የአለም ሰባኪ
እከዘለዓለመ አለም
ስለሚያኖረው አውርቶ
ከሚያስቀድሰው
የሚያስነውረውን አብዝቶ
በደቂቃ ደቀቀ ሳቱ ባላቸው ስቶ
የሳቱትም ፈረዱ መሳት በሳት በርክቶ
#seifetemam 2008
እከዘለዓለመ አለም
ስለሚያኖረው አውርቶ
ከሚያስቀድሰው
የሚያስነውረውን አብዝቶ
በደቂቃ ደቀቀ ሳቱ ባላቸው ስቶ
የሳቱትም ፈረዱ መሳት በሳት በርክቶ
#seifetemam 2008
የማለዳ ፀሎቴ
በቀኝህ አውለኝ ብሎ እንዲፀልይ ሰው
… እኔ ግን ብያለሁ
በየ ደረስኩበት እንደው በየቦታው
ወረፋና ሰልፉ እግሬን ስላዛለው
… እኔ ግን ብያለሁ በግራህ አውለኝ
ግድየለም ግዴለም
ግራውም ያንተው ነው
#seifetemam
በቀኝህ አውለኝ ብሎ እንዲፀልይ ሰው
… እኔ ግን ብያለሁ
በየ ደረስኩበት እንደው በየቦታው
ወረፋና ሰልፉ እግሬን ስላዛለው
… እኔ ግን ብያለሁ በግራህ አውለኝ
ግድየለም ግዴለም
ግራውም ያንተው ነው
#seifetemam
#gitemsitem #poetic_saturdays #ግጥም_ሲጥም #ግጥማዊ_ቅዳሜ #seifetemam
ህመሜን ላጣጥም
-----------------------
እስቲ ልንቆራጠጥ ተዉኝ ላቃስትበት
ህመሜን ላጣጥም እስክፈወስበት
እንዳትወጉኝ ማደንዘዣ
እንዳትሰጡኝ ማስታገሻ
በሰፊ አውታር መገናኛ
በብልጭልጭ መሸፈኛ
የዘመን ጎርፍ አግበስብሶ
በከሰተው መከወኛ
ከኔ በላይ ላያማችሁ
ከህመሜ ላይ ሰራርቃችሁ
በሽተኛ ስንኩል ሳለሁ
አታፍጥኑት ሞቴን ካለው
እያላችሁ ጤነኛ ሰው
ልዳን እንጂ አታስታግሱኝ
ተዉኝ ተዉኝ ልንቆራጠጥ
ላተኩሰው ሆዴ ይቁረጥ
እራሴ ይምታ አይኔ ይበጥ
ሰው አድርጉኝ የሚሰማው
ከራሱ ጋር የሚታደም
በሽታዬን ካልተቀማሁ
በህመሜ ነው የምታከም
ሰይፈ ተማም 2009
ህመሜን ላጣጥም
-----------------------
እስቲ ልንቆራጠጥ ተዉኝ ላቃስትበት
ህመሜን ላጣጥም እስክፈወስበት
እንዳትወጉኝ ማደንዘዣ
እንዳትሰጡኝ ማስታገሻ
በሰፊ አውታር መገናኛ
በብልጭልጭ መሸፈኛ
የዘመን ጎርፍ አግበስብሶ
በከሰተው መከወኛ
ከኔ በላይ ላያማችሁ
ከህመሜ ላይ ሰራርቃችሁ
በሽተኛ ስንኩል ሳለሁ
አታፍጥኑት ሞቴን ካለው
እያላችሁ ጤነኛ ሰው
ልዳን እንጂ አታስታግሱኝ
ተዉኝ ተዉኝ ልንቆራጠጥ
ላተኩሰው ሆዴ ይቁረጥ
እራሴ ይምታ አይኔ ይበጥ
ሰው አድርጉኝ የሚሰማው
ከራሱ ጋር የሚታደም
በሽታዬን ካልተቀማሁ
በህመሜ ነው የምታከም
ሰይፈ ተማም 2009
አንድ ሰው
‘ሜክሲኮ ሜክሲኮ’
ይጣራል ወያላ
ሰባት ሰው ይዞ
ባዶ ወንበርም ይዞ
‘አንድ ሰው የሞላ’
ይህ ታክሲ ሊሞላ ስንት ቀረው ብሎ
ተሳፋሪው አይኔ ይቆጥራል ቀላቅሎ
ወጪውን ከወራጅ ትርፉን አመሳቅሎ
‘አንድ ሰው አንድ ሰው’
ድምጹ እየከረረ
እንደኔ ላለ ሰው ቆንጆ ላፈቀረ
ወይም ለቀጠረ
የጊዜን ግፍ አውቆ
በመሙላት ተሳልቆ
‘ አንድ ሰው አንድ ሰው’
ይሄ ልጅ ምን ነካው
ትመጪ ይመስል ትገቢ ከታክሲው
አንድ ሰው የሚለው
እኔ በበኩሌ
በአንድ ሰው ብቻ የሞላሽ እማቀው
አንድ አንቺን ብቻ ነው
እንጂማ
እንዳንቺ አቀራረት በዚህ ልጅ አጠራር
ይህ ታክሲና ልቤ ባንድ ቢነጻጸር
‘ አንድ ሰው’ ማለቱን ወያላው አይጠላም
ቢገባም ባይገባም
ታክሲውና ልቤ
እንኳንስ ባንድ ሰው በተራው አይሞላም
‘የሞላ የሞላ’
ያልሞላለት ወያላ
ሰው በራሱ ካልተሟላ
እንደምን በሌላ
በጎዶሎ ዘመን
‘የሞላ የሞላ’
ከሞላ አይሄድም
የደከመ ልቤን ይባስ ከሚያደክም
አንድ እማይሞላ ሰው ከታክሲው አጭቆ
አንድ ሰው ይጣራል አንቺ እንዳልሆንሽ አውቆ
‘ኧረ እንሂድ ሹፌር’ ይላል ተሳፋሪ
አንቺን ቀጥሯል እንዴ
መድረሻ ቢስ ሁላ ይህ ሂያጅ እና ቀሪ
ይበሰጫጭ ይዟል በወያላው ጥሪ
‘ሜክሲኮ ሳርቤት ሜክሲኮ ሳርቤት’
ያጎደልሽው ልቤ ከጫናት ምናልባት
ቆንጆ ቀጥርያለሁ አንቺን ልረሳባት
የት? ሳርቤት
የምታነድ ፀሃይ የሚገማ ጫማ
የምታሽካካ ሴት ስልክ ተሸክማ
ምት አልባ ሙዚቃ ጮሆ ‘ማይሰማ
የሚዋጋ ወንበር የአርሴናል አርማ
‘በጣድቋ በቅድስት አርሴማ’
የተዘረጋ እጅ ሲቀበል ሊቀማ
ተላካፊ ጥቅሶች
ቁጥር ወሳጅ ወንዶች
እድል ያዞራቸው እድል አዟሪዎች
በከበቡት ታክሲ እኚህ እና ሌላ
ሞልቶ በማይሞላ በሚያፈስ መኪና
ተጭኜ ከኋላ
‘አንድ ሰው የሞላ’
‘አንድ ሰው የሞላ’
ቀጥሏል ወያላ
ይህ ታክሲ ሊሞላ ስንት ቀረው ብሎ
ተሳፋሪው አይኔ ይቆጥራል ቀላቅሎ
ወጪውን ከወራጅ ትርፉን አመሳቅሎ
ይሄ ልጅ ምን ነካው
ትመጪ ይመስል ትገቢ ከታክሲው
አንድ ሰው እያለ ስንትነው ‘ሚጣራው
ወራጅ ብለሽ ሄደሽ ባዶ ያረግሽው ልቤ
ቆንጆ በተርፍ ይዞ
ሊረሳሽ ተክዞ
ተጠጋጉ ሲባል ስጠጋ ላስጠጋ ብነቃ ከሃሳቤ
በትርፍ የገባሽው ለካ አንቺው ሆነሻል ይኧው ካጠገቤ
በል ወያላ ዝጋው - በልሹፌሩ ንዳው
ገብታለች አንድ ሰው
አታዩአቱም እንዴ ብቻዋን ስትሞላው
ሰይፈ ተማም
ጥር 2009 (poetic saturdays)
‘ሜክሲኮ ሜክሲኮ’
ይጣራል ወያላ
ሰባት ሰው ይዞ
ባዶ ወንበርም ይዞ
‘አንድ ሰው የሞላ’
ይህ ታክሲ ሊሞላ ስንት ቀረው ብሎ
ተሳፋሪው አይኔ ይቆጥራል ቀላቅሎ
ወጪውን ከወራጅ ትርፉን አመሳቅሎ
‘አንድ ሰው አንድ ሰው’
ድምጹ እየከረረ
እንደኔ ላለ ሰው ቆንጆ ላፈቀረ
ወይም ለቀጠረ
የጊዜን ግፍ አውቆ
በመሙላት ተሳልቆ
‘ አንድ ሰው አንድ ሰው’
ይሄ ልጅ ምን ነካው
ትመጪ ይመስል ትገቢ ከታክሲው
አንድ ሰው የሚለው
እኔ በበኩሌ
በአንድ ሰው ብቻ የሞላሽ እማቀው
አንድ አንቺን ብቻ ነው
እንጂማ
እንዳንቺ አቀራረት በዚህ ልጅ አጠራር
ይህ ታክሲና ልቤ ባንድ ቢነጻጸር
‘ አንድ ሰው’ ማለቱን ወያላው አይጠላም
ቢገባም ባይገባም
ታክሲውና ልቤ
እንኳንስ ባንድ ሰው በተራው አይሞላም
‘የሞላ የሞላ’
ያልሞላለት ወያላ
ሰው በራሱ ካልተሟላ
እንደምን በሌላ
በጎዶሎ ዘመን
‘የሞላ የሞላ’
ከሞላ አይሄድም
የደከመ ልቤን ይባስ ከሚያደክም
አንድ እማይሞላ ሰው ከታክሲው አጭቆ
አንድ ሰው ይጣራል አንቺ እንዳልሆንሽ አውቆ
‘ኧረ እንሂድ ሹፌር’ ይላል ተሳፋሪ
አንቺን ቀጥሯል እንዴ
መድረሻ ቢስ ሁላ ይህ ሂያጅ እና ቀሪ
ይበሰጫጭ ይዟል በወያላው ጥሪ
‘ሜክሲኮ ሳርቤት ሜክሲኮ ሳርቤት’
ያጎደልሽው ልቤ ከጫናት ምናልባት
ቆንጆ ቀጥርያለሁ አንቺን ልረሳባት
የት? ሳርቤት
የምታነድ ፀሃይ የሚገማ ጫማ
የምታሽካካ ሴት ስልክ ተሸክማ
ምት አልባ ሙዚቃ ጮሆ ‘ማይሰማ
የሚዋጋ ወንበር የአርሴናል አርማ
‘በጣድቋ በቅድስት አርሴማ’
የተዘረጋ እጅ ሲቀበል ሊቀማ
ተላካፊ ጥቅሶች
ቁጥር ወሳጅ ወንዶች
እድል ያዞራቸው እድል አዟሪዎች
በከበቡት ታክሲ እኚህ እና ሌላ
ሞልቶ በማይሞላ በሚያፈስ መኪና
ተጭኜ ከኋላ
‘አንድ ሰው የሞላ’
‘አንድ ሰው የሞላ’
ቀጥሏል ወያላ
ይህ ታክሲ ሊሞላ ስንት ቀረው ብሎ
ተሳፋሪው አይኔ ይቆጥራል ቀላቅሎ
ወጪውን ከወራጅ ትርፉን አመሳቅሎ
ይሄ ልጅ ምን ነካው
ትመጪ ይመስል ትገቢ ከታክሲው
አንድ ሰው እያለ ስንትነው ‘ሚጣራው
ወራጅ ብለሽ ሄደሽ ባዶ ያረግሽው ልቤ
ቆንጆ በተርፍ ይዞ
ሊረሳሽ ተክዞ
ተጠጋጉ ሲባል ስጠጋ ላስጠጋ ብነቃ ከሃሳቤ
በትርፍ የገባሽው ለካ አንቺው ሆነሻል ይኧው ካጠገቤ
በል ወያላ ዝጋው - በልሹፌሩ ንዳው
ገብታለች አንድ ሰው
አታዩአቱም እንዴ ብቻዋን ስትሞላው
ሰይፈ ተማም
ጥር 2009 (poetic saturdays)
❤1
መስመር ቢጤ
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
መጻፊያ ለጎመ ወረቀት ቀደደ
ስራ ገቡ መሰል መብራት አሁን ሄደ
ሻማም እንዳልገዛ ዋጋው ተንጋደደ
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
ወር አጭር ርቀት ተቀይሯል ለካ
የምገባበት በር በአከራይ ተንኳኳ
ጋሽ አያሌው ናቸው
ከደጄ ቆመዋል እንደደብር ዋርካ
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
መዝሙር ግዙኝ የሚል ዘፈን አቋረጠኝ
ስብከትም መሰለኝ ንቀትም መሰለኝ
ውስጤን እንዴት ልስማ ውጭው እያመመኝ
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
ከጎረቤታችን ይሰማል ኡኡታ
በመኪና አደጋ አንዲት ወጣት ሙታ
አወይ አንቺ ኑሮ አወይ አንቺ ሕይወት
ማሽከርከር መሽከርከር እንዲሁ እንደዘበት
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
እናቴን መሳይ ሴት ምስል እያሳዩ
እነ ዜና አንባቢ እነ አስመሳዩ
ያን ባዶ ማጀቷን ውሸት ይሞላሉ
ጠገበች፣ አገሳች ምናምን እያሉ
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
ይረብሻል ከጎን የሚሰማው ስድብ
የሚሰማው ሁከት
አንደኛው አግብቶ አንደኛው ገብቶበት
ሁለቱም ይጮሃል ደጋግሞ ለመርሳት
የኳስን፣ የኑሮን፣ የፍቅርን ክብነት
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
መከረኛ ስልኬ ይጮሃል ደጋግሞ
‘ውጣ እንውጣ’‘ሚል ሰው ውስጡ ተሸክሞ
ጀመረው እንግዲህ ሊያስነካካኝ ምስሉን
ቧልትና ለገጣ ያደባባይ ስጡን
ቲርኪሚርኪ፣ እንቶ ፈንቶ፣ አተካራ
መፈስበኪያው፣ ማሞጥሞጫና በግተራ
መስመር ቢጤ ነገር ብዬ ልጽፍልሽ …
ብዕሬን ተቀማሁ በዥጉርጉር ለባሽ
አንቺም እንዳ’ገሬ ቦለቲካ ሁነሽ
ሰይፈ ተማም ፪፼፰6
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
መጻፊያ ለጎመ ወረቀት ቀደደ
ስራ ገቡ መሰል መብራት አሁን ሄደ
ሻማም እንዳልገዛ ዋጋው ተንጋደደ
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
ወር አጭር ርቀት ተቀይሯል ለካ
የምገባበት በር በአከራይ ተንኳኳ
ጋሽ አያሌው ናቸው
ከደጄ ቆመዋል እንደደብር ዋርካ
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
መዝሙር ግዙኝ የሚል ዘፈን አቋረጠኝ
ስብከትም መሰለኝ ንቀትም መሰለኝ
ውስጤን እንዴት ልስማ ውጭው እያመመኝ
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
ከጎረቤታችን ይሰማል ኡኡታ
በመኪና አደጋ አንዲት ወጣት ሙታ
አወይ አንቺ ኑሮ አወይ አንቺ ሕይወት
ማሽከርከር መሽከርከር እንዲሁ እንደዘበት
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
እናቴን መሳይ ሴት ምስል እያሳዩ
እነ ዜና አንባቢ እነ አስመሳዩ
ያን ባዶ ማጀቷን ውሸት ይሞላሉ
ጠገበች፣ አገሳች ምናምን እያሉ
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
ይረብሻል ከጎን የሚሰማው ስድብ
የሚሰማው ሁከት
አንደኛው አግብቶ አንደኛው ገብቶበት
ሁለቱም ይጮሃል ደጋግሞ ለመርሳት
የኳስን፣ የኑሮን፣ የፍቅርን ክብነት
መስመር ቢጤ ነገር ልጽፍልሽ ብዬ …
መከረኛ ስልኬ ይጮሃል ደጋግሞ
‘ውጣ እንውጣ’‘ሚል ሰው ውስጡ ተሸክሞ
ጀመረው እንግዲህ ሊያስነካካኝ ምስሉን
ቧልትና ለገጣ ያደባባይ ስጡን
ቲርኪሚርኪ፣ እንቶ ፈንቶ፣ አተካራ
መፈስበኪያው፣ ማሞጥሞጫና በግተራ
መስመር ቢጤ ነገር ብዬ ልጽፍልሽ …
ብዕሬን ተቀማሁ በዥጉርጉር ለባሽ
አንቺም እንዳ’ገሬ ቦለቲካ ሁነሽ
ሰይፈ ተማም ፪፼፰6
የጎጇችን ተስፋ
ውዴ ይቺ ጎጆ ምንነክቷታል እሳ
አንዱን አንጠራርታ አንዱን አስጎንብሳ
ባንድ ወገን ደራርቃ ባንዱ ጋር በስብሳ
አንድ አይኗን ጎልጉላ አንዱን አጨናብሳ
ባልሞቀ ገል ጠብሳ
በባዶ አንጀት ምሳ
ምነው ይች ጎጆ ምንነክቷታል እሳ
ውዴ እኛ ነን ወይ
ሳርክዳኑን ስናይ
እንደከሳ በሬ የቁም ጎድን ጥብሱ
የግድግዳው ምርግ ወጨፎ አለቅልቆት
ጨፈቃና አግዳሚ ፈጠው ሲታዩበት
እኛ ነን ወይ ውዴ የኛ ነወይ ጥፋት
ማገሩን ስንደግፍ የአግዳሚው መግፋት
ጣራውን ስንደፍን ወለሉ መጨቅየት
መቀመጫ ጥግም አጣን
ማረፊያ መደብም ነሳን
መቆምም አልሆን አለን
ውዴ ይሁን ግዴለም የደረሰብንን
እንደመቻል ካልን
ግና ካንቺ ጉያ ያለች የኛ ተስፋ
እንደምንድን ይሆን ደርሳ ምትፋፋ
ነዳ የማትጠፋ
ጠፍታ የማትከፋ
ከፍታ የማትሰፋ
ሰፍታ የማትገፋ
እንደምንድን እንደምን ተጽፋ
የተስፋችን ቁልል እኛው ላይ ተንዶ
የረፈደው ንጋት ጽልመት እጁን ሰድዶ
ይቺን ጎጆ ሲንጥ ማገሩን አንጋድዶ
ደምሽና ደሜ የቋጠሯት ስንኝ
ማንይሆን አጣርቶ አንብቧት ሚገኝ
ሰይፈ ተማም 2007
ውዴ ይቺ ጎጆ ምንነክቷታል እሳ
አንዱን አንጠራርታ አንዱን አስጎንብሳ
ባንድ ወገን ደራርቃ ባንዱ ጋር በስብሳ
አንድ አይኗን ጎልጉላ አንዱን አጨናብሳ
ባልሞቀ ገል ጠብሳ
በባዶ አንጀት ምሳ
ምነው ይች ጎጆ ምንነክቷታል እሳ
ውዴ እኛ ነን ወይ
ሳርክዳኑን ስናይ
እንደከሳ በሬ የቁም ጎድን ጥብሱ
የግድግዳው ምርግ ወጨፎ አለቅልቆት
ጨፈቃና አግዳሚ ፈጠው ሲታዩበት
እኛ ነን ወይ ውዴ የኛ ነወይ ጥፋት
ማገሩን ስንደግፍ የአግዳሚው መግፋት
ጣራውን ስንደፍን ወለሉ መጨቅየት
መቀመጫ ጥግም አጣን
ማረፊያ መደብም ነሳን
መቆምም አልሆን አለን
ውዴ ይሁን ግዴለም የደረሰብንን
እንደመቻል ካልን
ግና ካንቺ ጉያ ያለች የኛ ተስፋ
እንደምንድን ይሆን ደርሳ ምትፋፋ
ነዳ የማትጠፋ
ጠፍታ የማትከፋ
ከፍታ የማትሰፋ
ሰፍታ የማትገፋ
እንደምንድን እንደምን ተጽፋ
የተስፋችን ቁልል እኛው ላይ ተንዶ
የረፈደው ንጋት ጽልመት እጁን ሰድዶ
ይቺን ጎጆ ሲንጥ ማገሩን አንጋድዶ
ደምሽና ደሜ የቋጠሯት ስንኝ
ማንይሆን አጣርቶ አንብቧት ሚገኝ
ሰይፈ ተማም 2007
...እንዲቀለኝ
ከታደልሽው ጎልቶ
የሚጎልሽ ሁሉ በታየኝ በርክቶ
አንቺ መንግስት ሁነሽ እኔ ተቃዋሚ
ስተትሽን ጥፋትሽን ጉዳትሽን ለቃሚ
ምናለ ባረገኝ
የሰማዩ ሰሚ
እንደዚህ ከምገኝ
ቴሌቭዥን መስዬ
ጥጋብ ‘ሚያወራ ርሃብ እየታዬ
እንደዚህ ከምገኝ
መስዬ አቃጣሪ
ደንድነሻል የሚል ሳለሽ ስንጣሪ
ሆኜ ቀባጣሪ
ጠፍቶ ፍርፋሪ
‘ምንገድ ነው ያማራት’
መንገድ መንገድ አላት
ወዘተ … ወዘታት..
ልማታዊ አፍቃሪ ብለሽ ላትሸልሚኝ
ዘወትር ሳሞግስሽ ስክብሽ ከሚያመኝ
በላዬ ደርጅተሽ አባል ከሚያረገኝ
ከታደልሽው ጎልቶ
የሚጎልሽ ሁሉ በርክቶ በታየኝ
ሰይፈ ተማም
ከታደልሽው ጎልቶ
የሚጎልሽ ሁሉ በታየኝ በርክቶ
አንቺ መንግስት ሁነሽ እኔ ተቃዋሚ
ስተትሽን ጥፋትሽን ጉዳትሽን ለቃሚ
ምናለ ባረገኝ
የሰማዩ ሰሚ
እንደዚህ ከምገኝ
ቴሌቭዥን መስዬ
ጥጋብ ‘ሚያወራ ርሃብ እየታዬ
እንደዚህ ከምገኝ
መስዬ አቃጣሪ
ደንድነሻል የሚል ሳለሽ ስንጣሪ
ሆኜ ቀባጣሪ
ጠፍቶ ፍርፋሪ
‘ምንገድ ነው ያማራት’
መንገድ መንገድ አላት
ወዘተ … ወዘታት..
ልማታዊ አፍቃሪ ብለሽ ላትሸልሚኝ
ዘወትር ሳሞግስሽ ስክብሽ ከሚያመኝ
በላዬ ደርጅተሽ አባል ከሚያረገኝ
ከታደልሽው ጎልቶ
የሚጎልሽ ሁሉ በርክቶ በታየኝ
ሰይፈ ተማም
መብላት እና መሽናት
መንገድ ላይ ሲሸና ምንም ያልመሰለው
መንገድ ላይ አይበላም እያለ ‘ነውር ነው’
ብላችሁ በዚህ ሰው አትዘባበቱ
ይኑር እንደራሱ ወይም እንደ አያቱ
የሚያባላ ሞልቶ የሚበላው ግን ብርቅ በሆነበት ሃገር
የዳቦ ባይ ልጆች እሞሉበት መንገድ
እጅ የሚዘረጋው ለመቀበል ብቻ እየሆነ እያደር
እየበሉ መሄድ እንዴት አይነወር?
አይገባውም ለሱ የተራበ ነዳይ በሞላው ጎዳና
ዳቦ እየገመጡ መጓዝ ይሉት ዝና
የህጻን ጨዋታ እንቁልልጭ አይነት አሮጌ ዝመና
መንገድ ላይ ሲሸናም ምንም ያልመሰለው
እሱና መንግ ስቱ በመራራቃቸው
የሚሰሩት መንገድ መስሎት ለራሳቸው
መንገድ ላይ ሲሸና ምንም ያልመሰለው
መንገድ ላይ አይበላም እያለ ‘ነውር ነው’
ብላችሁ በዚህ ሰው አትዘባበቱ
ለብቻ አይበላም ደንቡ ነው ከጥንቱ
ሰው ሞልቶ በሚያፈስ በዚህ አውራ ጎዳና
ጉርሻ ለመቋደስ ኪሱ አይችልምና
እያየም ለማለፍ ሆዱ አይችልምና
ርሃቡን ውጦ ምናል ቢያቀና
ሲያሻው እየተፋ ሲያሻው እየሸና
መቼም እዚህ ሰፈር ማሕበር ቢበዛም
እንብላ ነው እንጂ እንሽና አይባልም
መንገድ ላይ ሲሸና ምንም ያልመሰለው
መንገድ ላይ አይበላም እያለ ‘ነውር ነው’
ብላችሁ በዚህ ሰው አትዘኑ ከቶ
እንጀራ ነው ስራው የሚያበላው በልቶ
ቆሞ እንኳን አይበላም እንኳን መንገድ ወቶ
ሃሳቡን በልሣን በፅሁፍ መፈክር
ባ’ንደበት ነፃነት መንገድ ላይ ከማስፈር
በሽንት መፃፍ ነው እያራሱ አፈር
ከሁሉም ከሁሉ
ከመሰሎቹ ጋር ተባብረው ሲሸኑ
ቆርቆሮዎች ዝገው መንገዶች ቢገሙ
የበላትን ነጥቆ ሳይወረውር ሽታው
የኑሮ ብሶቱን በመሽኛው አነባው
ብለን እንለፈው?
አ - ስ - ለ - ቀ - ሰ - ው
ሰይፈ ተማም 2008
መንገድ ላይ ሲሸና ምንም ያልመሰለው
መንገድ ላይ አይበላም እያለ ‘ነውር ነው’
ብላችሁ በዚህ ሰው አትዘባበቱ
ይኑር እንደራሱ ወይም እንደ አያቱ
የሚያባላ ሞልቶ የሚበላው ግን ብርቅ በሆነበት ሃገር
የዳቦ ባይ ልጆች እሞሉበት መንገድ
እጅ የሚዘረጋው ለመቀበል ብቻ እየሆነ እያደር
እየበሉ መሄድ እንዴት አይነወር?
አይገባውም ለሱ የተራበ ነዳይ በሞላው ጎዳና
ዳቦ እየገመጡ መጓዝ ይሉት ዝና
የህጻን ጨዋታ እንቁልልጭ አይነት አሮጌ ዝመና
መንገድ ላይ ሲሸናም ምንም ያልመሰለው
እሱና መንግ ስቱ በመራራቃቸው
የሚሰሩት መንገድ መስሎት ለራሳቸው
መንገድ ላይ ሲሸና ምንም ያልመሰለው
መንገድ ላይ አይበላም እያለ ‘ነውር ነው’
ብላችሁ በዚህ ሰው አትዘባበቱ
ለብቻ አይበላም ደንቡ ነው ከጥንቱ
ሰው ሞልቶ በሚያፈስ በዚህ አውራ ጎዳና
ጉርሻ ለመቋደስ ኪሱ አይችልምና
እያየም ለማለፍ ሆዱ አይችልምና
ርሃቡን ውጦ ምናል ቢያቀና
ሲያሻው እየተፋ ሲያሻው እየሸና
መቼም እዚህ ሰፈር ማሕበር ቢበዛም
እንብላ ነው እንጂ እንሽና አይባልም
መንገድ ላይ ሲሸና ምንም ያልመሰለው
መንገድ ላይ አይበላም እያለ ‘ነውር ነው’
ብላችሁ በዚህ ሰው አትዘኑ ከቶ
እንጀራ ነው ስራው የሚያበላው በልቶ
ቆሞ እንኳን አይበላም እንኳን መንገድ ወቶ
ሃሳቡን በልሣን በፅሁፍ መፈክር
ባ’ንደበት ነፃነት መንገድ ላይ ከማስፈር
በሽንት መፃፍ ነው እያራሱ አፈር
ከሁሉም ከሁሉ
ከመሰሎቹ ጋር ተባብረው ሲሸኑ
ቆርቆሮዎች ዝገው መንገዶች ቢገሙ
የበላትን ነጥቆ ሳይወረውር ሽታው
የኑሮ ብሶቱን በመሽኛው አነባው
ብለን እንለፈው?
አ - ስ - ለ - ቀ - ሰ - ው
ሰይፈ ተማም 2008
👍1
የተዉሶ ኑሮ
ይቺን አካል እና አንዲቷን 'ራሴ
አሰባጥራ ይዛ በተሰጣት ሃገር በተሰጣት ግዜ
መልሽ እስክትባል ትኖራለች ነፍሴ
እኔ...
ይችን አካል ይዤ ከዝች 'ራሴ ጋር
ከኋላ እየመራሁ ከከብቶቼ 'ምማር
ከሜዳ የወረድኩ ግጦሽ ይሉት ሃገር
የፈጣሪው ምሱል ያው እረኛ ነገር
ሜዳው...
የግጦሹም ሜዳ ሳር አልባ መላጣ
'ሚያጎርሰው የለው 'ሚያለብሰው ያጣ
የሚያደነቃቅፍ አባጣ ጎርባጣ
በተውሶ ክምር እራሱን ያሳጣ
ክምሩ...
ቢመዙት ሜዳው ላይ አይገኝም ስሩ
ፕላስቲክ ነው ውስጡ አይሆንም ለአየሩ
አይሆንም ለአፈሩ
ከብቶች ሆይ ጠርጥሩ
ጠይቁ መርምሩ
የተውሶ ድርቆሽ ከየት ይሆን ዘሩ?
ነፍሴ...
ይቺን አካል እና አንዲቷን 'ራሴ
አሰባጥራ ይዛ በተሰጣት ሃገር በተሰጣት ግዜ
በተውሶ ኑሮ ትጓዛለች ነፍሴ
#seifetemam አሁን
ይቺን አካል እና አንዲቷን 'ራሴ
አሰባጥራ ይዛ በተሰጣት ሃገር በተሰጣት ግዜ
መልሽ እስክትባል ትኖራለች ነፍሴ
እኔ...
ይችን አካል ይዤ ከዝች 'ራሴ ጋር
ከኋላ እየመራሁ ከከብቶቼ 'ምማር
ከሜዳ የወረድኩ ግጦሽ ይሉት ሃገር
የፈጣሪው ምሱል ያው እረኛ ነገር
ሜዳው...
የግጦሹም ሜዳ ሳር አልባ መላጣ
'ሚያጎርሰው የለው 'ሚያለብሰው ያጣ
የሚያደነቃቅፍ አባጣ ጎርባጣ
በተውሶ ክምር እራሱን ያሳጣ
ክምሩ...
ቢመዙት ሜዳው ላይ አይገኝም ስሩ
ፕላስቲክ ነው ውስጡ አይሆንም ለአየሩ
አይሆንም ለአፈሩ
ከብቶች ሆይ ጠርጥሩ
ጠይቁ መርምሩ
የተውሶ ድርቆሽ ከየት ይሆን ዘሩ?
ነፍሴ...
ይቺን አካል እና አንዲቷን 'ራሴ
አሰባጥራ ይዛ በተሰጣት ሃገር በተሰጣት ግዜ
በተውሶ ኑሮ ትጓዛለች ነፍሴ
#seifetemam አሁን
እባክዎ ግጥሞን ያጋሩን @SeifesBot የሚለውን መንገድ በመጠቀም ያድርሱን በጥራት የተቀዱ እንዲሁም በአማርኛ ሆሄያት የተተየቡ ግጥሞችን እንጋራ እናጋራ ።
Forwarded from ቶኔቶር
# ወፍእናማለዳ
እንኳን ችግኙ ÷ሰዎች የተከሉት
ሥር ይዝ ነበረ ÷ አዕዋፋት የዘሩት፣
ዘንድሮ ግን ወፎች ÷ እንኳንስ ሊዘሩ
ናፍቆኛል ማለዳ ÷ መስማት ሲዘምሩ፡፡
ወፎች ከማለዳ በምን ተቃቃሩ?!
ፅልመቱ ሲገፈፍ አንዳላበሰሩ፣
ማዜም ተስኗቸው ተዘግቶ ጀንበሩ
ወደሚነጋበት ወዴትስ በረሩ?!
ምንጭ = ሀ-ሞትየግጥሞች ስብስብ ኄኖክ ስጦታው
እንኳን ችግኙ ÷ሰዎች የተከሉት
ሥር ይዝ ነበረ ÷ አዕዋፋት የዘሩት፣
ዘንድሮ ግን ወፎች ÷ እንኳንስ ሊዘሩ
ናፍቆኛል ማለዳ ÷ መስማት ሲዘምሩ፡፡
ወፎች ከማለዳ በምን ተቃቃሩ?!
ፅልመቱ ሲገፈፍ አንዳላበሰሩ፣
ማዜም ተስኗቸው ተዘግቶ ጀንበሩ
ወደሚነጋበት ወዴትስ በረሩ?!
ምንጭ = ሀ-ሞትየግጥሞች ስብስብ ኄኖክ ስጦታው
የመቆም ዑደት
የቅድም አያቴን አጽም ከአፈር አውጥተው
ቀጥ ብሎ መሄድን በሷ እንደጀመርነው
ይነግሩኛል ደፍረው
...እንደዚህ እያሉ
ከጥንቱ ጥንት ፊት ሰው ዝንጀሮ ሳለ
ዝንጀሮ ሰው ሁኖ መቆም ሰለጠነ
ለሱም ምልክቷ
ሙዝየም አኑረው ይቹትና አጥንቷ
ይህንን አምኜ ለእንግዳ ስናገር
ለመጣ ለሄደው ለኦባማ ሳይቀር
ቀድመን እንደሞቅነው የመቆምን ጀምበር
...ደሞ ከመንገዱ
ወይዘሪት ድንቄ እና እትዬ አረገዱ
ሸክም አጉብጧቸው 'በ' ን ሰርተው ሲሄዱ
እኔ ደሞ እላለሁ
ቀድመን እንደቆምን ቀድመን የወደቅነው
እኛው እንደጀመርን እኛው ልንጨርሰው
#seifetemam #አሁን
የቅድም አያቴን አጽም ከአፈር አውጥተው
ቀጥ ብሎ መሄድን በሷ እንደጀመርነው
ይነግሩኛል ደፍረው
...እንደዚህ እያሉ
ከጥንቱ ጥንት ፊት ሰው ዝንጀሮ ሳለ
ዝንጀሮ ሰው ሁኖ መቆም ሰለጠነ
ለሱም ምልክቷ
ሙዝየም አኑረው ይቹትና አጥንቷ
ይህንን አምኜ ለእንግዳ ስናገር
ለመጣ ለሄደው ለኦባማ ሳይቀር
ቀድመን እንደሞቅነው የመቆምን ጀምበር
...ደሞ ከመንገዱ
ወይዘሪት ድንቄ እና እትዬ አረገዱ
ሸክም አጉብጧቸው 'በ' ን ሰርተው ሲሄዱ
እኔ ደሞ እላለሁ
ቀድመን እንደቆምን ቀድመን የወደቅነው
እኛው እንደጀመርን እኛው ልንጨርሰው
#seifetemam #አሁን
ወዳጄን ምን ነካው
ከመንጋው መንጋጋ ፈልቅቆ እየወጣ
ተነጥሎም ሲቆም አጀቡን እያጣ
ለሞቀው ገበያ ምሽቱ ሲነጋ
እራሱን አሹሎ የሚሆን መንጋጋ
ለሌላኛው መንጋ
መሾሉስ ባልከፋ
መሳሉስ ባልከፋ
ወጀብ የፈጠረው ባጀብ እንዳይጠፋ
ወዳጄን ጥሩልኝ እናውራ በወጉ
ከመንጋው ቢጠፋ አይሸጥም በጉ
ሰይፈ ተማም 2008
ከመንጋው መንጋጋ ፈልቅቆ እየወጣ
ተነጥሎም ሲቆም አጀቡን እያጣ
ለሞቀው ገበያ ምሽቱ ሲነጋ
እራሱን አሹሎ የሚሆን መንጋጋ
ለሌላኛው መንጋ
መሾሉስ ባልከፋ
መሳሉስ ባልከፋ
ወጀብ የፈጠረው ባጀብ እንዳይጠፋ
ወዳጄን ጥሩልኝ እናውራ በወጉ
ከመንጋው ቢጠፋ አይሸጥም በጉ
ሰይፈ ተማም 2008
ቡሄ በሉ
ከ ሰይፈ ተማም
=======
ቡሄ የልጆች በዓል ነው። ልጅ እያለን ትዝ ይለኛል ከነ ሰይድ ጋራ ሆያሆዬ ስንጨፍር - እነ ጋሽ ጃፈር ቤት ሁሉ ብር ይሰጠናል እንጂ ተባረን አናውቅም።ሃገሪቷ ውስጥ የፈጠራ ችሎታ ማነሱን ከሚያመላክቱ ነገሮች አንዱ (ከዚህ ፅሁፍ ውጪ ማለት ነው)አዲስአባ ውስጥ እንዳሉ ታሪካዊ ህንፃዎች ያልታደሱት የሆያሆዬ ግጥሞች ናቸው።በቀን የሶስት ወይም የአራት ታክሲ ገቢ የሚያስገባ ልማታዊ ልጥጥ ሱቅ በር ላይ" እዛ ማዶ አንድ ካልሲእዚህ ማዶ አንድ ካልሲየዚህ ቤት ጌታ ባለታክሲ"ይህን ሲባል በየቀኑ እየተጋጨ እና በሹፌሩ ሰበብ እየታሰረ አማሮት የሸጠው ታክሲ አይኑ ላይ ድቅን ሲል የሆያሆዬ ባንዱን በንዴት ያፈራርሰዋል ልማታዊ ልጥጡ ይህን ሲያደርግ ያየ ለሃገርናባህል ተቆርቅሪ ነኝ ባይ አልፎ ሂያጅ በእርሱ የልጅነት ዘመን የተገጠሙ ቡሄ በሉ ግጥሞችን በውስጡ 'ሆ' እያለ በመስማት ላይ ሳለ ልማታዊ ልጥጡን ለባህል መጥፋት አንዱ ተጠያቂ አርጎ ኮንኖ ማስቲካውን ይለጥጣል።የግድ በየማዶው አንድ ነገር እንዲያሰፍር የተፈረደበት ቡሄበሉ ግጥም እንደምንም ብሎ ሌላ ማዶ ይቀጥላል...በሬ ላይ የቆሙትን ሶስት ሆያሆዬያን አዲስ ግጥም ያላቸው እንደሆን ጠየኳቸው ደሞዛቸው እንደ ግጥማቸው አሪፍነት እንደሚያድግም ነገርኳቸው"እዛ ማዶ አንድ ኮምፒተር" አሉ በወኔ እኔም ዘመኑን የመሰለ እንደ ቀበሌ ነው ወረዳ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ ሊሰሩ ነው ብዬ ስጠብቅ"እዚ ማዶ አንድ ኮምፒተርየዚህ ቤት ጌታ ሊሄድ ነው አሜሪካን" ያቺን የሳንቲም አንድ ብር ከማግኘታቸው በፊት በሆዴ ያልኩትን ፊቴ ላይ ሳያዩ አይቀርም እኔም 'እድሜ ልኬን የሞከርኩት ዲቪ ለማስተዛዘኛ ኤምባሲው ጋር እንኳን አድርሶኝ አያውቅም' ነበር ያልኩት። ልጆቹ ከሄዱ በኋላ ሳስበው ግን በዚች ከልጥጦች ልጥጥነት፣ ከጠባቦች ጠባብነት፣ ከሙሰኞች ሙሰኝነት እና ከመሳሰሉት ውጭ ነገሮች ወይ በበጎ በማይለዋወጡበት ወይ ማንነትን የሚገልፁቱ ከዘመኑ ጋር በማይቀጥሉበት ሃገር እየኖሩ ምን ፍጠሩ ሊባሉ ኖሯል? እስኪ አስቡት ሁለት ወጣት ባልና ሚስት ያዩ ልጆች"እዛ ማዶ አንድ አሞራአዚ ማዶ ሌላ አሞራየኔማ እንትና ዛራና ቻንድራ" ቢሉ... የአገልግሎት ግዜ ያለፈባቸው የቡሄ ግጥሞች ተጠቃሚው ጋር እንዳይደርሱ ተመልክቶ የማያውቀው የሚመለከተው አካል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል - አንዳንድ የአዱስ አበባ ነዋሪዎች ሳይሆኑ እኔ ነኝ ያልኩት። ለዚህም ጎረቤቴ ብርሃኑ ላይ የተገጠመውን ማየት በቂ ነው።"እዛ ማዶ አንድ ብር እዚ ማዶ አንድ ብርየዚ ቤት ጌታ ባለባቡር"ከውስጥ የነበረው ብሬ ይህ ጊዜው ያለፈበት ግጥም አቅለሽልሾት "የዚህ ቤት ጌታ ኢሃዲግ ነው አሏቹ?" ብሎ ልጆቹ ላይ አስታውኮ ይህንን ሲል የሰማው አዋቂ ያለ እንደሆን ዙሪያውን በፍጥነት ገለማምጦ በሩን ጠርቅሞት ገባ። እኔም አዳዲስ እና ነባር እንዲሁም ሪሚክስ የተደረጉ ስራዎችን የሚያ ቀርቡ አባላት ያሉት የሆያሆዬ ባንድ በምናቤ አቋቋምኩለት...እዛ ማዶ የላም ወተት(እንዴ የወተት ላም ነች የላም ወተት? ወይስ የለም ወተት? ቆይ እስኪ እዚ ማዶ ይድገሙትእዚ ማዶ የላም ወተትየኔማ ብሬ አይዘውም አተትኢሽሽ አሁን ይሄ ሟርት ነው ሙገሳ?... እዛ ማዶ አንድ ዶሮእዚ ማዶ አንድ ዶሮየኔማ ብሬ ቴዲ አፍሮ(ኧረ ሳያፍር ነው አሪፍ...ደሞ ሊያሳስሩን ነው እንዴ..)እዛ ማዶ አንድ ጠመኔ'ዝምበል!' አለ ብሬ በንዴት'ኧረ አሪፍ አዲስ ግጥም ነው' የባንዱ መሪ ነበር።ብሬም እጁን እያወናጨፈ 'በቃ በቃ ኔ በምትባል ፊደል የሚገጥም ምንም ደህና ነገር የለም' አለ። ... ብሬ ደሞ ያበዛዋል ገና ለገና ወ*ኔ ሊሉ ነው ብሎ...
ቡሄ
2008
ከ ሰይፈ ተማም
=======
ቡሄ የልጆች በዓል ነው። ልጅ እያለን ትዝ ይለኛል ከነ ሰይድ ጋራ ሆያሆዬ ስንጨፍር - እነ ጋሽ ጃፈር ቤት ሁሉ ብር ይሰጠናል እንጂ ተባረን አናውቅም።ሃገሪቷ ውስጥ የፈጠራ ችሎታ ማነሱን ከሚያመላክቱ ነገሮች አንዱ (ከዚህ ፅሁፍ ውጪ ማለት ነው)አዲስአባ ውስጥ እንዳሉ ታሪካዊ ህንፃዎች ያልታደሱት የሆያሆዬ ግጥሞች ናቸው።በቀን የሶስት ወይም የአራት ታክሲ ገቢ የሚያስገባ ልማታዊ ልጥጥ ሱቅ በር ላይ" እዛ ማዶ አንድ ካልሲእዚህ ማዶ አንድ ካልሲየዚህ ቤት ጌታ ባለታክሲ"ይህን ሲባል በየቀኑ እየተጋጨ እና በሹፌሩ ሰበብ እየታሰረ አማሮት የሸጠው ታክሲ አይኑ ላይ ድቅን ሲል የሆያሆዬ ባንዱን በንዴት ያፈራርሰዋል ልማታዊ ልጥጡ ይህን ሲያደርግ ያየ ለሃገርናባህል ተቆርቅሪ ነኝ ባይ አልፎ ሂያጅ በእርሱ የልጅነት ዘመን የተገጠሙ ቡሄ በሉ ግጥሞችን በውስጡ 'ሆ' እያለ በመስማት ላይ ሳለ ልማታዊ ልጥጡን ለባህል መጥፋት አንዱ ተጠያቂ አርጎ ኮንኖ ማስቲካውን ይለጥጣል።የግድ በየማዶው አንድ ነገር እንዲያሰፍር የተፈረደበት ቡሄበሉ ግጥም እንደምንም ብሎ ሌላ ማዶ ይቀጥላል...በሬ ላይ የቆሙትን ሶስት ሆያሆዬያን አዲስ ግጥም ያላቸው እንደሆን ጠየኳቸው ደሞዛቸው እንደ ግጥማቸው አሪፍነት እንደሚያድግም ነገርኳቸው"እዛ ማዶ አንድ ኮምፒተር" አሉ በወኔ እኔም ዘመኑን የመሰለ እንደ ቀበሌ ነው ወረዳ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ ሊሰሩ ነው ብዬ ስጠብቅ"እዚ ማዶ አንድ ኮምፒተርየዚህ ቤት ጌታ ሊሄድ ነው አሜሪካን" ያቺን የሳንቲም አንድ ብር ከማግኘታቸው በፊት በሆዴ ያልኩትን ፊቴ ላይ ሳያዩ አይቀርም እኔም 'እድሜ ልኬን የሞከርኩት ዲቪ ለማስተዛዘኛ ኤምባሲው ጋር እንኳን አድርሶኝ አያውቅም' ነበር ያልኩት። ልጆቹ ከሄዱ በኋላ ሳስበው ግን በዚች ከልጥጦች ልጥጥነት፣ ከጠባቦች ጠባብነት፣ ከሙሰኞች ሙሰኝነት እና ከመሳሰሉት ውጭ ነገሮች ወይ በበጎ በማይለዋወጡበት ወይ ማንነትን የሚገልፁቱ ከዘመኑ ጋር በማይቀጥሉበት ሃገር እየኖሩ ምን ፍጠሩ ሊባሉ ኖሯል? እስኪ አስቡት ሁለት ወጣት ባልና ሚስት ያዩ ልጆች"እዛ ማዶ አንድ አሞራአዚ ማዶ ሌላ አሞራየኔማ እንትና ዛራና ቻንድራ" ቢሉ... የአገልግሎት ግዜ ያለፈባቸው የቡሄ ግጥሞች ተጠቃሚው ጋር እንዳይደርሱ ተመልክቶ የማያውቀው የሚመለከተው አካል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል - አንዳንድ የአዱስ አበባ ነዋሪዎች ሳይሆኑ እኔ ነኝ ያልኩት። ለዚህም ጎረቤቴ ብርሃኑ ላይ የተገጠመውን ማየት በቂ ነው።"እዛ ማዶ አንድ ብር እዚ ማዶ አንድ ብርየዚ ቤት ጌታ ባለባቡር"ከውስጥ የነበረው ብሬ ይህ ጊዜው ያለፈበት ግጥም አቅለሽልሾት "የዚህ ቤት ጌታ ኢሃዲግ ነው አሏቹ?" ብሎ ልጆቹ ላይ አስታውኮ ይህንን ሲል የሰማው አዋቂ ያለ እንደሆን ዙሪያውን በፍጥነት ገለማምጦ በሩን ጠርቅሞት ገባ። እኔም አዳዲስ እና ነባር እንዲሁም ሪሚክስ የተደረጉ ስራዎችን የሚያ ቀርቡ አባላት ያሉት የሆያሆዬ ባንድ በምናቤ አቋቋምኩለት...እዛ ማዶ የላም ወተት(እንዴ የወተት ላም ነች የላም ወተት? ወይስ የለም ወተት? ቆይ እስኪ እዚ ማዶ ይድገሙትእዚ ማዶ የላም ወተትየኔማ ብሬ አይዘውም አተትኢሽሽ አሁን ይሄ ሟርት ነው ሙገሳ?... እዛ ማዶ አንድ ዶሮእዚ ማዶ አንድ ዶሮየኔማ ብሬ ቴዲ አፍሮ(ኧረ ሳያፍር ነው አሪፍ...ደሞ ሊያሳስሩን ነው እንዴ..)እዛ ማዶ አንድ ጠመኔ'ዝምበል!' አለ ብሬ በንዴት'ኧረ አሪፍ አዲስ ግጥም ነው' የባንዱ መሪ ነበር።ብሬም እጁን እያወናጨፈ 'በቃ በቃ ኔ በምትባል ፊደል የሚገጥም ምንም ደህና ነገር የለም' አለ። ... ብሬ ደሞ ያበዛዋል ገና ለገና ወ*ኔ ሊሉ ነው ብሎ...
ቡሄ
2008
የረሳሁት እኔ...
የዘነበው ዝናብ ካለሽበት ሃገር
ከጉንጬ ተንኖ ነው ናፍቆቴን ሊናገር
የነፈሰው ንፋስ ፊትሽን ‘ሚዳስስ
‘ኡፍ’ ያልኩት ትንፋሽ ነው ጭንቀቴ ሲባባስ
ያለሽበት ቦታ ምሽቱ ‘ማይመሸው
በሰቀቀን ሃሳብ
ያንቺን መምጣት ሳስብ
የኔቀን አጥሮ ነው
...
የሄድንበት መንገድ አንገትሽን ከእጄ
እጅሽ ከወገቤ
ልብሽን በልቤ
ፍቅርሽን አጥምጄ
ያረፍንበት ጥላ ካንደበት እርቀን አይኖችሽን ሳነብ
በመኖርሽ ስቄ በመኖሬ ስቀሽ ሃሴት ስንመገብ
በጠራራ ፀሃይ እንደምሽት መስለን
ደሞ በምሽቱ እንደፀሃይ ደምቀን
ተጓዥ መንገደኛው ካይን ያውጣቹ እያለ ከአይኑ ሲከተን
‘ባይኑ ሲከተለን
ጎርፍ ጭቃ ቁሩን መኖርሽ አስኪዶ
መኖሬም ወበቁን ንዳዱን አብርዶ
እኛ ዘንድ ተውበው ካፊያ ዶፍ በረዶ
ይህን እና ሌላ ካንቺ ጋር የሄዱ እየመላለሱ
የረሳሁት እኔን የማልረሳሽ አንቺን እየቀሰቀሱ
ማንኔተን ነቅሰው ፍቅር ነህ እያሉ እኔን አስታወሱ
#seifetemam #የረሳሁትእኔ
የዘነበው ዝናብ ካለሽበት ሃገር
ከጉንጬ ተንኖ ነው ናፍቆቴን ሊናገር
የነፈሰው ንፋስ ፊትሽን ‘ሚዳስስ
‘ኡፍ’ ያልኩት ትንፋሽ ነው ጭንቀቴ ሲባባስ
ያለሽበት ቦታ ምሽቱ ‘ማይመሸው
በሰቀቀን ሃሳብ
ያንቺን መምጣት ሳስብ
የኔቀን አጥሮ ነው
...
የሄድንበት መንገድ አንገትሽን ከእጄ
እጅሽ ከወገቤ
ልብሽን በልቤ
ፍቅርሽን አጥምጄ
ያረፍንበት ጥላ ካንደበት እርቀን አይኖችሽን ሳነብ
በመኖርሽ ስቄ በመኖሬ ስቀሽ ሃሴት ስንመገብ
በጠራራ ፀሃይ እንደምሽት መስለን
ደሞ በምሽቱ እንደፀሃይ ደምቀን
ተጓዥ መንገደኛው ካይን ያውጣቹ እያለ ከአይኑ ሲከተን
‘ባይኑ ሲከተለን
ጎርፍ ጭቃ ቁሩን መኖርሽ አስኪዶ
መኖሬም ወበቁን ንዳዱን አብርዶ
እኛ ዘንድ ተውበው ካፊያ ዶፍ በረዶ
ይህን እና ሌላ ካንቺ ጋር የሄዱ እየመላለሱ
የረሳሁት እኔን የማልረሳሽ አንቺን እየቀሰቀሱ
ማንኔተን ነቅሰው ፍቅር ነህ እያሉ እኔን አስታወሱ
#seifetemam #የረሳሁትእኔ
👍1
ለህይወትህ ዋጋ አትስጥ
ከዋጋም በላይ ነች
Priceless እንዲል ነጭ
ከምትወደው ሁሉ ነፍስህን አስበልጥ
ከፍ እንድታደርጋት ለህይወትህ ዋጋ አትስጥ
#seifetemam 2006 #ለህይወትህ_ዋጋ_አትስጥ
ከዋጋም በላይ ነች
Priceless እንዲል ነጭ
ከምትወደው ሁሉ ነፍስህን አስበልጥ
ከፍ እንድታደርጋት ለህይወትህ ዋጋ አትስጥ
#seifetemam 2006 #ለህይወትህ_ዋጋ_አትስጥ