ድርሻ
ከተቆላው ቡና አሁን ከጠጣነው
የትኛው ፍሬ ይሆን እንደዚህ ያጣመው?
የትኛው ልቃሚ ወደአፈር ተጣለ
የቱ ጋር በስብሶስ በፍግነት ዋለ
የቱ ምን ለየቱ ምን ምኑ ጋር ዘመደ
የቱ ዛፍ ተቆርጦ የቱ ከሰል ነዶ ጀበናው ተጣደ
ከየትኛው አፈር ጀበናው ተበጀ
የትኛው ሰው ሞቶ አፈሩ ደረጀ
የትኛውን ሰው ነው
ጀበና ነው ብለን ከእሳቱ የጣድነው
ጥኡም ቡና ብለን አሁን የጠጣነው
...
ግን...
የቱ ምን ለየቱ ምን ምኑ ተቆራኘ
የትኛው ቅንጣት ነው ይህንን የቃኘ
ወዘተ ተብሎ የቱ የት ተገኘ
የቡናስ ገለባ እንዴት ተሰናኘ?
የሰው መሆን አጽናፍ የጭንቅላት ዳሩ
የንዝረት ስብጥር የብርሃን በሩ
የጨረር ጥርቅም በራሳቸው 'ሚያዩ
እነዚህ አይኖች መሀል ሰውነት ተተክሎ
አንዱ ኳስ የሚለው ለሌላው አሎሎ
አንዱ የለቀመውን ሌላው ቡና ብሎ
ተሰጠን ፀጋ ግን እንካችሁ ተብሎ
የመንጻት ምድጃ የስልጣን ረከቦት
የኃይል መቁያ ምጣዱ የበረከት
በጥበብ ተለቅሞ እኩል ከተቆላ
የዶሮአይን ብለው ይጠጡታል ኋላ
የሰው ዓይንማ ፊትለፊቱን እንጂ ውስጡን እረስቷላ
የሰው መሆን አጽናፍ የጭንቅላት ዳሩ
የንዝረት ስብጥር የብርሃን በሩ
የጨረር ፍላጾች በውስጡ እንዳሉ
አያይማ
የቡናው ፍሬዎች መለከት ሲነፉ
ስስ ገለባዎችም ባየር ሲንሳፈፉ
አይሰማማ
በዓይኑ ማየት ትቶ ልቡን ካልቀኛኘ
ሁሉን ፍሬ አክብሮ ካላቆረኛኘ
አይጸድቅማ
ቡና እንኳን ጥሎበት ጥላ ይወዳል አሉ
ምነው ድርሻ አጣን ማኖሪያ ላምሳሉ
ምነው ልብ ያላልነው ፍሬዎች ሲጣሉ
ምነው እሳ ምነው ምነው የማትሉ
ከተቆላው ቡና አሁን ከጠጣነው
የትኛው ፍሬ ይሆን እንደዚህ ያጣመው?
የትኛው ልቃሚ ወደአፈር ተጣለ
የቱ ጋር በስብሶስ በፍግነት ዋለ
የቱ ምን ለየቱ ምን ምኑ ጋር ዘመደ
የቱ ዛፍ ተቆርጦ የቱ ከሰል ነዶ ጀበናው ተጣደ
ሰይፈ ተማም 2010 -
Neurodiversity at Lebawi
ከተቆላው ቡና አሁን ከጠጣነው
የትኛው ፍሬ ይሆን እንደዚህ ያጣመው?
የትኛው ልቃሚ ወደአፈር ተጣለ
የቱ ጋር በስብሶስ በፍግነት ዋለ
የቱ ምን ለየቱ ምን ምኑ ጋር ዘመደ
የቱ ዛፍ ተቆርጦ የቱ ከሰል ነዶ ጀበናው ተጣደ
ከየትኛው አፈር ጀበናው ተበጀ
የትኛው ሰው ሞቶ አፈሩ ደረጀ
የትኛውን ሰው ነው
ጀበና ነው ብለን ከእሳቱ የጣድነው
ጥኡም ቡና ብለን አሁን የጠጣነው
...
ግን...
የቱ ምን ለየቱ ምን ምኑ ተቆራኘ
የትኛው ቅንጣት ነው ይህንን የቃኘ
ወዘተ ተብሎ የቱ የት ተገኘ
የቡናስ ገለባ እንዴት ተሰናኘ?
የሰው መሆን አጽናፍ የጭንቅላት ዳሩ
የንዝረት ስብጥር የብርሃን በሩ
የጨረር ጥርቅም በራሳቸው 'ሚያዩ
እነዚህ አይኖች መሀል ሰውነት ተተክሎ
አንዱ ኳስ የሚለው ለሌላው አሎሎ
አንዱ የለቀመውን ሌላው ቡና ብሎ
ተሰጠን ፀጋ ግን እንካችሁ ተብሎ
የመንጻት ምድጃ የስልጣን ረከቦት
የኃይል መቁያ ምጣዱ የበረከት
በጥበብ ተለቅሞ እኩል ከተቆላ
የዶሮአይን ብለው ይጠጡታል ኋላ
የሰው ዓይንማ ፊትለፊቱን እንጂ ውስጡን እረስቷላ
የሰው መሆን አጽናፍ የጭንቅላት ዳሩ
የንዝረት ስብጥር የብርሃን በሩ
የጨረር ፍላጾች በውስጡ እንዳሉ
አያይማ
የቡናው ፍሬዎች መለከት ሲነፉ
ስስ ገለባዎችም ባየር ሲንሳፈፉ
አይሰማማ
በዓይኑ ማየት ትቶ ልቡን ካልቀኛኘ
ሁሉን ፍሬ አክብሮ ካላቆረኛኘ
አይጸድቅማ
ቡና እንኳን ጥሎበት ጥላ ይወዳል አሉ
ምነው ድርሻ አጣን ማኖሪያ ላምሳሉ
ምነው ልብ ያላልነው ፍሬዎች ሲጣሉ
ምነው እሳ ምነው ምነው የማትሉ
ከተቆላው ቡና አሁን ከጠጣነው
የትኛው ፍሬ ይሆን እንደዚህ ያጣመው?
የትኛው ልቃሚ ወደአፈር ተጣለ
የቱ ጋር በስብሶስ በፍግነት ዋለ
የቱ ምን ለየቱ ምን ምኑ ጋር ዘመደ
የቱ ዛፍ ተቆርጦ የቱ ከሰል ነዶ ጀበናው ተጣደ
ሰይፈ ተማም 2010 -
Neurodiversity at Lebawi
ውባለሜ
----------
አንቺን ማከም
እንዳሰብኩት ዋዛ አይደለም
አንቺ የኔ እኔም ያንቺ
እኔና አንቺም የሁሉ ነን
ሁሉም የኛ እኛም ሁሉን
ብለን ካመን
አምነን ካልን
ያልነውን
ስንሆን
ጥላቻ አይደል ወይም ስስት
'ራሴን ላክም የምታክት
ውባለሜ
በህመምሽ መታመሜ
ጎኔን ይዞኝ በመክሰሜ
አንቺን ማከም
እንዳሰብኩት ዋዛ አልሆነም
ውጋት ቁርጠት ትኩሳትሽ
በኔ ብሶ ታመምኩልሽ
የኔም ህመም ተጨምሮ
ከሚገፋሽ ጣርሽ ጥሮ
ይኧው ጉልበቴ በረከ
ልቤም መኖሬን ተረከ
የራሴን ጉድፍ ላጠራ
የጠፋ አይንሽ ባይበራ
ለቅሶሽን እንኳ ባባራ
እጄን ወደ ዓይኔ ላከ
ሌቱም ሲጠራ ማለዳ
ክብሬን ለአንገትሽ ማክዳ
ስሜን ከብርድ መዳኛ
አቅሜን ልክሽን ማፅኛ
አድርጌ አንቺን ላስታምም
ባልፈውስሽም እንኳ
ህመምሽ በኔ አይብስም...
እራሴን አቅፌ ስሜ
መቋሚያዪን አቅልሜ
ባላድንሽ እንዳያምሽ
'ደርስልሻለሁ አለሜ
ሰይፈ ተማም 2008ድሬ
----------
አንቺን ማከም
እንዳሰብኩት ዋዛ አይደለም
አንቺ የኔ እኔም ያንቺ
እኔና አንቺም የሁሉ ነን
ሁሉም የኛ እኛም ሁሉን
ብለን ካመን
አምነን ካልን
ያልነውን
ስንሆን
ጥላቻ አይደል ወይም ስስት
'ራሴን ላክም የምታክት
ውባለሜ
በህመምሽ መታመሜ
ጎኔን ይዞኝ በመክሰሜ
አንቺን ማከም
እንዳሰብኩት ዋዛ አልሆነም
ውጋት ቁርጠት ትኩሳትሽ
በኔ ብሶ ታመምኩልሽ
የኔም ህመም ተጨምሮ
ከሚገፋሽ ጣርሽ ጥሮ
ይኧው ጉልበቴ በረከ
ልቤም መኖሬን ተረከ
የራሴን ጉድፍ ላጠራ
የጠፋ አይንሽ ባይበራ
ለቅሶሽን እንኳ ባባራ
እጄን ወደ ዓይኔ ላከ
ሌቱም ሲጠራ ማለዳ
ክብሬን ለአንገትሽ ማክዳ
ስሜን ከብርድ መዳኛ
አቅሜን ልክሽን ማፅኛ
አድርጌ አንቺን ላስታምም
ባልፈውስሽም እንኳ
ህመምሽ በኔ አይብስም...
እራሴን አቅፌ ስሜ
መቋሚያዪን አቅልሜ
ባላድንሽ እንዳያምሽ
'ደርስልሻለሁ አለሜ
ሰይፈ ተማም 2008ድሬ
የጸባኦት ጣሪያ
(በ ሰይፈ ተማም)
ከደሜ ደም ተጣብቆ
የልቤን ልብ አርቆ
ከ ́እኔ ́ በላይ ዘልቆ
በመምጠቅ ህዋ ላይ
ከዛበ ላይ
መጥቆ
ሲፍለቀለቅ
ሲንዠቀዠቅ
ሲያብረቀርቅ
ሲርቅ
ሲመጥቅ
... ሲደባለቅ
አዩትና ይህ ንልዩ
አዩትና ́ከኔ ́በላይ
ካለው በላይ ከበላዩ
አዩትና በእንቅልፍልብ
አዩትና ባሳብ ክልብ
አዩትና . . .
(አይ ሰው ሞኙ
ስምወዳጁ ርዕስ ቀኙ)
. . .
ከደሜ አንጓ ተፈልቅቆ
ከ ́እኔ ́ በላይ ካጥናፍ ዘልቆ
በመምጠቅ ህዋ ላይ
ከዛ በላይ መጥቆ
ዘመን አልባ
ቅጽበት አልባ
የማይነጋ የማይጠባ
የማይተጋ የማይገባ
የማይለማ የማይሰባ
የጸጋ ለምድ የክብር ካባ
የንቁ አጸድ የፍቅር አምባ
መሻትን የማይሻ
ምሉዕ የሁሉ ድርሻ
ሰቶም እማይጎድል
ነዶም እማይከስል . . .
ያዩትን ብቻ ́ሚያዩ
ከትውስታ ሳይለዩ
አዩትና ይሄን ልዩ
አዩትና ካ ́ለምጋራ የዘገዩ
አይተው መስሏቸው ያዩ
ጻፍልን አሉኝ ስሙን
ጻፍልን አሉ ማሰሪያ
ጻፍልን አሉ ማጠሪያ
ጻፍልን አሉ መጠሪያ
ስም ያለው ይመስል
የጸባኦት ጣሪያ
(በ ሰይፈ ተማም)
ከደሜ ደም ተጣብቆ
የልቤን ልብ አርቆ
ከ ́እኔ ́ በላይ ዘልቆ
በመምጠቅ ህዋ ላይ
ከዛበ ላይ
መጥቆ
ሲፍለቀለቅ
ሲንዠቀዠቅ
ሲያብረቀርቅ
ሲርቅ
ሲመጥቅ
... ሲደባለቅ
አዩትና ይህ ንልዩ
አዩትና ́ከኔ ́በላይ
ካለው በላይ ከበላዩ
አዩትና በእንቅልፍልብ
አዩትና ባሳብ ክልብ
አዩትና . . .
(አይ ሰው ሞኙ
ስምወዳጁ ርዕስ ቀኙ)
. . .
ከደሜ አንጓ ተፈልቅቆ
ከ ́እኔ ́ በላይ ካጥናፍ ዘልቆ
በመምጠቅ ህዋ ላይ
ከዛ በላይ መጥቆ
ዘመን አልባ
ቅጽበት አልባ
የማይነጋ የማይጠባ
የማይተጋ የማይገባ
የማይለማ የማይሰባ
የጸጋ ለምድ የክብር ካባ
የንቁ አጸድ የፍቅር አምባ
መሻትን የማይሻ
ምሉዕ የሁሉ ድርሻ
ሰቶም እማይጎድል
ነዶም እማይከስል . . .
ያዩትን ብቻ ́ሚያዩ
ከትውስታ ሳይለዩ
አዩትና ይሄን ልዩ
አዩትና ካ ́ለምጋራ የዘገዩ
አይተው መስሏቸው ያዩ
ጻፍልን አሉኝ ስሙን
ጻፍልን አሉ ማሰሪያ
ጻፍልን አሉ ማጠሪያ
ጻፍልን አሉ መጠሪያ
ስም ያለው ይመስል
የጸባኦት ጣሪያ
ፍቅር ወይ ወንበዴ
አንገቴ ላይ ሽፍታ አለ
ልክ እንዳንቺ እየጠፋ የሚወረኝ ብቅ እያለ
የሳምሽኝ ለት ቻፒስቲክሽ ከቆዳዬ እንደታተመ
መኖርሽን ያህል ተስፋ መኖሬ ውስጥ አከረመ
ልነቀሰው ሁሉ ቃጣኝ የከንፈርሽን ቅርጽ አድምቄ
ማስታወሻ እንዲሆነን አሳሳምሽን አድንቄ
መሳም እፈራ ነበር
መሳም እፈራ ነበር
በሱ ነውና ጌትዬው ተሰቅሎ 'ሚቸነከር
ግና መቸንከር ሁሉ
አንድ አይደል እና ውሉ
ለተሳመም ሁላቸው
አንድነት ከየት አላቸው
ፍቅር ተስሞ ተሽጦ ተክዶ ተገርፎ ይደማል
ዝቅ ባረጉት ቁጥር አይሎ ጭራሽ ከፍ ይላል
ስመው ባስያዙት ቁጥር ተሰቅሎ ቤዛ ይሆናል
ማን ያውቃል?
የግራውንስ ወንበዴ ማን አሳልፎ ሰጥቶታል
ነጭ ለብሶ አስጠቁሮታል
የቱ ይሁዳ ስሞታል
ከፍቅር በተቃራኒ በማይመለክ መስቀል
ሳይቤዥ አሰቅሎታል
አንገቴ ላይ ሽፍታ አለ
ልክ እንዳንቺ እየጠፋ የሚወረኝ ብቅ እያለ
ተንጠራርተሽ ተንጠራርተሽ አንገቴ ላይ ስትስሚኝ
ፍቅርን ልሁን ወንበዴ ይሁዳዬ ስትሆኚልኝ??
ሰይፈ ተማም 2010
አንገቴ ላይ ሽፍታ አለ
ልክ እንዳንቺ እየጠፋ የሚወረኝ ብቅ እያለ
የሳምሽኝ ለት ቻፒስቲክሽ ከቆዳዬ እንደታተመ
መኖርሽን ያህል ተስፋ መኖሬ ውስጥ አከረመ
ልነቀሰው ሁሉ ቃጣኝ የከንፈርሽን ቅርጽ አድምቄ
ማስታወሻ እንዲሆነን አሳሳምሽን አድንቄ
መሳም እፈራ ነበር
መሳም እፈራ ነበር
በሱ ነውና ጌትዬው ተሰቅሎ 'ሚቸነከር
ግና መቸንከር ሁሉ
አንድ አይደል እና ውሉ
ለተሳመም ሁላቸው
አንድነት ከየት አላቸው
ፍቅር ተስሞ ተሽጦ ተክዶ ተገርፎ ይደማል
ዝቅ ባረጉት ቁጥር አይሎ ጭራሽ ከፍ ይላል
ስመው ባስያዙት ቁጥር ተሰቅሎ ቤዛ ይሆናል
ማን ያውቃል?
የግራውንስ ወንበዴ ማን አሳልፎ ሰጥቶታል
ነጭ ለብሶ አስጠቁሮታል
የቱ ይሁዳ ስሞታል
ከፍቅር በተቃራኒ በማይመለክ መስቀል
ሳይቤዥ አሰቅሎታል
አንገቴ ላይ ሽፍታ አለ
ልክ እንዳንቺ እየጠፋ የሚወረኝ ብቅ እያለ
ተንጠራርተሽ ተንጠራርተሽ አንገቴ ላይ ስትስሚኝ
ፍቅርን ልሁን ወንበዴ ይሁዳዬ ስትሆኚልኝ??
ሰይፈ ተማም 2010
#ያንቺ_ጭራ 1
ስልኳ ባልተነሳ ስልኳ ባልደወለ
አካሌ 'ሚሳሳ ቀልቤ የኮበለለ
ከቻት መዝገብ ባትኖር
ባይተዋር እምሆን
ሰልፊዬን ሰልፍዬ
ልቤን የማይመስል ልብቅርጽ አክዬ❤️
'ይወድሽ ነበረ' ከሚል ግጥም ጋራ
ታግ አርጊአት ነበር #ያንቺ_ጭራ
የምትስቅ ቢጫ ፊት የተንከተከተች 😁
ሰጥታኝ ደሞ ከታች ኮሜንት ኮመነተች
እሱን እስከማነብ ኔትወርኩ ተዘጋ
አጅሪት ቆየችኝ መአት ሰው አድ አርጋ
ቴሌ ፈቅዶ ድንገት ብገባ በመሃል
ወዬ የኔ ጭራ lol lol
ከሷ ስር ቀጥሎ ይጀነጅኗታል በገዛ ልጥፌ
ማሬ፣ ሴክሲ፣ የኔ ቆንጆ፣ wtኤፌ
😘 😍 💋 😍 😘
ግጥሙ ሲነበብ...
እወዳት ነበረ
እንደ ጥጋብ ዘመን ሁሉ እንደሞላለት
የኔን ነገር ትቼ በስሟ ስደሰት
እያደር እያደር ዋጋ ስለናረ
ሁሉ ርካሽ ሳለ እወዳት ነበረ
እኔ ያንቺ ጭራ
ኋላሽ ተለጥፌ ዝምብሽን 'እሽ' ባይ
ሁሌ 'ምከተልሽ ስትዞሪ ' ማልታይ
በየአደባባዩ ስምሽን የምጠራ
ሰርክ የምጠብቅሽ #ያንቺ_ጭራ
...ይቀጥላል
ሰይፈ ተማም 2010
ስልኳ ባልተነሳ ስልኳ ባልደወለ
አካሌ 'ሚሳሳ ቀልቤ የኮበለለ
ከቻት መዝገብ ባትኖር
ባይተዋር እምሆን
ሰልፊዬን ሰልፍዬ
ልቤን የማይመስል ልብቅርጽ አክዬ❤️
'ይወድሽ ነበረ' ከሚል ግጥም ጋራ
ታግ አርጊአት ነበር #ያንቺ_ጭራ
የምትስቅ ቢጫ ፊት የተንከተከተች 😁
ሰጥታኝ ደሞ ከታች ኮሜንት ኮመነተች
እሱን እስከማነብ ኔትወርኩ ተዘጋ
አጅሪት ቆየችኝ መአት ሰው አድ አርጋ
ቴሌ ፈቅዶ ድንገት ብገባ በመሃል
ወዬ የኔ ጭራ lol lol
ከሷ ስር ቀጥሎ ይጀነጅኗታል በገዛ ልጥፌ
ማሬ፣ ሴክሲ፣ የኔ ቆንጆ፣ wtኤፌ
😘 😍 💋 😍 😘
ግጥሙ ሲነበብ...
እወዳት ነበረ
እንደ ጥጋብ ዘመን ሁሉ እንደሞላለት
የኔን ነገር ትቼ በስሟ ስደሰት
እያደር እያደር ዋጋ ስለናረ
ሁሉ ርካሽ ሳለ እወዳት ነበረ
እኔ ያንቺ ጭራ
ኋላሽ ተለጥፌ ዝምብሽን 'እሽ' ባይ
ሁሌ 'ምከተልሽ ስትዞሪ ' ማልታይ
በየአደባባዩ ስምሽን የምጠራ
ሰርክ የምጠብቅሽ #ያንቺ_ጭራ
...ይቀጥላል
ሰይፈ ተማም 2010
3 አማራጭ አለህ
የጥበብ ሰው ሆይ
በልባቸው መጠን ነው ፍቅርን የምትጽፈው
ወይስ በፍቅር መጠን ልባቸውን ምትሰፍረው
ከመስመርህ ላይ አውጥተህ ስጋ ነው 'ምታለብሰው
ወይስ ሰጋ እየቀባህ ነፍስን ነው የምትስለው
ጥበብህን ስታሰፋ እንባ እና ሳቅ ጓጎሉብህ
ወይስ ሊጡ ቀለም ሆኖ እንጀራውም ቀለመብህ
የምትጽፈው የአለም ኑሮን እንደምነው ያስቀለለህ
ወይስ ቀላሉን ጻፍከው የአለም ኑሮ ነው ብለህ
አንደኛው
የሚፈልጉትን ስጣቸው የሚያስፈልጋቸውን አያውቁምና
ያጨብጭቡልህ ስማቸው ሰጥተሃቸዋል በቁና
ይሳቁ ጮቤ ይርገጡ ያልቅሱ ልባቸው ገብቶ
ይሰራጭ የጥበብ መልክህ በየሕዋሱ ተባዝቶ
ያድንቁህ ያምልኩህ ካሉ
ቃሎችህን እየጻፉ መስመሮችህን ይሳሉ
እንዳንተ ብቻ እንዲያስቡ በችሎታህ ይደመሙ
በቀለሞችህ አቅልመው በመስመሮችህ ይግጠሙ
ለስምህ ቢልቦርድ አቁመው ይጨቃጨቁ ባንተ
ደግሞ መልሰህ ሳላቸው ኑሮአቸውን 'ረጫጭተህ
የጥበብ ሰው ሆይ
ቆይ ግን
በብሶታቸው መጠን ነው ሃዘንን የምትጽፈው
ወይስ በሃዘናቸው ልክ ብሶትን የምትሰፈረው
ብሶቱን ውጦ ያዘነን በኩርፊያ ሆዱን ከባሰው
እንዴት ልታነቃው ነው አውቆ የተኛውን ሰው?
ሁለተኛው
የሚፈልጉትን አያውቁም እና የሚያስፈልጋቸውን ስጣቸው
በጸና ታመዋል እና መድሃኒት ሰርተህ ጋታቸው
አይሳቁ ይቁነጥነጡ ያጉረምርሙ
ያነዛንዛል በብዙ ምልክቱ ነው ህመሙ
አይስሙህ ዞር ብለው አይዩ
መስመሮችህን እረስተው ቀለሞችህን አይለዩ
እንደራሳቸው ይግባቸው ሳልላቸው እንዳንተ
ያልሰመረውን እያቀለመ በዝቷል መንገድ የሳተ
ስምህን በጉልህ አደብዝዘው ባንተ ይጨቃጨቁ
መልሰህ ደሞ ሳላቸው ከህልም አለም እንዲነቁ
የጥበብ ሰው ሆይ
በልባቸው መጠን ነው ፍቅርን የምትጽፈው
ወይስ በፍቅር መጠን ልባቸውን ምትሰፍረው
ከመስመርህ ላይ አውጥተህ ስጋ ነው 'ምታለብሰው
ወይስ ሰጋ እየቀባህ ነፍስን ነው የምትስለው
ጥበብህን ስታሰፋ እንባ እና ሳቅ ጓጎሉብህ
ወይስ ሊጡ ቀለም ሆኖ እንጀራውም ቀለመብህ
የምትጽፈው የአለም ኑሮን እንደምነው ያስቀለለህ
ወይስ ቀላሉን ጻፍከው የአለም ኑሮ ነው ብለህ
ወይስ አበጀህ መንገድ ቀላሉን ከበድ አድርገህ
ከባዱን ቀለል አድርገህ
ሶስተኛው
ዝምብለህ ጻፍ
ዝምብለህ ሳል
ዝምብለህ ጻፍ
ዝምብለህ ሳል
ሰይፈ ተማም 2010
ምስል: Robel Tekel
የጥበብ ሰው ሆይ
በልባቸው መጠን ነው ፍቅርን የምትጽፈው
ወይስ በፍቅር መጠን ልባቸውን ምትሰፍረው
ከመስመርህ ላይ አውጥተህ ስጋ ነው 'ምታለብሰው
ወይስ ሰጋ እየቀባህ ነፍስን ነው የምትስለው
ጥበብህን ስታሰፋ እንባ እና ሳቅ ጓጎሉብህ
ወይስ ሊጡ ቀለም ሆኖ እንጀራውም ቀለመብህ
የምትጽፈው የአለም ኑሮን እንደምነው ያስቀለለህ
ወይስ ቀላሉን ጻፍከው የአለም ኑሮ ነው ብለህ
አንደኛው
የሚፈልጉትን ስጣቸው የሚያስፈልጋቸውን አያውቁምና
ያጨብጭቡልህ ስማቸው ሰጥተሃቸዋል በቁና
ይሳቁ ጮቤ ይርገጡ ያልቅሱ ልባቸው ገብቶ
ይሰራጭ የጥበብ መልክህ በየሕዋሱ ተባዝቶ
ያድንቁህ ያምልኩህ ካሉ
ቃሎችህን እየጻፉ መስመሮችህን ይሳሉ
እንዳንተ ብቻ እንዲያስቡ በችሎታህ ይደመሙ
በቀለሞችህ አቅልመው በመስመሮችህ ይግጠሙ
ለስምህ ቢልቦርድ አቁመው ይጨቃጨቁ ባንተ
ደግሞ መልሰህ ሳላቸው ኑሮአቸውን 'ረጫጭተህ
የጥበብ ሰው ሆይ
ቆይ ግን
በብሶታቸው መጠን ነው ሃዘንን የምትጽፈው
ወይስ በሃዘናቸው ልክ ብሶትን የምትሰፈረው
ብሶቱን ውጦ ያዘነን በኩርፊያ ሆዱን ከባሰው
እንዴት ልታነቃው ነው አውቆ የተኛውን ሰው?
ሁለተኛው
የሚፈልጉትን አያውቁም እና የሚያስፈልጋቸውን ስጣቸው
በጸና ታመዋል እና መድሃኒት ሰርተህ ጋታቸው
አይሳቁ ይቁነጥነጡ ያጉረምርሙ
ያነዛንዛል በብዙ ምልክቱ ነው ህመሙ
አይስሙህ ዞር ብለው አይዩ
መስመሮችህን እረስተው ቀለሞችህን አይለዩ
እንደራሳቸው ይግባቸው ሳልላቸው እንዳንተ
ያልሰመረውን እያቀለመ በዝቷል መንገድ የሳተ
ስምህን በጉልህ አደብዝዘው ባንተ ይጨቃጨቁ
መልሰህ ደሞ ሳላቸው ከህልም አለም እንዲነቁ
የጥበብ ሰው ሆይ
በልባቸው መጠን ነው ፍቅርን የምትጽፈው
ወይስ በፍቅር መጠን ልባቸውን ምትሰፍረው
ከመስመርህ ላይ አውጥተህ ስጋ ነው 'ምታለብሰው
ወይስ ሰጋ እየቀባህ ነፍስን ነው የምትስለው
ጥበብህን ስታሰፋ እንባ እና ሳቅ ጓጎሉብህ
ወይስ ሊጡ ቀለም ሆኖ እንጀራውም ቀለመብህ
የምትጽፈው የአለም ኑሮን እንደምነው ያስቀለለህ
ወይስ ቀላሉን ጻፍከው የአለም ኑሮ ነው ብለህ
ወይስ አበጀህ መንገድ ቀላሉን ከበድ አድርገህ
ከባዱን ቀለል አድርገህ
ሶስተኛው
ዝምብለህ ጻፍ
ዝምብለህ ሳል
ዝምብለህ ጻፍ
ዝምብለህ ሳል
ሰይፈ ተማም 2010
ምስል: Robel Tekel
እምወድሽ
ለምን ሳልል በፊት አንቺን ማለት ቀድሞ
ያርበተብተኛል ልብሽ ልቤን ስሞ
የፊቴ ላይ ከንፈር ጉንጭሽ ላይ ይገኛል
ገጽሽን ተሳልሞ ካልተሳልኩ ይለኛል
የተንጠፈጠፈች ጭላጭ ቀናነቴ
የፍቅር ርጋፊ ይዛ በአከላቴ
ታላውሰኛለች አንቺን አንቺን ብላ
ቃል ቸግሯት ደሞ ከወደድኩሽ ሌላ
ለምን እንዳትይኝ እኔስ መች አውቄ
እንዲሁ ልውደድሽ ወይ ምክኒያት አርቅቄ
እምወድሽ
ተፈርዶ ነው ከላይ እንደ ትእዛዛቱ
እንደሰለጠኑ እንደብርሃናቱ
እንደጨረቃዋ እንደ ፀሃይቱ
'ይውደድሽ' ብሎ ነው የቃልም ቃላቱ
ቀን ዳምኖ ባይፈካ ቢያጥረው ወገግታ
አይኔን ቢጋርደው የልቤ ወለምታ
ከሰፌዶች መሃል የሰበዝ እይታ
የገጽሽ ብርሃን ነው አቅሜን ያበረታ
እምወድሽ
አንድ ሰበዝ ቀልማ ተሰፍታ በጥበብ
ነጠላነት ትታ ልታስውብ ስትከብ
እንዴት ዝም ልላት አስችሎኝ ልሸበብ
ለስንደዶነቴ ሰበዜን እማልክብ
ለምን ሳልል በፊት እንዴት ሳልል በፊት
እንደቤቴ እያለሁ አንቺም እንዳንቺ ቤት
ከሚያመሳስለን የሚለየን በዝቶም
የልብሽን መግቢያ አላጣውም ከቶ
እምወድሽ
እንደ እናቴ ጉርሻ ባልውጥሽ ደስታዬ
እንደ ጥሜ መቁረጥ ቅጽበተ ትንሳኤ
ድንገት እንዳገኙት እንደረሱት ገንዘብ
በአሳ እንደተሞላ የነ ጴጥሮስ መረብ
እንደ ልጅነት ሳቅ እንደ አባሮሽ እስር
እንደ እፉዬ ገላ የአሮጊት ፈስ ጭምር
ለምን እንዳትይኝ እኔስ መች አውቄ
እንዲሁ ልውደድሽ ወይ ምክኒያት አርቅቄ
እንዲያ እነደተሰማኝ በ'እንደ' አስቤ
እንዲሁስ አልወድሽ እግዜር አይደል ልቤ
ሰይፈ ተማም 2010
ለምን ሳልል በፊት አንቺን ማለት ቀድሞ
ያርበተብተኛል ልብሽ ልቤን ስሞ
የፊቴ ላይ ከንፈር ጉንጭሽ ላይ ይገኛል
ገጽሽን ተሳልሞ ካልተሳልኩ ይለኛል
የተንጠፈጠፈች ጭላጭ ቀናነቴ
የፍቅር ርጋፊ ይዛ በአከላቴ
ታላውሰኛለች አንቺን አንቺን ብላ
ቃል ቸግሯት ደሞ ከወደድኩሽ ሌላ
ለምን እንዳትይኝ እኔስ መች አውቄ
እንዲሁ ልውደድሽ ወይ ምክኒያት አርቅቄ
እምወድሽ
ተፈርዶ ነው ከላይ እንደ ትእዛዛቱ
እንደሰለጠኑ እንደብርሃናቱ
እንደጨረቃዋ እንደ ፀሃይቱ
'ይውደድሽ' ብሎ ነው የቃልም ቃላቱ
ቀን ዳምኖ ባይፈካ ቢያጥረው ወገግታ
አይኔን ቢጋርደው የልቤ ወለምታ
ከሰፌዶች መሃል የሰበዝ እይታ
የገጽሽ ብርሃን ነው አቅሜን ያበረታ
እምወድሽ
አንድ ሰበዝ ቀልማ ተሰፍታ በጥበብ
ነጠላነት ትታ ልታስውብ ስትከብ
እንዴት ዝም ልላት አስችሎኝ ልሸበብ
ለስንደዶነቴ ሰበዜን እማልክብ
ለምን ሳልል በፊት እንዴት ሳልል በፊት
እንደቤቴ እያለሁ አንቺም እንዳንቺ ቤት
ከሚያመሳስለን የሚለየን በዝቶም
የልብሽን መግቢያ አላጣውም ከቶ
እምወድሽ
እንደ እናቴ ጉርሻ ባልውጥሽ ደስታዬ
እንደ ጥሜ መቁረጥ ቅጽበተ ትንሳኤ
ድንገት እንዳገኙት እንደረሱት ገንዘብ
በአሳ እንደተሞላ የነ ጴጥሮስ መረብ
እንደ ልጅነት ሳቅ እንደ አባሮሽ እስር
እንደ እፉዬ ገላ የአሮጊት ፈስ ጭምር
ለምን እንዳትይኝ እኔስ መች አውቄ
እንዲሁ ልውደድሽ ወይ ምክኒያት አርቅቄ
እንዲያ እነደተሰማኝ በ'እንደ' አስቤ
እንዲሁስ አልወድሽ እግዜር አይደል ልቤ
ሰይፈ ተማም 2010
...እስካሁን...
ሀሳቤን ስሆነው ሀሳቤ ሲሆነኝ
እንደ ሀሳቤ ልሆን ማሰብ ሲያሳስበኝ
ሀሳብ ኖረኝ እንጂ መች ሀሳቤን ኖርኩኝ
ሰይፈ ተማም 2010
ሀሳቤን ስሆነው ሀሳቤ ሲሆነኝ
እንደ ሀሳቤ ልሆን ማሰብ ሲያሳስበኝ
ሀሳብ ኖረኝ እንጂ መች ሀሳቤን ኖርኩኝ
ሰይፈ ተማም 2010
ጸልያለሁ
========
እጸልያለሁ ለሰው ልጅ
በሰንሰለት ላለው እጅ
እጸልያለሁ ታትሬ
ህላዌን ያላወቀ አለም
ፍፃሜን እንዳያይ ዛሬ
እጸልያለሁ ጸሎቴን
ኩታዬን በኮት ስቀይር
ስለፈረሰው ቤቴ
ራቤን በም'ራብ ስሰፍር
ስለተራበው ጉልበቴ
ስሜን በሰም ሳሰፍር
ስለነደደው ውበቴ
ከራሴ ወጥቼ
ፀርሃ አርያም
ቅጥሩን ተጠግቼ
የዓይኖቼን ውሃ
በፍቅር አተንናለሁ
እ-ጸ-ል-ያ-ለ-ሁ
እጸልያለሁ ጸሎቴን
ዕለትን በአለት ሲያቆም ሲመትር
ስለደከመው አያቴ
ግንጥልጣይ ገጥሞ ሲቀምር
ስለተሰዋው አባቴ
ነፍስ ላይ ነፍጥ ሲከምር
ስለጠበበው አጎቴ
ከራሴ ወጥቼ
መንበረ ፀባዖት
ቅጥሩን ተጠግቼ
የወዜን ብልጭልጭ
በእምነት እጠርጋለሁ
እ-ጸ-ል-ያ-ለ-ሁ
እጸልያለሁ ለሰው ልጅ
በሰንሰለት ላለው እጅ
እጁ ለሰንሰለቱ ሳይጠብ
ሰንሰለት እጁላይ ሳይቀልጥ
ህላዌን እንዲያየው አለም
ፍፃሜን ተግቶ ከማለም
ሰይፈ ተማም 2008
========
እጸልያለሁ ለሰው ልጅ
በሰንሰለት ላለው እጅ
እጸልያለሁ ታትሬ
ህላዌን ያላወቀ አለም
ፍፃሜን እንዳያይ ዛሬ
እጸልያለሁ ጸሎቴን
ኩታዬን በኮት ስቀይር
ስለፈረሰው ቤቴ
ራቤን በም'ራብ ስሰፍር
ስለተራበው ጉልበቴ
ስሜን በሰም ሳሰፍር
ስለነደደው ውበቴ
ከራሴ ወጥቼ
ፀርሃ አርያም
ቅጥሩን ተጠግቼ
የዓይኖቼን ውሃ
በፍቅር አተንናለሁ
እ-ጸ-ል-ያ-ለ-ሁ
እጸልያለሁ ጸሎቴን
ዕለትን በአለት ሲያቆም ሲመትር
ስለደከመው አያቴ
ግንጥልጣይ ገጥሞ ሲቀምር
ስለተሰዋው አባቴ
ነፍስ ላይ ነፍጥ ሲከምር
ስለጠበበው አጎቴ
ከራሴ ወጥቼ
መንበረ ፀባዖት
ቅጥሩን ተጠግቼ
የወዜን ብልጭልጭ
በእምነት እጠርጋለሁ
እ-ጸ-ል-ያ-ለ-ሁ
እጸልያለሁ ለሰው ልጅ
በሰንሰለት ላለው እጅ
እጁ ለሰንሰለቱ ሳይጠብ
ሰንሰለት እጁላይ ሳይቀልጥ
ህላዌን እንዲያየው አለም
ፍፃሜን ተግቶ ከማለም
ሰይፈ ተማም 2008
የንብ ሰነፍ
ጥዝዝዝዝ...ጥዝጥዝ
አርጋኝ ስትከንፍ
ንጹህ ስትጠየፍ
ዝንብ ናት እያልኩኝ ንብ አካሏን ስገድፍ
ለካስ አላት ማሩ ለካስ አላት ሰፈፍ
ደም ቀስማ የሰራችው አበባ ስትነድፍ
ሰይፈ ተማም
ጥዝዝዝዝ...ጥዝጥዝ
አርጋኝ ስትከንፍ
ንጹህ ስትጠየፍ
ዝንብ ናት እያልኩኝ ንብ አካሏን ስገድፍ
ለካስ አላት ማሩ ለካስ አላት ሰፈፍ
ደም ቀስማ የሰራችው አበባ ስትነድፍ
ሰይፈ ተማም
ባነደድሽው ክሰል እያረግሽ እፍ እርግብ
እፍ እርግብ እርግብግብ
... ... አነስተኛ ነፋስ
ገጽ አየዳሰሰ እሳት የሚለውሰ
ከካርቶኑ ቅዳጅ ከእጅሽ ውዝዋዜ
የሚወጣ ዜማ የምቱ አባዜ
እኔን አደንዝዞ እንዳፈዛዘዘኝ
እሳትሽ ነደደ በቆሎሽ ፈነዳ
ልቤ ግን ከሰለ እሳት ሆኖት ዕዳ
እፍ እርግብ እርግብግብ
... ... አነስተኛ ነፋስ
ገጽ አየዳሰሰ እሳት የሚለውሰ
ከካርቶኑ ቅዳጅ ከእጅሽ ውዝዋዜ
የሚወጣ ዜማ የምቱ አባዜ
እኔን አደንዝዞ እንዳፈዛዘዘኝ
እሳትሽ ነደደ በቆሎሽ ፈነዳ
ልቤ ግን ከሰለ እሳት ሆኖት ዕዳ
ስበት
ልብሽ ቢጠራኝ ነው ልቤን አሳከከኝ
መንገድ ብትጀምሪ ስትመጪ ታወቀኝ
እንደበጋ መሬት ውስጤ መሰንጠቁ
የስክነትን ለዛ ድንገት መነጠቁ
ተነሳሽ ማለትነው ልትመጪ እየወጣሽ
ወደኔ ነው ታክሲ አዋክቦ 'ሚያመጣሽ
መግነጢሳም ልብሽ ሲቀርበኝ አውቃለሁ
ሳቢውን ይስባል እኔም ስመጣ'ለሁ
ሰይፈ ተማም 2011
ልብሽ ቢጠራኝ ነው ልቤን አሳከከኝ
መንገድ ብትጀምሪ ስትመጪ ታወቀኝ
እንደበጋ መሬት ውስጤ መሰንጠቁ
የስክነትን ለዛ ድንገት መነጠቁ
ተነሳሽ ማለትነው ልትመጪ እየወጣሽ
ወደኔ ነው ታክሲ አዋክቦ 'ሚያመጣሽ
መግነጢሳም ልብሽ ሲቀርበኝ አውቃለሁ
ሳቢውን ይስባል እኔም ስመጣ'ለሁ
ሰይፈ ተማም 2011
ናፍቆትሽ
የቀዘቀዘ ልብ የተደፋ ወተት
የጨበረ ጸጉር ያዘነበለ አንገት
የተሰበረ ገል ያልተቆላ ቡና
የታረደ ዶሮ የሸተተ ቡላ
ሞልቶ ያልሞላ ታክሲ የሌለው ወያላ
ጨረቃ ስትስቅ ጥርሰሽ ይታየኛል ግልጥልጥ እያለ
ትናፍቂኛለሽ ደግሜ ስስምሽ ለአይኔ እየተሳለ
በቀዘቀዘ ልብ ግድም እማይለው ሰው ለመውደድ ሲሻ
ሁሉን አስበርዶ እያንቀጠቀጠ 'ሚፈልግ መሸሻ
ጉራንጉር አይምሮ ከመጪ ሂያጂዋ አንቺን የሚፈልግ
'ለምን' ሲል ጠያቂ ከመልሱ መልሶ ጥያቄ 'ሚመርግ
ከደረቴ መሃል ፀሀይሽ ሲጠፋ ክረምት ሆኖ 'ሚያዘንብ
እንደተራራ ጫፍ እንዳላበው ቢራ የቀዘቀዘ ልብ
በጠራ ሰማይ ላይ ጥጥ መሳይ ደመና ሳቋ ነው እያለ
ትናፍቂኛለሽ ደግሜ ስስምሽ ለአይኔ እየተሳለ
የተደፋ ወተት ከታቹ ከንፈርሽ ስትስቂ የወጣ
ትዝታውን መዝዞ ቀልቤን የሚቀጣ
ጣቴ እየለኮሰ የጥርሴ ላይ ብልዝ እንደ እከክ ሰፋ
የጣድኩት ገንፍሎ በአሳር ያነደድኩት እሳቴን አጠፋ
ከከንፈሬ ቀርቶ የመሳቂያሽ ቅርጹ በነከስሽኝ ድንገት
የማይሳም ከንፈር 'ማይታፈስ ሃሳብ የተደፋ ወተት
የቀዘቀዘ ልብ የተደፋ ወተት
የጨበረ ጸጉር ያዘነበለ አንገት
የተሰበረ ገል ያልተቆላ ቡና
የታረደ ዶሮ የሸተተ ቡላ
ሞልቶ ያልሞላ ታክሲ የሌለው ወያላ
የሚሸረብ ዞማ መዳፍሽ ያወዛው እያቀማጠለ
ትናፍቂኛለሽ
ጣቴ ሲንቀዠቀዥ
አናቴ መሃል ላይ አንቺን እየሳለ
የጨበረ ጸጉር የተንጨፋረረ የሚነካው ያጣ
ይኸው ካንቺ ወዲህ ባለው አስተዳደር ሰንደቅ ሆኖ ወጣ
ጫፍ ጫፉ ይቋጫል ይኸው እለት እለት
የመቆረጫው ልክ የጣትሽ መለኪያው ጣቴ ቢጠፋበት
ጉራንጉር አይምሮን በሸፈነው አናት የተከመረ ዱር
ናፍቆት የሚያቃጥር የጨበረ ጸጉር
ወዳጁን በስስት የሚያይ ታማኝ ውሻ ከፊቴ እየታየኝ
ያለቃል ሳወጋሽ ላ'ይኔ እየተሳለ ትናፍቂኛለሽ
ያዘነበለ አንገት እንደመሬት ዛቢያ ወዳንቺ ያጋደለ
በትዝታ ቅኝት ክራሩ ሲገረፍ አብሮ ያዘነበለ
አንቺን ፈላጊ አይኖች
ድምጽሽ የጠማቸው ዲሽ መሳይ ጆሮዎች
አነፈናፊ አፍንጫ ከአደይ ከቅጠሉ ጠረንሽን 'ሚያሸት
በናፍቆት ተመዝዞ ያዘነበለ አንገት
ምንም አትጠይቂኝ
የተሰበረ ገል ያልተቆላ ቡና
የታረደ ዶሮ የሸተተ ቡላ
ሞልቶ ያልሞላ ታክሲ የሌለው ወያላ
ምንድናቸው ብለሽ ምንም አትጠይቂኝ
ሁሉም ልቤ ናቸው ሁሉም እራሴ ነኝ
ሰይፈ ተማም 2011
የቀዘቀዘ ልብ የተደፋ ወተት
የጨበረ ጸጉር ያዘነበለ አንገት
የተሰበረ ገል ያልተቆላ ቡና
የታረደ ዶሮ የሸተተ ቡላ
ሞልቶ ያልሞላ ታክሲ የሌለው ወያላ
ጨረቃ ስትስቅ ጥርሰሽ ይታየኛል ግልጥልጥ እያለ
ትናፍቂኛለሽ ደግሜ ስስምሽ ለአይኔ እየተሳለ
በቀዘቀዘ ልብ ግድም እማይለው ሰው ለመውደድ ሲሻ
ሁሉን አስበርዶ እያንቀጠቀጠ 'ሚፈልግ መሸሻ
ጉራንጉር አይምሮ ከመጪ ሂያጂዋ አንቺን የሚፈልግ
'ለምን' ሲል ጠያቂ ከመልሱ መልሶ ጥያቄ 'ሚመርግ
ከደረቴ መሃል ፀሀይሽ ሲጠፋ ክረምት ሆኖ 'ሚያዘንብ
እንደተራራ ጫፍ እንዳላበው ቢራ የቀዘቀዘ ልብ
በጠራ ሰማይ ላይ ጥጥ መሳይ ደመና ሳቋ ነው እያለ
ትናፍቂኛለሽ ደግሜ ስስምሽ ለአይኔ እየተሳለ
የተደፋ ወተት ከታቹ ከንፈርሽ ስትስቂ የወጣ
ትዝታውን መዝዞ ቀልቤን የሚቀጣ
ጣቴ እየለኮሰ የጥርሴ ላይ ብልዝ እንደ እከክ ሰፋ
የጣድኩት ገንፍሎ በአሳር ያነደድኩት እሳቴን አጠፋ
ከከንፈሬ ቀርቶ የመሳቂያሽ ቅርጹ በነከስሽኝ ድንገት
የማይሳም ከንፈር 'ማይታፈስ ሃሳብ የተደፋ ወተት
የቀዘቀዘ ልብ የተደፋ ወተት
የጨበረ ጸጉር ያዘነበለ አንገት
የተሰበረ ገል ያልተቆላ ቡና
የታረደ ዶሮ የሸተተ ቡላ
ሞልቶ ያልሞላ ታክሲ የሌለው ወያላ
የሚሸረብ ዞማ መዳፍሽ ያወዛው እያቀማጠለ
ትናፍቂኛለሽ
ጣቴ ሲንቀዠቀዥ
አናቴ መሃል ላይ አንቺን እየሳለ
የጨበረ ጸጉር የተንጨፋረረ የሚነካው ያጣ
ይኸው ካንቺ ወዲህ ባለው አስተዳደር ሰንደቅ ሆኖ ወጣ
ጫፍ ጫፉ ይቋጫል ይኸው እለት እለት
የመቆረጫው ልክ የጣትሽ መለኪያው ጣቴ ቢጠፋበት
ጉራንጉር አይምሮን በሸፈነው አናት የተከመረ ዱር
ናፍቆት የሚያቃጥር የጨበረ ጸጉር
ወዳጁን በስስት የሚያይ ታማኝ ውሻ ከፊቴ እየታየኝ
ያለቃል ሳወጋሽ ላ'ይኔ እየተሳለ ትናፍቂኛለሽ
ያዘነበለ አንገት እንደመሬት ዛቢያ ወዳንቺ ያጋደለ
በትዝታ ቅኝት ክራሩ ሲገረፍ አብሮ ያዘነበለ
አንቺን ፈላጊ አይኖች
ድምጽሽ የጠማቸው ዲሽ መሳይ ጆሮዎች
አነፈናፊ አፍንጫ ከአደይ ከቅጠሉ ጠረንሽን 'ሚያሸት
በናፍቆት ተመዝዞ ያዘነበለ አንገት
ምንም አትጠይቂኝ
የተሰበረ ገል ያልተቆላ ቡና
የታረደ ዶሮ የሸተተ ቡላ
ሞልቶ ያልሞላ ታክሲ የሌለው ወያላ
ምንድናቸው ብለሽ ምንም አትጠይቂኝ
ሁሉም ልቤ ናቸው ሁሉም እራሴ ነኝ
ሰይፈ ተማም 2011
ስፈራ ስፈራ
የሃሳቤን አጥር
ያጠረኝን ቅጥር
የቅጥሩን ጌታ
ስፈራ ቆይቼ አፌ እንደተፈታ
የምለው ሳላጣ
የፈራሁት 'ሰሚ' ሆኖት ሰላረፈው
አሁን አይሰሜውን ህዝብ ፈርቻለሁ
ሰይፈ ተማም 2011
የሃሳቤን አጥር
ያጠረኝን ቅጥር
የቅጥሩን ጌታ
ስፈራ ቆይቼ አፌ እንደተፈታ
የምለው ሳላጣ
የፈራሁት 'ሰሚ' ሆኖት ሰላረፈው
አሁን አይሰሜውን ህዝብ ፈርቻለሁ
ሰይፈ ተማም 2011
Forwarded from Bruh Club
The Arts Mailing List newsletter - 11th March 2019 is out now,
featuring @Royalphotography22, Fekat Circus, @behagerlij, Habesha Animation, Fano Creatives, Association of Ethiopian Architects, Designlab ETH, Everted, Artistic Ethiopia, Art in Addis, Zoma Museum - https://bit.ly/2Ho5ZvO We hope you enjoy!!
featuring @Royalphotography22, Fekat Circus, @behagerlij, Habesha Animation, Fano Creatives, Association of Ethiopian Architects, Designlab ETH, Everted, Artistic Ethiopia, Art in Addis, Zoma Museum - https://bit.ly/2Ho5ZvO We hope you enjoy!!