መኖር
ሲገፉህ ተገፍተህ
ሲያገኙ ሲረሡህ
ስታገኝ ሲመጡ አንድ ያለህን ሠጥተህ።!
ሀዘን ለቅሷቸውን ወደ አን እያጋቡ አንተን ሲያስለቅሡ
ሀዘናቸው ወስዶህ ቀና ሳትል አንተ ሀሴት ነው ለነሡ።
ላጣ ለተጎዳ
ላገኘ ከበርቴ በዲናሩ ብዛት ለሚበላ ፍዳ
ለሁሉም ሠው ሆነህ
ያለህን ትልቁን ክቡር ጊዜ ሠጥተህ
ምንም እንደማይሠጥ እንደ ንፉግ ታይተህ
ማንም ካንተ ሳይሆን አንተ ለሠው ሆነህ
ከማንም ሳጠብቅ ሁሌም እየሠጠህ
መኖር በመኖር ታስተምረኛለህ።
እንዲህ ቃል የሚሆን ነፍስ ያለው አንድ እውነት
እንኳን ካጠገብህ ከየትስ ይገኛል ቢፈለግ ካለበት።
ፈልጎ አለመድከም አግኝቶ አለመርካት
ያው የልብን መኖር ያው የልብን መንካት።!!!
መኖር ነው አንተነት
መኖር ነው እኔነት።!!!!
©️ተስፋልደት በለጠ
https://t.me/GitemSitem
ሲገፉህ ተገፍተህ
ሲያገኙ ሲረሡህ
ስታገኝ ሲመጡ አንድ ያለህን ሠጥተህ።!
ሀዘን ለቅሷቸውን ወደ አን እያጋቡ አንተን ሲያስለቅሡ
ሀዘናቸው ወስዶህ ቀና ሳትል አንተ ሀሴት ነው ለነሡ።
ላጣ ለተጎዳ
ላገኘ ከበርቴ በዲናሩ ብዛት ለሚበላ ፍዳ
ለሁሉም ሠው ሆነህ
ያለህን ትልቁን ክቡር ጊዜ ሠጥተህ
ምንም እንደማይሠጥ እንደ ንፉግ ታይተህ
ማንም ካንተ ሳይሆን አንተ ለሠው ሆነህ
ከማንም ሳጠብቅ ሁሌም እየሠጠህ
መኖር በመኖር ታስተምረኛለህ።
እንዲህ ቃል የሚሆን ነፍስ ያለው አንድ እውነት
እንኳን ካጠገብህ ከየትስ ይገኛል ቢፈለግ ካለበት።
ፈልጎ አለመድከም አግኝቶ አለመርካት
ያው የልብን መኖር ያው የልብን መንካት።!!!
መኖር ነው አንተነት
መኖር ነው እኔነት።!!!!
©️ተስፋልደት በለጠ
https://t.me/GitemSitem
የግጥም መጽሐፍ ምረቃ
ርእስ፦ ርእስ የለውም
ገጣሚ፦ ኤልያስ ሽታሁን
በጥዑም ግጥሞቹ እና ግሩም ለዛ ባለው አቀራረቡ በርካታ መድረኮች ላይ የምታውቁትና የምትወዱት ኤልያስ ሽታኹን 'ርእስ የለውም' በሚል ርእስ የመጀመሪያ መጽሐፉን ለንባብ አብቅቷል።
ቦታ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር
ቀን፦ ሐምሌ 5
ሰዓት፦ 11 ሰዓት
አዘጋጅ፦ ሰምና ወርቅ
#ኤልያስ_ሽታኹን #ርእስ_የለውም #ሰምናወርቅ
https://t.me/GitemSitem
ርእስ፦ ርእስ የለውም
ገጣሚ፦ ኤልያስ ሽታሁን
በጥዑም ግጥሞቹ እና ግሩም ለዛ ባለው አቀራረቡ በርካታ መድረኮች ላይ የምታውቁትና የምትወዱት ኤልያስ ሽታኹን 'ርእስ የለውም' በሚል ርእስ የመጀመሪያ መጽሐፉን ለንባብ አብቅቷል።
ቦታ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር
ቀን፦ ሐምሌ 5
ሰዓት፦ 11 ሰዓት
አዘጋጅ፦ ሰምና ወርቅ
#ኤልያስ_ሽታኹን #ርእስ_የለውም #ሰምናወርቅ
https://t.me/GitemSitem
ቀድሼ ላግባሽ
እምነ በሃ ቅድስት ቤተክርስቲያን
,.... ወስዕልት በእንቆጳዝዮን
በሚለው ቃል ዜማ ስርአት መልሼ
እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ:
ተንስኡ እያልኩኝ በቅድስቱ ስፍራ
በቀኖናው ድርስት ከእግዜሩ ጋር ላውራ
በሚፈተትበት የቁርባኑ መና
ከልቤ ላመስግን የግሌ ሁኚና
የልቤ ህዋሶች በእንግዳ ስሜት
በፍሰሐ ሰክረው በተመስጦ ስሌት
በምስጋና ድምፀት የማወጣው ዜማ
የጠለቀ እንዲሆን ከሰማይ ደመና
ነጠላ አጣፍተሽ አክሊሉንም ደፍተሽ
ህግሽን ጠብቀሽ ክብርን ተጎናፅፈሽ
ካባውን ደርበን በእምነት ኪዳን ጥላ
በፈገግታ ልይሽ የግሌ ሁኚና
የኔታ የሰጡኝ የወንጌሉ በፍታ
ጠንክሮ እንዲፀና ፍፁም ሳይረታ
በግዕዝ ባራራይ ስርአት መልሼ
'እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ!
የህይወቴን ምስጢር የኑሮዬን ድርሳን
ልቤን ገልጩልሽ እያዜምኩኝ ምልጣን
በክርስትናሽ ስም ፀሎትን አድርሼ
የእለቱን ምስባክ ስንክሳር ከልሼ
እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ!
የተላለፍኩትን የኃጢአት ደዌ
በንስሐ ስሽር በገሐድ ነነዌ
የፈጣሪ ምሕረት ላንቺም እንዲመጣ
በተክሊል ሱባዔ ከበደሌ ልንጣ
አዎ የኔ መውደድ አንቺም ተለመኚ
ገነትም ቀላል ናት ብቻ ከኔ ሁኚ!
አንድም ለኔ ፅናት አንድም ላንቺ ጸጋ
ቃልሽን ሸልሚኝ ልቤ ባንቺ ይርጋ።
ውዴ
ስብሐት ለአብ ብዬ ሠራዊት ዘልቄ
በሐሴት ሰክሬ በደስታ ጠልቄ
ተክህኖ ለብሼ ስርአት መልሼ
እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ!
©️ዳዊት ጥዑማይ
@jawithpoetdeva
2/9/2013
https://t.me/GitemSitem
እምነ በሃ ቅድስት ቤተክርስቲያን
,.... ወስዕልት በእንቆጳዝዮን
በሚለው ቃል ዜማ ስርአት መልሼ
እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ:
ተንስኡ እያልኩኝ በቅድስቱ ስፍራ
በቀኖናው ድርስት ከእግዜሩ ጋር ላውራ
በሚፈተትበት የቁርባኑ መና
ከልቤ ላመስግን የግሌ ሁኚና
የልቤ ህዋሶች በእንግዳ ስሜት
በፍሰሐ ሰክረው በተመስጦ ስሌት
በምስጋና ድምፀት የማወጣው ዜማ
የጠለቀ እንዲሆን ከሰማይ ደመና
ነጠላ አጣፍተሽ አክሊሉንም ደፍተሽ
ህግሽን ጠብቀሽ ክብርን ተጎናፅፈሽ
ካባውን ደርበን በእምነት ኪዳን ጥላ
በፈገግታ ልይሽ የግሌ ሁኚና
የኔታ የሰጡኝ የወንጌሉ በፍታ
ጠንክሮ እንዲፀና ፍፁም ሳይረታ
በግዕዝ ባራራይ ስርአት መልሼ
'እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ!
የህይወቴን ምስጢር የኑሮዬን ድርሳን
ልቤን ገልጩልሽ እያዜምኩኝ ምልጣን
በክርስትናሽ ስም ፀሎትን አድርሼ
የእለቱን ምስባክ ስንክሳር ከልሼ
እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ!
የተላለፍኩትን የኃጢአት ደዌ
በንስሐ ስሽር በገሐድ ነነዌ
የፈጣሪ ምሕረት ላንቺም እንዲመጣ
በተክሊል ሱባዔ ከበደሌ ልንጣ
አዎ የኔ መውደድ አንቺም ተለመኚ
ገነትም ቀላል ናት ብቻ ከኔ ሁኚ!
አንድም ለኔ ፅናት አንድም ላንቺ ጸጋ
ቃልሽን ሸልሚኝ ልቤ ባንቺ ይርጋ።
ውዴ
ስብሐት ለአብ ብዬ ሠራዊት ዘልቄ
በሐሴት ሰክሬ በደስታ ጠልቄ
ተክህኖ ለብሼ ስርአት መልሼ
እባክሽን ላግባሽ ራሴው ቀድሼ!
©️ዳዊት ጥዑማይ
@jawithpoetdeva
2/9/2013
https://t.me/GitemSitem
Forwarded from ኩነት - Kunet
Live Painting & Poetry Night
Gojo Bar presents you a live painting and poetry night along with other entertainments. The show will be hosted by Gitem Sitem's co-host Seife Temam.
Saturday, July 17
7PM - 8PM
Hill Bottom Recreation Center
Entrance fee is ETB 100.
#July_17_21 https://t.me/Kunet_Sitem
#Gojo_Bar #poetry #livepainting #gitemsitem #seifetemam #Hill_bottom
Gojo Bar presents you a live painting and poetry night along with other entertainments. The show will be hosted by Gitem Sitem's co-host Seife Temam.
Saturday, July 17
7PM - 8PM
Hill Bottom Recreation Center
Entrance fee is ETB 100.
#July_17_21 https://t.me/Kunet_Sitem
#Gojo_Bar #poetry #livepainting #gitemsitem #seifetemam #Hill_bottom
አዝኛለሁ…
በልፋቴ በድካሜ ባቆየሁት
ሳቃችንን‐ ተንከርፍፎ ስላየሁት!
አዝኛለሁ…
ለተዝካሩ ለሙሾው ድንኳን ተክሎ እንዳይወጣ
ዕድሜያችን‐የኩርፊያ እንኳን ትዝታ ቢያጣ።
የደስታ የፈገግታ አሻራ ባናስቀር ደርሰን
እንዴት
በባዶ እንዲያው ዝም ብሎ ያለ እድሜው፣ እድሜ ያፍርሰን!
አዝኛለሁ…
ቀና ችን‐ቀን ሳለ ሳይዳምን ፀሐይ ባይወጣበት
እንደሌላው እለት ወዝ ስለታጣበት።
ፀሐይ ያጣ ተብሎ ቀን አይሰረዝም
እድሜ ላይ ይጫናል ታሪክ እንዲያስረዝም።
ሕይወታችን‐ድግሱ ውብ ነበር
እንኳን ቁም ነገሩ ዋዛና ለበጣው
አዝኛለሁ…
ከተነሳንበት ተመልሰን ሄደን ፈልገን ስናጣው።
©️ያዴል ትዕዛዙ
በልፋቴ በድካሜ ባቆየሁት
ሳቃችንን‐ ተንከርፍፎ ስላየሁት!
አዝኛለሁ…
ለተዝካሩ ለሙሾው ድንኳን ተክሎ እንዳይወጣ
ዕድሜያችን‐የኩርፊያ እንኳን ትዝታ ቢያጣ።
የደስታ የፈገግታ አሻራ ባናስቀር ደርሰን
እንዴት
በባዶ እንዲያው ዝም ብሎ ያለ እድሜው፣ እድሜ ያፍርሰን!
አዝኛለሁ…
ቀና ችን‐ቀን ሳለ ሳይዳምን ፀሐይ ባይወጣበት
እንደሌላው እለት ወዝ ስለታጣበት።
ፀሐይ ያጣ ተብሎ ቀን አይሰረዝም
እድሜ ላይ ይጫናል ታሪክ እንዲያስረዝም።
ሕይወታችን‐ድግሱ ውብ ነበር
እንኳን ቁም ነገሩ ዋዛና ለበጣው
አዝኛለሁ…
ከተነሳንበት ተመልሰን ሄደን ፈልገን ስናጣው።
©️ያዴል ትዕዛዙ
Forwarded from Poetic Saturdays
ሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ የመጀመሪያ ዙር ከሰኞ ሐምሌ 12 እስከ ቅዳሜ ሐምሌ 17 ድረስ በኦንላይን ይካሔዳል።
ሀገራችንም በድንቅ ልጃችን "ሰይፈ ተማም" ትወከላለች!
#CASP #CupOfAfricanSlamPoetry #CASP2021 #CASPEthiopia
ሀገራችንም በድንቅ ልጃችን "ሰይፈ ተማም" ትወከላለች!
#CASP #CupOfAfricanSlamPoetry #CASP2021 #CASPEthiopia
Forwarded from Poetic Saturdays
የመክፈቻው ቀን ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቅቋል፡፡
የ33 የአፍሪካ ሀገራት ሻምፒዮኖች ይሳተፉበታል፡፡
ከነገ ጀምሮ የሚጀምረው ውድድር ቅደም ተከተል ምድብም ዕጣ ወጥቶ ነበር፡፡
ሻምፒዮናችን Seife Temam 9 ሀገራት ባሉበት የመጨረሻው ቀን ምድብ የደረሰው ሲሆን የመጀመሪያ ውድድሩን አርብ ዕለት ያደርጋል፡፡
ደቡብ ሱዳን ፣ ሞሮኮ ፣ ሞዛምቢክ ፣ ኬፕቬርድ ፣ ማዳጋስካር ፣ ማላዊ ፣ ኒጀር እና ቡሩንዲ በዚህ ምድብ ይገኛሉ፡፡
ቻድ ላይ በተደረገው የመጀመሪያው ውድድር ላይ አሸናፊ ሻምፒዮን የነበረው እና በሞት ያጣነው ሴኔጋላዊው አልፋሩቅ ም ታስቦ ነበር፡፡
________
ውድድሩ ነገ ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ላይ ይጀምራል፡፡ በፌስቡክ ቀጥታ በመግባት እንድትከታተሉን እንጋብዛለን፡፡
በአካል መገኘት የምንችል ደግሞ ቀጥታ ስርጭታችንን ከሽፍታ ነውና የምናደርገው ብቅ ብላችሁ ደመቅ ደመቅ እናድርገው!
Coupe d'Afrique de Slam poésie, CASP Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም #casp2021 #CaspEthiopia #slampoetry #Africa #Ethiopia
የ33 የአፍሪካ ሀገራት ሻምፒዮኖች ይሳተፉበታል፡፡
ከነገ ጀምሮ የሚጀምረው ውድድር ቅደም ተከተል ምድብም ዕጣ ወጥቶ ነበር፡፡
ሻምፒዮናችን Seife Temam 9 ሀገራት ባሉበት የመጨረሻው ቀን ምድብ የደረሰው ሲሆን የመጀመሪያ ውድድሩን አርብ ዕለት ያደርጋል፡፡
ደቡብ ሱዳን ፣ ሞሮኮ ፣ ሞዛምቢክ ፣ ኬፕቬርድ ፣ ማዳጋስካር ፣ ማላዊ ፣ ኒጀር እና ቡሩንዲ በዚህ ምድብ ይገኛሉ፡፡
ቻድ ላይ በተደረገው የመጀመሪያው ውድድር ላይ አሸናፊ ሻምፒዮን የነበረው እና በሞት ያጣነው ሴኔጋላዊው አልፋሩቅ ም ታስቦ ነበር፡፡
________
ውድድሩ ነገ ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ላይ ይጀምራል፡፡ በፌስቡክ ቀጥታ በመግባት እንድትከታተሉን እንጋብዛለን፡፡
በአካል መገኘት የምንችል ደግሞ ቀጥታ ስርጭታችንን ከሽፍታ ነውና የምናደርገው ብቅ ብላችሁ ደመቅ ደመቅ እናድርገው!
Coupe d'Afrique de Slam poésie, CASP Gitem Sitem - ግጥም ሲጥም #casp2021 #CaspEthiopia #slampoetry #Africa #Ethiopia