሙት ከበሮ
ለሰከነ - ለነፍስ ጆሮ
በህመም ውስጥ ተቀምሮ
ውብ ዜማ አለ በተፈጥሮ
አስተምረኝ
የማየትን ጥልቀት፣ ርቀት
አሠልጥነኝ
የማድመጥን ስር መሠረት
በሸለቆ
በከፍታ፣ በቁልቀለት
ህመም ሳልሸሽ
ያለህመም ልኑርበት
#አስተምረኝ።
#ምራኝ!
#ማረኝ!
( ሠይፈ ወርቅ )
#አስተምረኝ
#ሰይፉወርቁ #ሰይፈወርቅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ