ነገ ዛሬ
ዛሬ ሲቻል ለነገ አልኩ
ነገም ደርሶ ነገን አከልኩ
ከነገወዲያም ደሞ መቶ
ነገ ሊባል ሰበብ ሞልቶ
ነገ ሲባል ተጎትቶ
በነ ነገ ነገር ተወግቶ
ባንዱ ነገ ውስጥ ተካቶ
እቅድ ተገኘ ሞቶ
እምጽ አምጵጽ
#seifetemam
ዛሬ ሲቻል ለነገ አልኩ
ነገም ደርሶ ነገን አከልኩ
ከነገወዲያም ደሞ መቶ
ነገ ሊባል ሰበብ ሞልቶ
ነገ ሲባል ተጎትቶ
በነ ነገ ነገር ተወግቶ
ባንዱ ነገ ውስጥ ተካቶ
እቅድ ተገኘ ሞቶ
እምጽ አምጵጽ
#seifetemam
ግጥም ሲጥም:
ቀና ልብ
ያልቀጠረውን ሰው ናፍቆ የሚጠብቅ
በውድቅት ለሊት ጨረቃን የሚሞቅ
ካለም ብርሃናት ላይ ወዳጁን የሚስል
በወደደው መጠን መውደዱን 'ሚያክል
በደም እና በ'ምነት በተስፋ የጸና
ልብስ ይኸውልሽ በፍቅር የቀና
#seifetemam
ቀና ልብ
ያልቀጠረውን ሰው ናፍቆ የሚጠብቅ
በውድቅት ለሊት ጨረቃን የሚሞቅ
ካለም ብርሃናት ላይ ወዳጁን የሚስል
በወደደው መጠን መውደዱን 'ሚያክል
በደም እና በ'ምነት በተስፋ የጸና
ልብስ ይኸውልሽ በፍቅር የቀና
#seifetemam
እውነቱን ልንገርሽ
(በ ሰይፈ ተማም)
እውነቱን ልንገርሽ
ከራሴ አስበልጬ አንቺን የምወደው
እያለሽ ናፋቂ
እየሄድሽ አድናቂ
ተራግመሽ መራቂ
ልቤን ብጠላ ነው
እውነቱን ልንገርሽ
ከራሴ አስበልጬ አንቺን እምወድሽ
ከፋት ብሎ ሚያምጥ
ሳቀች ብሎ ሚያገጥ
ኖረሽ የማይወዛ
ሄደሽ የማይከሳ
ሆኜ ብገኝልሽ
አንቺን የምወደው አብልጬ ከራሴ
አይንሽን ለማየት ጨረር እማይፈራ
አለሽበት ሊደርስ መንገድ ሚሰራ
ጣትሽን ለመንካት ጣቱን ሚሰዋ
ቃልሽን ለመስማት መናኝ እስከ ህዋ
የሆነው አካሌን ብትጠላው ነፍሴ
ከማንም አብልጬ አንቺን የወደድኩኝ
የወደድሽው ሁሉ...
በፍቅር አሳቦ
ቅናትን ሰብስቦ
ቢያስጨንቀኝ ከቦ
(አንቺን ከማስበለጥ) አማራጭ አጣሁኝ
ህዳር ፳፬፣ ፪፼፯ ዓም
#seifetemam
(በ ሰይፈ ተማም)
እውነቱን ልንገርሽ
ከራሴ አስበልጬ አንቺን የምወደው
እያለሽ ናፋቂ
እየሄድሽ አድናቂ
ተራግመሽ መራቂ
ልቤን ብጠላ ነው
እውነቱን ልንገርሽ
ከራሴ አስበልጬ አንቺን እምወድሽ
ከፋት ብሎ ሚያምጥ
ሳቀች ብሎ ሚያገጥ
ኖረሽ የማይወዛ
ሄደሽ የማይከሳ
ሆኜ ብገኝልሽ
አንቺን የምወደው አብልጬ ከራሴ
አይንሽን ለማየት ጨረር እማይፈራ
አለሽበት ሊደርስ መንገድ ሚሰራ
ጣትሽን ለመንካት ጣቱን ሚሰዋ
ቃልሽን ለመስማት መናኝ እስከ ህዋ
የሆነው አካሌን ብትጠላው ነፍሴ
ከማንም አብልጬ አንቺን የወደድኩኝ
የወደድሽው ሁሉ...
በፍቅር አሳቦ
ቅናትን ሰብስቦ
ቢያስጨንቀኝ ከቦ
(አንቺን ከማስበለጥ) አማራጭ አጣሁኝ
ህዳር ፳፬፣ ፪፼፯ ዓም
#seifetemam
ወዳጄ
ጠጥቶ ጠጥቶ ጠጥቶ
ውሃም ይሁን ጠላ ተግቶ ተግቶ
ግድግዳ ይጠጋል
አጥር ይደገፋል ጀርባ ለሰው ሰጥቶ
አጥር ስር ማስለቀስ ህቅም እንኳን ሳይለው
ሊከልል ይጥራል
የሰውነቱ አካል ሆኖበት ማፈሪያው
(ጋሼ Seife ...አስለቃሽህ ወዳጅህን ጠምጄዋለሁ ዛሬ)
የጌታነህ ልጅ
ሐምሌ 22, 2009
ጠጥቶ ጠጥቶ ጠጥቶ
ውሃም ይሁን ጠላ ተግቶ ተግቶ
ግድግዳ ይጠጋል
አጥር ይደገፋል ጀርባ ለሰው ሰጥቶ
አጥር ስር ማስለቀስ ህቅም እንኳን ሳይለው
ሊከልል ይጥራል
የሰውነቱ አካል ሆኖበት ማፈሪያው
(ጋሼ Seife ...አስለቃሽህ ወዳጅህን ጠምጄዋለሁ ዛሬ)
የጌታነህ ልጅ
ሐምሌ 22, 2009
ዋጋ የለሽም
ምክንያቴን ሁሌም ተረጂው
ቢለይብሽም መንገዴ
ተመን የለኝም ላንቺ
ከቶም አልልሽ ውዴ
በዚች ኮተታም አለም
ኦና ቤቴን ካሻሽም
ውድነት ቢያረክስሽ እንጂ
አንቺስ ዋጋ የለሽም
#seifetemam
ምክንያቴን ሁሌም ተረጂው
ቢለይብሽም መንገዴ
ተመን የለኝም ላንቺ
ከቶም አልልሽ ውዴ
በዚች ኮተታም አለም
ኦና ቤቴን ካሻሽም
ውድነት ቢያረክስሽ እንጂ
አንቺስ ዋጋ የለሽም
#seifetemam
ለ አባባ ተስፋዬ 1
'ዛሬ አበባዎች
የነገ ፍሬዎች'
ብለው ከጠሯቸው ስንቶቹ ረገፉ?
ለሳሎን ጌጥነት ስንቶች ተቀጠፉ?
እርሶስ ፍሬ ሆነው ተዘርተው አለፉ::
#seifetemam
'ዛሬ አበባዎች
የነገ ፍሬዎች'
ብለው ከጠሯቸው ስንቶቹ ረገፉ?
ለሳሎን ጌጥነት ስንቶች ተቀጠፉ?
እርሶስ ፍሬ ሆነው ተዘርተው አለፉ::
#seifetemam
ለአባባ ተስፋዬ 2
ያኔ...
የፕላስቲክ ኮዳ የሞባይል ካርዱ
መንገድ ሳይከመር
መስኮትና ጣሪያው በዲሽ ሳይወረር
አንድ ቲቪ ብቻ ላንድ ሙሉ ሰፈር
አንድ ቲቪ ቻናል ላንድ ሙሉ ሃገር
አንድ ሰው ብቻውን ስንቱን ያስቆም ነበር?
ኋላ ላይ...
እንደ'ውቀት ፍሬ ልጅ ሁሉ እድሜ በላ
እንደ አዳም ባነነ ጩጬ ና ፈልፈላ
ገባው እንደሌሉ አባባ ተስፋዬ
ከስክሪኑ ኋላ
ፎገሩኝ እያለ ተካቸው በሌላ
ከዛም...
ቴሌቭዥኑም ከስቶ እንደእንጀራ ሳሳ
ገብስ ወረረው ፈልቶ የአበባውን ማሳ
ልጅ ባገሩ በዝቶም ልጅ ሁላ ተረሳ
(በአካል ተከስቶም) ለአባባ ተስፋዬ ጠፋ የሚነሳ
ከዛም በኋላ...
ለገዢው መደብ ጦር ተሰለፉ ልጆች
ለአባይ ዘመሩ ጮሁ ለታጋዮች
'ብሔር ብሔረሰቦች'
ከ'ዛ በኋላም በኋላ...
እነዛን ተወዝዋዥ እጆች
እስኪዘክራቸው ታሪክ
እስኪገኝ የአባባ ምትክ
አዋቂው እንደ ልጅ ይጃጃል
ልጅም ይቅበጥ በአዋቂ ልክ
ማንም ለማንም አይነሳ
እራሱን ያክብር ዘመኑ
'1' እና '0'ን ቀምሩ
የ'1' እና '0' ነው ቀኑ
በሉ ልጆች ደህና ሁኑ
ደህና ሁኑ ደህና ሁኑ
#seifetemam
ያኔ...
የፕላስቲክ ኮዳ የሞባይል ካርዱ
መንገድ ሳይከመር
መስኮትና ጣሪያው በዲሽ ሳይወረር
አንድ ቲቪ ብቻ ላንድ ሙሉ ሰፈር
አንድ ቲቪ ቻናል ላንድ ሙሉ ሃገር
አንድ ሰው ብቻውን ስንቱን ያስቆም ነበር?
ኋላ ላይ...
እንደ'ውቀት ፍሬ ልጅ ሁሉ እድሜ በላ
እንደ አዳም ባነነ ጩጬ ና ፈልፈላ
ገባው እንደሌሉ አባባ ተስፋዬ
ከስክሪኑ ኋላ
ፎገሩኝ እያለ ተካቸው በሌላ
ከዛም...
ቴሌቭዥኑም ከስቶ እንደእንጀራ ሳሳ
ገብስ ወረረው ፈልቶ የአበባውን ማሳ
ልጅ ባገሩ በዝቶም ልጅ ሁላ ተረሳ
(በአካል ተከስቶም) ለአባባ ተስፋዬ ጠፋ የሚነሳ
ከዛም በኋላ...
ለገዢው መደብ ጦር ተሰለፉ ልጆች
ለአባይ ዘመሩ ጮሁ ለታጋዮች
'ብሔር ብሔረሰቦች'
ከ'ዛ በኋላም በኋላ...
እነዛን ተወዝዋዥ እጆች
እስኪዘክራቸው ታሪክ
እስኪገኝ የአባባ ምትክ
አዋቂው እንደ ልጅ ይጃጃል
ልጅም ይቅበጥ በአዋቂ ልክ
ማንም ለማንም አይነሳ
እራሱን ያክብር ዘመኑ
'1' እና '0'ን ቀምሩ
የ'1' እና '0' ነው ቀኑ
በሉ ልጆች ደህና ሁኑ
ደህና ሁኑ ደህና ሁኑ
#seifetemam
ለማፍቀር ቀጠሮ
ሸትታ 'ምትገለማ
መርቅዛ 'ምትገማ
ወፍፋ ያበደች
ጨርቋን ጥላ የሄደች
ማንነቷን ስታ
ከሆነው ተጣልታ
ካልሆነው ተጣብታ
ያልሆነውን ሽታ
ማስመሰል አብዝታ
በመክሰም ለማበብ
በመግደል ለማከም
በምታደክም አለም
ውዴ አንቺን ልወድሽ
'ሚገባ አይደለም
...
... ... ስለዚህ
...
በናርዶስ ምዓዛሽ የዝች ቅርናት አለም ሽታዋ ከጠፋ
ወይ ሰናይ ፀባይሽ አሽሏት እንደሆን እንዳትቀር ወፍፋ
ማስመሰሏን ከሳ
እራሷን ስትሆነው ደግሞ ተመልሳ
ቀጠሮ ስላለኝ ያንግዜ ልወድሽ
አለሜን አክምያት እንዳይረፍድ ባክሽ
#seifetemam
ሸትታ 'ምትገለማ
መርቅዛ 'ምትገማ
ወፍፋ ያበደች
ጨርቋን ጥላ የሄደች
ማንነቷን ስታ
ከሆነው ተጣልታ
ካልሆነው ተጣብታ
ያልሆነውን ሽታ
ማስመሰል አብዝታ
በመክሰም ለማበብ
በመግደል ለማከም
በምታደክም አለም
ውዴ አንቺን ልወድሽ
'ሚገባ አይደለም
...
... ... ስለዚህ
...
በናርዶስ ምዓዛሽ የዝች ቅርናት አለም ሽታዋ ከጠፋ
ወይ ሰናይ ፀባይሽ አሽሏት እንደሆን እንዳትቀር ወፍፋ
ማስመሰሏን ከሳ
እራሷን ስትሆነው ደግሞ ተመልሳ
ቀጠሮ ስላለኝ ያንግዜ ልወድሽ
አለሜን አክምያት እንዳይረፍድ ባክሽ
#seifetemam
የገጣችን ታዳሚዎች ሆይ
ከስር በተቀመጠው ማግኛ (link) ከ9500 በላይ ወዳጆች ያሉትን የ ፌስቡክ ገጣችንን ትጎበኙት ዘንድ ተጋብዛችኋል https://www.facebook.com/gitemsitem/
ከስር በተቀመጠው ማግኛ (link) ከ9500 በላይ ወዳጆች ያሉትን የ ፌስቡክ ገጣችንን ትጎበኙት ዘንድ ተጋብዛችኋል https://www.facebook.com/gitemsitem/
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
