ፍርፋሪ ታሪክ
- - - — - - -
"ከጅምሩ ማን ፍጠር አለህ እንዲህ ያለ ነገር? ይሄ ነው ፍርድህ? ዛሬስ አትወርድም፣ አትጽፍም ከግንባሩ ላይ ኃጢያቱን የሚያጽፍ ድፍን የቀዮ ጎረምሳ ተሰልፏል..."
"ተው አርዮስ! ተው! ከፈጣሪ አትጋፋ!...አዋቂ ነው...ተው"
"ድንቄም አዋቂ! ሲታወቅ እንዲህ ከሆነ እውቀት በአፍንጫዬ ይውጣ። አይገርምህም!"
"ለአንዲት ጋለሞታ ፈጣሪህን...ትክዳለህን!"
"ጋለሞታ? ጋለሞታ አልህ?...የት አየህ ስትዘሙት?...የት?...አዘሟች ከሌለ ዘማዊት ትፈጠር ይመስል።እንደወይራ፣እንደቀጋ አትበቅል ዘማዊት..."
"ይወራል።...ድፍን መቂ እሱኑ ነው የሚያወራው"
"እና አመንህ አንተ?"
"ምን አማራጭ ይኖራል? ሰው ተኩኖ።...ሁሉ አምኗል እኔ ማነኝና ሰው ያመነውን አላምን የምለው?"
"አልገባኝም?"
"አይገባህም። አንተ ብቻ ከሰው፣ ከቀየው ተነጥለህ፣ ለዘማዊት ሴት ጥብቅና የሚያስቆምህ ነገር። ብቻህን ከአድባር ትጋጫለህ?...ሴት ጠፋ? ከሸርሙጣ?"
"ዝም በል አንተ!!...ምፅዋ ሸርሙጣ አይደለችም።"
"ነች!"
"አይደለችም! ምፅዋ ሸ...ር...ሙ...ጣ... አይደለችም!! ትሰማኛለህ...አንተ ካላባለግኃት አንዲት ምስኪን ሯጭ ከመሬት ተነስታ ሸርሙጣ አትሆንም።"
"ትጠረጥረኛለህ?"
"አላምንህም"
"አህመድንስ ትጠረጥራለህ? ከእርሳቸው አፍ ነው ቀድሜ የሰማሁት።"
"እሳቸው ቅዱስ ገብርኤል ናቸው? የማልጠረጥራቸው?"
"እና እርሳቸውንም ጠርጥረህ?"
"እንክት! ምፅዋዬ እኮ ናት!"
"በል ወግድልኝ ልሂድበት መንገዴን! እውነትም አሪዎስ!...ያሳደጉህ የእናትህ ጡት ሳይሆን ስምህ እንደሆነ ገና ዛሬ ገባኝ!"
"የምን መንገድ?...የሰው መንገድ አበላሽቶ ...ወዴት?"
"የማን መንገድ ተበላሸ? አንተ ኩሩሩ ወግድልኝ!"
"የምፅዋ። የምስኪኗ...በወሬ ገፍታችሁ የጣላችኋት።...ህልሟ መንገዷ አልነበረም? እ!"
"የምን ህልም አላት ደግሞ ሸርሙጣ? ምን ትሰራበታለች ቢኖራትስ?"
"አንተም አለህ አይደል፤ አይደል እሷ? ሯጭ ነበረች ታውቃለህ።... አቦ ሸማኔ የሚያሳድድ ፍጥነት ነበራት።...የጥንቸል ሳንባ ምታስተፋ ነበረች ይህን አንተም ታውቃለህ....ምን ያረጋል!"
"ጋለሞቶች።"
"አልገለሞተችም።....አንተ ውሻ እንዳልዘነጥልህ በዚህ ከዘራ!"
"ኧረ በህግ...በህግ አምላክ!...ምን ታረግበት ነው እሱ...ኧረ ኡ!...ኡ!...ኧረ በህግ!..."
"ልጄን!...አይኔን!...በማህፀኗ...እንደያዘች...አስኮበለላችኋት...ምፅዋዬን አሸሻችኋት"
"ተው አሪዎስ!...ተው አንተ ከሐዲ!...ባለውለታህን?"
"የት ብዬ ልፈልጋት እሺ አሁን?...ንገረኝ!...እ!..."
"እንካ ቅመስ ይችን ለምፅዋዬ!!...እ!...ይህችን ደግሞ በማህፀኗ ይዛ ለተሰደደችው ልጄ...እንካ!!"
"ኡ!...ኡ!...ኡ!...ኧረ የሰው ያለህ!!!"
"የት ብዬ ነው የምፈልጋት አሁን?...እ!...ምፅዋዬ...የበኩር ልጄን እናት?"
©ምግባር ሲራጅ
ዘንባባ
ከገፅ 132 - 134
#ዘንባባ #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
- - - — - - -
"ከጅምሩ ማን ፍጠር አለህ እንዲህ ያለ ነገር? ይሄ ነው ፍርድህ? ዛሬስ አትወርድም፣ አትጽፍም ከግንባሩ ላይ ኃጢያቱን የሚያጽፍ ድፍን የቀዮ ጎረምሳ ተሰልፏል..."
"ተው አርዮስ! ተው! ከፈጣሪ አትጋፋ!...አዋቂ ነው...ተው"
"ድንቄም አዋቂ! ሲታወቅ እንዲህ ከሆነ እውቀት በአፍንጫዬ ይውጣ። አይገርምህም!"
"ለአንዲት ጋለሞታ ፈጣሪህን...ትክዳለህን!"
"ጋለሞታ? ጋለሞታ አልህ?...የት አየህ ስትዘሙት?...የት?...አዘሟች ከሌለ ዘማዊት ትፈጠር ይመስል።እንደወይራ፣እንደቀጋ አትበቅል ዘማዊት..."
"ይወራል።...ድፍን መቂ እሱኑ ነው የሚያወራው"
"እና አመንህ አንተ?"
"ምን አማራጭ ይኖራል? ሰው ተኩኖ።...ሁሉ አምኗል እኔ ማነኝና ሰው ያመነውን አላምን የምለው?"
"አልገባኝም?"
"አይገባህም። አንተ ብቻ ከሰው፣ ከቀየው ተነጥለህ፣ ለዘማዊት ሴት ጥብቅና የሚያስቆምህ ነገር። ብቻህን ከአድባር ትጋጫለህ?...ሴት ጠፋ? ከሸርሙጣ?"
"ዝም በል አንተ!!...ምፅዋ ሸርሙጣ አይደለችም።"
"ነች!"
"አይደለችም! ምፅዋ ሸ...ር...ሙ...ጣ... አይደለችም!! ትሰማኛለህ...አንተ ካላባለግኃት አንዲት ምስኪን ሯጭ ከመሬት ተነስታ ሸርሙጣ አትሆንም።"
"ትጠረጥረኛለህ?"
"አላምንህም"
"አህመድንስ ትጠረጥራለህ? ከእርሳቸው አፍ ነው ቀድሜ የሰማሁት።"
"እሳቸው ቅዱስ ገብርኤል ናቸው? የማልጠረጥራቸው?"
"እና እርሳቸውንም ጠርጥረህ?"
"እንክት! ምፅዋዬ እኮ ናት!"
"በል ወግድልኝ ልሂድበት መንገዴን! እውነትም አሪዎስ!...ያሳደጉህ የእናትህ ጡት ሳይሆን ስምህ እንደሆነ ገና ዛሬ ገባኝ!"
"የምን መንገድ?...የሰው መንገድ አበላሽቶ ...ወዴት?"
"የማን መንገድ ተበላሸ? አንተ ኩሩሩ ወግድልኝ!"
"የምፅዋ። የምስኪኗ...በወሬ ገፍታችሁ የጣላችኋት።...ህልሟ መንገዷ አልነበረም? እ!"
"የምን ህልም አላት ደግሞ ሸርሙጣ? ምን ትሰራበታለች ቢኖራትስ?"
"አንተም አለህ አይደል፤ አይደል እሷ? ሯጭ ነበረች ታውቃለህ።... አቦ ሸማኔ የሚያሳድድ ፍጥነት ነበራት።...የጥንቸል ሳንባ ምታስተፋ ነበረች ይህን አንተም ታውቃለህ....ምን ያረጋል!"
"ጋለሞቶች።"
"አልገለሞተችም።....አንተ ውሻ እንዳልዘነጥልህ በዚህ ከዘራ!"
"ኧረ በህግ...በህግ አምላክ!...ምን ታረግበት ነው እሱ...ኧረ ኡ!...ኡ!...ኧረ በህግ!..."
"ልጄን!...አይኔን!...በማህፀኗ...እንደያዘች...አስኮበለላችኋት...ምፅዋዬን አሸሻችኋት"
"ተው አሪዎስ!...ተው አንተ ከሐዲ!...ባለውለታህን?"
"የት ብዬ ልፈልጋት እሺ አሁን?...ንገረኝ!...እ!..."
"እንካ ቅመስ ይችን ለምፅዋዬ!!...እ!...ይህችን ደግሞ በማህፀኗ ይዛ ለተሰደደችው ልጄ...እንካ!!"
"ኡ!...ኡ!...ኡ!...ኧረ የሰው ያለህ!!!"
"የት ብዬ ነው የምፈልጋት አሁን?...እ!...ምፅዋዬ...የበኩር ልጄን እናት?"
©ምግባር ሲራጅ
ዘንባባ
ከገፅ 132 - 134
#ዘንባባ #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
Forwarded from Tibeb Be Adebabay-TBA
“Feelings along the Sidewalk” is open now!
Find it on the Sidewalk of the Italian Cultural Institute and, online on http://tibebbeadebabay.org
#tba #tibebbeadebabay #digitalart #digitalartfestival #artinaddis
Find it on the Sidewalk of the Italian Cultural Institute and, online on http://tibebbeadebabay.org
#tba #tibebbeadebabay #digitalart #digitalartfestival #artinaddis
Meet one of the poets we've spotted following our call to artists. This emerging poet is ready to share her perspectives and express her self through poetry.
#AdomiaFekede #gitemsitem #poeticsaturdays #migbarsiraj
#አዶሚያፈቀደ #ግጥምሲጥም #ግጣምዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
#AdomiaFekede #gitemsitem #poeticsaturdays #migbarsiraj
#አዶሚያፈቀደ #ግጥምሲጥም #ግጣምዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
Due to security issues in our city, we are forced to move the event to the 21st of November (next Saturday).
We thank you all for your interest in our event. We hope you understand how the situation is beyond our power and we hope you excuse us.
Please stay tuned to Gitem Sitem's channels for more updates.
We thank you all for your interest in our event. We hope you understand how the situation is beyond our power and we hope you excuse us.
Please stay tuned to Gitem Sitem's channels for more updates.
Forwarded from ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem (Seife Temam)
ጸልያለሁ
========
እጸልያለሁ ለሰው ልጅ
በሰንሰለት ላለው እጅ
እጸልያለሁ ታትሬ
ህላዌን ያላወቀ አለም
ፍፃሜን እንዳያይ ዛሬ
እጸልያለሁ ጸሎቴን
ኩታዬን በኮት ስቀይር
ስለፈረሰው ቤቴ
ራቤን በም'ራብ ስሰፍር
ስለተራበው ጉልበቴ
ስሜን በሰም ሳሰፍር
ስለነደደው ውበቴ
ከራሴ ወጥቼ
ፀርሃ አርያም
ቅጥሩን ተጠግቼ
የዓይኖቼን ውሃ
በፍቅር አተንናለሁ
እ-ጸ-ል-ያ-ለ-ሁ
እጸልያለሁ ጸሎቴን
ዕለትን በአለት ሲያቆም ሲመትር
ስለደከመው አያቴ
ግንጥልጣይ ገጥሞ ሲቀምር
ስለተሰዋው አባቴ
ነፍስ ላይ ነፍጥ ሲከምር
ስለጠበበው አጎቴ
ከራሴ ወጥቼ
መንበረ ፀባዖት
ቅጥሩን ተጠግቼ
የወዜን ብልጭልጭ
በእምነት እጠርጋለሁ
እ-ጸ-ል-ያ-ለ-ሁ
እጸልያለሁ ለሰው ልጅ
በሰንሰለት ላለው እጅ
እጁ ለሰንሰለቱ ሳይጠብ
ሰንሰለት እጁላይ ሳይቀልጥ
ህላዌን እንዲያየው አለም
ፍፃሜን ተግቶ ከማለም
ሰይፈ ተማም 2008
========
እጸልያለሁ ለሰው ልጅ
በሰንሰለት ላለው እጅ
እጸልያለሁ ታትሬ
ህላዌን ያላወቀ አለም
ፍፃሜን እንዳያይ ዛሬ
እጸልያለሁ ጸሎቴን
ኩታዬን በኮት ስቀይር
ስለፈረሰው ቤቴ
ራቤን በም'ራብ ስሰፍር
ስለተራበው ጉልበቴ
ስሜን በሰም ሳሰፍር
ስለነደደው ውበቴ
ከራሴ ወጥቼ
ፀርሃ አርያም
ቅጥሩን ተጠግቼ
የዓይኖቼን ውሃ
በፍቅር አተንናለሁ
እ-ጸ-ል-ያ-ለ-ሁ
እጸልያለሁ ጸሎቴን
ዕለትን በአለት ሲያቆም ሲመትር
ስለደከመው አያቴ
ግንጥልጣይ ገጥሞ ሲቀምር
ስለተሰዋው አባቴ
ነፍስ ላይ ነፍጥ ሲከምር
ስለጠበበው አጎቴ
ከራሴ ወጥቼ
መንበረ ፀባዖት
ቅጥሩን ተጠግቼ
የወዜን ብልጭልጭ
በእምነት እጠርጋለሁ
እ-ጸ-ል-ያ-ለ-ሁ
እጸልያለሁ ለሰው ልጅ
በሰንሰለት ላለው እጅ
እጁ ለሰንሰለቱ ሳይጠብ
ሰንሰለት እጁላይ ሳይቀልጥ
ህላዌን እንዲያየው አለም
ፍፃሜን ተግቶ ከማለም
ሰይፈ ተማም 2008
በአርትስ tv እንዲሁም በታላላቅ መድረኮች ላይ የምናውቀው ገጣሚ ኤልያስ ሽታሁን አዲስ የ telegram ቻናል ከፍቷል በመቀላቀል ከጥበብ ማዕህድ ይቋደሱ
👇👇👇👇
@Eliasshitahun
@Eliasshitahun
@Eliasshitahun
👇👇👇👇
@Eliasshitahun
@Eliasshitahun
@Eliasshitahun
Forwarded from የኤልያስ ሽታሁን ግጥሞች እና እይታዎች via @like
Elias Shitahun:
ምስጢረ ሰው መሆን ከምንመረምር
እስቲ አንዳንድ ጊዜ ከአሜን እንጀምር።
ድረሰቱን ዜማውን መሰደር አቁመን
በትርጉም ከምንሞት ከሀሳብ አድመን
ሁሉ እንዲቃናልን ከደቡብ ከሰሜን
ሁሉን ገታ አርገን እንጀምር ከአሜን።
ያመንከውን አስስ
አሜንን ፍለጋ ሰው ከተሰደደ
እንደመስቀል ችቦ በአንድ ከነደደ
ጨለማ ይቀናል በብርሀን ዳና
ሰማይ ቀን ይመስላል ሰው ሰማይ ነውና።
ያመንከውን ፈልግ ከቶ አታፍነው
ጭስ ያበረታኻል ቆሻሻ ቢደፍነው
ያመንከውን ፈልግ
ከሰው በታች ቀብሮህ መቻልህን ገድሎህ
ያልታደለ ሰቃይ
ያነሰ ይመስለዋል መሬት እንኳን ጥሎህ።
ሰቃይ እንደዚህ ነው
የአለምን ድውይ ስትፈውስ ሰትሽር
ጠላትህ ይነሳል ማዳንህን ሊሽር።
ችቦህን አጠራቅም ደመራህን ለኩስ
በአላማህ መንን በሰው ህብረት መንኩስ
ጠላትህን ቀማው የመጥላቱን አቅም
መውደድህን አወጋው
መውጋትን አያውቅም።
ከሰቃይህ ብለጥ ከክፋት ብርሀን
እሳት ይወለዳል በስንጥሮች መሀል።
ከስንጥሮች ቅሰም የህይወትን ትርጉም
ተጋግዞ መብራት ነው የሚያባረረው ጉም።
ደግ ዛሬ ያለው ነገውን ያምጣል
ሁሉን ተወውና ክፉን ትናንት ጣል
ተገኘሁኝ ብለህ ዛሬ እንድትዘምር
ከመታሰብ ቀጥል ከመጀመር ጀምር።
ምስጢረ ሰው መሆን ከምንመረምር
እስቲ አንዳንድ ጊዜ ከአሜን እንጀምር።
ምስጢረ ሰው መሆን ከምንመረምር
እስቲ አንዳንድ ጊዜ ከአሜን እንጀምር።
ድረሰቱን ዜማውን መሰደር አቁመን
በትርጉም ከምንሞት ከሀሳብ አድመን
ሁሉ እንዲቃናልን ከደቡብ ከሰሜን
ሁሉን ገታ አርገን እንጀምር ከአሜን።
ያመንከውን አስስ
አሜንን ፍለጋ ሰው ከተሰደደ
እንደመስቀል ችቦ በአንድ ከነደደ
ጨለማ ይቀናል በብርሀን ዳና
ሰማይ ቀን ይመስላል ሰው ሰማይ ነውና።
ያመንከውን ፈልግ ከቶ አታፍነው
ጭስ ያበረታኻል ቆሻሻ ቢደፍነው
ያመንከውን ፈልግ
ከሰው በታች ቀብሮህ መቻልህን ገድሎህ
ያልታደለ ሰቃይ
ያነሰ ይመስለዋል መሬት እንኳን ጥሎህ።
ሰቃይ እንደዚህ ነው
የአለምን ድውይ ስትፈውስ ሰትሽር
ጠላትህ ይነሳል ማዳንህን ሊሽር።
ችቦህን አጠራቅም ደመራህን ለኩስ
በአላማህ መንን በሰው ህብረት መንኩስ
ጠላትህን ቀማው የመጥላቱን አቅም
መውደድህን አወጋው
መውጋትን አያውቅም።
ከሰቃይህ ብለጥ ከክፋት ብርሀን
እሳት ይወለዳል በስንጥሮች መሀል።
ከስንጥሮች ቅሰም የህይወትን ትርጉም
ተጋግዞ መብራት ነው የሚያባረረው ጉም።
ደግ ዛሬ ያለው ነገውን ያምጣል
ሁሉን ተወውና ክፉን ትናንት ጣል
ተገኘሁኝ ብለህ ዛሬ እንድትዘምር
ከመታሰብ ቀጥል ከመጀመር ጀምር።
ምስጢረ ሰው መሆን ከምንመረምር
እስቲ አንዳንድ ጊዜ ከአሜን እንጀምር።
የምስል ጥበብ ስነ-ግጥምን ስታውቃት. . . !
When photography meets poetry...!
@ribkiphoto
#ርብቃሲሳይ #ribkasisay
#ግጥምሲጥም #gitemsitem
When photography meets poetry...!
@ribkiphoto
#ርብቃሲሳይ #ribkasisay
#ግጥምሲጥም #gitemsitem
Forwarded from Jafer Books 📚 (Zee - Se)
የጋዜጠኛና ገጣሚ ወሰንሰገድ ገብረኪዳን አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቃ ::
" ነጻነት " የተሰኘውና በ 112 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፍ ግጥሞችንና ወጎችን ሰብስቦ ይዟል ::
ጋዜጠኛና ገጣሚ ወሰንሰገድ ከዚህ ቀደም " የቃሊቲ ምስጥሮች " የተሰኘ የእስር ቤት ማስታወሻና " ሕዝብ ማለት " የተሰኘ የግጥም መድብል አስነብቦናል ::
ይህን ነጻነት የተሰኘውን የግጥም መድብሉ በመደብራችን እየተሸጠ ነው ::
Join. @jafbok
" ነጻነት " የተሰኘውና በ 112 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፍ ግጥሞችንና ወጎችን ሰብስቦ ይዟል ::
ጋዜጠኛና ገጣሚ ወሰንሰገድ ከዚህ ቀደም " የቃሊቲ ምስጥሮች " የተሰኘ የእስር ቤት ማስታወሻና " ሕዝብ ማለት " የተሰኘ የግጥም መድብል አስነብቦናል ::
ይህን ነጻነት የተሰኘውን የግጥም መድብሉ በመደብራችን እየተሸጠ ነው ::
Join. @jafbok